፡
አንቺ ስትቀሪ
ሽፋን ታቅፊያለው
ሲያይዋት የምታምር ልብ የምትሰረስር
አበባ ይዣለው
የሚያምር አበባ ከሽፋኑዋ ሆድ ስር
ትመጣለች ይሆን!
እያልኩኝ ጠበኩዋት
ጠበኩዋት
ጠበኩዋት
እንዳትቀር ያሰበች ልቤን አስጨነኩዋት
ኮቴሽን ናፍቄ መምጫሽን ናፍቄ
ጠብቂያት እላለው
እንዳትከፋብኝ አበባዬን ስቄ
ገፁዋ ጠወለገ ሟሸሸ ቅጠሏ
ብትቀሪ ጊዜ ነው ባንቺ መቃጠሏ
እያልኩኝ ….....
እያልኩኝ .......
በሳምሺው መዳፌ ውብ ፊቴን ከለልኩኝ
አይኔ የሚያየው አጣ እንባ ከለከለኝ
..... ልቤ ደነገጠ ቀርተሻል መሰለኝ
ቀርተሻል
ቀርተሻል
ቀርተሻል
ቀርተሻል
ከራሱ የራቀ ወደማን ይሸሻል!?
ታዲያ ስትቀሪ
የያዝኩት አበባ ደርቆ ጠወለገ
ፀሀይ ወቶ ሳለ
የሚያስጠላ ሆኖ ቀኑ ጨፈገገ
ይህው አበባዬ
ሲጠብቅሽ ዉሎ አዘነ ተከፋ
ፀአዳው ፀዳሉ
ጠረኑን ለውጦ እጅጉን ከረፋ
አንቺ ስትቀሪ ……
ሽፋን ውስጥ ያለውን
ውዱን ስጦታዬን የሚከፍተው አጣ
የዘላለሙ ቤት
መቃብር ሆነበት አዘነ ተቆጣ
ተቆጥቶ እንዲህ አለኝ ምስኪን አበባዬ
ናፍቆት የደፈነው
ምን ጆሮ አለውና ሰማሁት በእንባዬ
"አስተውል ወዳጄ!!
ለወደድካት እንስት ላፈቀርካት ወጣት
አበባህን እንጂ ልብህን አትስጣት
ምክንያቱም .......
እኔ ብጠወልግ ብዙ አበቦች አሉ
ለወደድከው ሁሉ መሆን የሚችሉ"
አሊያ ግን ለዛች ሴት
ከአበባህ ቀድመህ ልብህን ካቀናህ
ድንገት የቀረች'ለት
ከ አበባህ ቀድመህ ትሞታለህና
ለወደድካት እንስት ላፈቀርካት ወጣት
አበባህን እንጂ ልብህን አትስጣት።"
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
አንቺ ስትቀሪ
ሽፋን ታቅፊያለው
ሲያይዋት የምታምር ልብ የምትሰረስር
አበባ ይዣለው
የሚያምር አበባ ከሽፋኑዋ ሆድ ስር
ትመጣለች ይሆን!
እያልኩኝ ጠበኩዋት
ጠበኩዋት
ጠበኩዋት
እንዳትቀር ያሰበች ልቤን አስጨነኩዋት
ኮቴሽን ናፍቄ መምጫሽን ናፍቄ
ጠብቂያት እላለው
እንዳትከፋብኝ አበባዬን ስቄ
ገፁዋ ጠወለገ ሟሸሸ ቅጠሏ
ብትቀሪ ጊዜ ነው ባንቺ መቃጠሏ
እያልኩኝ ….....
እያልኩኝ .......
በሳምሺው መዳፌ ውብ ፊቴን ከለልኩኝ
አይኔ የሚያየው አጣ እንባ ከለከለኝ
..... ልቤ ደነገጠ ቀርተሻል መሰለኝ
ቀርተሻል
ቀርተሻል
ቀርተሻል
ቀርተሻል
ከራሱ የራቀ ወደማን ይሸሻል!?
ታዲያ ስትቀሪ
የያዝኩት አበባ ደርቆ ጠወለገ
ፀሀይ ወቶ ሳለ
የሚያስጠላ ሆኖ ቀኑ ጨፈገገ
ይህው አበባዬ
ሲጠብቅሽ ዉሎ አዘነ ተከፋ
ፀአዳው ፀዳሉ
ጠረኑን ለውጦ እጅጉን ከረፋ
አንቺ ስትቀሪ ……
ሽፋን ውስጥ ያለውን
ውዱን ስጦታዬን የሚከፍተው አጣ
የዘላለሙ ቤት
መቃብር ሆነበት አዘነ ተቆጣ
ተቆጥቶ እንዲህ አለኝ ምስኪን አበባዬ
ናፍቆት የደፈነው
ምን ጆሮ አለውና ሰማሁት በእንባዬ
"አስተውል ወዳጄ!!
ለወደድካት እንስት ላፈቀርካት ወጣት
አበባህን እንጂ ልብህን አትስጣት
ምክንያቱም .......
እኔ ብጠወልግ ብዙ አበቦች አሉ
ለወደድከው ሁሉ መሆን የሚችሉ"
አሊያ ግን ለዛች ሴት
ከአበባህ ቀድመህ ልብህን ካቀናህ
ድንገት የቀረች'ለት
ከ አበባህ ቀድመህ ትሞታለህና
ለወደድካት እንስት ላፈቀርካት ወጣት
አበባህን እንጂ ልብህን አትስጣት።"
(አስታወሰኝ ረጋሳ)
👍16❤1
፡
አስደግማብኝ ነው ......
(ሰለሞን ሳህለ)
ለሰባት ጠንቋይ ልጅ ለደብተራ ምርኩዝ
ጠጠር ገበጣ አርጋ ላኬር እጣው እርኩዝ
"ይቺን ያየ" አስብላ
መሬት ልታስገባ ደቼ ልታስበላ
የስር ማሽ እንጉዳይ የኮከብ ቆጣሪ
የነ መገን ቦቃ የነ ጥና ጠሪ
እንደርቢ ቁጣ የአመድ ላይ ዘዋሪ
ለመቃብር አፈር መንገድ ላይ ቀጣሪ
መተተኛ ፍቅር ልብ ላይ ቀባሪ
የቀን ስደተኛ አርጋኝ የሌት ዟሪ
አቅሌን እያሳተች 'ምታስብለኝ እሪ
አስደግማብኝ ነው ....
"በርሶ መጀን" ብላ
የልቤ ሳይበቃት ልቦናየን በልታ
ጨፌ እየነከሰች በጉልበት ተደፍታ
ኩራቴን ልትነጥቀኝ ኮርታ ልትማታ
.... ተማ'ታም ልትረታ
ጥላዬን ጀማው ፊት መሬቱ ላይ ዘርታ
"ያዙልኝ" እያለች በጠንቋይ ቱፍታ
መለመላ ነፍሴን ወናየን ዘርግታ
'ታሞ ይኑር' ብላ እኔን አስወግታ
እርጋታዬን ነጥቃ እኔን ከኔ አጣልታ
በደብተራው ምርኩዝ ባስነካችው ኩታ
እንዳነክስላት ጅስሜን አስመትታ
ህልሜን እንዳልሰማ ልቤን አስደብታ
አስደግማብኝ ነው "ናልኝ" ብላ ጠርታ
የሆንኩ አንገት ደፊ የሆንኩት ከርታታ
መለየት ያቃተኝ ቀኑንና ማታ
አስደግማብኝ ነው ......
ለነ ጥላ ወጊ ለመጫኛ ነካሽ
ለነ አፍዝ አደንግዝ ለዱር ቅጠል በጣሽ
ላውልያ ለጠንቋዩ ለኑግ ቂጣ ቆራሽ
ለመንገድ ገርጋሪ ለውቃቢ ዘራሽ
ለገሃድ ስውሩ ለነ ጽናት አፍራሽ
ለምድር ላየሩ ለየሎስ አጎንባሽ
ለባህር ለየብሱ ለጠቋሪት ደጋሽ
አስደግማብኝ ነው
ወለም ያላለኝን ዘላለም የምታሽ
አስደግማብኝ ነው.......
አስደግማብኝ ነው ......
(ሰለሞን ሳህለ)
ለሰባት ጠንቋይ ልጅ ለደብተራ ምርኩዝ
ጠጠር ገበጣ አርጋ ላኬር እጣው እርኩዝ
"ይቺን ያየ" አስብላ
መሬት ልታስገባ ደቼ ልታስበላ
የስር ማሽ እንጉዳይ የኮከብ ቆጣሪ
የነ መገን ቦቃ የነ ጥና ጠሪ
እንደርቢ ቁጣ የአመድ ላይ ዘዋሪ
ለመቃብር አፈር መንገድ ላይ ቀጣሪ
መተተኛ ፍቅር ልብ ላይ ቀባሪ
የቀን ስደተኛ አርጋኝ የሌት ዟሪ
አቅሌን እያሳተች 'ምታስብለኝ እሪ
አስደግማብኝ ነው ....
"በርሶ መጀን" ብላ
የልቤ ሳይበቃት ልቦናየን በልታ
ጨፌ እየነከሰች በጉልበት ተደፍታ
ኩራቴን ልትነጥቀኝ ኮርታ ልትማታ
.... ተማ'ታም ልትረታ
ጥላዬን ጀማው ፊት መሬቱ ላይ ዘርታ
"ያዙልኝ" እያለች በጠንቋይ ቱፍታ
መለመላ ነፍሴን ወናየን ዘርግታ
'ታሞ ይኑር' ብላ እኔን አስወግታ
እርጋታዬን ነጥቃ እኔን ከኔ አጣልታ
በደብተራው ምርኩዝ ባስነካችው ኩታ
እንዳነክስላት ጅስሜን አስመትታ
ህልሜን እንዳልሰማ ልቤን አስደብታ
አስደግማብኝ ነው "ናልኝ" ብላ ጠርታ
የሆንኩ አንገት ደፊ የሆንኩት ከርታታ
መለየት ያቃተኝ ቀኑንና ማታ
አስደግማብኝ ነው ......
ለነ ጥላ ወጊ ለመጫኛ ነካሽ
ለነ አፍዝ አደንግዝ ለዱር ቅጠል በጣሽ
ላውልያ ለጠንቋዩ ለኑግ ቂጣ ቆራሽ
ለመንገድ ገርጋሪ ለውቃቢ ዘራሽ
ለገሃድ ስውሩ ለነ ጽናት አፍራሽ
ለምድር ላየሩ ለየሎስ አጎንባሽ
ለባህር ለየብሱ ለጠቋሪት ደጋሽ
አስደግማብኝ ነው
ወለም ያላለኝን ዘላለም የምታሽ
አስደግማብኝ ነው.......
❤5👍3
እየውልሽ ዉዴ ወንድ ልጅ አይደለሁ
አኮረፍሺኝ ብዬ እስኪነጋ ድረስ እጠጣልሻለሁ።
በተቀመጥኩበት ሌቱ እስከሚነጋ
በተፈጠርኩበት አለም እስኪረጋ
እሰክርልሻለሁ
ወንድ ልጅ አይደለሁ...
የላንቺ እንዳላልኩኝ ሴት ሁሉ አትፈጠር
ዛሬ ሰው አላውቅም ከ ኮማሪ በቀር
ደስታ እንደሞላኝ...
ቀ-ጭን ወገብሽን በጆቼ አቅፌ
ቅፅበቱ ይገርመኛል
ያረቄ መለኪያ ሲውል ከመዳፌ
የኮማሪት ገላ ሲኖር ከጉንፌ
ከትንፋሽሽ ውጪ አልሞቅም ያልኩኝ ሰው
ላረቄ ሽታ ነው ልቤ ሚናውዘው
ይምታታብኝ ያዘ
ያንቺና ያረቄው አመልና ነገር
ያንቺና መለኪያው አቋም አፈጣጠር
ብስቅ ብፈነድቅ ካንቺ ጋር አልነበር
ዛሬ አያምርብኝም ካልጠጣሁኝ በቀር
ካልሰከርኩኝ በቀር።
ተይ አታስኮንኚኝ
እንደ መጥፎ ቅዠት ደርሰሽ አታባኚኝ
ነይ እስኪ ልጋብዝሽ..
ትንሽ ጎንጨት በይ ይህን ካቲካላ
መውደዴን ቢያሳይሽ አስክሮ በመላ
ነይማ እንሞክረው...
ችለን ስንሔድበት የጣለንን መንገድ
ያሰምርልን እንደው ሰክሮ መንገዳገድ
ግድ የለም አትፍሪ ዝምብለን እንጠጣ
በዛ ከተባለ..
ብትወጂኝ ነውንጂ ሌላ ምን ሊመጣ።
ስካር የተባለ አንድ እንዳይቀርብሽ
አቅላችንን ስተን ሰፈር እንረብሽ
ማን ያውቃል
ስትሰክሪ ይሆናል 'ርምጃ ሚያምርብሽ።
ያዢና ፉት በይ እንጠጣ ገዴለም
የሰከርሽ ጊዜ 10 ብትሆን አለም
ኣላፊ አይጠፋበት ጎዳናው ምን ግዱ
ስትንገዳገጂ ቢቀናስ መንገዱ
ግዴለም ስከሪ
ቅጡን ያጣ መንደር በውሎ ትርምስ
ስትለፈልፊ ሰላሙስ ቢመለስ
ግዴለም እንጠጣ ግዴለም እንስከር
ሰበብ ስንፈልግ ተኳርፈን ከምንቀር
ግዴለም እንስከር...
@getmtg
@getmtg
አኮረፍሺኝ ብዬ እስኪነጋ ድረስ እጠጣልሻለሁ።
በተቀመጥኩበት ሌቱ እስከሚነጋ
በተፈጠርኩበት አለም እስኪረጋ
እሰክርልሻለሁ
ወንድ ልጅ አይደለሁ...
የላንቺ እንዳላልኩኝ ሴት ሁሉ አትፈጠር
ዛሬ ሰው አላውቅም ከ ኮማሪ በቀር
ደስታ እንደሞላኝ...
ቀ-ጭን ወገብሽን በጆቼ አቅፌ
ቅፅበቱ ይገርመኛል
ያረቄ መለኪያ ሲውል ከመዳፌ
የኮማሪት ገላ ሲኖር ከጉንፌ
ከትንፋሽሽ ውጪ አልሞቅም ያልኩኝ ሰው
ላረቄ ሽታ ነው ልቤ ሚናውዘው
ይምታታብኝ ያዘ
ያንቺና ያረቄው አመልና ነገር
ያንቺና መለኪያው አቋም አፈጣጠር
ብስቅ ብፈነድቅ ካንቺ ጋር አልነበር
ዛሬ አያምርብኝም ካልጠጣሁኝ በቀር
ካልሰከርኩኝ በቀር።
ተይ አታስኮንኚኝ
እንደ መጥፎ ቅዠት ደርሰሽ አታባኚኝ
ነይ እስኪ ልጋብዝሽ..
ትንሽ ጎንጨት በይ ይህን ካቲካላ
መውደዴን ቢያሳይሽ አስክሮ በመላ
ነይማ እንሞክረው...
ችለን ስንሔድበት የጣለንን መንገድ
ያሰምርልን እንደው ሰክሮ መንገዳገድ
ግድ የለም አትፍሪ ዝምብለን እንጠጣ
በዛ ከተባለ..
ብትወጂኝ ነውንጂ ሌላ ምን ሊመጣ።
ስካር የተባለ አንድ እንዳይቀርብሽ
አቅላችንን ስተን ሰፈር እንረብሽ
ማን ያውቃል
ስትሰክሪ ይሆናል 'ርምጃ ሚያምርብሽ።
ያዢና ፉት በይ እንጠጣ ገዴለም
የሰከርሽ ጊዜ 10 ብትሆን አለም
ኣላፊ አይጠፋበት ጎዳናው ምን ግዱ
ስትንገዳገጂ ቢቀናስ መንገዱ
ግዴለም ስከሪ
ቅጡን ያጣ መንደር በውሎ ትርምስ
ስትለፈልፊ ሰላሙስ ቢመለስ
ግዴለም እንጠጣ ግዴለም እንስከር
ሰበብ ስንፈልግ ተኳርፈን ከምንቀር
ግዴለም እንስከር...
@getmtg
@getmtg
👏5❤3👍2🥰1😍1
፡
።።።።።በእንተ ቅንዐት።።።።።።
መቼም! መቼም! አላቅ ዝቼም ፡
አላውቅም ተኩሼ ስቼም፣
ያባቴ ልጅ ፀጉሬ ጎፈር ፡
ያምላኬ ልጅ ገላዬ አፈር፣
ሰራሁ ብዬ ጠንከር ደፈር ፡
ሲሳካ መጠጡ ከንፈር፣
ሳብ አረጉኝ ትንሽ ጎተት ፡
ግን አልፈራም አስማት መተት፣
ትንቢት አናጋሪ ፡ እውነት አመስካሪ ፣
እኔው ነኝ ጠበቃው የቅዬው ተጠሪ ፣
አሳየሁት ለነገሌ ፡ ያለመውን ይዤ ግሌ፣
ገና ብዙ ታያላችሁ ፡
ክብሬ ዱዳ እስኪያረጋችሁ!
©Based on true story
✍️Zemed
@getmtg
@getmtg
።።።።።በእንተ ቅንዐት።።።።።።
መቼም! መቼም! አላቅ ዝቼም ፡
አላውቅም ተኩሼ ስቼም፣
ያባቴ ልጅ ፀጉሬ ጎፈር ፡
ያምላኬ ልጅ ገላዬ አፈር፣
ሰራሁ ብዬ ጠንከር ደፈር ፡
ሲሳካ መጠጡ ከንፈር፣
ሳብ አረጉኝ ትንሽ ጎተት ፡
ግን አልፈራም አስማት መተት፣
ትንቢት አናጋሪ ፡ እውነት አመስካሪ ፣
እኔው ነኝ ጠበቃው የቅዬው ተጠሪ ፣
አሳየሁት ለነገሌ ፡ ያለመውን ይዤ ግሌ፣
ገና ብዙ ታያላችሁ ፡
ክብሬ ዱዳ እስኪያረጋችሁ!
©Based on true story
✍️Zemed
@getmtg
@getmtg
🔥4❤3👏3
፡
ላየኝማ ......
ስፈግግ ደልቶኝ ይመስላል
ሳቀና ያልጎደለብኝ
ለቃኘኝ ለአይን ሞልቼ
እንደፈካሁኝ ታይቼ
ለእኔ ግን መች አማረብኝ
ባዶ ነው ሁለ ድባቡ
ተማምነውበት አለልኝ
ያሉት ሰው ሲታጣ ከጎን
ምን አለ ልብ የሚያጨልም
ሙሉነት እየናፈቁ
ሰው ከቦት ብቻ እንደመሆን
ተጓዝኩኝ በቀናው መንገድ
ወና ቤት መሆኔን ሳ'ቅ ነው
ተስቶኝ የምንገዳገድ
እረገጥኩ የእግዜር ደጁን
ዝምታው ቢበረታ እንኳ
አይተውምና ወዳጁን
፡
ከራስ ጋር መኗኗር ይዞት
ብቻነት ዙሯን ስታጦፍ ለፀና እየታገለ
ምንጊዜም ከርሞ እንዳዲስ
ሰው መቅረብ ያስፈራስ የለ?
ቀን ደርሶ ስኬት ሲለግስ
"ታድሎ" ሲሉ ሰማሁኝ
ለራሴ ከሰው ጎድዬ
በናቀኝ ባከበረኝ አፍ
ስመጥር ሆኜ ታማሁኝ
መች አዩትና የውስጤን
ወዳጁ በራቀው ቁጥር
ተዛዝኖ እንደጠቆረ
አብሮነት ትርጉሙን ሲያጣ
ያኔ ነው እንደ ልማዱ
............ ባዶነት ጓዙን ያቆረ፡፡
(ሀሳቡን በግጥም እንድፅፍለት ለጠየቀኝ ሰው ይድረስልኝ😊)
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
ላየኝማ ......
ስፈግግ ደልቶኝ ይመስላል
ሳቀና ያልጎደለብኝ
ለቃኘኝ ለአይን ሞልቼ
እንደፈካሁኝ ታይቼ
ለእኔ ግን መች አማረብኝ
ባዶ ነው ሁለ ድባቡ
ተማምነውበት አለልኝ
ያሉት ሰው ሲታጣ ከጎን
ምን አለ ልብ የሚያጨልም
ሙሉነት እየናፈቁ
ሰው ከቦት ብቻ እንደመሆን
ተጓዝኩኝ በቀናው መንገድ
ወና ቤት መሆኔን ሳ'ቅ ነው
ተስቶኝ የምንገዳገድ
እረገጥኩ የእግዜር ደጁን
ዝምታው ቢበረታ እንኳ
አይተውምና ወዳጁን
፡
ከራስ ጋር መኗኗር ይዞት
ብቻነት ዙሯን ስታጦፍ ለፀና እየታገለ
ምንጊዜም ከርሞ እንዳዲስ
ሰው መቅረብ ያስፈራስ የለ?
ቀን ደርሶ ስኬት ሲለግስ
"ታድሎ" ሲሉ ሰማሁኝ
ለራሴ ከሰው ጎድዬ
በናቀኝ ባከበረኝ አፍ
ስመጥር ሆኜ ታማሁኝ
መች አዩትና የውስጤን
ወዳጁ በራቀው ቁጥር
ተዛዝኖ እንደጠቆረ
አብሮነት ትርጉሙን ሲያጣ
ያኔ ነው እንደ ልማዱ
............ ባዶነት ጓዙን ያቆረ፡፡
(ሀሳቡን በግጥም እንድፅፍለት ለጠየቀኝ ሰው ይድረስልኝ😊)
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
👏6👍2❤1😭1
፡
በዜሮ ...
(አሌክስ አብርሃም)
አንድ ጓደኛየ መንጃ ፈቃድ አውጥቶ መኪና መንዳት በጀመረ በመጀመሪያው ቀን በሰላም በእግሬ ከምሄድበት ጠራኝና
"ና ግባ አደባባዮን ላሻግርህ" አለኝ
"ግዴለም በእግሬ እሻገራለሁ" አልኩ። ነዝንዞ አስገባኝና ጋቢና አስቀመጠኝ። መንግስትና ህዝብ ንዳ ብሎ ፈቃድ ከሰጠው እኔ ማነኝ ችሎታውን የምጠራጠር ብየ ተመቻቸሁ። ገና በሩን ከመዝጋቴ ስለመኪና ባህሪና ስለአነዳድ ቴክኒክ ልቤ እስኪደክም ያስረዳኝ ጀመር። ያለምንም ዓላማ ከተማችንን አንድ ጊዜ አዞረኝ። እስከዚህ ደህና ነበር።
"ይሄ ፍሬን ይባላል፣ ድንገተኛ ነገር ...ለምሳሌ ሰው ፣ አህያ ወይም የተናኘ ባል የሚነዳው መኪና ቢገቡብህ ማቆሚያ ነው" አለና አጎንብሶ ፍሬኑንን ይፈልግ ጀመረ...(ተናኘ ሹፌር ያገባች የቀድሞ ፍቅረኛው ናት፤ከነቂሙ ነው መንጃ ፈቃድ የያዘው?) "ፍሬኑን እስክትፈልግ ግን ....ከማለቴ ፍሬኑን አግኝቶ ባለ በሌለ ሀይሉ ረገጠው። ወደፊት ተወርውሬ የሆነ ነገር ጋር ተጋጭቸ ተመለስኩ። ዘና ብሎ "አሁን የገጨኸው ዳሽ ቦርድ ይባላል የትም አገር የሚያጋጥም ነገር ነው" አለና ቀጠለ። ደረቴን ደግፌ እያሳልኩ ዝም አልኩ።
ብቻ እንዲህ አሰቃይቶኝ በመጨረሻ "አንዲት ብዙ ሹፌሮች ያልባነኑባት ቴክኒክ ላሳይህ ወደፊት ይጠቅምህ ይሆናል" አለኝ። ወይ እዳየ። ከዚህ ሁሉ ለዓመታት የነዳ ሹፌር ተደብቆ ገና በአንድ ቀን ምን ተገልጦለት ይሆን እያልኩ ሳስብ በከተማችን አለ ወደሚባለው ቁልቁለት መንገድ ወሰደኝና "አሁን እዚህ ቁልቁለት ላይ ሞተሩን ታጠፋውና በዜሮ ትሄዳለህ ...መሪዋ ላይ ብቻ መጫወት ነው...ነዳጅ አተረፍክ ማለት ነው አባቴ" ብሎ ትልቅ ግኝት እንደነገረኝ አይነት በኩራት ሀሀሀሀሀ ብሎ ሳቀ። እኔ ግን ነፍሴ ተጨነቀች። መኪናው ወደታች ፍጥነት እየጨመረ መምዘግዘግ ጀመረ ። ወገኖቸ ባጭሩ ፍሬን ቢረግጥ ምን ቢረግጥ (እኔን ሁሉ እግሬን ቢረግጥ) መኪናው አልቆምም አለ። አታምኑኝም ዞር ስል የሹፌሩ በር ተከፍቶ አጅሬው ሲዘል ተገጣጠምን። ለደይቃወች ራሱን በሚነዳ መኪና ከተጓዝኩ በኋላ .... መኪናዋና እኔ ለግንባታ ፒራሚድ መስሎ የተከመረ አሸዋና ጠጠር ክምር ጫፍ ላይ ጉብ አልን። እዚህ ቴውድሮስ አደባባይ ያለውን የአፄ ቴውድሮስን የመድፍ ሀውልት ነበር የምንመስለው።
አሁን ያለንበትን የኑሮ ሁኔታ ሳየው፣ የሆነ ቴክኒክ ላሳያችሁ ብሎ ያሳፈረን ሹፌር ዘሎ የወረደ እስኪመስለኝ ቀላል እየተምዘገዘግን ነው?! ብቻ ማረፊያችንን ያሳምረው። ለእኔ በነጠላው የደረሰ አምላክ በጅምላ ይድረስልን።
@getmtg
@getmtg
በዜሮ ...
(አሌክስ አብርሃም)
አንድ ጓደኛየ መንጃ ፈቃድ አውጥቶ መኪና መንዳት በጀመረ በመጀመሪያው ቀን በሰላም በእግሬ ከምሄድበት ጠራኝና
"ና ግባ አደባባዮን ላሻግርህ" አለኝ
"ግዴለም በእግሬ እሻገራለሁ" አልኩ። ነዝንዞ አስገባኝና ጋቢና አስቀመጠኝ። መንግስትና ህዝብ ንዳ ብሎ ፈቃድ ከሰጠው እኔ ማነኝ ችሎታውን የምጠራጠር ብየ ተመቻቸሁ። ገና በሩን ከመዝጋቴ ስለመኪና ባህሪና ስለአነዳድ ቴክኒክ ልቤ እስኪደክም ያስረዳኝ ጀመር። ያለምንም ዓላማ ከተማችንን አንድ ጊዜ አዞረኝ። እስከዚህ ደህና ነበር።
"ይሄ ፍሬን ይባላል፣ ድንገተኛ ነገር ...ለምሳሌ ሰው ፣ አህያ ወይም የተናኘ ባል የሚነዳው መኪና ቢገቡብህ ማቆሚያ ነው" አለና አጎንብሶ ፍሬኑንን ይፈልግ ጀመረ...(ተናኘ ሹፌር ያገባች የቀድሞ ፍቅረኛው ናት፤ከነቂሙ ነው መንጃ ፈቃድ የያዘው?) "ፍሬኑን እስክትፈልግ ግን ....ከማለቴ ፍሬኑን አግኝቶ ባለ በሌለ ሀይሉ ረገጠው። ወደፊት ተወርውሬ የሆነ ነገር ጋር ተጋጭቸ ተመለስኩ። ዘና ብሎ "አሁን የገጨኸው ዳሽ ቦርድ ይባላል የትም አገር የሚያጋጥም ነገር ነው" አለና ቀጠለ። ደረቴን ደግፌ እያሳልኩ ዝም አልኩ።
ብቻ እንዲህ አሰቃይቶኝ በመጨረሻ "አንዲት ብዙ ሹፌሮች ያልባነኑባት ቴክኒክ ላሳይህ ወደፊት ይጠቅምህ ይሆናል" አለኝ። ወይ እዳየ። ከዚህ ሁሉ ለዓመታት የነዳ ሹፌር ተደብቆ ገና በአንድ ቀን ምን ተገልጦለት ይሆን እያልኩ ሳስብ በከተማችን አለ ወደሚባለው ቁልቁለት መንገድ ወሰደኝና "አሁን እዚህ ቁልቁለት ላይ ሞተሩን ታጠፋውና በዜሮ ትሄዳለህ ...መሪዋ ላይ ብቻ መጫወት ነው...ነዳጅ አተረፍክ ማለት ነው አባቴ" ብሎ ትልቅ ግኝት እንደነገረኝ አይነት በኩራት ሀሀሀሀሀ ብሎ ሳቀ። እኔ ግን ነፍሴ ተጨነቀች። መኪናው ወደታች ፍጥነት እየጨመረ መምዘግዘግ ጀመረ ። ወገኖቸ ባጭሩ ፍሬን ቢረግጥ ምን ቢረግጥ (እኔን ሁሉ እግሬን ቢረግጥ) መኪናው አልቆምም አለ። አታምኑኝም ዞር ስል የሹፌሩ በር ተከፍቶ አጅሬው ሲዘል ተገጣጠምን። ለደይቃወች ራሱን በሚነዳ መኪና ከተጓዝኩ በኋላ .... መኪናዋና እኔ ለግንባታ ፒራሚድ መስሎ የተከመረ አሸዋና ጠጠር ክምር ጫፍ ላይ ጉብ አልን። እዚህ ቴውድሮስ አደባባይ ያለውን የአፄ ቴውድሮስን የመድፍ ሀውልት ነበር የምንመስለው።
አሁን ያለንበትን የኑሮ ሁኔታ ሳየው፣ የሆነ ቴክኒክ ላሳያችሁ ብሎ ያሳፈረን ሹፌር ዘሎ የወረደ እስኪመስለኝ ቀላል እየተምዘገዘግን ነው?! ብቻ ማረፊያችንን ያሳምረው። ለእኔ በነጠላው የደረሰ አምላክ በጅምላ ይድረስልን።
@getmtg
@getmtg
😁7👏3❤2
፡
አለሽ ወይ
(በዕውቀቱ ስዩም)
አለሽ ወይ አለሽ ወይ
አለሽ ወይ በጤና
ይመስገን ደመና
በገበሬው አጥንት መሬቴን እያረስኩ
እንጀራ ሲጠፋ ገበሬ እየጎረስኩ
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ደመና
ሰው ሲያፈርስ እያየሁ ሰው ሆኖ ቡልዶዘር
አንዱ ጭቃ ነገድ ሌላው የብረት ዘር
በፈረሰ ሰው ላይ በቆመ ሰገነት
ሲዖል አናቱ ላይ በታነፀ ገነት
ይኽን ኑሮ ብለው ጥቂቶች ሲኖሩ
ያለምንም ፀፀት ያለምንም ሃፍረት
ይህንን እያየሁ በታላቅ ፅሞና
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ዳመና
በምቾት መዲና የምንዱባን ትዝብት
እንደ ሀሩር ልፎኝ
በጠዳው ጎዳና
ለማኝ ብላቴና
እንደ ጉቶ አናቅፎኝ
ሃፍረት እንደ ዝናር ከፊት ከኋላ ኣቅፎኝ
ልክ እንደ ገባሮች ለመኖር እያቀድሁ
በጌቶች መሶብም እጄን እየሰደድሁ
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ደመና
ወይ በሩን አሳዪን ወይ ጠቁሚን መላ
ማዕበል ሲቃረብ ያመልጣል ሺመላ
በነፋስ ገፅ ፊት ይሸሻል ደመና
የኔ አዚም ያለበት ያ’ገሬ ሰው ግና
በስጋ ደም አጥንት የተሰራ አይመስል
እንደ ኮንሶ ሃውልት የመቃብር ምስል
አይሸሽ አያባርር ወይ አይተነፍስ ቃል
እንጨት ሆኖ ቆሞ ሰደድ ይጠብቃል
ይህንን እያየሁ
ሁኘ በጥሞና
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ደመና
አንቺ ግን አለሽ ወይ እኔ አለሁ በደህና
አለሁ ግርምት ወሮኝ
ምላሱን በምላጭ እንደተሰለበ
ምናገረው ኖሮኝ
የምለው ቸግሮኝ።
@getmtg
@getmtg
አለሽ ወይ
(በዕውቀቱ ስዩም)
አለሽ ወይ አለሽ ወይ
አለሽ ወይ በጤና
ይመስገን ደመና
በገበሬው አጥንት መሬቴን እያረስኩ
እንጀራ ሲጠፋ ገበሬ እየጎረስኩ
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ደመና
ሰው ሲያፈርስ እያየሁ ሰው ሆኖ ቡልዶዘር
አንዱ ጭቃ ነገድ ሌላው የብረት ዘር
በፈረሰ ሰው ላይ በቆመ ሰገነት
ሲዖል አናቱ ላይ በታነፀ ገነት
ይኽን ኑሮ ብለው ጥቂቶች ሲኖሩ
ያለምንም ፀፀት ያለምንም ሃፍረት
ይህንን እያየሁ በታላቅ ፅሞና
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ዳመና
በምቾት መዲና የምንዱባን ትዝብት
እንደ ሀሩር ልፎኝ
በጠዳው ጎዳና
ለማኝ ብላቴና
እንደ ጉቶ አናቅፎኝ
ሃፍረት እንደ ዝናር ከፊት ከኋላ ኣቅፎኝ
ልክ እንደ ገባሮች ለመኖር እያቀድሁ
በጌቶች መሶብም እጄን እየሰደድሁ
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ደመና
ወይ በሩን አሳዪን ወይ ጠቁሚን መላ
ማዕበል ሲቃረብ ያመልጣል ሺመላ
በነፋስ ገፅ ፊት ይሸሻል ደመና
የኔ አዚም ያለበት ያ’ገሬ ሰው ግና
በስጋ ደም አጥንት የተሰራ አይመስል
እንደ ኮንሶ ሃውልት የመቃብር ምስል
አይሸሽ አያባርር ወይ አይተነፍስ ቃል
እንጨት ሆኖ ቆሞ ሰደድ ይጠብቃል
ይህንን እያየሁ
ሁኘ በጥሞና
አለሁኝ በደህና
ይመስገን ደመና
አንቺ ግን አለሽ ወይ እኔ አለሁ በደህና
አለሁ ግርምት ወሮኝ
ምላሱን በምላጭ እንደተሰለበ
ምናገረው ኖሮኝ
የምለው ቸግሮኝ።
@getmtg
@getmtg
❤3👏2
፡
ከእለታት ባንዱ ሀሳብ
ያልመንህ ነገር ውጦት
ምስኪን ልቡን ያሸፈተ
እንደ ተራ ቀላል ነገር
እልህ መንገድ ሲጠርግለት
የጥል በሩን የከፈተ
ወይም ወይም ........
ከእለታት ሌላው ሲያዝን
ግድየለቱን በሳቅ ሞልቶ
በንቀቱ የተመካ
ከራስ በላይ ንፋስ ባዩ
ያልሞላለት ባዶነቱን
አለኝ በሚል ቃል የለካ
ንፉግ ሆኖ እንደ ለጋስ
ጥሩ መስሎ ግፍ የሆነ
ለሰው ቀርቶ ለሱነቱ
ታምኖም እንኳን ያልታመነ
የጭልምቱን ጓዳ ሲሞቅ
በድን ገላን ተሸክሞ
የቁም ሞቱን የሚያፋጥን
አጉል ጥጋብ ልቡን አንቆት
የጠፋበት የሀቅ ውጥን
ደረት ነፍቶ የሚያቅራራ
በአጉል አልህ የተኳለ
ስድ አመሉን ተከናንቦ
መሀላችን ድንገት ካለ
የወጠረው ተንፍሶለት
በልብነት አደብ ገዝቶ
ቅን እሳቤን እስኪቀበል
መንገድ ሁሉ ጨርቅ ሆኖለት
በእንቅፋት ሳይናጋ
በመጣበት ጥርግ ይበል!
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
ከእለታት ባንዱ ሀሳብ
ያልመንህ ነገር ውጦት
ምስኪን ልቡን ያሸፈተ
እንደ ተራ ቀላል ነገር
እልህ መንገድ ሲጠርግለት
የጥል በሩን የከፈተ
ወይም ወይም ........
ከእለታት ሌላው ሲያዝን
ግድየለቱን በሳቅ ሞልቶ
በንቀቱ የተመካ
ከራስ በላይ ንፋስ ባዩ
ያልሞላለት ባዶነቱን
አለኝ በሚል ቃል የለካ
ንፉግ ሆኖ እንደ ለጋስ
ጥሩ መስሎ ግፍ የሆነ
ለሰው ቀርቶ ለሱነቱ
ታምኖም እንኳን ያልታመነ
የጭልምቱን ጓዳ ሲሞቅ
በድን ገላን ተሸክሞ
የቁም ሞቱን የሚያፋጥን
አጉል ጥጋብ ልቡን አንቆት
የጠፋበት የሀቅ ውጥን
ደረት ነፍቶ የሚያቅራራ
በአጉል አልህ የተኳለ
ስድ አመሉን ተከናንቦ
መሀላችን ድንገት ካለ
የወጠረው ተንፍሶለት
በልብነት አደብ ገዝቶ
ቅን እሳቤን እስኪቀበል
መንገድ ሁሉ ጨርቅ ሆኖለት
በእንቅፋት ሳይናጋ
በመጣበት ጥርግ ይበል!
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
❤4👍2💯1
😁(18+)
።።።።አንቀፀ ንሰሐ።።።።
ይኸው ልናዘዘው የክፋት ልፋፌን፣
ከፊትሽ ልቅደደው የበደል እራፌን፣
ኑዛዜ ቢያጠዳው የክህደት እድፌን፣
አንቺን የቀረብሁሽ ለአልጋ መአዱ፣
በሰው ስለቀናሁ ከሴት ጋር ....
ልጠቀምብሽ ነው ጎጆ የምወጣ፣
ብዙ ጥሪት አለሽ 'ካባትሽ የመጣ፣
ልሞላብሽ አሰብሁ ባዶ ጉሮሮዬን፣
ልከብርብሽ ነበር ላስውበው ጓሮዬን፣
ከሰው ላለማነስ አንቺን አገባሁሽ፣
'ካምሮቴ እንዳልጎል አንቺን አረከስሁሽ፣
እርግጥ ነው አልክድም ሌላም ሴት አምሮኛል፣
ልክስክስ አመሌ ለእህትሽ ድሮኛል፣
ይሄ ሁሉ ሲሆን ይህ ሁሉ ሲወድም፣
ያንቺ ቀና ልብሽ እኔኑ ቢወድም፣
ሌላ ባያሰኝሽ ክፋቴ ባይገፋሽ ፣
ልቀጥል አልችልም በደሌን በጭራሽ፣
እናም አሰናብቺኝ ከማዕሰረ ግፌ፣
ይቅርታሽን ላንባ በሬን ተደግፌ።
✍️Zemed
@getmtg
@getmtg
።።።።አንቀፀ ንሰሐ።።።።
ይኸው ልናዘዘው የክፋት ልፋፌን፣
ከፊትሽ ልቅደደው የበደል እራፌን፣
ኑዛዜ ቢያጠዳው የክህደት እድፌን፣
አንቺን የቀረብሁሽ ለአልጋ መአዱ፣
በሰው ስለቀናሁ ከሴት ጋር ....
ልጠቀምብሽ ነው ጎጆ የምወጣ፣
ብዙ ጥሪት አለሽ 'ካባትሽ የመጣ፣
ልሞላብሽ አሰብሁ ባዶ ጉሮሮዬን፣
ልከብርብሽ ነበር ላስውበው ጓሮዬን፣
ከሰው ላለማነስ አንቺን አገባሁሽ፣
'ካምሮቴ እንዳልጎል አንቺን አረከስሁሽ፣
እርግጥ ነው አልክድም ሌላም ሴት አምሮኛል፣
ልክስክስ አመሌ ለእህትሽ ድሮኛል፣
ይሄ ሁሉ ሲሆን ይህ ሁሉ ሲወድም፣
ያንቺ ቀና ልብሽ እኔኑ ቢወድም፣
ሌላ ባያሰኝሽ ክፋቴ ባይገፋሽ ፣
ልቀጥል አልችልም በደሌን በጭራሽ፣
እናም አሰናብቺኝ ከማዕሰረ ግፌ፣
ይቅርታሽን ላንባ በሬን ተደግፌ።
✍️Zemed
@getmtg
@getmtg
❤3😭2🔥1👏1
፡
ለእግዜር የተላከ ደብዳቤ
(አሌክስ አብርሃም)
እንደምነህ እግዜር
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
እመጣለሁ ብለህ ቆየህሳ ምነው
እኛማ ......
ለእልፍ አእላፍ ጠበቃ
ማመልከቻ ፅፈን
ለወፈ ሰማይ ህዝብ
መድረክ ላይ ለፍፈን
ፀሎት ቤታችንን እኛው ላይ ቆልፈን
የምድር አተካራ ህግጋቱን አልፈን
ደብዳቤ ላክንልህ .......
አይንህን ካየነው
ሁለት ሺህ ዘመን እንደቀልድ አለፈ
የመምጣትህ ዘመን
እየኮሰመነ መቅረትህ ገዘፈ
እንደውም እንደውም
በእመጣለሁ ተስፋ
ሁለት ሺህ ዘመን ገትሮን ከጠፋ
በቀጠሮ ሰአት መምጣት ከተሳነው
....... እግዜር ሀበሻ ነው
እያሉ ያሙሃል
እኔ ምን አውቃለሁ ....
አመስግነው ሲሉኝ እልልታ የማቀልጥ
ቃሉን ስማ ሱሉኝ
ሰባኪው እግር ስር በደስታ 'ምቀመጥ
እግዚኦ በል ሲሉኝ እንባዮን የማፈስ
ሃሌሉያ ሲሉኝ በሳቅ ልቤ 'ሚፈስ
ምናምንቴ እውቀት ውስጤ ያልፀደቀ
እንበረከክበት ጉልበቴ ያለቀ
.... እኔ ምን አውቃለሁ ....
ግን አንተ ደህና ነህ .....
ከምር እንደሚያሙት ምፅአት ቀረ እንዴ
የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ
አትከፋም አንዳንዴ?
ከሆነስ ሆነና
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
አብረሃም ሰላም ነው?
እዛስ ቤት ገነባ
ዛሬስ በድንኳን ነው?
እኛማ ይኸውልህ
በቤት ኪራይ ችንካር እየተሰቀልን
ኤሎሄ እንላለን ዳቦ እንድትጥልልን
ወደ ላይ ገነባን
ወደ ጎን አሰፋን
ወደላይም ከላይ ወደ ግንም ከጎን
እንደ ጉድ ተገፋን
ቤት ለእንግዳ ማለት ጭራሹኑ ጠፋን
አባታችን ሙሴ እንዴት ነው ለክብሩ
ውቅያኖስ መግፊያው ደህና ናት በትሩ
እኛማ ይኸውልህ
እንጀራ ፍለጋ ባህር ስናቋስጥ
የተስፋዋን ምድር አሸዋ ሳንረግጥ
የትም ውሃ በላን የትም አሳ ላሰን
ንገርልንና በትሩን ያውሰን
እናልህ እግዜር ሆይ
ከተስፋዋ ምድር
ወደሌላ ተስፋ አለን እየኳተን
መሄጃው ሲገርመን
መመለሻው መንገድ መቆሚያ ቦታ አጥተን
ለአባታችን ሙሴ እንደምትልልን
የመሄድ ዘመን ነው
ባህር የመሻገር ዱላህን ላክልን
....... ብሎሃል በልልኝ
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
ዳዊትስ ደህና ነው?
ዛሬም ይዘምራል
ዛሬም ይፎክራል
ሰላም ነው ጠጠሩ ሰላም ናት ወንጭፉ
እዛስ አቅል ገዛ
ጎልያድ ተራራው ጎልያድ ግዙፉ
እልፍ አእላፍ ጎልያድ
ከቦን ሲደነፋ
ወንጭፉን ጠቅልሎ
ምነው ዳዊት ጠፋ
ብሎሃል በልልኝ
ለረከሰ ጠጠር ለሞላ ወርዋሪ
ወንጭፍህን ስጠው
ለዚህ ታሪክ አውሪ
ብለህ እዘዝልን
እንዴት ነህ ጌታ ሆይ
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
የሙሴ አልጋ ወራሽ
እያሱስ ሰላም ነው?
ያቆማትን ፀሀይ ግቢ ቢላት ምነው
አንተ እንደምታውቀው
እስራ ሶስት ወራት ነው
ፀሀይ የምንሞቀው
አረ ፀሀይ በዛ
አረ ፀሀይ በዛ
የመጣው ወር ሁሉ ፀሀይ እየዘለ
የተሾመው ሁሉ ፀሀይ ነኝ እያለ
የአስራ ሶስት ወር የእግዜር ፀሀይ
የአስራ ስስት ወር የእግዜር ጀንበር
ባቃጠላት ምድጃ ሀገር
ምን ተአምር ሊኖር ይችላል
ፀሀይ ሆኖ እንደመፈጠር
አረ እግዜር በእናትህ በጭንቅ አማላጇ
ባዘለ ጀርባዋ ባቀፉት እጆቿ
ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሆነህ ና
...... ሙቀት ገደለና
እናልህ ጌታ ሆይ ማጣፊያው አጥሮናል
ስም ያለው ሞኝ ነው ሁሉም ይጠራናል
ጳውሎስ ሲሉን አቤት
ጴጥሮስ ሲሉን ወዬ
ይሁዳ ሲሉንም አቤት እንላለን
ስማችንን ሸጠን
ሰላሳ ጭብጨባ እንቀበላለን
ተወው የእኛን ነገር
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
ሄዋንስ ደህና ናት?
ያው የልጅ ልጆቿ በእግሯ ተተክተው
የፍሬው ሲገርመን ግንዱንም አንክተው
ለፍጥረተ አዳም ባይኑ ይገምጡታል
ሴጣንም ደህና ነው ኑሮ ተስማምቶታል
ሰውን ለማሳሳት ላይ ታች ማለት ትቷል
ሳይጠራው የሚጎርፍ ህዝብ በዝቶለታል
አረ እግዜር በእናትህ በጭንቅ አማላጇ
ባዘለ ጀርባዋ ባቀፉት እጆቿ
ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሆነህ ና
...... ሙቀት ገደለና
@getmtg
@getmtg
ለእግዜር የተላከ ደብዳቤ
(አሌክስ አብርሃም)
እንደምነህ እግዜር
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
እመጣለሁ ብለህ ቆየህሳ ምነው
እኛማ ......
ለእልፍ አእላፍ ጠበቃ
ማመልከቻ ፅፈን
ለወፈ ሰማይ ህዝብ
መድረክ ላይ ለፍፈን
ፀሎት ቤታችንን እኛው ላይ ቆልፈን
የምድር አተካራ ህግጋቱን አልፈን
ደብዳቤ ላክንልህ .......
አይንህን ካየነው
ሁለት ሺህ ዘመን እንደቀልድ አለፈ
የመምጣትህ ዘመን
እየኮሰመነ መቅረትህ ገዘፈ
እንደውም እንደውም
በእመጣለሁ ተስፋ
ሁለት ሺህ ዘመን ገትሮን ከጠፋ
በቀጠሮ ሰአት መምጣት ከተሳነው
....... እግዜር ሀበሻ ነው
እያሉ ያሙሃል
እኔ ምን አውቃለሁ ....
አመስግነው ሲሉኝ እልልታ የማቀልጥ
ቃሉን ስማ ሱሉኝ
ሰባኪው እግር ስር በደስታ 'ምቀመጥ
እግዚኦ በል ሲሉኝ እንባዮን የማፈስ
ሃሌሉያ ሲሉኝ በሳቅ ልቤ 'ሚፈስ
ምናምንቴ እውቀት ውስጤ ያልፀደቀ
እንበረከክበት ጉልበቴ ያለቀ
.... እኔ ምን አውቃለሁ ....
ግን አንተ ደህና ነህ .....
ከምር እንደሚያሙት ምፅአት ቀረ እንዴ
የስናፍጭ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ
አትከፋም አንዳንዴ?
ከሆነስ ሆነና
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
አብረሃም ሰላም ነው?
እዛስ ቤት ገነባ
ዛሬስ በድንኳን ነው?
እኛማ ይኸውልህ
በቤት ኪራይ ችንካር እየተሰቀልን
ኤሎሄ እንላለን ዳቦ እንድትጥልልን
ወደ ላይ ገነባን
ወደ ጎን አሰፋን
ወደላይም ከላይ ወደ ግንም ከጎን
እንደ ጉድ ተገፋን
ቤት ለእንግዳ ማለት ጭራሹኑ ጠፋን
አባታችን ሙሴ እንዴት ነው ለክብሩ
ውቅያኖስ መግፊያው ደህና ናት በትሩ
እኛማ ይኸውልህ
እንጀራ ፍለጋ ባህር ስናቋስጥ
የተስፋዋን ምድር አሸዋ ሳንረግጥ
የትም ውሃ በላን የትም አሳ ላሰን
ንገርልንና በትሩን ያውሰን
እናልህ እግዜር ሆይ
ከተስፋዋ ምድር
ወደሌላ ተስፋ አለን እየኳተን
መሄጃው ሲገርመን
መመለሻው መንገድ መቆሚያ ቦታ አጥተን
ለአባታችን ሙሴ እንደምትልልን
የመሄድ ዘመን ነው
ባህር የመሻገር ዱላህን ላክልን
....... ብሎሃል በልልኝ
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
ዳዊትስ ደህና ነው?
ዛሬም ይዘምራል
ዛሬም ይፎክራል
ሰላም ነው ጠጠሩ ሰላም ናት ወንጭፉ
እዛስ አቅል ገዛ
ጎልያድ ተራራው ጎልያድ ግዙፉ
እልፍ አእላፍ ጎልያድ
ከቦን ሲደነፋ
ወንጭፉን ጠቅልሎ
ምነው ዳዊት ጠፋ
ብሎሃል በልልኝ
ለረከሰ ጠጠር ለሞላ ወርዋሪ
ወንጭፍህን ስጠው
ለዚህ ታሪክ አውሪ
ብለህ እዘዝልን
እንዴት ነህ ጌታ ሆይ
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
የሙሴ አልጋ ወራሽ
እያሱስ ሰላም ነው?
ያቆማትን ፀሀይ ግቢ ቢላት ምነው
አንተ እንደምታውቀው
እስራ ሶስት ወራት ነው
ፀሀይ የምንሞቀው
አረ ፀሀይ በዛ
አረ ፀሀይ በዛ
የመጣው ወር ሁሉ ፀሀይ እየዘለ
የተሾመው ሁሉ ፀሀይ ነኝ እያለ
የአስራ ሶስት ወር የእግዜር ፀሀይ
የአስራ ስስት ወር የእግዜር ጀንበር
ባቃጠላት ምድጃ ሀገር
ምን ተአምር ሊኖር ይችላል
ፀሀይ ሆኖ እንደመፈጠር
አረ እግዜር በእናትህ በጭንቅ አማላጇ
ባዘለ ጀርባዋ ባቀፉት እጆቿ
ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሆነህ ና
...... ሙቀት ገደለና
እናልህ ጌታ ሆይ ማጣፊያው አጥሮናል
ስም ያለው ሞኝ ነው ሁሉም ይጠራናል
ጳውሎስ ሲሉን አቤት
ጴጥሮስ ሲሉን ወዬ
ይሁዳ ሲሉንም አቤት እንላለን
ስማችንን ሸጠን
ሰላሳ ጭብጨባ እንቀበላለን
ተወው የእኛን ነገር
ሰማይ ቤት እንዴት ነው
ሄዋንስ ደህና ናት?
ያው የልጅ ልጆቿ በእግሯ ተተክተው
የፍሬው ሲገርመን ግንዱንም አንክተው
ለፍጥረተ አዳም ባይኑ ይገምጡታል
ሴጣንም ደህና ነው ኑሮ ተስማምቶታል
ሰውን ለማሳሳት ላይ ታች ማለት ትቷል
ሳይጠራው የሚጎርፍ ህዝብ በዝቶለታል
አረ እግዜር በእናትህ በጭንቅ አማላጇ
ባዘለ ጀርባዋ ባቀፉት እጆቿ
ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሆነህ ና
...... ሙቀት ገደለና
@getmtg
@getmtg
❤8👏1
፡
ያምር ነበር እሱነቱ
ቅን እሳቤው ያኖር ነበር
ቀን መሻቱን ባያላላው
ደረስኩኝ ሲል ስኬት ደጃፍ
አለፍኩ ሲል ኑሮ ክሱን
የድንገቱን ውሃ በላው
ወትሮ ጎኑ የነበረ
እንደልቡ እየተራጨ
ክንዱን ሰዶ ያደገበት
የዛሬን ግን ምነው ከዳው?
ና ልንገርህ ብሎ ጠርቶ
ነፍሱን ስቦ ወሰደበት
ሂድ እንዳለው ታቹን ሄደ
ላዩን ሰማይ እየራቀው
ትጉ አይኖቹ ደርቀው ቀሩ
ከመንገዱ ሞት አነቀው
(መታሰቢያነቱ ለማላውቀው በድንገት ለተለየን ወንድማችን ይሁንልኝ፡፡)
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
ያምር ነበር እሱነቱ
ቅን እሳቤው ያኖር ነበር
ቀን መሻቱን ባያላላው
ደረስኩኝ ሲል ስኬት ደጃፍ
አለፍኩ ሲል ኑሮ ክሱን
የድንገቱን ውሃ በላው
ወትሮ ጎኑ የነበረ
እንደልቡ እየተራጨ
ክንዱን ሰዶ ያደገበት
የዛሬን ግን ምነው ከዳው?
ና ልንገርህ ብሎ ጠርቶ
ነፍሱን ስቦ ወሰደበት
ሂድ እንዳለው ታቹን ሄደ
ላዩን ሰማይ እየራቀው
ትጉ አይኖቹ ደርቀው ቀሩ
ከመንገዱ ሞት አነቀው
(መታሰቢያነቱ ለማላውቀው በድንገት ለተለየን ወንድማችን ይሁንልኝ፡፡)
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
😭6❤2👏1
፡
ስታየኝ
ስታየኝ!
ሰውነቴ ትርክክ
ጉልበቴ ብርክ ብርክ
ልቤ ድንብርብርብር
ሆዴ ሽብር ሽብር
አይኔ መሬት ስብር
ሀሞቴ ፍስስስ
ሀሳቤም ትርምስምስ
ቆዳዬ ልውጥውጥ
እሷን እያሰብኩ ከፍቅር አለም ጭልጥ።
ስታየኝ!
እኔነቴን እርስት
አዲስ ሆኜ ክስት
በአዲስ አለም ውስጥ
ያለመጠን ምስጥ
ክንፍ አውጥቼ ብርር
ሳይገድበኝ ድንበር
አድማስን ስሻገር
ከአድማስ በስተጀርባ
ሰማይ ቤት ስገባ
ከሰማይ ከፍ ስል
ሰማየ ሰማያት ወስዶ የሚከተኝ
በነዛ ውብ አይኖች ያቺ ልጅ ስታየኝ።
አይኖቿ ተአምር
ልብን የሚሰውር
ራስን የሚያስረሳ
ቀልብን የሚነሳ
ፍቅርን አስይዞ
ወደ ሰማይ ጉዞ
ወደ አዲስ አለም
ሳይተኙ በማለም።
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
ስታየኝ
ስታየኝ!
ሰውነቴ ትርክክ
ጉልበቴ ብርክ ብርክ
ልቤ ድንብርብርብር
ሆዴ ሽብር ሽብር
አይኔ መሬት ስብር
ሀሞቴ ፍስስስ
ሀሳቤም ትርምስምስ
ቆዳዬ ልውጥውጥ
እሷን እያሰብኩ ከፍቅር አለም ጭልጥ።
ስታየኝ!
እኔነቴን እርስት
አዲስ ሆኜ ክስት
በአዲስ አለም ውስጥ
ያለመጠን ምስጥ
ክንፍ አውጥቼ ብርር
ሳይገድበኝ ድንበር
አድማስን ስሻገር
ከአድማስ በስተጀርባ
ሰማይ ቤት ስገባ
ከሰማይ ከፍ ስል
ሰማየ ሰማያት ወስዶ የሚከተኝ
በነዛ ውብ አይኖች ያቺ ልጅ ስታየኝ።
አይኖቿ ተአምር
ልብን የሚሰውር
ራስን የሚያስረሳ
ቀልብን የሚነሳ
ፍቅርን አስይዞ
ወደ ሰማይ ጉዞ
ወደ አዲስ አለም
ሳይተኙ በማለም።
✍ Abosina
@getmtg
@getmtg
👏7❤3