፡
የኔ እህት አዚህ ሰፈር ነሽ?
(አሌክስ አብርሃም)
አንድ የሰፈራችን ባለሱቅ የሆነ ቀን በበሩ ሳልፍ "ወንድሜ" ብሎ በአክብሮት ጠራኝና እዚህ ሰፈር ነው የምትኖረው? ብሎ ጠየቀኝ! "አወ" አልኩት እንዴት ረሳኝ ብየ በመገረም! የረዢም አመት ደንበኛየ ነበር። ቀጠል አድርጎ
ሲጃራ ታጨሳለህ እንዴ?
አይ አላጨስም
አቁመህ ነው?
አይ ከመጀመሪያውም አላጨስም
ጫትስ ትቅማለህ እንዴ?
አይ አልቅምም
አቁመህ ነው?
ቅሜ አላውቅም! ለምንድነው ግን የምትጠይቀኝ አልኩ ገርሞኝ ። ጥያቄየን ችላ ብሎ
እ...የስልክ ካርድ ከኔ ትወስድ ነበር እንዴ?
አወ (ደግሞ እውነቴን ነው ከሱ ሱቅ ነበር የምገዛው)
ባለስንት ነበር የምትገዛው?
ባለመቶም ፣ ባለ ሃምሳም ...ባለ ....
ተወው አስታወስኩ! የመቶ ብር ካርድ አለብህ ስምህን መዝገብ ላይ አይቸዋለሁ
ማነው ስሜ ?
ስምህ ምን ያረጋል ጋሸ? ዋናው ካርዱ ነው ....😀
በኋላ ስሰማ ይሄ ሚስኪን ባለሱቅ አእምሮውን ታሞ አማኑኤል ሆስፒታል ገብቶ ነበር አሉኝ። ሚስቱን ነበር ሱቁ ውስጥ ለረዢም ጊዜ የማያት! እና ዘለግ ላለ ጊዜ ታክሞ ከአማኑኤል ተሽሎት ወጣ። ሁሉ ነገር ተስተካክሎ አንድ ነገር ብቻ ትንሽ ልክ አልመጣለትም እየተባለ ይወራል። ማንኛውም በሱቁ በር የሚያለፍ ሰው ዱቤ ወስዶ ያልከፈለው ይመስለው ስለነበር እያስቆመ አጭር መስቀለኛ ኢንተርቪው ያደርጋል። ከምንም በላይ ግን ያሳቀቀን እትየ ማርታን ጠርቶ ጠየቃት የተባለው ነገር ነው። እትየ ማርታ ዕድሜዋ 40 የተሻገረ ዘናጭ ሴት ናት!
"እህቴ ይቅርታ እዚህ ሰፈር ነሽ?" አላት
አወ ምን ልርዳህ? አለች በሚያምር ፈገግታ
ፔሬድ ማየት አቁመሻል እንዴ ወይስ ታያለሽ ? አበደች ...
"ስድ ምናባህ አገባህ?" በኋላ ባሏ ተነግሮት ሊያናፍጠው ወደሱቁ ሲሄድ "ሞዴስ በዱቤ ወስዳ ያልከፈለችኝ መስሎኝ ነው ጋሸ ! ግን ከመጣህ አይቀር ታጨሳለህ እንዴ.....😀"
@getmtg
@getmtg
የኔ እህት አዚህ ሰፈር ነሽ?
(አሌክስ አብርሃም)
አንድ የሰፈራችን ባለሱቅ የሆነ ቀን በበሩ ሳልፍ "ወንድሜ" ብሎ በአክብሮት ጠራኝና እዚህ ሰፈር ነው የምትኖረው? ብሎ ጠየቀኝ! "አወ" አልኩት እንዴት ረሳኝ ብየ በመገረም! የረዢም አመት ደንበኛየ ነበር። ቀጠል አድርጎ
ሲጃራ ታጨሳለህ እንዴ?
አይ አላጨስም
አቁመህ ነው?
አይ ከመጀመሪያውም አላጨስም
ጫትስ ትቅማለህ እንዴ?
አይ አልቅምም
አቁመህ ነው?
ቅሜ አላውቅም! ለምንድነው ግን የምትጠይቀኝ አልኩ ገርሞኝ ። ጥያቄየን ችላ ብሎ
እ...የስልክ ካርድ ከኔ ትወስድ ነበር እንዴ?
አወ (ደግሞ እውነቴን ነው ከሱ ሱቅ ነበር የምገዛው)
ባለስንት ነበር የምትገዛው?
ባለመቶም ፣ ባለ ሃምሳም ...ባለ ....
ተወው አስታወስኩ! የመቶ ብር ካርድ አለብህ ስምህን መዝገብ ላይ አይቸዋለሁ
ማነው ስሜ ?
ስምህ ምን ያረጋል ጋሸ? ዋናው ካርዱ ነው ....😀
በኋላ ስሰማ ይሄ ሚስኪን ባለሱቅ አእምሮውን ታሞ አማኑኤል ሆስፒታል ገብቶ ነበር አሉኝ። ሚስቱን ነበር ሱቁ ውስጥ ለረዢም ጊዜ የማያት! እና ዘለግ ላለ ጊዜ ታክሞ ከአማኑኤል ተሽሎት ወጣ። ሁሉ ነገር ተስተካክሎ አንድ ነገር ብቻ ትንሽ ልክ አልመጣለትም እየተባለ ይወራል። ማንኛውም በሱቁ በር የሚያለፍ ሰው ዱቤ ወስዶ ያልከፈለው ይመስለው ስለነበር እያስቆመ አጭር መስቀለኛ ኢንተርቪው ያደርጋል። ከምንም በላይ ግን ያሳቀቀን እትየ ማርታን ጠርቶ ጠየቃት የተባለው ነገር ነው። እትየ ማርታ ዕድሜዋ 40 የተሻገረ ዘናጭ ሴት ናት!
"እህቴ ይቅርታ እዚህ ሰፈር ነሽ?" አላት
አወ ምን ልርዳህ? አለች በሚያምር ፈገግታ
ፔሬድ ማየት አቁመሻል እንዴ ወይስ ታያለሽ ? አበደች ...
"ስድ ምናባህ አገባህ?" በኋላ ባሏ ተነግሮት ሊያናፍጠው ወደሱቁ ሲሄድ "ሞዴስ በዱቤ ወስዳ ያልከፈለችኝ መስሎኝ ነው ጋሸ ! ግን ከመጣህ አይቀር ታጨሳለህ እንዴ.....😀"
@getmtg
@getmtg
😁7
፡
ቀጨኔ አድባርሽ ማነው
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
"ጋራው ሚካኤል ባይሰማን
ጋሽ ቸሬ ባለውቃቢው
የኛን ልመና አይዘነጋም
በጨለማ ሹክ ያሉት ፀሎት
እስኪፈታ ጀንበር አትነጋም"
ብለውኝ ለሊቱን ሙሉ
ካደምኩት ተሰዋ እንቅልፌ
ሲነጋስ_!?
ትዝታዋ እንጂ የለችም እሷ ከቅፌ፤
እግዚአብሔር አብ ከተራራው ጫፍ
ሞገሱን ይዞ ተቀምጧል
ፀበሉን እያፈለቀ
የስንቱን የንባ ሀዘን ውጧል!
ታዲያሳ እግዚሐርዬ
የኔ እና የሷን ነገር ምነው!
በቶሎ ያልፈጠምክልኝ
ጠንቋይ ቤት ሂዷል ብለህ ነው!?
ከእንጦጦ ዳገት እስከ ሾላ ጫፍ
እሷው ነች በሩቁ ተለጥፋልኝ
እንግዲህ ማምጣት ካቃተህ
በል ቶሎ አይኔን አጥፋልኝ
ማዞሪያን ስዞረው ውዬ
በቅርበት እሷን ካላየው
አይን አለኝ ማለት ምንድር ነው!?
"ሸክላ ሰሪ ናት" ቢሉኝ
አፈር ሆኜ ምነው ብታፍሰኝ
በማርያም ወንዝ ውሃ አልቆጥቁጣኝ
ክንዷ ላይ ብታንተርሰኝ
ሸማዬን ላንተ አላነጥፍም
ከንግዲስ ግጥም አልጥፍም
/አምጣልኝ አልኩህ አምጣልኝ/
እምቢየው እሷ ከሌለች
ብቻዬን አልባረክም
እንግዲህስ አምላክ ነህ ብዬም
ለክብርህ ዣንጥላ አልልክም
ብትፈልግ ሲኦል ወርውረኝ
አድርገኝ ለሚፋጅ ቅጣት
አይበልጥም እሷን ከማጣት።
@getmtg
@getmtg
ቀጨኔ አድባርሽ ማነው
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
"ጋራው ሚካኤል ባይሰማን
ጋሽ ቸሬ ባለውቃቢው
የኛን ልመና አይዘነጋም
በጨለማ ሹክ ያሉት ፀሎት
እስኪፈታ ጀንበር አትነጋም"
ብለውኝ ለሊቱን ሙሉ
ካደምኩት ተሰዋ እንቅልፌ
ሲነጋስ_!?
ትዝታዋ እንጂ የለችም እሷ ከቅፌ፤
እግዚአብሔር አብ ከተራራው ጫፍ
ሞገሱን ይዞ ተቀምጧል
ፀበሉን እያፈለቀ
የስንቱን የንባ ሀዘን ውጧል!
ታዲያሳ እግዚሐርዬ
የኔ እና የሷን ነገር ምነው!
በቶሎ ያልፈጠምክልኝ
ጠንቋይ ቤት ሂዷል ብለህ ነው!?
ከእንጦጦ ዳገት እስከ ሾላ ጫፍ
እሷው ነች በሩቁ ተለጥፋልኝ
እንግዲህ ማምጣት ካቃተህ
በል ቶሎ አይኔን አጥፋልኝ
ማዞሪያን ስዞረው ውዬ
በቅርበት እሷን ካላየው
አይን አለኝ ማለት ምንድር ነው!?
"ሸክላ ሰሪ ናት" ቢሉኝ
አፈር ሆኜ ምነው ብታፍሰኝ
በማርያም ወንዝ ውሃ አልቆጥቁጣኝ
ክንዷ ላይ ብታንተርሰኝ
ሸማዬን ላንተ አላነጥፍም
ከንግዲስ ግጥም አልጥፍም
/አምጣልኝ አልኩህ አምጣልኝ/
እምቢየው እሷ ከሌለች
ብቻዬን አልባረክም
እንግዲህስ አምላክ ነህ ብዬም
ለክብርህ ዣንጥላ አልልክም
ብትፈልግ ሲኦል ወርውረኝ
አድርገኝ ለሚፋጅ ቅጣት
አይበልጥም እሷን ከማጣት።
@getmtg
@getmtg
❤3
ባለቅኔ ነበርኩ
ባለኝ ሰዓት ቅኔ
ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ
አፍኜ ስመግብ
ስታዜም ስሰማት
መዝሙሯን ስቀማት
ቀምቼ ሳፏጨው
የሷን እየቀዳሁ፡ አድማስ ላይ ስረጨው፤
የሰማ ታማሚ፡ መስሎት የፈለቀኝ
ወደኔ እየመጣ፡ ፈውስ ሲጠይቀኝ፤
እሷ የምትለውን፡ ስሰማ ሳቀብል
ከሷ የሚፈሰውን፡ ስቀዳ ሳፀብል
የዳነው መስካሪ፡ ታምሬን ሲነዛ
ደጄን የሚናፍቅ፡ አማኝ እየበዛ
ለፀጋ ለስሜ፡ ሲመታለት ድቤ
በድንገት አምልጣኝ፡ በረረች እርግቤ።
ሄደች ከነድምጿ፡ በስም አስቀርታኝ
ሄደች ከነፈውሷ፡ ከገድሌ ጋር ትታኝ
የምበትንላት፡ ጥሬ ቀርቶኝ ከጄ
ቢረክስም በዜማ የፀደቀው ደጄ
በፈውስ ናፋቂ፡ ሰርክ ይጨናነቃል
ምስኪን! ኪን እርግቤ
እንኳንስ መሄዷን ፡መኖሯን ማን ያውቃል?
ብቻዬን አዘልኩት፡ አግኝቶ ማጣቱን
ጸጋው የተቀማ ፡ስም ሆኖ መቅረቱን
ማቃቴን አፍኜ፡ ብቻዬን ታመምኩት
በነበር ስወደስ ፡መቻልን ቃተትኩት፥
ግን አልሆነልኝም
አልጮህ ድምፅ የለኝም
ያድናቂዬ ድቤ፡ ዜማው ይበልጠኛል
አልጠፋ እንደርግቤ ማን ክንፍ ይሰጠኛል?
ታዲያ ከዚህ ስቃይ፡ ማን ያስመልጠኛል?
እውነት!
ባለቅኔ ነበርኩ፡ ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ፡ እያለች ከጎኔ
ዜማዋ ሲያደምቀኝ ትንፋሿ ሲሞቀኝ
አርፎ እንደማጣጣም፡ እየቀዳሁ ስቀኝ
ያየ ሲያጨበጭብ፡ የሰማ ሲያደንቀኝ
ስጨምቃት ተጨንቃ የምታስጨንቀኝ
አንድ እርግብ ነበረች፤
አሁን ግን የለችም!
ለጠየቀኝ ሁሉ ፡እሺ ስል በርራለች።
ልክ እንደዛ ተረት፡ የልጅ መጫወቻ
ባለቅኔ ነበርኩ፡ አሁን ግን ፍራቻ
ሁሉን ነገር ላጣው፡ የቀረኝ ስም ብቻ።
(Red-8)
፡
ባለኝ ሰዓት ቅኔ
ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ
አፍኜ ስመግብ
ስታዜም ስሰማት
መዝሙሯን ስቀማት
ቀምቼ ሳፏጨው
የሷን እየቀዳሁ፡ አድማስ ላይ ስረጨው፤
የሰማ ታማሚ፡ መስሎት የፈለቀኝ
ወደኔ እየመጣ፡ ፈውስ ሲጠይቀኝ፤
እሷ የምትለውን፡ ስሰማ ሳቀብል
ከሷ የሚፈሰውን፡ ስቀዳ ሳፀብል
የዳነው መስካሪ፡ ታምሬን ሲነዛ
ደጄን የሚናፍቅ፡ አማኝ እየበዛ
ለፀጋ ለስሜ፡ ሲመታለት ድቤ
በድንገት አምልጣኝ፡ በረረች እርግቤ።
ሄደች ከነድምጿ፡ በስም አስቀርታኝ
ሄደች ከነፈውሷ፡ ከገድሌ ጋር ትታኝ
የምበትንላት፡ ጥሬ ቀርቶኝ ከጄ
ቢረክስም በዜማ የፀደቀው ደጄ
በፈውስ ናፋቂ፡ ሰርክ ይጨናነቃል
ምስኪን! ኪን እርግቤ
እንኳንስ መሄዷን ፡መኖሯን ማን ያውቃል?
ብቻዬን አዘልኩት፡ አግኝቶ ማጣቱን
ጸጋው የተቀማ ፡ስም ሆኖ መቅረቱን
ማቃቴን አፍኜ፡ ብቻዬን ታመምኩት
በነበር ስወደስ ፡መቻልን ቃተትኩት፥
ግን አልሆነልኝም
አልጮህ ድምፅ የለኝም
ያድናቂዬ ድቤ፡ ዜማው ይበልጠኛል
አልጠፋ እንደርግቤ ማን ክንፍ ይሰጠኛል?
ታዲያ ከዚህ ስቃይ፡ ማን ያስመልጠኛል?
እውነት!
ባለቅኔ ነበርኩ፡ ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ፡ እያለች ከጎኔ
ዜማዋ ሲያደምቀኝ ትንፋሿ ሲሞቀኝ
አርፎ እንደማጣጣም፡ እየቀዳሁ ስቀኝ
ያየ ሲያጨበጭብ፡ የሰማ ሲያደንቀኝ
ስጨምቃት ተጨንቃ የምታስጨንቀኝ
አንድ እርግብ ነበረች፤
አሁን ግን የለችም!
ለጠየቀኝ ሁሉ ፡እሺ ስል በርራለች።
ልክ እንደዛ ተረት፡ የልጅ መጫወቻ
ባለቅኔ ነበርኩ፡ አሁን ግን ፍራቻ
ሁሉን ነገር ላጣው፡ የቀረኝ ስም ብቻ።
(Red-8)
፡
👍5❤1👏1
፡
ደስታ ቢራቢሮ
(በእውቀቱ ስዩም)
ደስታ ቢራቢሮ
እኔ ጀብደኛ አዳኝ
ስትከንፊ ስከተል የእድሜ መንገድ ከዳኝ
ሳሎኔ ዱር ሆኖ
በግንድ በቅርንጫፍ በሣር ተሸፍኖ
ከኮርኒሴ በታች ወፍራም ጭጋግ ሰፍኖ
እኔም እድሜ ልኬን የማያድግ ሕፃን
እድገቱ
ቁመቱ
ባስማት የተገታ
ነጋ ጠባ ዝላይ ሁለዜ ጨዋታ
በሄደበት ለማጅ
ነፋስን በመንፊት ውሀን በጨርቅ አጥማጅ
ዓመት ታመት ጮርቃ
ለሹመት የማይታጭ ለዋስ የማይበቃ
ሆኘ ቀረሁ በቃ?
ደስታ ቢራቢሮ
በጣቶቸ ማሀል ቀለምሽ ተነነ
ተከትዬሽ ስከንፍ ላባዬ በነነ
ክንፌ ተመለጠ
ጥላሽን ሳሳድድ ዘመኔ አመለጠ፡፡
@getmtg
@getmtg
ደስታ ቢራቢሮ
(በእውቀቱ ስዩም)
ደስታ ቢራቢሮ
እኔ ጀብደኛ አዳኝ
ስትከንፊ ስከተል የእድሜ መንገድ ከዳኝ
ሳሎኔ ዱር ሆኖ
በግንድ በቅርንጫፍ በሣር ተሸፍኖ
ከኮርኒሴ በታች ወፍራም ጭጋግ ሰፍኖ
እኔም እድሜ ልኬን የማያድግ ሕፃን
እድገቱ
ቁመቱ
ባስማት የተገታ
ነጋ ጠባ ዝላይ ሁለዜ ጨዋታ
በሄደበት ለማጅ
ነፋስን በመንፊት ውሀን በጨርቅ አጥማጅ
ዓመት ታመት ጮርቃ
ለሹመት የማይታጭ ለዋስ የማይበቃ
ሆኘ ቀረሁ በቃ?
ደስታ ቢራቢሮ
በጣቶቸ ማሀል ቀለምሽ ተነነ
ተከትዬሽ ስከንፍ ላባዬ በነነ
ክንፌ ተመለጠ
ጥላሽን ሳሳድድ ዘመኔ አመለጠ፡፡
@getmtg
@getmtg
👍2👏2❤1