እግዜር ቅርብ ሳለ .......
እውነት ፍርዱ ሲታይ
ሀቅ እንቅጩን ሲመርጥ እያንዷን ሳይሰብር
ብርሀን ለወረደ
ቦታው ተብሎ ኖሯል የብርሀን ደብር
እግዜር ቅርብ ሳለ .......
ለትግል ቢያስፈራ
'ማይመች ቢመስል
ኮሳሳ አካል ሊጥል ግዙፉን ጎልያድ
ዳዊት አሳይቶናል
ደልዳላ ቁመናው
ምቹ እንደነበረ
በወንጭፍ ታልሞ በአንድ ጠጠር ሲናድ
እግዜር ቅርብ ሳለ ......
እንደ ጌትነቱ
የፃዲቅን ፍሬ በህዝቡ ሲዘራ ፍቅርን ሲያስተምር
ጭንቁን ሰው ከህመም
ድሃን ከችግሩ
ጨካኙን ከሀጥያት
በደልን ሲያነፃ ሲያድንና ሲምር
የአዳም የሞት እዳ
በእለተ አርብ ቀን ሲሻር በመስቀሉ
ሞቶ ያተረፈ
ሰላም ነው ትንሳኤው ጌታ በጥቅሉ
እግዜር ቅርብ ሳለ ......
ተፈጥሮ ውበቱ
ሰው ቀለቡ ፍቅር መሬት ምርቷ ፍሬ
የዘበት አይደለም
ድል መሆን ታውቆት ነው የጀግና ፉካሬ
ዘምቶ ቢደክም እንኳ
ከግንባሩ ታቹን ላቡ እንደጉድ ቸፎ
ጨውነቱን ቢያቁር
ፀሀይና ግለት
ዝናብና ብርዱ
ወዙን አሟጦበት ቢከሳ ቢጠቁር
በረገጣት መሬት
ክብር እንዲቀለም ንድፍ ሀሳብ ለሳለ
..... እግዜር ቅርብ ሳለ .....
ቢዳፋ ቢያቀና
ፍርዱ እስኪለይለት እስኪጠራ መልኩ
አረ እናንተሆዬ
ሀገር አይደለም ወይ ሰው የመሆን ልኩ
✍Mekdi
እውነት ፍርዱ ሲታይ
ሀቅ እንቅጩን ሲመርጥ እያንዷን ሳይሰብር
ብርሀን ለወረደ
ቦታው ተብሎ ኖሯል የብርሀን ደብር
እግዜር ቅርብ ሳለ .......
ለትግል ቢያስፈራ
'ማይመች ቢመስል
ኮሳሳ አካል ሊጥል ግዙፉን ጎልያድ
ዳዊት አሳይቶናል
ደልዳላ ቁመናው
ምቹ እንደነበረ
በወንጭፍ ታልሞ በአንድ ጠጠር ሲናድ
እግዜር ቅርብ ሳለ ......
እንደ ጌትነቱ
የፃዲቅን ፍሬ በህዝቡ ሲዘራ ፍቅርን ሲያስተምር
ጭንቁን ሰው ከህመም
ድሃን ከችግሩ
ጨካኙን ከሀጥያት
በደልን ሲያነፃ ሲያድንና ሲምር
የአዳም የሞት እዳ
በእለተ አርብ ቀን ሲሻር በመስቀሉ
ሞቶ ያተረፈ
ሰላም ነው ትንሳኤው ጌታ በጥቅሉ
እግዜር ቅርብ ሳለ ......
ተፈጥሮ ውበቱ
ሰው ቀለቡ ፍቅር መሬት ምርቷ ፍሬ
የዘበት አይደለም
ድል መሆን ታውቆት ነው የጀግና ፉካሬ
ዘምቶ ቢደክም እንኳ
ከግንባሩ ታቹን ላቡ እንደጉድ ቸፎ
ጨውነቱን ቢያቁር
ፀሀይና ግለት
ዝናብና ብርዱ
ወዙን አሟጦበት ቢከሳ ቢጠቁር
በረገጣት መሬት
ክብር እንዲቀለም ንድፍ ሀሳብ ለሳለ
..... እግዜር ቅርብ ሳለ .....
ቢዳፋ ቢያቀና
ፍርዱ እስኪለይለት እስኪጠራ መልኩ
አረ እናንተሆዬ
ሀገር አይደለም ወይ ሰው የመሆን ልኩ
✍Mekdi
👍3
፡
"ህይወት ረቂቅ ሚስጢር ናት፡ አምላክ በጥበቡ በዚህ አለም ላይ ይህችን ሚስጥራዊት ሕይወት እድሜ በሚባል አነስተኛ የጊዜ ከረጢት ዐደለን፡፡ ይህቺም ከረጢት በውስጧ እድል በተሰኙ ፈርጦች ተሞልታለች፡፡ ከረጢቷን እንዳትሰረቅና ያለጊዜዋ አርጅታ ከጥቅም ውጪ እንዳትሆን፡ ኀላፊነቱን ፈጣሪ ለኛው ነው የሰጠን፡፡ በከረጢቷ ውስጥ ያሉትም ፈርጦች አንድ በአንድ፡ አንዳንዴም ከአንድ በላይ ባንዴ እያብለጨለጩ ከባለከረጢቱ እጅ ላይ ይወድቃሉ፡፡ ከጊዜ ጋር የተቆራኙ ናቸውና በጊዜው ያልተጠቀምንባቸው የእድል ፈርጦች ከጊዜ ጋር ላይመለሱ ትዝታቸውን አስታቅፈውን ይነጉዳሉ፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
"ህይወት ረቂቅ ሚስጢር ናት፡ አምላክ በጥበቡ በዚህ አለም ላይ ይህችን ሚስጥራዊት ሕይወት እድሜ በሚባል አነስተኛ የጊዜ ከረጢት ዐደለን፡፡ ይህቺም ከረጢት በውስጧ እድል በተሰኙ ፈርጦች ተሞልታለች፡፡ ከረጢቷን እንዳትሰረቅና ያለጊዜዋ አርጅታ ከጥቅም ውጪ እንዳትሆን፡ ኀላፊነቱን ፈጣሪ ለኛው ነው የሰጠን፡፡ በከረጢቷ ውስጥ ያሉትም ፈርጦች አንድ በአንድ፡ አንዳንዴም ከአንድ በላይ ባንዴ እያብለጨለጩ ከባለከረጢቱ እጅ ላይ ይወድቃሉ፡፡ ከጊዜ ጋር የተቆራኙ ናቸውና በጊዜው ያልተጠቀምንባቸው የእድል ፈርጦች ከጊዜ ጋር ላይመለሱ ትዝታቸውን አስታቅፈውን ይነጉዳሉ፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
👍2
፡
ለመረሳት ተብሎ ኑረት
ለመታወቅ ሲሉ ውድቀት
'ልታይ ልታይ' መባከን ነው
የልብ ስር አጉል ሙቀት
፡
ልኩራ ካሉስ በዝምታ
ልኑር ካሉ ከቅን ልብ ውስጥ
ከወደዱት ዘልቀው ገብተው
ነፃነትን ከእውነት ደጃፍ
ያለ እራስን ላለማጣት
መኖር ካሉስ ሁሉን ትተው
በቃ .........
✍️Mekdi
ለመረሳት ተብሎ ኑረት
ለመታወቅ ሲሉ ውድቀት
'ልታይ ልታይ' መባከን ነው
የልብ ስር አጉል ሙቀት
፡
ልኩራ ካሉስ በዝምታ
ልኑር ካሉ ከቅን ልብ ውስጥ
ከወደዱት ዘልቀው ገብተው
ነፃነትን ከእውነት ደጃፍ
ያለ እራስን ላለማጣት
መኖር ካሉስ ሁሉን ትተው
በቃ .........
✍️Mekdi
👍2
፡
"ማፍቀር እንጂ መፈቀር መለኪያ የለውም፡፡ መፈቀር እምነት ነው፡፡ ማፍቀር ደግሞ እውነት፡፡ ....... ፍቅር ብፁዕነትም ነው፡፡ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው እነዲል መጽሐፍ፡፡"
"አለመኖር"
"ማፍቀር እንጂ መፈቀር መለኪያ የለውም፡፡ መፈቀር እምነት ነው፡፡ ማፍቀር ደግሞ እውነት፡፡ ....... ፍቅር ብፁዕነትም ነው፡፡ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው እነዲል መጽሐፍ፡፡"
"አለመኖር"
👍2
፡
ይገርማል ....
ተፈጥሮ ልኩ ሲያምርበት
ውበት መአዛው ሲደራ
ሰው መሻቱን ሲያጣጥም
ድፍርስ እሳቤው ሲጠራ
ያይላል ግርማው ላዩበት
ይስባል መልከ ፍጥረቱ
የጭንቅ እሪያውን ወስዶ
ንፁህ ልቦናን መስጠቱ
ተመስገን!
✍️Mekdi
@getmtg
@getmtg
ይገርማል ....
ተፈጥሮ ልኩ ሲያምርበት
ውበት መአዛው ሲደራ
ሰው መሻቱን ሲያጣጥም
ድፍርስ እሳቤው ሲጠራ
ያይላል ግርማው ላዩበት
ይስባል መልከ ፍጥረቱ
የጭንቅ እሪያውን ወስዶ
ንፁህ ልቦናን መስጠቱ
ተመስገን!
✍️Mekdi
@getmtg
@getmtg
Telegram
የግጥም ጥግ
ያ ዶሮዬ ጮኈ መንጋቱን ነገረኝ፥
ሲነጋጋ ላርደው ቀጠሮ ነበረኝ።
የተለያዩ ምርጥ ግጥሞችን እዚህ
ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት
በ @Esamif
@amen1995 መጠየቅና መስጠት ይችላሉ።
ሲነጋጋ ላርደው ቀጠሮ ነበረኝ።
የተለያዩ ምርጥ ግጥሞችን እዚህ
ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት
በ @Esamif
@amen1995 መጠየቅና መስጠት ይችላሉ።
፡
"የምናውቀው የሚመስለን ነገር በጥያቄ ሲቀርብ፡ በምናውቀው ከመቆም ይልቅ ሃሳብ መቀየር ይቀናናል፡፡ ለምን?"
"አለማወቅ"
"የምናውቀው የሚመስለን ነገር በጥያቄ ሲቀርብ፡ በምናውቀው ከመቆም ይልቅ ሃሳብ መቀየር ይቀናናል፡፡ ለምን?"
"አለማወቅ"
፡
የወደደን ወዶ መያዝ
የናቀን ሰው ትቶ ለቀቅ
ከእራስ አለም ሞቅ ደመቅ
ሰላም ይዞ ወጣ ገባ
መልካም ሆኖ ሽር ብትን
የጠላን ሰው ግፍ እስኪያንቀው
የክፋቱን እስኪለው ትን
✍Mekdi
@getmtg
የወደደን ወዶ መያዝ
የናቀን ሰው ትቶ ለቀቅ
ከእራስ አለም ሞቅ ደመቅ
ሰላም ይዞ ወጣ ገባ
መልካም ሆኖ ሽር ብትን
የጠላን ሰው ግፍ እስኪያንቀው
የክፋቱን እስኪለው ትን
✍Mekdi
@getmtg
Telegram
የግጥም ጥግ
ያ ዶሮዬ ጮኈ መንጋቱን ነገረኝ፥
ሲነጋጋ ላርደው ቀጠሮ ነበረኝ።
የተለያዩ ምርጥ ግጥሞችን እዚህ
ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት
በ @Esamif
@amen1995 መጠየቅና መስጠት ይችላሉ።
ሲነጋጋ ላርደው ቀጠሮ ነበረኝ።
የተለያዩ ምርጥ ግጥሞችን እዚህ
ለማንኛውም ጥያቄና አስተያየት
በ @Esamif
@amen1995 መጠየቅና መስጠት ይችላሉ።
👍2
፡
"መኖር! - በአንድ ወገን የሚሆኑትን እየተመኙ፡ በሌላው ደግሞ የነበሩትን መሻት መሆኑ ይገርማል፡፡ በሚሆነውና በነበረው መካከል መወጠር! የነበረውንም ሆነ የሚሆነውን አለማወቅ!"
"አለማወቅ"
"መኖር! - በአንድ ወገን የሚሆኑትን እየተመኙ፡ በሌላው ደግሞ የነበሩትን መሻት መሆኑ ይገርማል፡፡ በሚሆነውና በነበረው መካከል መወጠር! የነበረውንም ሆነ የሚሆነውን አለማወቅ!"
"አለማወቅ"
👍2
፡
"ብዙሀኑን የኔ ከምንለው ሰው ጋር በአንድ ሚዛን ልናስቀምጠው አይገባም፡፡ ለብዙሀኑ ብዙ ሆነው መገኘት በመፈለጋቸው አንዱንም ሳይዙት ምንም ሆነው እንዲቀሩ ያደረጋቸው ብዙ ናቸው፡፡"
"ዙቤይዳ"
"ብዙሀኑን የኔ ከምንለው ሰው ጋር በአንድ ሚዛን ልናስቀምጠው አይገባም፡፡ ለብዙሀኑ ብዙ ሆነው መገኘት በመፈለጋቸው አንዱንም ሳይዙት ምንም ሆነው እንዲቀሩ ያደረጋቸው ብዙ ናቸው፡፡"
"ዙቤይዳ"
👍2
፡
"ልቦናችንን ከእውነቱ ይልቅ እውነት ነው ብለን የያዝነው፡ ያመንነው ጉዳይ ይገዛዋል፡፡ የውሸት ኀይል ደግሞ እውነት መስሎት በተቀበለው አእምሮ ላይ ነው፡፡ ምድር በውሸታሞች የተሞላች ከመሆኗም ባሻገር ውሸትን በቀላሉ እውነት አድርገው የሚቀበሉ ሰዎችም ከዚያው አይተናነሱም፡፡ ስሜታችን የተጠመደበት ጉዳይ ሲሆን ደግሞ የበለጠ ለውሸት የተጋለጥን ያደርገናል፡፡ ይህም ምናልባት ስሜት ከምክንያትና ከማስረጃ ይልቅ በእምነትና በግንኙነት ላይ ስለሚደገፍ ይሆናል፡፡ ያመንነውና የተጠጋነው ሰው ደግሞ የስሜታችን ሹፌር መሆኑ አይቀርም፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
"ልቦናችንን ከእውነቱ ይልቅ እውነት ነው ብለን የያዝነው፡ ያመንነው ጉዳይ ይገዛዋል፡፡ የውሸት ኀይል ደግሞ እውነት መስሎት በተቀበለው አእምሮ ላይ ነው፡፡ ምድር በውሸታሞች የተሞላች ከመሆኗም ባሻገር ውሸትን በቀላሉ እውነት አድርገው የሚቀበሉ ሰዎችም ከዚያው አይተናነሱም፡፡ ስሜታችን የተጠመደበት ጉዳይ ሲሆን ደግሞ የበለጠ ለውሸት የተጋለጥን ያደርገናል፡፡ ይህም ምናልባት ስሜት ከምክንያትና ከማስረጃ ይልቅ በእምነትና በግንኙነት ላይ ስለሚደገፍ ይሆናል፡፡ ያመንነውና የተጠጋነው ሰው ደግሞ የስሜታችን ሹፌር መሆኑ አይቀርም፡፡"
"የተቆለፈበት ቁልፍ"
👍2