፡
"እንደው አንቺን ሳጣ
ሰላሜ ተለየኝ ልልሽ አሰብኩና
ደግሞም ትዝ ሲለኝ
አልተለየሽኝም
ከእኔው ጋር ነው ያለሽ
እንዲህም አልኩና
ሀሳቤን ቀየርኩኝ ........
፡
ልክ እንደ ውሃ ጥም
ደግሞ ናፍቀሽኛል ለማለት አስቤ
ተውኩት 'ረሳሁት
ጥሜን ልቆርጥበት ውሃውን አቅርቤ
፡
እንዲህ ብዬ ነበር
ደግሞ ካንቺ ሌላ የቱንስ ሀብት አለኝ
( ያው እንደ ልማዴ)
ዛሬም አላጣሁሽ
ምን ምክንያት ሊኖር
እንዲህ የሚያስብለኝ
፡
ደግሞም አንድ 'ለታ
ሳስብሽ ደስ አለኝ ከድሮ ሳቄ አለሽ
ያው እንደነገሩ
አሁን ሕይወቴ ነሽ
........ ብዬ እንዳላሞገስኩ
ካንቺው ላንቺው ሆኖ
ይህን አልኩ የምለው
የውስጤን ልነግርሽ
እንዲህ የምሆነው
ለምን ይሆን?"
(የሚልም ሰው አለ😊)
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
"እንደው አንቺን ሳጣ
ሰላሜ ተለየኝ ልልሽ አሰብኩና
ደግሞም ትዝ ሲለኝ
አልተለየሽኝም
ከእኔው ጋር ነው ያለሽ
እንዲህም አልኩና
ሀሳቤን ቀየርኩኝ ........
፡
ልክ እንደ ውሃ ጥም
ደግሞ ናፍቀሽኛል ለማለት አስቤ
ተውኩት 'ረሳሁት
ጥሜን ልቆርጥበት ውሃውን አቅርቤ
፡
እንዲህ ብዬ ነበር
ደግሞ ካንቺ ሌላ የቱንስ ሀብት አለኝ
( ያው እንደ ልማዴ)
ዛሬም አላጣሁሽ
ምን ምክንያት ሊኖር
እንዲህ የሚያስብለኝ
፡
ደግሞም አንድ 'ለታ
ሳስብሽ ደስ አለኝ ከድሮ ሳቄ አለሽ
ያው እንደነገሩ
አሁን ሕይወቴ ነሽ
........ ብዬ እንዳላሞገስኩ
ካንቺው ላንቺው ሆኖ
ይህን አልኩ የምለው
የውስጤን ልነግርሽ
እንዲህ የምሆነው
ለምን ይሆን?"
(የሚልም ሰው አለ😊)
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
❤4😁3
፡
ኬሬዳሽ
እኔ ስለ እሷ
እኔ ስለ እሷ
ሁሌም አስባለሁ ሁሌ እጨነቃለሁ
በነጋ በጠባ
ውሎና አዳሯን አረጋግጣለሁ
ምን በላች ምን ጠጣች
በምን ተደሰተች
በምንስ ተከፋች
በምን ተቸገረች
ምን እጅስ አጠራት
እጆቼን ቆርጬ እንድተባበራት
አሁን አሁንማ ከሷም አለፍ ብዬ
ስለቤተሰቧ
ስለእህት ወንድሟ ስለእማ አባብዬ
እጠይቃታለሁ እንዴት ሆኑ ብዬ
፡
እሷ ግን ስለእኔ
እሷ ግን ስለእኔ ከቶ ግድ የላትም
ታሟል እንኳን ቢሏት
ምንም አይመስላትም
አይሞቃት አይበርዳት
እኔን ችላ ማለት በፍጹም አይከብዳት
በቃ በጥቅሉ ሆናለች ኬሬዳሽ
ማፍቀሬ ማይገባት
የመውደድ ግዴለሽ፡፡
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
ኬሬዳሽ
እኔ ስለ እሷ
እኔ ስለ እሷ
ሁሌም አስባለሁ ሁሌ እጨነቃለሁ
በነጋ በጠባ
ውሎና አዳሯን አረጋግጣለሁ
ምን በላች ምን ጠጣች
በምን ተደሰተች
በምንስ ተከፋች
በምን ተቸገረች
ምን እጅስ አጠራት
እጆቼን ቆርጬ እንድተባበራት
አሁን አሁንማ ከሷም አለፍ ብዬ
ስለቤተሰቧ
ስለእህት ወንድሟ ስለእማ አባብዬ
እጠይቃታለሁ እንዴት ሆኑ ብዬ
፡
እሷ ግን ስለእኔ
እሷ ግን ስለእኔ ከቶ ግድ የላትም
ታሟል እንኳን ቢሏት
ምንም አይመስላትም
አይሞቃት አይበርዳት
እኔን ችላ ማለት በፍጹም አይከብዳት
በቃ በጥቅሉ ሆናለች ኬሬዳሽ
ማፍቀሬ ማይገባት
የመውደድ ግዴለሽ፡፡
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
👏4❤3👍1
፡
ከ80 በላይ
አለም ባዶ ሆና እኔና አንቺ ብቻ
ማንም በሌለበት ቀርበን ለጋብቻ
ሱፍ ቬሎ ሳናደርግ ሰርግም ሳይሰረግ
ሚዜ አጃቢ ሳይኖር
ቀለበት ሳንገዛ ምንም ሳይደረግ
ሱፌ ያንቺ ፍቅር ቬሎሽ ፍቅሬ ሆኖ
ሰርጋችን ዘላለም ማይኖር ተወስኖ
አጃቢ ከዋክብት
ሚዜዎች ብርሃናት ፀሐይም ጨረቃ
ሰማይ ድንኳናችን ለሁሉ የሚበቃ
እንግዶች ፍጥረታት ሰው ያልተገኘበት
ሰው እኔና አንቺ ብቻ ሆነን ያለንበት።
ፍቅር ቀለበት ነው በልብ የሚታሰር
ወልቆ የማይጠፋ ወድቆ የማይሰበር
እግዜር የነገር አባት እኛን ያጣመረን
ሁለት አርጎ ፈጥሮ
አንድ አርጎ የሚያኖረን
ውል የሌለው ትዳር 80 ያልወሰነው
እንዲህ ያለ ፍቅር
ከየት ነው የሚገኘው።
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
ከ80 በላይ
አለም ባዶ ሆና እኔና አንቺ ብቻ
ማንም በሌለበት ቀርበን ለጋብቻ
ሱፍ ቬሎ ሳናደርግ ሰርግም ሳይሰረግ
ሚዜ አጃቢ ሳይኖር
ቀለበት ሳንገዛ ምንም ሳይደረግ
ሱፌ ያንቺ ፍቅር ቬሎሽ ፍቅሬ ሆኖ
ሰርጋችን ዘላለም ማይኖር ተወስኖ
አጃቢ ከዋክብት
ሚዜዎች ብርሃናት ፀሐይም ጨረቃ
ሰማይ ድንኳናችን ለሁሉ የሚበቃ
እንግዶች ፍጥረታት ሰው ያልተገኘበት
ሰው እኔና አንቺ ብቻ ሆነን ያለንበት።
ፍቅር ቀለበት ነው በልብ የሚታሰር
ወልቆ የማይጠፋ ወድቆ የማይሰበር
እግዜር የነገር አባት እኛን ያጣመረን
ሁለት አርጎ ፈጥሮ
አንድ አርጎ የሚያኖረን
ውል የሌለው ትዳር 80 ያልወሰነው
እንዲህ ያለ ፍቅር
ከየት ነው የሚገኘው።
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
❤6👍2
፡
እኔ ማን ነኝ?
ማንነቴን ስብዕናዬን ብዙ እንዳውቀው
"እኔ ማን ነኝ?" ስል እራሴን ብጠይቀው
“እኔ ማለት ........ ” ሲል ጀምሮ
ክፉነቴን አስታወሰኝ ሁሉን ነግሮ
"እኔ ማለት
ንግግሬ ያላማረ
ለዛ ቃናው ያልሰመረ
በንጭንጭ የተሞላ
ለአድማጭ ጆሮ አሜኬላ
ቅስም ሰባሪ ሰቅጣጭ ቃላት
ርካሽ ሆሄ ረባሽ ድምፀት
ለአፍ ወለምታ ማልፀፀት
ለፈጣሪ ማልገዛ
ማማረርን የማበዛ
ችግሮቼን
በአምላኬ ላይ የማሳብብ
የእምነት ካባን የማልደርብ
ባለኝ ነገር የምኮራ
ለመጀነን የማልፈራ
ምንቀባረር ምመፃደቅ
በሄድኩበት ራሴን ማደንቅ
የሰው ችግር የማይገኝ
ቅንጣት ታክል ርህራሄ ማይሰማኝ
መልካም ስራን የማልሰራ
የህይወት ፍሬን ማላፈራ
ፅድቅ የራቀኝ
እሱም ቀርቶ በቅጡ እንኳን ማይኮንነኝ
እኔ ማለት ክፉ ሰው ነኝ"
ብሎ አለኝ፡፡
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
እኔ ማን ነኝ?
ማንነቴን ስብዕናዬን ብዙ እንዳውቀው
"እኔ ማን ነኝ?" ስል እራሴን ብጠይቀው
“እኔ ማለት ........ ” ሲል ጀምሮ
ክፉነቴን አስታወሰኝ ሁሉን ነግሮ
"እኔ ማለት
ንግግሬ ያላማረ
ለዛ ቃናው ያልሰመረ
በንጭንጭ የተሞላ
ለአድማጭ ጆሮ አሜኬላ
ቅስም ሰባሪ ሰቅጣጭ ቃላት
ርካሽ ሆሄ ረባሽ ድምፀት
ለአፍ ወለምታ ማልፀፀት
ለፈጣሪ ማልገዛ
ማማረርን የማበዛ
ችግሮቼን
በአምላኬ ላይ የማሳብብ
የእምነት ካባን የማልደርብ
ባለኝ ነገር የምኮራ
ለመጀነን የማልፈራ
ምንቀባረር ምመፃደቅ
በሄድኩበት ራሴን ማደንቅ
የሰው ችግር የማይገኝ
ቅንጣት ታክል ርህራሄ ማይሰማኝ
መልካም ስራን የማልሰራ
የህይወት ፍሬን ማላፈራ
ፅድቅ የራቀኝ
እሱም ቀርቶ በቅጡ እንኳን ማይኮንነኝ
እኔ ማለት ክፉ ሰው ነኝ"
ብሎ አለኝ፡፡
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
❤7👍4👏1
፡
"ያልፋል ይለኛል ሰው"
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
ያለወቅቱ መሽቶ ጨልሞበት ቀኑ
ለልቤ ምኑ ነው ተስፋ ማቀንቀኑ
አስማት የለኝ ፀጋ
ጥበብ የለኝ መክሊት
እንዴት ልሸውደው ይህን ክፉ ለሊት
"ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል"
ሁሉም ጦሩን ስሎ ጋሻውን አንግቦ
ቁርስ ምሳ ራቱን ንዴት ተመግቦ
ሲሸልል ለግዳይ ሲፎክር ለበቀል
አይመክተው ሼሁ
አይበግረው መስቀል
ከቀን እስካመሻሽ ከሌት እስከ ንጋት
እሰከመቼ ልግፋው ኑሮዬን በስጋት
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
"የሞተው ወንድምሽ
የገደለው ባልሽ"
የሚባለው ተረት
መች ቀረ በወርት
ምን ጆሮ ተገኝቶ ምክር የሚሰማ
ዘወትር ለጦርነት ነጋሪት ጉሰማ
በለው ነው .....
ግፋው ነው .....
ግዝቱ ስብከቱ ልብ አያልፈሰፍስ
ያልፋል ያላችሁት
ይህ ዘመን ባያልፍስ!?
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
@getmtg
@getmtg
"ያልፋል ይለኛል ሰው"
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
ያለወቅቱ መሽቶ ጨልሞበት ቀኑ
ለልቤ ምኑ ነው ተስፋ ማቀንቀኑ
አስማት የለኝ ፀጋ
ጥበብ የለኝ መክሊት
እንዴት ልሸውደው ይህን ክፉ ለሊት
"ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል"
ሁሉም ጦሩን ስሎ ጋሻውን አንግቦ
ቁርስ ምሳ ራቱን ንዴት ተመግቦ
ሲሸልል ለግዳይ ሲፎክር ለበቀል
አይመክተው ሼሁ
አይበግረው መስቀል
ከቀን እስካመሻሽ ከሌት እስከ ንጋት
እሰከመቼ ልግፋው ኑሮዬን በስጋት
ያልፋል .... ያልፋል .... ያልፋል
"የሞተው ወንድምሽ
የገደለው ባልሽ"
የሚባለው ተረት
መች ቀረ በወርት
ምን ጆሮ ተገኝቶ ምክር የሚሰማ
ዘወትር ለጦርነት ነጋሪት ጉሰማ
በለው ነው .....
ግፋው ነው .....
ግዝቱ ስብከቱ ልብ አያልፈሰፍስ
ያልፋል ያላችሁት
ይህ ዘመን ባያልፍስ!?
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
@getmtg
@getmtg
😭5
የግጥም ጥግ
፡ ያማል! (በሰለሞን ሳህለ) እና እንደነገርኩሽ የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ የነፍሰጡርን ሞት አይቶ እንደመሳቀቅ ባልታሰበ ናዳ ተመቶ እንደመድቀቅ ከተስፋ ጉልላት ተከፍቶ እንደመውደቅ ተአምር በበዛባት በዚች ቧልተኛ አለም ከዚህ የበለጠ ምንም ህመም የለም አውቶቢሱ ያማል ሚኒባሱ ያማል ላዳ ታክሲው ያማል የማይጎል የሰው…
፡
ህመምህ አሞኛል
(አሌክስ አብርሃም)
የጥበብን ቀኝ እጅ
በቀኝ አጁ የዘየረ
ነብዩ ሰለሞን ያማል ይል ነበረ
ቆሞ ሲጠብቃት ቀርታበት ወዳጁ
አንድ እሷ የምትሞላው ኦና ቢሆን ደጁ
ግትልትል መኪናው
ታክሲው አውቶቢሱ
የሰው ግሳንግሱ
የሰው አጋሰሱ
ለአይኑ አልሞላ ብሎት ለተራበች ነፍሱ
.... ያማል ይል ነበረ .....
በአይኖቿ አንቀልባ
በእንባ መቀነቻ
ተስፋ እንደቋጠረ
ማዶ ማዶ እያየ
በተሰበረ ቅስም ያማል ይል ነበረ
እኔ መች ተሰማኝ የጓዴ ህመሙ
የታባቴ ገብቶን የጥበቃ ጥሙ
ዛሬ ግን አወኩት
ብቻዬን ባወራው እብድ ይሉኛል ብዬ
ህመምን ላለፍካት
ህመሜን ላኩልህ በአረቄ ጠቅልዬ
እይውልህ ጓዴ
ያቺ የነገርኩህ ልጅ የፍቅር እትብቴ
ለተስፋዬ ደብር ያኖርኳት ፅላቴ
በራችንን ዘግተን
ሲንቆረቆር ህልሜ ሲንቆረቆር ህልምህ
ትዝ አይልህም ጓዴ
እልፍ ዝምበል ያልኩህ
........... እሷ
የሰው ሁሉ ዳና የእሷ ነው እያልኩኝ
ከበሬ ሲርቁ ተስፋ እያሶረድኩኝ
የጠበኳት ፍቅሬ መቼ ለታ መጣች
ጓዴ ሃሌሉያ የኔ ፀሀይ ወጣች
ከምዕራብ አድማስ ብርሀኗን ነዛች
ተዘግቶ የነበረ በሬ ተከፈተ
ገድሎኝ የነበረው ብቸኝነት ሞተ
ሊተን የነበረ የመውደዴ ተስፋ
ፀጉሬ ጫፍ ላይ ሲደርስ ተመልሶ ፋፋ
ጥቋቁር ተራሮች ፍቅሬን የጋረዲ
የእግሯን ዳና ሰምተው ከፊቴ ተናዱ
ጓዴ ሀሌሉያ አበቦች ደመቁ
የመከኑ ምንጮች ኩል ውሃ አፈለቁ
በጠራራ ግንቦት አደይ ምድሩን ሞላ
ምን ልበልህ ሌላ
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
እኔ እምልህ ጓዴ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
ነበር አይደል ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
፡
እና የነገርኩህ ልጅ
መኖሬን እረስታ
በሬን ክፍቱን ትታ
እግዜር የሰማውን
የእምነት ቃሏን ክዳ
ከባዕድ ተዛምዳ ከባዕድ ተዋልዳ
"አንተ እስካሁን አለህ"
አትለኝ መሰለህ
ልሙትልህ ጓዴ
እንዲህ ነው ያለችኝ
ቁልቁል እያየችኝ
እንዲህ ናህ ቅፅበቷ
እሷ ከፊቴ አለች
የጎደፈ እምነቷን በቃል እያጠበች
ውራጅ ፍቅሯን ገዝቶ ደረቱን የነፋ
ፈረንጅ ጎኗ ቆሟል
ከእሷና እሱ ኃላ
ተራራ ሸንተረር ዛፍ ቅጠሉ ታሟል
ደመናውም ደክሟል
ከደመናው በላይ
አፉን በእጁ ይዞ እግዜርም ተደሟል
ወቸ ጉድ እያለ
ፈረንጁ ......
እጁን መክሊቴ ላይ ጣል አርጎ ያየኛል
ያኔ ያልከው ህመም ጎኔን ይወጋኛል
የምትወዳትን ልጅ በሌላ መታቀፍ
ከዚህ በላይ ስቃይ ከዚህ በላይ መቅፈፍ
ምናለበት እሱ ግዴለም ይቀፋት
በፈራረሰ ቤት ጭቃው በረገፈ
በንፁህ ልቦና በቀን ባልጎደፈ
አንዲት አግዳሚ ላይ
ጎን ለጎን ተቀምጠን
አንድ እርሳት ተካፍለን
አንድ መፅሃፍ ገልጠን
የአበበን በሶ የጫላን ስል ጩቤ
እኔ እንጂ የማስታውስ
ልቤ ላይ ከትቤ
ፈረንጁ ምን እዳው ከሀዲን ያስከዳው
የአየለን ብርታት የጫልቱን እንስራ
በቀዳዳ ጣራ
ጉንጯ ላይ ያረፈች የምታምር ጮራ
ቆዳዋ ላይ ያሉ ገራገር ስስ ፀጉሮች
ጥቁር ሰሌዳ ላይ
ተስፋን የሚቃርሙ የልጅነት አይኖች
አርፈው የማይቆሙ ተወዛዋዥ እግሮች
እሱ መች አያቸው
ከአንጎሉ ጥልቀት
በትዝታ መረብ መች አጠመዳቸው
ምቾት ያደለበው ስጋዋን ይቀፈው
እንደመሲህ ካባ
በእምነት የምነካው
ሰገባ ቀሚሷን በድፍረት ይግፈፈው
ከሰማይ የራቁኝ
ጡቶቿ መካከል በእፎይታ ይረፍ
በአርያም ይንሳፈፍ
ልሙትልህ ጓዴ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ
እከካም ክህደት
የምፎክትበት ጥፍርህን አውሰኝ
የኔና እሷን ነበር ዛሬ ያላወራው
እናቱን ሸለቆ እናቱን ተራራው
ከፊቴ የቆመው እናቱን ፈረንጁ
ወገቧን ያቀፈው እናቱን ቀኝ እጁ
ስማኝማ አንተ ሰው
የሚወዱትን ሰው
ቀጥሮ እንደመጠበቅ አልነበረ ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
አይዞን ወዳጄ ......
ያው እንዳንተ ደጃፍ ኦና ሆኗል ደጄ
አሁን ናፍቀኸኛል
እጠብቀው የለኝ ትጠብቀው የለህ
እንገናኝና አረቄ እየጠጣን
ግጥም እንፃፍለት
ለድህነታችን ጥበቃን ላሳጣን
እናቱን ድህነት
እናቱን ጥበቃ
............ በቃ!
@getmtg
@getmtg
ህመምህ አሞኛል
(አሌክስ አብርሃም)
የጥበብን ቀኝ እጅ
በቀኝ አጁ የዘየረ
ነብዩ ሰለሞን ያማል ይል ነበረ
ቆሞ ሲጠብቃት ቀርታበት ወዳጁ
አንድ እሷ የምትሞላው ኦና ቢሆን ደጁ
ግትልትል መኪናው
ታክሲው አውቶቢሱ
የሰው ግሳንግሱ
የሰው አጋሰሱ
ለአይኑ አልሞላ ብሎት ለተራበች ነፍሱ
.... ያማል ይል ነበረ .....
በአይኖቿ አንቀልባ
በእንባ መቀነቻ
ተስፋ እንደቋጠረ
ማዶ ማዶ እያየ
በተሰበረ ቅስም ያማል ይል ነበረ
እኔ መች ተሰማኝ የጓዴ ህመሙ
የታባቴ ገብቶን የጥበቃ ጥሙ
ዛሬ ግን አወኩት
ብቻዬን ባወራው እብድ ይሉኛል ብዬ
ህመምን ላለፍካት
ህመሜን ላኩልህ በአረቄ ጠቅልዬ
እይውልህ ጓዴ
ያቺ የነገርኩህ ልጅ የፍቅር እትብቴ
ለተስፋዬ ደብር ያኖርኳት ፅላቴ
በራችንን ዘግተን
ሲንቆረቆር ህልሜ ሲንቆረቆር ህልምህ
ትዝ አይልህም ጓዴ
እልፍ ዝምበል ያልኩህ
........... እሷ
የሰው ሁሉ ዳና የእሷ ነው እያልኩኝ
ከበሬ ሲርቁ ተስፋ እያሶረድኩኝ
የጠበኳት ፍቅሬ መቼ ለታ መጣች
ጓዴ ሃሌሉያ የኔ ፀሀይ ወጣች
ከምዕራብ አድማስ ብርሀኗን ነዛች
ተዘግቶ የነበረ በሬ ተከፈተ
ገድሎኝ የነበረው ብቸኝነት ሞተ
ሊተን የነበረ የመውደዴ ተስፋ
ፀጉሬ ጫፍ ላይ ሲደርስ ተመልሶ ፋፋ
ጥቋቁር ተራሮች ፍቅሬን የጋረዲ
የእግሯን ዳና ሰምተው ከፊቴ ተናዱ
ጓዴ ሀሌሉያ አበቦች ደመቁ
የመከኑ ምንጮች ኩል ውሃ አፈለቁ
በጠራራ ግንቦት አደይ ምድሩን ሞላ
ምን ልበልህ ሌላ
ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ
እኔ እምልህ ጓዴ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
ነበር አይደል ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
፡
እና የነገርኩህ ልጅ
መኖሬን እረስታ
በሬን ክፍቱን ትታ
እግዜር የሰማውን
የእምነት ቃሏን ክዳ
ከባዕድ ተዛምዳ ከባዕድ ተዋልዳ
"አንተ እስካሁን አለህ"
አትለኝ መሰለህ
ልሙትልህ ጓዴ
እንዲህ ነው ያለችኝ
ቁልቁል እያየችኝ
እንዲህ ናህ ቅፅበቷ
እሷ ከፊቴ አለች
የጎደፈ እምነቷን በቃል እያጠበች
ውራጅ ፍቅሯን ገዝቶ ደረቱን የነፋ
ፈረንጅ ጎኗ ቆሟል
ከእሷና እሱ ኃላ
ተራራ ሸንተረር ዛፍ ቅጠሉ ታሟል
ደመናውም ደክሟል
ከደመናው በላይ
አፉን በእጁ ይዞ እግዜርም ተደሟል
ወቸ ጉድ እያለ
ፈረንጁ ......
እጁን መክሊቴ ላይ ጣል አርጎ ያየኛል
ያኔ ያልከው ህመም ጎኔን ይወጋኛል
የምትወዳትን ልጅ በሌላ መታቀፍ
ከዚህ በላይ ስቃይ ከዚህ በላይ መቅፈፍ
ምናለበት እሱ ግዴለም ይቀፋት
በፈራረሰ ቤት ጭቃው በረገፈ
በንፁህ ልቦና በቀን ባልጎደፈ
አንዲት አግዳሚ ላይ
ጎን ለጎን ተቀምጠን
አንድ እርሳት ተካፍለን
አንድ መፅሃፍ ገልጠን
የአበበን በሶ የጫላን ስል ጩቤ
እኔ እንጂ የማስታውስ
ልቤ ላይ ከትቤ
ፈረንጁ ምን እዳው ከሀዲን ያስከዳው
የአየለን ብርታት የጫልቱን እንስራ
በቀዳዳ ጣራ
ጉንጯ ላይ ያረፈች የምታምር ጮራ
ቆዳዋ ላይ ያሉ ገራገር ስስ ፀጉሮች
ጥቁር ሰሌዳ ላይ
ተስፋን የሚቃርሙ የልጅነት አይኖች
አርፈው የማይቆሙ ተወዛዋዥ እግሮች
እሱ መች አያቸው
ከአንጎሉ ጥልቀት
በትዝታ መረብ መች አጠመዳቸው
ምቾት ያደለበው ስጋዋን ይቀፈው
እንደመሲህ ካባ
በእምነት የምነካው
ሰገባ ቀሚሷን በድፍረት ይግፈፈው
ከሰማይ የራቁኝ
ጡቶቿ መካከል በእፎይታ ይረፍ
በአርያም ይንሳፈፍ
ልሙትልህ ጓዴ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ ከጎኔ ብትኖር
እናቷን ጨረቃ
ያስባለህ ህመምህ
በጠራራ ፀሀይ ይነሳብህ ነበር
እኔ ተነሳብኝ
ሴጣን ወሰወሰኝ
እከካም ክህደት
የምፎክትበት ጥፍርህን አውሰኝ
የኔና እሷን ነበር ዛሬ ያላወራው
እናቱን ሸለቆ እናቱን ተራራው
ከፊቴ የቆመው እናቱን ፈረንጁ
ወገቧን ያቀፈው እናቱን ቀኝ እጁ
ስማኝማ አንተ ሰው
የሚወዱትን ሰው
ቀጥሮ እንደመጠበቅ አልነበረ ያልከው?!
ከመቅረት የባሰ
አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወከው
አይዞን ወዳጄ ......
ያው እንዳንተ ደጃፍ ኦና ሆኗል ደጄ
አሁን ናፍቀኸኛል
እጠብቀው የለኝ ትጠብቀው የለህ
እንገናኝና አረቄ እየጠጣን
ግጥም እንፃፍለት
ለድህነታችን ጥበቃን ላሳጣን
እናቱን ድህነት
እናቱን ጥበቃ
............ በቃ!
@getmtg
@getmtg
👏6