፡
"ብዙ ጊዜ ሰው አደገኛ ወጥመድ ውስጥ የሚወድቀው በሁለት መንገድ ነው፡፡ አንዱ የሰራሁትን ሰው አያውቅብኝም ሲል ሁለተኛው መቼም ታውቆብኛል ይሁን ምናባቱ ሲል ነው፡፡"
"ፍቅር_እስከ_መቃብር"
"ብዙ ጊዜ ሰው አደገኛ ወጥመድ ውስጥ የሚወድቀው በሁለት መንገድ ነው፡፡ አንዱ የሰራሁትን ሰው አያውቅብኝም ሲል ሁለተኛው መቼም ታውቆብኛል ይሁን ምናባቱ ሲል ነው፡፡"
"ፍቅር_እስከ_መቃብር"
👍3
፡
እንዳልታጣ እንዳልጎደለ
ሁሉ ሀሳቡ እንደሞላለት
ሀዘን ደርሶ እንዳልጎበኘው
ተስፋን ይዞ የጠበቀ
ከደስታ አለም ሰላም ደጃፍ
ከርሞ ራሱን ባያገኘው
ሲያመጣ ቀን ሁሉን ባንዴ
ሲደራርብ እለት በእለት
ባይቀል እንኳን ኑሮ ጓዙ
በጊዜው ልክ በእድሜ ጥላ
ያልሆኑትን አይሆን ሆነው
የሚያልፍ ቀን አለ ብዙ
ላይወራ ላይነገር
ዝም ማለት ያደረጀው
የጠቆረው እስኪነጣ
ሆድ ያባውን እስኪፈጀው
ነገር ሊጥል ሲጠላለፍ
ቀን ሊያነሳ ሲያንገዳግድ
ወደ ቀናው ኑሮ መንገድ
ብርቱነትን እስኪማግድ
ቀን ማለፉ ተስፋው ሆኖ
በነጋልኝ 'ለት ጥበቃ
ወትሮ ራሱን ያባበለ
ከዛሬው ላይ በድን ሆኖ
አለ መባል እየቀጣው
ስንቱን ስቃይ ተቀበለ
ሰላም ነግቶ እንደመሸለት
ከዙሪያው ጋር ተመሳስሎ
ባይሞላ እንኳን ላለመጉደል
ሰው ብሶቱን እያሰበ
ለአይን ደስታን ተመስሎ
ያሳልፋል ስንቱን በደል
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
እንዳልታጣ እንዳልጎደለ
ሁሉ ሀሳቡ እንደሞላለት
ሀዘን ደርሶ እንዳልጎበኘው
ተስፋን ይዞ የጠበቀ
ከደስታ አለም ሰላም ደጃፍ
ከርሞ ራሱን ባያገኘው
ሲያመጣ ቀን ሁሉን ባንዴ
ሲደራርብ እለት በእለት
ባይቀል እንኳን ኑሮ ጓዙ
በጊዜው ልክ በእድሜ ጥላ
ያልሆኑትን አይሆን ሆነው
የሚያልፍ ቀን አለ ብዙ
ላይወራ ላይነገር
ዝም ማለት ያደረጀው
የጠቆረው እስኪነጣ
ሆድ ያባውን እስኪፈጀው
ነገር ሊጥል ሲጠላለፍ
ቀን ሊያነሳ ሲያንገዳግድ
ወደ ቀናው ኑሮ መንገድ
ብርቱነትን እስኪማግድ
ቀን ማለፉ ተስፋው ሆኖ
በነጋልኝ 'ለት ጥበቃ
ወትሮ ራሱን ያባበለ
ከዛሬው ላይ በድን ሆኖ
አለ መባል እየቀጣው
ስንቱን ስቃይ ተቀበለ
ሰላም ነግቶ እንደመሸለት
ከዙሪያው ጋር ተመሳስሎ
ባይሞላ እንኳን ላለመጉደል
ሰው ብሶቱን እያሰበ
ለአይን ደስታን ተመስሎ
ያሳልፋል ስንቱን በደል
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
👍1
፡
"ሰው ጥሩ ሲሆንልህ ጥሩ ለመሆን የሚያስገድድ አፀፋዊ ግዴታን የሚፈጥር ነገር በሰው ውስጥ ሳይኖር አይቀርም፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
"ሰው ጥሩ ሲሆንልህ ጥሩ ለመሆን የሚያስገድድ አፀፋዊ ግዴታን የሚፈጥር ነገር በሰው ውስጥ ሳይኖር አይቀርም፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
፡
"እውነተኛ ነጻነት የኅሊና ነጻነት ነው፡፡ የኅሊና ነጻነት ደግሞ እውነትን በማወቅና በመኖር ነጻ ከወጣ አእምሮ ብቻ የሚገኝ ጸጋ ነው፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
"እውነተኛ ነጻነት የኅሊና ነጻነት ነው፡፡ የኅሊና ነጻነት ደግሞ እውነትን በማወቅና በመኖር ነጻ ከወጣ አእምሮ ብቻ የሚገኝ ጸጋ ነው፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
👍2
፡
"በመምከር ውስጥ ተመካሪውን ደካማ አድርጎ የማየት ስስ መታበይ አለ፡ ሲኖሩት ግን ሌላ አለም ነው፡፡""
"አልተዘዋወረችም"
"በመምከር ውስጥ ተመካሪውን ደካማ አድርጎ የማየት ስስ መታበይ አለ፡ ሲኖሩት ግን ሌላ አለም ነው፡፡""
"አልተዘዋወረችም"
👍1
፡
ይቆጭ የለም እንዴ ....
በእጅ የያዙትን ወርቅ
መዳብ ነው እያሉ ክብሩን ያረክሱታል
እንደሆነ እንዳይሆን
ካለበት አውርደው ሁሉን ይነሱታል
ታድያ ......
የይለፍ ይለፍ ቀን
የረከሰ ስሙን የትዝብቱን ውጦ
ህያው እሱነቱን
መዳብነት ወርቁን ያሳያል ገልብጦ
፡
ይለፍለት እንጁ
ቀላል አልነበረም ባልሆኑት መታሰብ
ወትሮም ያለ ቦታው
ቅይምትን የሚጭር ከንቱ ቃል መሰብሰብ
ቀላል አልነበረም
ከሆኑበት ወርደው በአጉል ስም መጠራት
በሰው አፍ ውሎ አድሮ
በይሉኝታ እሳቤ
የአልሆን ኑሮን መፍራት
....... ቀላል አልነበረም
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
ይቆጭ የለም እንዴ ....
በእጅ የያዙትን ወርቅ
መዳብ ነው እያሉ ክብሩን ያረክሱታል
እንደሆነ እንዳይሆን
ካለበት አውርደው ሁሉን ይነሱታል
ታድያ ......
የይለፍ ይለፍ ቀን
የረከሰ ስሙን የትዝብቱን ውጦ
ህያው እሱነቱን
መዳብነት ወርቁን ያሳያል ገልብጦ
፡
ይለፍለት እንጁ
ቀላል አልነበረም ባልሆኑት መታሰብ
ወትሮም ያለ ቦታው
ቅይምትን የሚጭር ከንቱ ቃል መሰብሰብ
ቀላል አልነበረም
ከሆኑበት ወርደው በአጉል ስም መጠራት
በሰው አፍ ውሎ አድሮ
በይሉኝታ እሳቤ
የአልሆን ኑሮን መፍራት
....... ቀላል አልነበረም
✍Mekdi
@getmtg
@getmtg
፡
እልህ
ለጥበብ ቀዳሚው
ጥበብ መጀመሪያው ሲጋራ ማጤስ ነው
እያለ የሚያወራው
ያ ከንቱ ወዳጅሽ
እንዲህ ስላወራሽ .... ስቀሽ ነበር አሉ
ያውም .....
እጅሽን ዘርግተሽ
እግርሽን አንስተሽ
ይሁን
ይሁን
ይሁን
ሳቂ ችግር የለም
ግን
እኔ የምናደድ የምበሽቅ መስሎሽ
እንዴት ከ"ማንም" ጋር የትም ትሆኛለሽ፡፡
(በኤፍሬም ስዩም)
እልህ
ለጥበብ ቀዳሚው
ጥበብ መጀመሪያው ሲጋራ ማጤስ ነው
እያለ የሚያወራው
ያ ከንቱ ወዳጅሽ
እንዲህ ስላወራሽ .... ስቀሽ ነበር አሉ
ያውም .....
እጅሽን ዘርግተሽ
እግርሽን አንስተሽ
ይሁን
ይሁን
ይሁን
ሳቂ ችግር የለም
ግን
እኔ የምናደድ የምበሽቅ መስሎሽ
እንዴት ከ"ማንም" ጋር የትም ትሆኛለሽ፡፡
(በኤፍሬም ስዩም)
👍2
፡
አንዲት ፍሬ የአበባ ዘር
ተራራ ጫፍ የበቀለች
ሳትታቀድ እንደ ድንገት
አፈር ገልጣ ብቅ ያለች
ቅን ልቦናን የምትመኝ
አጎልባቿን የምትሻ
ወተው ከቅርብ የማያዩያት
ቢያዩዋት እንኳን 'ምትታለፍ በጥቅሻ
ለአይን ሞልቶ የሚያማልል
የሚያስቀና ፍካት ያላት
ደፍረው ጎኗ የማይቆሙ
በሩቁ ግን ሳር ቅጠሉ የሚመኛት
ያቺን ፍሬ ውብ አበባ
አንዱም ቆርጦ ሳይጠጋት
ሳያንኳኳ የአለሟን ደጅ
ያስፈራኛል መሽቶ እንዳይቀር
እሰጋለሁ በጊዜዋ ሳትቀጠፍ እንዳታረጅ
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
አንዲት ፍሬ የአበባ ዘር
ተራራ ጫፍ የበቀለች
ሳትታቀድ እንደ ድንገት
አፈር ገልጣ ብቅ ያለች
ቅን ልቦናን የምትመኝ
አጎልባቿን የምትሻ
ወተው ከቅርብ የማያዩያት
ቢያዩዋት እንኳን 'ምትታለፍ በጥቅሻ
ለአይን ሞልቶ የሚያማልል
የሚያስቀና ፍካት ያላት
ደፍረው ጎኗ የማይቆሙ
በሩቁ ግን ሳር ቅጠሉ የሚመኛት
ያቺን ፍሬ ውብ አበባ
አንዱም ቆርጦ ሳይጠጋት
ሳያንኳኳ የአለሟን ደጅ
ያስፈራኛል መሽቶ እንዳይቀር
እሰጋለሁ በጊዜዋ ሳትቀጠፍ እንዳታረጅ
✍ Mekdi
@getmtg
@getmtg
👍4
፡
ዝግመተ ለውጥ
"እንጋባ" ሲል ጠየቃት አሳምነው፡፡
አልተቀበለችውም አስማሩ፡፡ "ወንድምና እህትነቱ ይበልጣል" አለችው፡፡
ተስማሙ፡፡
ቤቷ እየመጣ ይጠይቃታል፡፡
ቡና ታፈላለች ይጠጣሉ፡ ካላት ታቀርባለች - ይበላሉ፡፡
አውግተው ይለያያሉ፡፡
የትዳር ነገር ዳግም አልተነሳም፡፡
አሳምነው አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ መጣ፡፡
እንደመጣ የደረበውን ሹራብ አውልቆ አስቀመጠ፡፡ ስለሙቀቱ ብዙ አውርተው ተለያዩ፡፡
አስማሩ አሳምነው እረስቶት የሄደውን ሹራብ ልብሷን ስታጥብ አጠበችለት፡፡
ዳግም ሲመጣ ደርቦ ደራርቦ ነበርና የሚያወልቀው እንጂ የሚደርበው ልብስ አላስፈለገውም፡፡
ጃኬቱን አውልቅ ሄደ፡፡
አስማሩ አሁንም አጥባ አኖረችው፡፡
ሱሪውን ደርቦ መጣ "ወበቀኝ!" አወለቀው፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡
ካፓርቱን ጥሎ ሄደ፡
አጥባ አኖረችው፡፡
አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ ብርድ ልብሱን ለብሶ መጣ፡
አስማሩ "ምነው?" አለችው፡፡
"በጠራራ ፀሀይ ብርድ ሆዴ ገባ" አላት፡፡
"ምች ይሆናል" አለችው፡፡ የምች መድኃኒት ብታሽለት ተሻለው፡፡
ሲሻለው ብርድ ልብሱ አላስፈለገውም ጥሎት ሄደ፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡፡
ትንሽ ቆይቶ፡ ፍራሹን ተሸክሞ መጣ፡፡
"ምነው?" አለችው፡፡
"ላሳድሰው መሄዴ ነው፡፡ አይቼሽ ልለፍ ብዬ ነው" አላት፡፡
አመነችው፡፡
ጨዋታው ደራ፡ ፍራሹን እረስቶት ሄዶ ኖሮ እኩለ ሌሊት ቢመጣ አስማሩ ቦታ ስላጣች ፍራሹን ፍራሿ ላይ ደርባው ደረሰ፡፡ ያኔ "ተነሽ" ከማለት "ጠጋ በይ" ማለት ቀልሎ ተገኘ፡፡
ጠጋ አለች፡፡
(ኩርቢት)
ዝግመተ ለውጥ
"እንጋባ" ሲል ጠየቃት አሳምነው፡፡
አልተቀበለችውም አስማሩ፡፡ "ወንድምና እህትነቱ ይበልጣል" አለችው፡፡
ተስማሙ፡፡
ቤቷ እየመጣ ይጠይቃታል፡፡
ቡና ታፈላለች ይጠጣሉ፡ ካላት ታቀርባለች - ይበላሉ፡፡
አውግተው ይለያያሉ፡፡
የትዳር ነገር ዳግም አልተነሳም፡፡
አሳምነው አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ መጣ፡፡
እንደመጣ የደረበውን ሹራብ አውልቆ አስቀመጠ፡፡ ስለሙቀቱ ብዙ አውርተው ተለያዩ፡፡
አስማሩ አሳምነው እረስቶት የሄደውን ሹራብ ልብሷን ስታጥብ አጠበችለት፡፡
ዳግም ሲመጣ ደርቦ ደራርቦ ነበርና የሚያወልቀው እንጂ የሚደርበው ልብስ አላስፈለገውም፡፡
ጃኬቱን አውልቅ ሄደ፡፡
አስማሩ አሁንም አጥባ አኖረችው፡፡
ሱሪውን ደርቦ መጣ "ወበቀኝ!" አወለቀው፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡
ካፓርቱን ጥሎ ሄደ፡
አጥባ አኖረችው፡፡
አንድ ቀን በጠራራ ፀሀይ ብርድ ልብሱን ለብሶ መጣ፡
አስማሩ "ምነው?" አለችው፡፡
"በጠራራ ፀሀይ ብርድ ሆዴ ገባ" አላት፡፡
"ምች ይሆናል" አለችው፡፡ የምች መድኃኒት ብታሽለት ተሻለው፡፡
ሲሻለው ብርድ ልብሱ አላስፈለገውም ጥሎት ሄደ፡፡
አስማሩ አጥባ አኖረችው፡፡
ትንሽ ቆይቶ፡ ፍራሹን ተሸክሞ መጣ፡፡
"ምነው?" አለችው፡፡
"ላሳድሰው መሄዴ ነው፡፡ አይቼሽ ልለፍ ብዬ ነው" አላት፡፡
አመነችው፡፡
ጨዋታው ደራ፡ ፍራሹን እረስቶት ሄዶ ኖሮ እኩለ ሌሊት ቢመጣ አስማሩ ቦታ ስላጣች ፍራሹን ፍራሿ ላይ ደርባው ደረሰ፡፡ ያኔ "ተነሽ" ከማለት "ጠጋ በይ" ማለት ቀልሎ ተገኘ፡፡
ጠጋ አለች፡፡
(ኩርቢት)
😁8