፡
"ሰው ጥሩ ሲሆንልህ ጥሩ ለመሆን የሚያስገድድ አፀፋዊ ግዴታን የሚፈጥር ነገር በሰው ውስጥ ሳይኖር አይቀርም፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
"ሰው ጥሩ ሲሆንልህ ጥሩ ለመሆን የሚያስገድድ አፀፋዊ ግዴታን የሚፈጥር ነገር በሰው ውስጥ ሳይኖር አይቀርም፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
፡
"እውነተኛ ነጻነት የኅሊና ነጻነት ነው፡፡ የኅሊና ነጻነት ደግሞ እውነትን በማወቅና በመኖር ነጻ ከወጣ አእምሮ ብቻ የሚገኝ ጸጋ ነው፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
"እውነተኛ ነጻነት የኅሊና ነጻነት ነው፡፡ የኅሊና ነጻነት ደግሞ እውነትን በማወቅና በመኖር ነጻ ከወጣ አእምሮ ብቻ የሚገኝ ጸጋ ነው፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
👍2
፡
"በመምከር ውስጥ ተመካሪውን ደካማ አድርጎ የማየት ስስ መታበይ አለ፡ ሲኖሩት ግን ሌላ አለም ነው፡፡""
"አልተዘዋወረችም"
"በመምከር ውስጥ ተመካሪውን ደካማ አድርጎ የማየት ስስ መታበይ አለ፡ ሲኖሩት ግን ሌላ አለም ነው፡፡""
"አልተዘዋወረችም"
👍1
፡
ይቆጭ የለም እንዴ ....
በእጅ የያዙትን ወርቅ
መዳብ ነው እያሉ ክብሩን ያረክሱታል
እንደሆነ እንዳይሆን
ካለበት አውርደው ሁሉን ይነሱታል
ታድያ ......
የይለፍ ይለፍ ቀን
የረከሰ ስሙን የትዝብቱን ውጦ
ህያው እሱነቱን
መዳብነት ወርቁን ያሳያል ገልብጦ
፡
ይለፍለት እንጁ
ቀላል አልነበረም ባልሆኑት መታሰብ
ወትሮም ያለ ቦታው
ቅይምትን የሚጭር ከንቱ ቃል መሰብሰብ
ቀላል አልነበረም
ከሆኑበት ወርደው በአጉል ስም መጠራት
በሰው አፍ ውሎ አድሮ
በይሉኝታ እሳቤ
የአልሆን ኑሮን መፍራት
....... ቀላል አልነበረም
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
ይቆጭ የለም እንዴ ....
በእጅ የያዙትን ወርቅ
መዳብ ነው እያሉ ክብሩን ያረክሱታል
እንደሆነ እንዳይሆን
ካለበት አውርደው ሁሉን ይነሱታል
ታድያ ......
የይለፍ ይለፍ ቀን
የረከሰ ስሙን የትዝብቱን ውጦ
ህያው እሱነቱን
መዳብነት ወርቁን ያሳያል ገልብጦ
፡
ይለፍለት እንጁ
ቀላል አልነበረም ባልሆኑት መታሰብ
ወትሮም ያለ ቦታው
ቅይምትን የሚጭር ከንቱ ቃል መሰብሰብ
ቀላል አልነበረም
ከሆኑበት ወርደው በአጉል ስም መጠራት
በሰው አፍ ውሎ አድሮ
በይሉኝታ እሳቤ
የአልሆን ኑሮን መፍራት
....... ቀላል አልነበረም
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
፡
እልህ
ለጥበብ ቀዳሚው
ጥበብ መጀመሪያው ሲጋራ ማጤስ ነው
እያለ የሚያወራው
ያ ከንቱ ወዳጅሽ
እንዲህ ስላወራሽ .... ስቀሽ ነበር አሉ
ያውም .....
እጅሽን ዘርግተሽ
እግርሽን አንስተሽ
ይሁን
ይሁን
ይሁን
ሳቂ ችግር የለም
ግን
እኔ የምናደድ የምበሽቅ መስሎሽ
እንዴት ከ"ማንም" ጋር የትም ትሆኛለሽ፡፡
(በኤፍሬም ስዩም)
እልህ
ለጥበብ ቀዳሚው
ጥበብ መጀመሪያው ሲጋራ ማጤስ ነው
እያለ የሚያወራው
ያ ከንቱ ወዳጅሽ
እንዲህ ስላወራሽ .... ስቀሽ ነበር አሉ
ያውም .....
እጅሽን ዘርግተሽ
እግርሽን አንስተሽ
ይሁን
ይሁን
ይሁን
ሳቂ ችግር የለም
ግን
እኔ የምናደድ የምበሽቅ መስሎሽ
እንዴት ከ"ማንም" ጋር የትም ትሆኛለሽ፡፡
(በኤፍሬም ስዩም)
👍2
፡
አንዲት ፍሬ የአበባ ዘር
ተራራ ጫፍ የበቀለች
ሳትታቀድ እንደ ድንገት
አፈር ገልጣ ብቅ ያለች
ቅን ልቦናን የምትመኝ
አጎልባቿን የምትሻ
ወተው ከቅርብ የማያዩያት
ቢያዩዋት እንኳን 'ምትታለፍ በጥቅሻ
ለአይን ሞልቶ የሚያማልል
የሚያስቀና ፍካት ያላት
ደፍረው ጎኗ የማይቆሙ
በሩቁ ግን ሳር ቅጠሉ የሚመኛት
ያቺን ፍሬ ውብ አበባ
አንዱም ቆርጦ ሳይጠጋት
ሳያንኳኳ የአለሟን ደጅ
ያስፈራኛል መሽቶ እንዳይቀር
እሰጋለሁ በጊዜዋ ሳትቀጠፍ እንዳታረጅ
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
አንዲት ፍሬ የአበባ ዘር
ተራራ ጫፍ የበቀለች
ሳትታቀድ እንደ ድንገት
አፈር ገልጣ ብቅ ያለች
ቅን ልቦናን የምትመኝ
አጎልባቿን የምትሻ
ወተው ከቅርብ የማያዩያት
ቢያዩዋት እንኳን 'ምትታለፍ በጥቅሻ
ለአይን ሞልቶ የሚያማልል
የሚያስቀና ፍካት ያላት
ደፍረው ጎኗ የማይቆሙ
በሩቁ ግን ሳር ቅጠሉ የሚመኛት
ያቺን ፍሬ ውብ አበባ
አንዱም ቆርጦ ሳይጠጋት
ሳያንኳኳ የአለሟን ደጅ
ያስፈራኛል መሽቶ እንዳይቀር
እሰጋለሁ በጊዜዋ ሳትቀጠፍ እንዳታረጅ
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
👍4
፡
ዝግመተ ለውጥ
"እንጋባ" ሲል ጠየቃት አሳምነው፡፡
አልተቀበለችውም አስማሩ፡፡ "ወንድምና እህትነቱ ይበልጣል" አለችው፡፡
ተስማሙ፡፡
ቤቷ እየመጣ ይጠይቃታል፡፡
ቡና ታፈላለች ይጠጣሉ፡ ካላት ታቀርባለች - ይበላሉ፡፡
አውግተው ይለያያሉ፡፡
የትዳር ነገር ዳግም አልተነሳም፡፡
አሳምነው አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ መጣ፡፡
እንደመጣ የደረበውን ሹራብ አውልቆ አስቀመጠ፡፡ ስለሙቀቱ ብዙ አውርተው ተለያዩ፡፡
አስማሩ አሳምነው እረስቶት የሄደውን ሹራብ ልብሷን ስታጥብ አጠበችለት፡፡
ዳግም ሲመጣ ደርቦ ደራርቦ ነበርና የሚያወልቀው እንጂ የሚደርበው ልብስ አላስፈለገውም፡፡
ጃኬቱን አውልቅ ሄደ፡፡
አስማሩ አሁንም አጥባ አኖረችው፡፡
ሱሪውን ደርቦ መጣ "ወበቀኝ!" አወለቀው፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡
ካፓርቱን ጥሎ ሄደ፡
አጥባ አኖረችው፡፡
አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ ብርድ ልብሱን ለብሶ መጣ፡
አስማሩ "ምነው?" አለችው፡፡
"በጠራራ ፀሀይ ብርድ ሆዴ ገባ" አላት፡፡
"ምች ይሆናል" አለችው፡፡ የምች መድኃኒት ብታሽለት ተሻለው፡፡
ሲሻለው ብርድ ልብሱ አላስፈለገውም ጥሎት ሄደ፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡፡
ትንሽ ቆይቶ፡ ፍራሹን ተሸክሞ መጣ፡፡
"ምነው?" አለችው፡፡
"ላሳድሰው መሄዴ ነው፡፡ አይቼሽ ልለፍ ብዬ ነው" አላት፡፡
አመነችው፡፡
ጨዋታው ደራ፡ ፍራሹን እረስቶት ሄዶ ኖሮ እኩለ ሌሊት ቢመጣ አስማሩ ቦታ ስላጣች ፍራሹን ፍራሿ ላይ ደርባው ደረሰ፡፡ ያኔ "ተነሽ" ከማለት "ጠጋ በይ" ማለት ቀልሎ ተገኘ፡፡
ጠጋ አለች፡፡
(ኩርቢት)
ዝግመተ ለውጥ
"እንጋባ" ሲል ጠየቃት አሳምነው፡፡
አልተቀበለችውም አስማሩ፡፡ "ወንድምና እህትነቱ ይበልጣል" አለችው፡፡
ተስማሙ፡፡
ቤቷ እየመጣ ይጠይቃታል፡፡
ቡና ታፈላለች ይጠጣሉ፡ ካላት ታቀርባለች - ይበላሉ፡፡
አውግተው ይለያያሉ፡፡
የትዳር ነገር ዳግም አልተነሳም፡፡
አሳምነው አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ መጣ፡፡
እንደመጣ የደረበውን ሹራብ አውልቆ አስቀመጠ፡፡ ስለሙቀቱ ብዙ አውርተው ተለያዩ፡፡
አስማሩ አሳምነው እረስቶት የሄደውን ሹራብ ልብሷን ስታጥብ አጠበችለት፡፡
ዳግም ሲመጣ ደርቦ ደራርቦ ነበርና የሚያወልቀው እንጂ የሚደርበው ልብስ አላስፈለገውም፡፡
ጃኬቱን አውልቅ ሄደ፡፡
አስማሩ አሁንም አጥባ አኖረችው፡፡
ሱሪውን ደርቦ መጣ "ወበቀኝ!" አወለቀው፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡
ካፓርቱን ጥሎ ሄደ፡
አጥባ አኖረችው፡፡
አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ ብርድ ልብሱን ለብሶ መጣ፡
አስማሩ "ምነው?" አለችው፡፡
"በጠራራ ፀሀይ ብርድ ሆዴ ገባ" አላት፡፡
"ምች ይሆናል" አለችው፡፡ የምች መድኃኒት ብታሽለት ተሻለው፡፡
ሲሻለው ብርድ ልብሱ አላስፈለገውም ጥሎት ሄደ፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡፡
ትንሽ ቆይቶ፡ ፍራሹን ተሸክሞ መጣ፡፡
"ምነው?" አለችው፡፡
"ላሳድሰው መሄዴ ነው፡፡ አይቼሽ ልለፍ ብዬ ነው" አላት፡፡
አመነችው፡፡
ጨዋታው ደራ፡ ፍራሹን እረስቶት ሄዶ ኖሮ እኩለ ሌሊት ቢመጣ አስማሩ ቦታ ስላጣች ፍራሹን ፍራሿ ላይ ደርባው ደረሰ፡፡ ያኔ "ተነሽ" ከማለት "ጠጋ በይ" ማለት ቀልሎ ተገኘ፡፡
ጠጋ አለች፡፡
(ኩርቢት)
😁8
፡
ተ ሸ ክ መ ና ታ ል !!
እናቴ ሁልጊዜ እንድናጠና ስትመክረን እንዲህ ትላለች:-
“እናንተ ልጆች አጥኑ፣ ተማሩ እባካችሁ ! ...እኔ ባለመማሬ ነው ጉዴን ተሸክሜ የዋልኩት!"
ማንበብም መፃፍም ስለማትችል ንግግሯ በቁጭት ነበር፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ይሄ ተሸክማ የዋለችው ጉድ ምን እንደሆነ ለማወቅ ጓጉቼ ጠየቅኳት፣
"ማሚ የምን ጉድ ነው ተሽከመሽ የዋልሽው ?”
አወራችኝ ...
.......... ........ ..........
በደርግ ጊዜ መስከረም ሁለት ቀን ሕዝቡ በግድም ሆነ በውድ የድጋፍ ሰልፍ ይወጣ ነበር፡፡መስከረም ሁለት ደርግ ንጉሱን ገልብጦ ሥልጣን የያዘበት ቀን ነው፡፡ በአጭር አገላለፅ መስከረም ሁለት የደርግ ግንቦት ሃያ ነበር፡፡ ታዲያ እናቴ በወቅቱ የነበረውን የግዳጅ ውትድርና በመፍራት የመጀመሪያ ልጁን ወታደር ቤት እንዳይወስዱባት ከከተማው ወጣ ያለ አከስታችን ቤት ደብቃ፣ሁለተኛ ልጁንም ገጠር እናቷ ጋር ልካ፣ ሦስተኛውን ልጇን አልጋ ስር አስቀምጣ፣ አባቴንም
"ታምሜያለሁ በል!" ብላው፣ እሷ ግን ነጭ ልብስ ለብላ ሰልፍ ወጣች፡፡ ግዴታ ነዋ!
ቀበሌ ስትደርስ ሴት ወንዱ ያለውን ለብሶ ተሽቀርቅሮ፣ ቀበሌውም በተለያዩ መፈከሮችና በባለ ቀለም መብራቶች አጊጦ ጠበቃት፡፡ የቀበሌው የአ..ሴ.ማ ኃላፊ የነበረች ሴት በባለእጀታ የጣውላ ሰሌዳ ላይ ተፅፈው የተዘጋጁ በመቶ የሚቆጠሩ መፈከሮችን ለእናቴ እያሳየቻት፣ ምረጭና አንዱን ያዥ አለቻት፡፡
እናቴ ቀለል ያለችና በደማቅ ቀይ ቀለም የተሽሞነሞነች መፈክር መርጣ አነሳችና ወደ ሰልፉ ተቀላቀለች፡፡ ከለበሰችው የሚያምር የአበሻ ቀሚስ እና ከራሷም ቁንጅና ጋር ተዳምሮ የኦሎምፒክ መከፈቻ ላይ 'ኢትዮጲያ የሚል ምልከት ይዛ ሰልፉን የምትመራ ቆንጆ የአበሻ ሴት ትመስል ነበር፡፡
በዕለቱ መስቀል አደባባይ እናቴን በርካታ ሰዎች በግርምትና በአድናቆት ሲመለከቷት ዋሉ፡፡ ታዲያ በዚያ ሰሞን ማታ በቴሌቪዥን ደጋግመው እናቴን ከነመፈhሯ ያሳይዋት ጀመረ፡፡ ምን ይሄ ብቻ፡ አመቱን ሙሉ ፎክረውም እናቴን ማሳየት፣ ኢህአፓ ብለውም እናቴን፣ መኢሶን ብለውም እናቴን፣ ቀይ ሽብር ብለውም እናቴን፣ ጓድ ሊቀመንበር ተናግረው ሲያበቁም እናቴን ማሳየት::
ጭራሽ ብሔራዊ ውትድርና ተብሎ ምድረ ወጣት ሰጓፈፍ ፣ የብሔራዊ ውትድርና አገር አቀፍ ዓርማ የእናቴ ፎቶ ሆኖ በየቦታው ተለጠፈ፡፡ በነጭ ልብስ ተውባ መፈክር ይዛ የቆመች እናቴ የብሔራዊ ውትድርና አገር አቀፍ አርማ ሆነች፡፡ እንድ ጋዜጣ ላይ የእናቴ ፎቶ ስር እንዲህ የሚል ጽሑፍ ሰፍሮ ነበር
"እብዮታዊት ሶሻሊስት ኢትዮጵያ ነጭ ቀሚስ ለብሳ"
እናቴ ታዲያ መጀመሪያ አካባቢ በቴሌቪዥን በታየች ቁጥር በቁንጅናዋ የተመረጠች መስሏት አባቴ ላይ በኩራት ትነሰነስበት ነበር፣
"ጓዳ ለጓዳ ስውል ቀላል ሰው አድርገኸኝ፣ እግሬ ወጣ ካለ አገር ነው የሚሰግድልኝ" ትለዋለች ኮራ
ብላ፡፡ አባቴ አፉን ሸርመም አድርጎ፣ "እዩኝ እዩኝ ማለት ደብቁኝ ደብቁኝ ያመጣል !" ይላታል::
የቅናት ወሬ ነው ይሄ ትልና ሆነ ብላ ለማበሳጨት በቴሌቪዥን ደጋግሞ የሚታየውን ምስሏን አተኩራ እየተመለከተች፤
“እንዲት ፍሬ ልጅ እኮ ነኝ" ትላለች፡፡ አባባ ታዲያ “ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…” ብሎ በረዥሙ ይስቅና
"ሰልፍ ላይማ መንግስትም አንድ ፍሬ ነኝ ነው የሚለው" ይላል፡፡
“ኤዲያ እንግዲህ ቦለቲካህን ልትጀምር ነው…” ብላ ወደ ጓዳዋ ትገባለች፡፡
ይሁንና እናቴ እየቆየች በቴሌቪዥን መታየቱ እና ስለ እርሷ መወራቱም ሲደጋገምባት ፈራች::
በተለይም ጓድ መንግስቱ ኃይለማሪያም መስቀል አደባባይ በትልቁ የተሰቀለውን የእናቴን ፎቶ ለተሰበሰበው ሕዝብ እያሳዩ በደም ፍላት፣
"እንደነዚህ ዓይነት ጀግና እናቶች ያሉባት አገር በማንም ወመኔ ከሃዲ ስትወረር እንዴት ወንዶቿ አልጋ ስር ይደበቃሉ? እነዚህን ቦቅቧቃ ወንዳገረዶች ቂጣቸውን በሳንጃ…” እያሉ ንግግር ካደረጉ በኋላ እናቴ ስጋቷ ከፍ አለ፡፡
ስጋቷን ለማስታገስ፣ “ኧረ ይሄ መፈክር ምንድን ነው የሚለው?” ብላ የተማረ ሰው ጠየቀች፡፡ መስከረም ሁለት ሰልፍ ላይ ይዛ ስለወጣችው መፈክር ተሸክማው ስለነበረው ጽሑፍ ሚያዚያ ላይ "ምንድን ነው?" ብላ ጠየቀች፡፡ሲነበብላት አመዷ ቡን አለ ፡ ብርክ ያዛት፡፡
መፈክሩ እንዲህ ነበር የሚለው....
"የአብዮት ጠላቶችን ለማደባየት እኛ እናቶች ልጆቻችንን፣ ካስፈለገም ባሎቻችንን በደስታ እናዘምታለን!!"
(ዶክተር አሸብር እና ሌሎችም)
ተ ሸ ክ መ ና ታ ል !!
እናቴ ሁልጊዜ እንድናጠና ስትመክረን እንዲህ ትላለች:-
“እናንተ ልጆች አጥኑ፣ ተማሩ እባካችሁ ! ...እኔ ባለመማሬ ነው ጉዴን ተሸክሜ የዋልኩት!"
ማንበብም መፃፍም ስለማትችል ንግግሯ በቁጭት ነበር፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ይሄ ተሸክማ የዋለችው ጉድ ምን እንደሆነ ለማወቅ ጓጉቼ ጠየቅኳት፣
"ማሚ የምን ጉድ ነው ተሽከመሽ የዋልሽው ?”
አወራችኝ ...
.......... ........ ..........
በደርግ ጊዜ መስከረም ሁለት ቀን ሕዝቡ በግድም ሆነ በውድ የድጋፍ ሰልፍ ይወጣ ነበር፡፡መስከረም ሁለት ደርግ ንጉሱን ገልብጦ ሥልጣን የያዘበት ቀን ነው፡፡ በአጭር አገላለፅ መስከረም ሁለት የደርግ ግንቦት ሃያ ነበር፡፡ ታዲያ እናቴ በወቅቱ የነበረውን የግዳጅ ውትድርና በመፍራት የመጀመሪያ ልጁን ወታደር ቤት እንዳይወስዱባት ከከተማው ወጣ ያለ አከስታችን ቤት ደብቃ፣ሁለተኛ ልጁንም ገጠር እናቷ ጋር ልካ፣ ሦስተኛውን ልጇን አልጋ ስር አስቀምጣ፣ አባቴንም
"ታምሜያለሁ በል!" ብላው፣ እሷ ግን ነጭ ልብስ ለብላ ሰልፍ ወጣች፡፡ ግዴታ ነዋ!
ቀበሌ ስትደርስ ሴት ወንዱ ያለውን ለብሶ ተሽቀርቅሮ፣ ቀበሌውም በተለያዩ መፈከሮችና በባለ ቀለም መብራቶች አጊጦ ጠበቃት፡፡ የቀበሌው የአ..ሴ.ማ ኃላፊ የነበረች ሴት በባለእጀታ የጣውላ ሰሌዳ ላይ ተፅፈው የተዘጋጁ በመቶ የሚቆጠሩ መፈከሮችን ለእናቴ እያሳየቻት፣ ምረጭና አንዱን ያዥ አለቻት፡፡
እናቴ ቀለል ያለችና በደማቅ ቀይ ቀለም የተሽሞነሞነች መፈክር መርጣ አነሳችና ወደ ሰልፉ ተቀላቀለች፡፡ ከለበሰችው የሚያምር የአበሻ ቀሚስ እና ከራሷም ቁንጅና ጋር ተዳምሮ የኦሎምፒክ መከፈቻ ላይ 'ኢትዮጲያ የሚል ምልከት ይዛ ሰልፉን የምትመራ ቆንጆ የአበሻ ሴት ትመስል ነበር፡፡
በዕለቱ መስቀል አደባባይ እናቴን በርካታ ሰዎች በግርምትና በአድናቆት ሲመለከቷት ዋሉ፡፡ ታዲያ በዚያ ሰሞን ማታ በቴሌቪዥን ደጋግመው እናቴን ከነመፈhሯ ያሳይዋት ጀመረ፡፡ ምን ይሄ ብቻ፡ አመቱን ሙሉ ፎክረውም እናቴን ማሳየት፣ ኢህአፓ ብለውም እናቴን፣ መኢሶን ብለውም እናቴን፣ ቀይ ሽብር ብለውም እናቴን፣ ጓድ ሊቀመንበር ተናግረው ሲያበቁም እናቴን ማሳየት::
ጭራሽ ብሔራዊ ውትድርና ተብሎ ምድረ ወጣት ሰጓፈፍ ፣ የብሔራዊ ውትድርና አገር አቀፍ ዓርማ የእናቴ ፎቶ ሆኖ በየቦታው ተለጠፈ፡፡ በነጭ ልብስ ተውባ መፈክር ይዛ የቆመች እናቴ የብሔራዊ ውትድርና አገር አቀፍ አርማ ሆነች፡፡ እንድ ጋዜጣ ላይ የእናቴ ፎቶ ስር እንዲህ የሚል ጽሑፍ ሰፍሮ ነበር
"እብዮታዊት ሶሻሊስት ኢትዮጵያ ነጭ ቀሚስ ለብሳ"
እናቴ ታዲያ መጀመሪያ አካባቢ በቴሌቪዥን በታየች ቁጥር በቁንጅናዋ የተመረጠች መስሏት አባቴ ላይ በኩራት ትነሰነስበት ነበር፣
"ጓዳ ለጓዳ ስውል ቀላል ሰው አድርገኸኝ፣ እግሬ ወጣ ካለ አገር ነው የሚሰግድልኝ" ትለዋለች ኮራ
ብላ፡፡ አባቴ አፉን ሸርመም አድርጎ፣ "እዩኝ እዩኝ ማለት ደብቁኝ ደብቁኝ ያመጣል !" ይላታል::
የቅናት ወሬ ነው ይሄ ትልና ሆነ ብላ ለማበሳጨት በቴሌቪዥን ደጋግሞ የሚታየውን ምስሏን አተኩራ እየተመለከተች፤
“እንዲት ፍሬ ልጅ እኮ ነኝ" ትላለች፡፡ አባባ ታዲያ “ሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…” ብሎ በረዥሙ ይስቅና
"ሰልፍ ላይማ መንግስትም አንድ ፍሬ ነኝ ነው የሚለው" ይላል፡፡
“ኤዲያ እንግዲህ ቦለቲካህን ልትጀምር ነው…” ብላ ወደ ጓዳዋ ትገባለች፡፡
ይሁንና እናቴ እየቆየች በቴሌቪዥን መታየቱ እና ስለ እርሷ መወራቱም ሲደጋገምባት ፈራች::
በተለይም ጓድ መንግስቱ ኃይለማሪያም መስቀል አደባባይ በትልቁ የተሰቀለውን የእናቴን ፎቶ ለተሰበሰበው ሕዝብ እያሳዩ በደም ፍላት፣
"እንደነዚህ ዓይነት ጀግና እናቶች ያሉባት አገር በማንም ወመኔ ከሃዲ ስትወረር እንዴት ወንዶቿ አልጋ ስር ይደበቃሉ? እነዚህን ቦቅቧቃ ወንዳገረዶች ቂጣቸውን በሳንጃ…” እያሉ ንግግር ካደረጉ በኋላ እናቴ ስጋቷ ከፍ አለ፡፡
ስጋቷን ለማስታገስ፣ “ኧረ ይሄ መፈክር ምንድን ነው የሚለው?” ብላ የተማረ ሰው ጠየቀች፡፡ መስከረም ሁለት ሰልፍ ላይ ይዛ ስለወጣችው መፈክር ተሸክማው ስለነበረው ጽሑፍ ሚያዚያ ላይ "ምንድን ነው?" ብላ ጠየቀች፡፡ሲነበብላት አመዷ ቡን አለ ፡ ብርክ ያዛት፡፡
መፈክሩ እንዲህ ነበር የሚለው....
"የአብዮት ጠላቶችን ለማደባየት እኛ እናቶች ልጆቻችንን፣ ካስፈለገም ባሎቻችንን በደስታ እናዘምታለን!!"
(ዶክተር አሸብር እና ሌሎችም)
😁8
ያኔ...
በልክ አርጊው ሲሉኝ ሁሉም ነገር ያልቃል
ያፋቸው ቃል እንጂ መች መስሎኝ ትንቢት ቃል
መቼም አያበቃም ገደብ የለው ያልኩት
መውደዴ ሲያልቅ ነው ልቤን የታዘብኩት።
ጥልቅ ነው እያልኩኝ ብዙ ነው እያልኩኝ
ከልብ አንጠፍጥፌ መውደድን ጨረስኩኝ
ያኔ....
ባገኝህ...ባዋይህ
እንደ ምስለ ቅዱስ ደጋግሜ ባይህ
እንደ አጥቢያ ደብር ነግቶ ብሳለምህ
ወይ እንደ ዉቃቢ ሠርክ ብለምንህ
አይበቃኝ የነበር
አፍታም አልፈጀበት መዉደዴ ሲሰበር።
ያኔ...
ጠዋት ፀሀይ ሞቃ
ሌት ጨረቃ ደምቃ
እወድህ የነበር ልኬት እሰካይኖረኝ
ዛሬ ምን ቀየረኝ?
ይኸው..
ፍቅር አንቱ ተብሎ እነዳልነገሰበት
ጥላቻም በኔ ልብ ተራዉ ደረሰለት
ጠላሁህ አንተዬ ከልቤ አወጣሁህ
ላይኔ እንደናፈከኝ አያሳየኝ አልኩህ
ደግሞ ጠብቃለሁ
ጊዜ በጎዳናዉ ተሸራርፎ ወድቆ
ምን እንደሚፈጠር ጥላቻዬም አልቆ
በልክ አርጊው ሲሉኝ ሁሉም ነገር ያልቃል
ያፋቸው ቃል እንጂ መች መስሎኝ ትንቢት ቃል
መቼም አያበቃም ገደብ የለው ያልኩት
መውደዴ ሲያልቅ ነው ልቤን የታዘብኩት።
ጥልቅ ነው እያልኩኝ ብዙ ነው እያልኩኝ
ከልብ አንጠፍጥፌ መውደድን ጨረስኩኝ
ያኔ....
ባገኝህ...ባዋይህ
እንደ ምስለ ቅዱስ ደጋግሜ ባይህ
እንደ አጥቢያ ደብር ነግቶ ብሳለምህ
ወይ እንደ ዉቃቢ ሠርክ ብለምንህ
አይበቃኝ የነበር
አፍታም አልፈጀበት መዉደዴ ሲሰበር።
ያኔ...
ጠዋት ፀሀይ ሞቃ
ሌት ጨረቃ ደምቃ
እወድህ የነበር ልኬት እሰካይኖረኝ
ዛሬ ምን ቀየረኝ?
ይኸው..
ፍቅር አንቱ ተብሎ እነዳልነገሰበት
ጥላቻም በኔ ልብ ተራዉ ደረሰለት
ጠላሁህ አንተዬ ከልቤ አወጣሁህ
ላይኔ እንደናፈከኝ አያሳየኝ አልኩህ
ደግሞ ጠብቃለሁ
ጊዜ በጎዳናዉ ተሸራርፎ ወድቆ
ምን እንደሚፈጠር ጥላቻዬም አልቆ
👍7👏2
፡
ባዶነት ወዳጄ ነበር
ጠፍቼ ነበር ከራሴ አለኝ ያልኩትስ መች አለኝ
አሁን ላይ ቀኑ ተለየ
በድንገት አይኔን ሳማትር ሳይሽ ግን አለሜ ታየኝ
ሳላውቅሽ መናፈቅ ተማርኩ
ያልነጋው ጨለማው ልቤ የተስፋ ፀሀይ ወጣለት
እንቺነት ነፍስን ሲዘራ
የመኖር ትርጉሙ ገባኝ ያየሁሽ የዛችን እለት
በሳቅሽ ሰርክ አማረብኝ
እያደር መሻቴ ወዛ ምኞቴ ግቡን ተጓዘ
እጦት ስር ወድቆ የነበረ
በብሶት ዝብርቅርቅ ያለው እኔነት መስመሩን ያዘ
ሄድንበት ጎዳና ምድሩን
ዋልንበት ጫካ ሜዳውን ሀሴትን አጎናፀፈን
ከፍ አልን በመውደድ ግርማ
እንደልጅ ፍንድቅድቅ አልን አያረጅ ፍቅር አቀፈን
በምናብ ነገን ቃኘነው
አሰላን ኑሮ ቀመሩን አንድ ሆነ የእኛነት ውሉ
አሙቀሽ በረዶ አካሌን
ፈጥረሽኝ ነበር እንዳዲስ አድርገሽ አለሜን ሙሉ
ደምቄ ነበር ካንቺ ጋር
ታይቼ ነበር አምሮብኝ ሆነሽኝ የልቤ ሀገር
ምን ትርጉም ምንስ ዋጋ አለው
ይህ ሁሉ እያለሽ ነበር
ስትመጪ ቀን የወጣለት
ያነሳኝ ያቀናኝ ፍቅርሽ ስትሄጂ ጠቁሮ ዳመነ
የመኖር ትርጉሜን አጣሁ
ይባሱን ከራሴ ጠፋሁ ባዶነት ወዳጄ ሆነ
ያማረው ፊቴ ገረጣ
በናፍቆትሽ ጣር ከስሜ አግኝቶ ማጣት ሰበረኝ
ሄድሽ እንጂ በእኔ ጨክነሽ
ከአንቺነት መፅናኛ ፍቅር ሌላ እንኳ ምንስ ነበረኝ
ብሶቴን እንዳዲስ ዘራሽ
በፍቅርሽ የረጋው ልቤ ስትሄጂ መስመሩ ራቀው
መልሶ ዝብርቅርቅ አለ
ዳግሙን ፀንቶ እስኪፈካ ያንቺ ቃል እየናፈቀው
@getmtg
@getmtg
ባዶነት ወዳጄ ነበር
ጠፍቼ ነበር ከራሴ አለኝ ያልኩትስ መች አለኝ
አሁን ላይ ቀኑ ተለየ
በድንገት አይኔን ሳማትር ሳይሽ ግን አለሜ ታየኝ
ሳላውቅሽ መናፈቅ ተማርኩ
ያልነጋው ጨለማው ልቤ የተስፋ ፀሀይ ወጣለት
እንቺነት ነፍስን ሲዘራ
የመኖር ትርጉሙ ገባኝ ያየሁሽ የዛችን እለት
በሳቅሽ ሰርክ አማረብኝ
እያደር መሻቴ ወዛ ምኞቴ ግቡን ተጓዘ
እጦት ስር ወድቆ የነበረ
በብሶት ዝብርቅርቅ ያለው እኔነት መስመሩን ያዘ
ሄድንበት ጎዳና ምድሩን
ዋልንበት ጫካ ሜዳውን ሀሴትን አጎናፀፈን
ከፍ አልን በመውደድ ግርማ
እንደልጅ ፍንድቅድቅ አልን አያረጅ ፍቅር አቀፈን
በምናብ ነገን ቃኘነው
አሰላን ኑሮ ቀመሩን አንድ ሆነ የእኛነት ውሉ
አሙቀሽ በረዶ አካሌን
ፈጥረሽኝ ነበር እንዳዲስ አድርገሽ አለሜን ሙሉ
ደምቄ ነበር ካንቺ ጋር
ታይቼ ነበር አምሮብኝ ሆነሽኝ የልቤ ሀገር
ምን ትርጉም ምንስ ዋጋ አለው
ይህ ሁሉ እያለሽ ነበር
ስትመጪ ቀን የወጣለት
ያነሳኝ ያቀናኝ ፍቅርሽ ስትሄጂ ጠቁሮ ዳመነ
የመኖር ትርጉሜን አጣሁ
ይባሱን ከራሴ ጠፋሁ ባዶነት ወዳጄ ሆነ
ያማረው ፊቴ ገረጣ
በናፍቆትሽ ጣር ከስሜ አግኝቶ ማጣት ሰበረኝ
ሄድሽ እንጂ በእኔ ጨክነሽ
ከአንቺነት መፅናኛ ፍቅር ሌላ እንኳ ምንስ ነበረኝ
ብሶቴን እንዳዲስ ዘራሽ
በፍቅርሽ የረጋው ልቤ ስትሄጂ መስመሩ ራቀው
መልሶ ዝብርቅርቅ አለ
ዳግሙን ፀንቶ እስኪፈካ ያንቺ ቃል እየናፈቀው
@getmtg
@getmtg
👏4❤1👍1
፡
የደራሲ ቅጣት ...
የሆነ ሰውዬ ይሞትና ገነትንም፣ ሲዖልንም ይጎበኛል፡፡ ገነት ሲደርስ በጎ ምግባሮች እንደቀጠሉ ናቸው። መልካም ሰርተው የፀደቁትንም አስተዋለ፡፡ ይልቅ የገረመው አንዲት ዛፍ ስር ቁጭ ብሎ የሚፅፍ ሰው ተመለከተ። ገረመውና ምን እንደሆነ ቢጠይቅ "ደራሲ ነው" አሉት። እየተደነቀ “አይ ደራሲ ፀድቆም አያርፍ፣ አሁኑም ይፅፋል” ሲል ተደመመ።
ከሚንቀለቀል የእሳት እቶትን ውስጥ የሲዖልም ሕይወት ቀጥላለች። አመፅ፣ ግርግሩ፣ ጦርነቱ…ኃጥያቱ አናት ባናቱ ይደራረባል። አሁንም አንድ ሰውዬ ከእሳት ዛፍ ስር አረፍ ብሎ በእሳት ብዕር፣ በእሳት ወረቀት ይቸከችካል። ተመልካቹ ሰውዬ ግራ ተጋባም ምን ሊሆን ይችላል ሲል እያሰበ ጠየቀ "ደራሲ ነው፣ ይከትባል" አሉት።
እየተገረመ፣ እየተደነቀ መልዓኩን "ቆይ ደራሲ እዚህም ሲፅፍ አይቼዋለሁ… እዛም ሲቸከችክ ተመልክቼዋለሁ ካዲያ ገነትም ገባ፣ ሲዖልም ወረደ ምን ቀረበት? ምንድነው ቅጣቱ? ምን ተጎዳ?" ሲል ጠየቀው።
መልዓኩም መለሰለት “ገነት ያሉት ይታተምላቸዋል"
(By Alemayew Gelagay)
የደራሲ ቅጣት ...
የሆነ ሰውዬ ይሞትና ገነትንም፣ ሲዖልንም ይጎበኛል፡፡ ገነት ሲደርስ በጎ ምግባሮች እንደቀጠሉ ናቸው። መልካም ሰርተው የፀደቁትንም አስተዋለ፡፡ ይልቅ የገረመው አንዲት ዛፍ ስር ቁጭ ብሎ የሚፅፍ ሰው ተመለከተ። ገረመውና ምን እንደሆነ ቢጠይቅ "ደራሲ ነው" አሉት። እየተደነቀ “አይ ደራሲ ፀድቆም አያርፍ፣ አሁኑም ይፅፋል” ሲል ተደመመ።
ከሚንቀለቀል የእሳት እቶትን ውስጥ የሲዖልም ሕይወት ቀጥላለች። አመፅ፣ ግርግሩ፣ ጦርነቱ…ኃጥያቱ አናት ባናቱ ይደራረባል። አሁንም አንድ ሰውዬ ከእሳት ዛፍ ስር አረፍ ብሎ በእሳት ብዕር፣ በእሳት ወረቀት ይቸከችካል። ተመልካቹ ሰውዬ ግራ ተጋባም ምን ሊሆን ይችላል ሲል እያሰበ ጠየቀ "ደራሲ ነው፣ ይከትባል" አሉት።
እየተገረመ፣ እየተደነቀ መልዓኩን "ቆይ ደራሲ እዚህም ሲፅፍ አይቼዋለሁ… እዛም ሲቸከችክ ተመልክቼዋለሁ ካዲያ ገነትም ገባ፣ ሲዖልም ወረደ ምን ቀረበት? ምንድነው ቅጣቱ? ምን ተጎዳ?" ሲል ጠየቀው።
መልዓኩም መለሰለት “ገነት ያሉት ይታተምላቸዋል"
(By Alemayew Gelagay)
😁9
፡
"ደህና ነህ ወይ?" ስለው
ሁሉ እንደሞላለት "ደህና ነኝ" ይለኛል
ለዚህ ጥያቄ መልስ
ተመሳሳይ ውሸት
"ደህና ነኝ" መሆኑን ቀድሞ አሳውቆኛል
የእውነት ደህና አይደለም .......
ምን ሆንክ እንዳልለው
ምንም ነው መልሱ
አትዋሽ እንዳልል
'ለምን'ታ ነው ክሱ
ጭንቁን በፈገግታው
ሊሸፍን ቢቃጣም
እንደተረበሸ ያስታውቅበታል
ይህ ጊዜ አደብ ገዝቶ
ተስፋው ያነሳው 'ለት
ሳይሰስት ከልቡ ሲያልፍ ይስቀበታል
(መቼ እንደሚያልፍ ባላውቅም)
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
"ደህና ነህ ወይ?" ስለው
ሁሉ እንደሞላለት "ደህና ነኝ" ይለኛል
ለዚህ ጥያቄ መልስ
ተመሳሳይ ውሸት
"ደህና ነኝ" መሆኑን ቀድሞ አሳውቆኛል
የእውነት ደህና አይደለም .......
ምን ሆንክ እንዳልለው
ምንም ነው መልሱ
አትዋሽ እንዳልል
'ለምን'ታ ነው ክሱ
ጭንቁን በፈገግታው
ሊሸፍን ቢቃጣም
እንደተረበሸ ያስታውቅበታል
ይህ ጊዜ አደብ ገዝቶ
ተስፋው ያነሳው 'ለት
ሳይሰስት ከልቡ ሲያልፍ ይስቀበታል
(መቼ እንደሚያልፍ ባላውቅም)
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
👏9👍3❤1