፡
እኔ ማን ነኝ?
ማንነቴን ስብዕናዬን ብዙ እንዳውቀው
"እኔ ማን ነኝ?" ስል እራሴን ብጠይቀው
“እኔ ማለት ........ ” ሲል ጀምሮ
ክፉነቴን አስታወሰኝ ሁሉን ነግሮ
"እኔ ማለት
ንግግሬ ያላማረ
ለዛ ቃናው ያልሰመረ
በንጭንጭ የተሞላ
ለአድማጭ ጆሮ አሜኬላ
ቅስም ሰባሪ ሰቅጣጭ ቃላት
ርካሽ ሆሄ ረባሽ ድምፀት
ለአፍ ወለምታ ማልፀፀት
ለፈጣሪ ማልገዛ
ማማረርን የማበዛ
ችግሮቼን
በአምላኬ ላይ የማሳብብ
የእምነት ካባን የማልደርብ
ባለኝ ነገር የምኮራ
ለመጀነን የማልፈራ
ምንቀባረር ምመፃደቅ
በሄድኩበት ራሴን ማደንቅ
የሰው ችግር የማይገኝ
ቅንጣት ታክል ርህራሄ ማይሰማኝ
መልካም ስራን የማልሰራ
የህይወት ፍሬን ማላፈራ
ፅድቅ የራቀኝ
እሱም ቀርቶ በቅጡ እንኳን ማይኮንነኝ
እኔ ማለት ክፉ ሰው ነኝ"
ብሎ አለኝ፡፡
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
እኔ ማን ነኝ?
ማንነቴን ስብዕናዬን ብዙ እንዳውቀው
"እኔ ማን ነኝ?" ስል እራሴን ብጠይቀው
“እኔ ማለት ........ ” ሲል ጀምሮ
ክፉነቴን አስታወሰኝ ሁሉን ነግሮ
"እኔ ማለት
ንግግሬ ያላማረ
ለዛ ቃናው ያልሰመረ
በንጭንጭ የተሞላ
ለአድማጭ ጆሮ አሜኬላ
ቅስም ሰባሪ ሰቅጣጭ ቃላት
ርካሽ ሆሄ ረባሽ ድምፀት
ለአፍ ወለምታ ማልፀፀት
ለፈጣሪ ማልገዛ
ማማረርን የማበዛ
ችግሮቼን
በአምላኬ ላይ የማሳብብ
የእምነት ካባን የማልደርብ
ባለኝ ነገር የምኮራ
ለመጀነን የማልፈራ
ምንቀባረር ምመፃደቅ
በሄድኩበት ራሴን ማደንቅ
የሰው ችግር የማይገኝ
ቅንጣት ታክል ርህራሄ ማይሰማኝ
መልካም ስራን የማልሰራ
የህይወት ፍሬን ማላፈራ
ፅድቅ የራቀኝ
እሱም ቀርቶ በቅጡ እንኳን ማይኮንነኝ
እኔ ማለት ክፉ ሰው ነኝ"
ብሎ አለኝ፡፡
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
❤7👍4👏1
፡
"ያልፋል ይለኛል ሰው"
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
ያለወቅቱ መሽቶ ጨልሞበት ቀኑ
ለልቤ ምኑ ነው ተስፋ ማቀንቀኑ
አስማት የለኝ ፀጋ
ጥበብ የለኝ መክሊት
እንዴት ልሸውደው ይህን ክፉ ለሊት
"ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል"
ሁሉም ጦሩን ስሎ ጋሻውን አንግቦ
ቁርስ ምሳ ራቱን ንዴት ተመግቦ
ሲሸልል ለግዳይ ሲፎክር ለበቀል
አይመክተው ሼሁ
አይበግረው መስቀል
ከቀን እስካመሻሽ ከሌት እስከ ንጋት
እሰከመቼ ልግፋው ኑሮዬን በስጋት
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
"የሞተው ወንድምሽ
የገደለው ባልሽ"
የሚባለው ተረት
መች ቀረ በወርት
ምን ጆሮ ተገኝቶ ምክር የሚሰማ
ዘወትር ለጦርነት ነጋሪት ጉሰማ
በለው ነው .....
ግፋው ነው .....
ግዝቱ ስብከቱ ልብ አያልፈሰፍስ
ያልፋል ያላችሁት
ይህ ዘመን ባያልፍስ!?
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
@getmtg
@getmtg
"ያልፋል ይለኛል ሰው"
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
ያለወቅቱ መሽቶ ጨልሞበት ቀኑ
ለልቤ ምኑ ነው ተስፋ ማቀንቀኑ
አስማት የለኝ ፀጋ
ጥበብ የለኝ መክሊት
እንዴት ልሸውደው ይህን ክፉ ለሊት
"ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል"
ሁሉም ጦሩን ስሎ ጋሻውን አንግቦ
ቁርስ ምሳ ራቱን ንዴት ተመግቦ
ሲሸልል ለግዳይ ሲፎክር ለበቀል
አይመክተው ሼሁ
አይበግረው መስቀል
ከቀን እስካመሻሽ ከሌት እስከ ንጋት
እሰከመቼ ልግፋው ኑሮዬን በስጋት
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
"የሞተው ወንድምሽ
የገደለው ባልሽ"
የሚባለው ተረት
መች ቀረ በወርት
ምን ጆሮ ተገኝቶ ምክር የሚሰማ
ዘወትር ለጦርነት ነጋሪት ጉሰማ
በለው ነው .....
ግፋው ነው .....
ግዝቱ ስብከቱ ልብ አያልፈሰፍስ
ያልፋል ያላችሁት
ይህ ዘመን ባያልፍስ!?
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
@getmtg
@getmtg
😭5
የግጥም ጥግ
፡ ያማል! (በሰለሞን ሳህለ) እና እንደነገርኩሽ የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ የነፍሰጡርን ሞት አይቶ እንደመሳቀቅ ባልታሰበ ናዳ ተመቶ እንደመድቀቅ ከተስፋ ጉልላት ተከፍቶ እንደመውደቅ ተአምር በበዛባት በዚች ቧልተኛ አለም ከዚህ የበለጠ ምንም ህመም የለም አውቶቢሱ ያማል ሚኒባሱ ያማል ላዳ ታክሲው ያማል የማይጎል የሰው…
፡
ህመምህ አሞኛል
(አሌክስ አብርሃም)
የጥበብን ቀኝ እጅ
በቀኝ አጁ የዘየረ
ነብዩ ሰለሞን ያማል ይል ነበረ
ቆሞ ሲጠብቃት ቀርታበት ወዳጁ
አንድ እሷ የምትሞላው ኦና ቢሆን ደጁ
ግትልትል መኪናው
ታክሲው አውቶቢሱ
የሰው ግሳንግሱ
የሰው አጋሰሱ
ለአይኑ አልሞላ ብሎት ለተራበች ነፍሱ
.... ያማል ይል ነበረ .....
በአይኖቿ አንቀልባ
በእንባ መቀነቻ
ተስፋ እንደቋጠረ
ማዶ ማዶ እያየ
በተሰበረ ቅስም ያማል ይል ነበረ
እኔ መች ተሰማኝ የጓዴ ህመሙ
የታባቴ ገብቶን የጥበቃ ጥሙ
ዛሬ ግን አወኩት
ብቻዬን ባወራው እብድ ይሉኛል ብዬ
ህመምን ላለፍካት
ህመሜን ላኩልህ በአረቄ ጠቅልዬ
እይውልህ ጓዴ
ያቺ የነገርኩህ ልጅ የፍቅር እትብቴ
ለተስፋዬ ደብር ያኖርኳት ፅላቴ
በራችንን ዘግተን
ሲንቆረቆር ህልሜ ሲንቆረቆር ህልምህ
ትዝ አይልህም ጓዴ
እልፍ ዝምበል ያልኩህ
........... እሷ
የሰው ሁሉ ዳና የእሷ ነው እያልኩኝ
ከበሬ ሲርቁ ተስፋ እያሶረድኩኝ
የጠበኳት ፍቅሬ መቼ ለታ መጣች
ጓዴ ሃሌሉያ የኔ ፀሀይ ወጣች
ከምዕራብ አድማስ ብርሀኗን ነዛች
ተዘግቶ የነበረ በሬ ተከፈተ
ገድሎኝ የነበረው ብቸኝነት ሞተ
ሊተን የነበረ የመውደዴ ተስፋ
ፀጉሬ ጫፍ ላይ ሲደርስ ተመልሶ ፋፋ
ጥቋቁር ተራሮች ፍቅሬን የጋረዲ
የእግሯን ዳና ሰምተው ከፊቴ ተናዱ
ጓዴ ሀሌሉያ አበቦች ደመቁ
የመከኑ ምንጮች ኩል ውሃ አፈለቁ
በጠራራ ግንቦት አደይ ምድሩን ሞላ
ምን ልበልህ ሌላ
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
እኔ እምልህ ጓዴ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
ነበር አይደል ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
፡
እና የነገርኩህ ልጅ
መኖሬን እረስታ
በሬን ክፍቱን ትታ
እግዜር የሰማውን
የእምነት ቃሏን ክዳ
ከባዕድ ተዛምዳ ከባዕድ ተዋልዳ
"አንተ እስካሁን አለህ"
አትለኝ መሰለህ
ልሙትልህ ጓዴ
እንዲህ ነው ያለችኝ
ቁልቁል እያየችኝ
እንዲህ ናህ ቅፅበቷ
እሷ ከፊቴ አለች
የጎደፈ እምነቷን በቃል እያጠበች
ውራጅ ፍቅሯን ገዝቶ ደረቱን የነፋ
ፈረንጅ ጎኗ ቆሟል
ከእሷና እሱ ኃላ
ተራራ ሸንተረር ዛፍ ቅጠሉ ታሟል
ደመናውም ደክሟል
ከደመናው በላይ
አፉን በእጁ ይዞ እግዜርም ተደሟል
ወቸ ጉድ እያለ
ፈረንጁ ......
እጁን መክሊቴ ላይ ጣል አርጎ ያየኛል
ያኔ ያልከው ህመም ጎኔን ይወጋኛል
የምትወዳትን ልጅ በሌላ መታቀፍ
ከዚህ በላይ ስቃይ ከዚህ በላይ መቅፈፍ
ምናለበት እሱ ግዴለም ይቀፋት
በፈራረሰ ቤት ጭቃው በረገፈ
በንፁህ ልቦና በቀን ባልጎደፈ
አንዲት አግዳሚ ላይ
ጎን ለጎን ተቀምጠን
አንድ እርሳት ተካፍለን
አንድ መፅሃፍ ገልጠን
የአበበን በሶ የጫላን ስል ጩቤ
እኔ እንጂ የማስታውስ
ልቤ ላይ ከትቤ
ፈረንጁ ምን እዳው ከሀዲን ያስከዳው
የአየለን ብርታት የጫልቱን እንስራ
በቀዳዳ ጣራ
ጉንጯ ላይ ያረፈች የምታምር ጮራ
ቆዳዋ ላይ ያሉ ገራገር ስስ ፀጉሮች
ጥቁር ሰሌዳ ላይ
ተስፋን የሚቃርሙ የልጅነት አይኖች
አርፈው የማይቆሙ ተወዛዋዥ እግሮች
እሱ መች አያቸው
ከአንጎሉ ጥልቀት
በትዝታ መረብ መች አጠመዳቸው
ምቾት ያደለበው ስጋዋን ይቀፈው
እንደመሲህ ካባ
በእምነት የምነካው
ሰገባ ቀሚሷን በድፍረት ይግፈፈው
ከሰማይ የራቁኝ
ጡቶቿ መካከል በእፎይታ ይረፍ
በአርያም ይንሳፈፍ
ልሙትልህ ጓዴ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ
እከካም ክህደት
የምፎክትበት ጥፍርህን አውሰኝ
የኔና እሷን ነበር ዛሬ ያላወራው
እናቱን ሸለቆ እናቱን ተራራው
ከፊቴ የቆመው እናቱን ፈረንጁ
ወገቧን ያቀፈው እናቱን ቀኝ እጁ
ስማኝማ አንተ ሰው
የሚወዱትን ሰው
ቀጥሮ እንደመጠበቅ አልነበረ ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
አይዞን ወዳጄ ......
ያው እንዳንተ ደጃፍ ኦና ሆኗል ደጄ
አሁን ናፍቀኸኛል
እጠብቀው የለኝ ትጠብቀው የለህ
እንገናኝና አረቄ እየጠጣን
ግጥም እንፃፍለት
ለድህነታችን ጥበቃን ላሳጣን
እናቱን ድህነት
እናቱን ጥበቃ
............ በቃ!
@getmtg
@getmtg
ህመምህ አሞኛል
(አሌክስ አብርሃም)
የጥበብን ቀኝ እጅ
በቀኝ አጁ የዘየረ
ነብዩ ሰለሞን ያማል ይል ነበረ
ቆሞ ሲጠብቃት ቀርታበት ወዳጁ
አንድ እሷ የምትሞላው ኦና ቢሆን ደጁ
ግትልትል መኪናው
ታክሲው አውቶቢሱ
የሰው ግሳንግሱ
የሰው አጋሰሱ
ለአይኑ አልሞላ ብሎት ለተራበች ነፍሱ
.... ያማል ይል ነበረ .....
በአይኖቿ አንቀልባ
በእንባ መቀነቻ
ተስፋ እንደቋጠረ
ማዶ ማዶ እያየ
በተሰበረ ቅስም ያማል ይል ነበረ
እኔ መች ተሰማኝ የጓዴ ህመሙ
የታባቴ ገብቶን የጥበቃ ጥሙ
ዛሬ ግን አወኩት
ብቻዬን ባወራው እብድ ይሉኛል ብዬ
ህመምን ላለፍካት
ህመሜን ላኩልህ በአረቄ ጠቅልዬ
እይውልህ ጓዴ
ያቺ የነገርኩህ ልጅ የፍቅር እትብቴ
ለተስፋዬ ደብር ያኖርኳት ፅላቴ
በራችንን ዘግተን
ሲንቆረቆር ህልሜ ሲንቆረቆር ህልምህ
ትዝ አይልህም ጓዴ
እልፍ ዝምበል ያልኩህ
........... እሷ
የሰው ሁሉ ዳና የእሷ ነው እያልኩኝ
ከበሬ ሲርቁ ተስፋ እያሶረድኩኝ
የጠበኳት ፍቅሬ መቼ ለታ መጣች
ጓዴ ሃሌሉያ የኔ ፀሀይ ወጣች
ከምዕራብ አድማስ ብርሀኗን ነዛች
ተዘግቶ የነበረ በሬ ተከፈተ
ገድሎኝ የነበረው ብቸኝነት ሞተ
ሊተን የነበረ የመውደዴ ተስፋ
ፀጉሬ ጫፍ ላይ ሲደርስ ተመልሶ ፋፋ
ጥቋቁር ተራሮች ፍቅሬን የጋረዲ
የእግሯን ዳና ሰምተው ከፊቴ ተናዱ
ጓዴ ሀሌሉያ አበቦች ደመቁ
የመከኑ ምንጮች ኩል ውሃ አፈለቁ
በጠራራ ግንቦት አደይ ምድሩን ሞላ
ምን ልበልህ ሌላ
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
እኔ እምልህ ጓዴ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
ነበር አይደል ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
፡
እና የነገርኩህ ልጅ
መኖሬን እረስታ
በሬን ክፍቱን ትታ
እግዜር የሰማውን
የእምነት ቃሏን ክዳ
ከባዕድ ተዛምዳ ከባዕድ ተዋልዳ
"አንተ እስካሁን አለህ"
አትለኝ መሰለህ
ልሙትልህ ጓዴ
እንዲህ ነው ያለችኝ
ቁልቁል እያየችኝ
እንዲህ ናህ ቅፅበቷ
እሷ ከፊቴ አለች
የጎደፈ እምነቷን በቃል እያጠበች
ውራጅ ፍቅሯን ገዝቶ ደረቱን የነፋ
ፈረንጅ ጎኗ ቆሟል
ከእሷና እሱ ኃላ
ተራራ ሸንተረር ዛፍ ቅጠሉ ታሟል
ደመናውም ደክሟል
ከደመናው በላይ
አፉን በእጁ ይዞ እግዜርም ተደሟል
ወቸ ጉድ እያለ
ፈረንጁ ......
እጁን መክሊቴ ላይ ጣል አርጎ ያየኛል
ያኔ ያልከው ህመም ጎኔን ይወጋኛል
የምትወዳትን ልጅ በሌላ መታቀፍ
ከዚህ በላይ ስቃይ ከዚህ በላይ መቅፈፍ
ምናለበት እሱ ግዴለም ይቀፋት
በፈራረሰ ቤት ጭቃው በረገፈ
በንፁህ ልቦና በቀን ባልጎደፈ
አንዲት አግዳሚ ላይ
ጎን ለጎን ተቀምጠን
አንድ እርሳት ተካፍለን
አንድ መፅሃፍ ገልጠን
የአበበን በሶ የጫላን ስል ጩቤ
እኔ እንጂ የማስታውስ
ልቤ ላይ ከትቤ
ፈረንጁ ምን እዳው ከሀዲን ያስከዳው
የአየለን ብርታት የጫልቱን እንስራ
በቀዳዳ ጣራ
ጉንጯ ላይ ያረፈች የምታምር ጮራ
ቆዳዋ ላይ ያሉ ገራገር ስስ ፀጉሮች
ጥቁር ሰሌዳ ላይ
ተስፋን የሚቃርሙ የልጅነት አይኖች
አርፈው የማይቆሙ ተወዛዋዥ እግሮች
እሱ መች አያቸው
ከአንጎሉ ጥልቀት
በትዝታ መረብ መች አጠመዳቸው
ምቾት ያደለበው ስጋዋን ይቀፈው
እንደመሲህ ካባ
በእምነት የምነካው
ሰገባ ቀሚሷን በድፍረት ይግፈፈው
ከሰማይ የራቁኝ
ጡቶቿ መካከል በእፎይታ ይረፍ
በአርያም ይንሳፈፍ
ልሙትልህ ጓዴ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ
እከካም ክህደት
የምፎክትበት ጥፍርህን አውሰኝ
የኔና እሷን ነበር ዛሬ ያላወራው
እናቱን ሸለቆ እናቱን ተራራው
ከፊቴ የቆመው እናቱን ፈረንጁ
ወገቧን ያቀፈው እናቱን ቀኝ እጁ
ስማኝማ አንተ ሰው
የሚወዱትን ሰው
ቀጥሮ እንደመጠበቅ አልነበረ ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
አይዞን ወዳጄ ......
ያው እንዳንተ ደጃፍ ኦና ሆኗል ደጄ
አሁን ናፍቀኸኛል
እጠብቀው የለኝ ትጠብቀው የለህ
እንገናኝና አረቄ እየጠጣን
ግጥም እንፃፍለት
ለድህነታችን ጥበቃን ላሳጣን
እናቱን ድህነት
እናቱን ጥበቃ
............ በቃ!
@getmtg
@getmtg
👏6
፡
እንደ ሰርከስ
(በእውቀቱ ስዩም)
መኖር በሀገርህ
የሰርከስ ትርኢት እንደማሳየት ነው
...... ስልጠናው ሳይኖርህ
በሚያድጥ ዳገት ላይ በብጤህ መጋለብ
በሁለት መዳፎች ሳይፎርሹ መቅለብ
ደርዘን ሙሉ አሎሎ
አሎሎ ቢጠፋ እሾህ ተድበልብሎ
በሳት ቀለበት ውስጥ ማለፍ ሹልክ ብሎ
እንደ ህልም እሪታ በሰለለ ገመድ
...... ባንድ እግር መራመድ
ይሄን ሁሉ አድርገህ ትርኢቱም አልቆ
ካጥንቶችህ መሃል አንዱ ተሰንጥቆ
አንደኛው ደንድኖ
እጅህ ወንፊት ሆኖ
ምንም ባትታደል አንቱ የሚባል ስም
አሞጋሽ ለክብርህ ነጋሪት ባይጎስም
ምናልባት ካተረፍክ .....
ያልተራገፈ ጥርስ ያልተሰበረ ቅስም
የድል ሳቅህን ሳቅ በተረፈው ጥርስህ
በወንፊት መዳፍህ አጨብጭብ ለራስህ
@getmtg
@getmtg
እንደ ሰርከስ
(በእውቀቱ ስዩም)
መኖር በሀገርህ
የሰርከስ ትርኢት እንደማሳየት ነው
...... ስልጠናው ሳይኖርህ
በሚያድጥ ዳገት ላይ በብጤህ መጋለብ
በሁለት መዳፎች ሳይፎርሹ መቅለብ
ደርዘን ሙሉ አሎሎ
አሎሎ ቢጠፋ እሾህ ተድበልብሎ
በሳት ቀለበት ውስጥ ማለፍ ሹልክ ብሎ
እንደ ህልም እሪታ በሰለለ ገመድ
...... ባንድ እግር መራመድ
ይሄን ሁሉ አድርገህ ትርኢቱም አልቆ
ካጥንቶችህ መሃል አንዱ ተሰንጥቆ
አንደኛው ደንድኖ
እጅህ ወንፊት ሆኖ
ምንም ባትታደል አንቱ የሚባል ስም
አሞጋሽ ለክብርህ ነጋሪት ባይጎስም
ምናልባት ካተረፍክ .....
ያልተራገፈ ጥርስ ያልተሰበረ ቅስም
የድል ሳቅህን ሳቅ በተረፈው ጥርስህ
በወንፊት መዳፍህ አጨብጭብ ለራስህ
@getmtg
@getmtg
👍5❤2
፡
ከልቡ ነው መውደድ ጥጉ
ምርቃቱ ደርሶ የሚያኖር
ቁጣው እንኳ 'ሚያለመልም
መሰረቱን ጠበቅ አርጎ
ስብዕናን 'ሚገነባ ማንነትን የሚቀልም
በርትቶ የሚያበረታ
ምክሩ ከክፉ የሚያርቅ
የሚያበቃ ለቁምነገር
ለፍቶ ደክሞ ያሳደገ
እንዴትስ ከሀሳብ ይጠፋል
መች ይረሳል ያባት ነገር
አባት እኮ ......
ለልጁ እንቁ ጌጡ ነው
መመኪያ ምሳሌነቱ
ክብርና ሞገስ የሞላው
ያረገ ፍቅርን እምነቱ
ይመራል በቀና መንገድ
ያሳያል ስኬት ጥበቡን
ተዘርቶ የተጠበቀ
በብቃት ማፍራት ማበቡን
አባት እኮ ......
ባይታይ ሀሳብ ሲገባው
ይዞት ነው ውስጡን በውስጡ
አክብረው ለወደዱት ሰው
ስቀው ነው ፍቅር የሚሰጡ
በርትቶ እያበረታ
አለሁ እያለ የሚያፀድቅ
የሚያበቃ ለቁም ነገር
እንዴትስ ከሀሳብ ይጠፋል
መች ይረሳል ያባት ነገር
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
ከልቡ ነው መውደድ ጥጉ
ምርቃቱ ደርሶ የሚያኖር
ቁጣው እንኳ 'ሚያለመልም
መሰረቱን ጠበቅ አርጎ
ስብዕናን 'ሚገነባ ማንነትን የሚቀልም
በርትቶ የሚያበረታ
ምክሩ ከክፉ የሚያርቅ
የሚያበቃ ለቁምነገር
ለፍቶ ደክሞ ያሳደገ
እንዴትስ ከሀሳብ ይጠፋል
መች ይረሳል ያባት ነገር
አባት እኮ ......
ለልጁ እንቁ ጌጡ ነው
መመኪያ ምሳሌነቱ
ክብርና ሞገስ የሞላው
ያረገ ፍቅርን እምነቱ
ይመራል በቀና መንገድ
ያሳያል ስኬት ጥበቡን
ተዘርቶ የተጠበቀ
በብቃት ማፍራት ማበቡን
አባት እኮ ......
ባይታይ ሀሳብ ሲገባው
ይዞት ነው ውስጡን በውስጡ
አክብረው ለወደዱት ሰው
ስቀው ነው ፍቅር የሚሰጡ
በርትቶ እያበረታ
አለሁ እያለ የሚያፀድቅ
የሚያበቃ ለቁም ነገር
እንዴትስ ከሀሳብ ይጠፋል
መች ይረሳል ያባት ነገር
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
❤6
፡
ጩኸት
እጣ ክፍሌ ሆኖ የአርባ ቀን እድሌ
በችግር መከራ በሀጢያት ኩነኔ;
ስኖር በዚህ አለም ሰላም እንደራቀኝ፣
ይኸው አሁን ደግሞ ጩኸት አስጨነቀኝ።
ከውጪ
ሰዉ አራዊቱ አእዋፍ ነፍሳቱ
ማሽኑ መኪናው አውሮፕላን ጀቱ
ሙዚቃው ዳንኪራው የመንገድ መብራቱ;
በአይን በጆሮዬ ገብተው ሲራኮቱ
ሰላሜን አጣለሁ
ስጋዬ ረክሳ ከምድራዊ ሲኦል ደርሼ መጣለሁ።
ደግሞ እሱን ሸሽቼ
ከሰው ተለይቼ
ጭር ባለ ቦታ ብቻዬን ቁጭ ስል
ደግሞ ሌላ ጩኸት ደግሞ ሌላ ቁስል
ከራሴው ከውስጤ ይመጣና ደርሶ
ያቃጭልብኛል ፀፀትን ተላብሶ።
ህሊናዬ ልቤ አንጎል አእምሮዬ
ለውስጥ ህዋሶቼ ለውስጥ አይን ጆሮዬ
ሀጥያቴን በደሌን ከፍ አርገው እያሰሙ
በትናንትና እንጨት ቁስሌን እያደሙ
ነፍሴን ሰላም ነስተው ሲኦል ይከቷታል
እርኩስ ነች እያሉ በአንድነት ያሟታል።
እና እኔ ከወዴት ልኑር እና እኔ ከየትስ ልግባ፣
በየሄድኩበት ሁሉ ጩኸት አብሮኝ ከገባ
ዝምታን መቼ ላገኘው ፀጥታ መቼ ሊመጣ፣
ከውስጥም ከውጭም ያለው እሪታ ከኔ ሳይወጣ
በርታ አይዞህ በማለት ሁሌ ከምታደርቁኝ፣
እስኪ ሰዎች ለአንድ ቀን
ጩኸት ከማይደርስበት ወስዳቹ እኔን ደብቁኝ።
please ደብቁኝ።
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
ጩኸት
እጣ ክፍሌ ሆኖ የአርባ ቀን እድሌ
በችግር መከራ በሀጢያት ኩነኔ;
ስኖር በዚህ አለም ሰላም እንደራቀኝ፣
ይኸው አሁን ደግሞ ጩኸት አስጨነቀኝ።
ከውጪ
ሰዉ አራዊቱ አእዋፍ ነፍሳቱ
ማሽኑ መኪናው አውሮፕላን ጀቱ
ሙዚቃው ዳንኪራው የመንገድ መብራቱ;
በአይን በጆሮዬ ገብተው ሲራኮቱ
ሰላሜን አጣለሁ
ስጋዬ ረክሳ ከምድራዊ ሲኦል ደርሼ መጣለሁ።
ደግሞ እሱን ሸሽቼ
ከሰው ተለይቼ
ጭር ባለ ቦታ ብቻዬን ቁጭ ስል
ደግሞ ሌላ ጩኸት ደግሞ ሌላ ቁስል
ከራሴው ከውስጤ ይመጣና ደርሶ
ያቃጭልብኛል ፀፀትን ተላብሶ።
ህሊናዬ ልቤ አንጎል አእምሮዬ
ለውስጥ ህዋሶቼ ለውስጥ አይን ጆሮዬ
ሀጥያቴን በደሌን ከፍ አርገው እያሰሙ
በትናንትና እንጨት ቁስሌን እያደሙ
ነፍሴን ሰላም ነስተው ሲኦል ይከቷታል
እርኩስ ነች እያሉ በአንድነት ያሟታል።
እና እኔ ከወዴት ልኑር እና እኔ ከየትስ ልግባ፣
በየሄድኩበት ሁሉ ጩኸት አብሮኝ ከገባ
ዝምታን መቼ ላገኘው ፀጥታ መቼ ሊመጣ፣
ከውስጥም ከውጭም ያለው እሪታ ከኔ ሳይወጣ
በርታ አይዞህ በማለት ሁሌ ከምታደርቁኝ፣
እስኪ ሰዎች ለአንድ ቀን
ጩኸት ከማይደርስበት ወስዳቹ እኔን ደብቁኝ።
please ደብቁኝ።
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
❤3👏2👍1