#እንቁ_ለጌጥሽ
🌼🌼🌼🌼🌼
እንዴት ያለ እድል ፥ አወይ ጥቁር ምላስ
ባከላትሽ ታዞ
በትንታግ ዘመንሽ አዲስ እጣሽ ሲላስ
ምርቃት ይሁን እርግማን
ዋርሳ ይሁን ስጦታ .....ሳይገባሽ
እንቁ-ለጣጣሽ ብትባይ
ስለምን ለቤ'ክ አልሽ?
እልፍ አዲስ አመት ፥ አያሌ መባቻ
ጌጡ የት ሄዶብሽ ?
ችጋር የተረፈሽ ፥ ባያትሽ ስልቻ
አንድ ቀን እልልታ ፥ ሶስት መቶ ቀን ለቅሶ
ዘረኛ ቋቁቻ
እንደ ሸማ ጥለት ፥ ሰውነትሽን ወርሶ
አንጀቱ የቀናው ፥ መብሉን አስመልሶ
የሚበላው ያጣም
ጥሬውን ቆርጥሞ ፥ በምራቅ ለውሶ
እኩል ...እየ-ዬ ነው !!!
ባሳለፍነው ዘመን ፥ ከእልልታው ለጥቆ
ለነብስ እየሰጉ ፥ ለስጋ ተሳቆ
አይሻገር የለ ፥ ሶስት መቶ ቀን አልቆ
አዲስ ዘመን መጣ
ካለንበት ቡኮ ፥:ከማጡ ሳንወጣ።
አዲስ አመት በሚል ፥ ደስታ ልትቃርሚ
ጭቃ መደላድል ፥ ምን አምነሽ ትቆሚ?
ጣትሽ ሳይጠነከር እድፍሽ ሳይጠራ
ሽንሽን ብትለብሺ ከሀር የተሰራ
ያዳለጠሽ ግዜ
መሬት ባለጌ ነው ስጋሽን አይፈራ
ለቀን አያውልሽ የጥበብሽ ጮራ።
እና ከተረዳሽ ከገባሽ መልእክቴ
እርግማንሽን አንሺ !!!
ላይተር ሳያጠፉ ፥ መመፃደቅ ይቅር ፥ መዘወሩ ቦቴ
የተመረቀ ቀን
እንኳንስ በእንቁ ፥ ይከብራል በአርቴ
እንቁ ለጣጣሽ ይታጠፍ
እንቁ ለጌጥሽ #እናቴ !! ።
✍ #አብርሀም_ተክሉ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
#መልካም_አዲስ_አመት_ጣጣችን_ይፈንገል_በሰላም_በፍቅር_በደስታ_በብልፅግና_ማጌጫ_2012_ይሁንልን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@getem
@getem
@getem
🌼🌼🌼🌼🌼
እንዴት ያለ እድል ፥ አወይ ጥቁር ምላስ
ባከላትሽ ታዞ
በትንታግ ዘመንሽ አዲስ እጣሽ ሲላስ
ምርቃት ይሁን እርግማን
ዋርሳ ይሁን ስጦታ .....ሳይገባሽ
እንቁ-ለጣጣሽ ብትባይ
ስለምን ለቤ'ክ አልሽ?
እልፍ አዲስ አመት ፥ አያሌ መባቻ
ጌጡ የት ሄዶብሽ ?
ችጋር የተረፈሽ ፥ ባያትሽ ስልቻ
አንድ ቀን እልልታ ፥ ሶስት መቶ ቀን ለቅሶ
ዘረኛ ቋቁቻ
እንደ ሸማ ጥለት ፥ ሰውነትሽን ወርሶ
አንጀቱ የቀናው ፥ መብሉን አስመልሶ
የሚበላው ያጣም
ጥሬውን ቆርጥሞ ፥ በምራቅ ለውሶ
እኩል ...እየ-ዬ ነው !!!
ባሳለፍነው ዘመን ፥ ከእልልታው ለጥቆ
ለነብስ እየሰጉ ፥ ለስጋ ተሳቆ
አይሻገር የለ ፥ ሶስት መቶ ቀን አልቆ
አዲስ ዘመን መጣ
ካለንበት ቡኮ ፥:ከማጡ ሳንወጣ።
አዲስ አመት በሚል ፥ ደስታ ልትቃርሚ
ጭቃ መደላድል ፥ ምን አምነሽ ትቆሚ?
ጣትሽ ሳይጠነከር እድፍሽ ሳይጠራ
ሽንሽን ብትለብሺ ከሀር የተሰራ
ያዳለጠሽ ግዜ
መሬት ባለጌ ነው ስጋሽን አይፈራ
ለቀን አያውልሽ የጥበብሽ ጮራ።
እና ከተረዳሽ ከገባሽ መልእክቴ
እርግማንሽን አንሺ !!!
ላይተር ሳያጠፉ ፥ መመፃደቅ ይቅር ፥ መዘወሩ ቦቴ
የተመረቀ ቀን
እንኳንስ በእንቁ ፥ ይከብራል በአርቴ
እንቁ ለጣጣሽ ይታጠፍ
እንቁ ለጌጥሽ #እናቴ !! ።
✍ #አብርሀም_ተክሉ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
#መልካም_አዲስ_አመት_ጣጣችን_ይፈንገል_በሰላም_በፍቅር_በደስታ_በብልፅግና_ማጌጫ_2012_ይሁንልን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@getem
@getem
@getem
"ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን"
(ይኸው ነው!)
"የዘመን ዕውነት ነን በደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን
ትግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል
ካገር ፍቅር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል
ንገሩት_ለዛ_ሰው
ከአለም ጫፍ እስከ ጫፍ
ሀይል እንደተራራ ገዝፎ ቢከመርም
ክንዱን አፈርጥሞ
እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰደርም
ዓለም የሞተበት
የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም
በአንድ አይናችን ሰላም
በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም "
ገጣሚ ህሊና ደሳለኝ
@getem
@getem
@getem
(ይኸው ነው!)
"የዘመን ዕውነት ነን በደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን
ትግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል
ካገር ፍቅር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል
ንገሩት_ለዛ_ሰው
ከአለም ጫፍ እስከ ጫፍ
ሀይል እንደተራራ ገዝፎ ቢከመርም
ክንዱን አፈርጥሞ
እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰደርም
ዓለም የሞተበት
የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም
በአንድ አይናችን ሰላም
በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም "
ገጣሚ ህሊና ደሳለኝ
@getem
@getem
@getem
ግጥም ሲፃፍበት!!!
ሲሄድ እያየነው ፤
እንደ ደራሽ ውሃ በስሜት ገንፍሎ፤
ጉልፍልፍ እያለ፤
ትልቁን ትንሹን በጉያው አጅሎ፤
ሃገሬው እያየው፤
ይሉኝታ ጠፍቶበት በአጀብ በሆሆታ ሲሄዴ ተግተልትሎ፤
ወንድሙን እንደ በግ፤
ሆ ብሎ በደቦ ዛፍ ላይ አንጠልጥሎ፤
በመንጋ ጉባኤ፤ ንፁሃንን ሰቅሎ፤
የገዛ ወገኑን በድንጋይ ውርጅብኝ በአደባባይ ወግሮ፤
በሜንጫ በዱላ ምስኪኖቹን ቀብሮ፤
መኪና እያስቆመ ፤
የገዛ ወገኑን ንብረት እየቀማ በሽፍትነት አድሮ፤
ዘሎ እየዘረፈ የሰው ድንኳን ሰብሮ፤
ወንድሙን ሲያደማ ሙቅ ውሃ እየደፋ ጀበና ወርውሮ፤
እንዴት መንጋ ይክፋው ፤
ግጥም ሲፃፍበት መንጋ ነህ ተብሎ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
ሲሄድ እያየነው ፤
እንደ ደራሽ ውሃ በስሜት ገንፍሎ፤
ጉልፍልፍ እያለ፤
ትልቁን ትንሹን በጉያው አጅሎ፤
ሃገሬው እያየው፤
ይሉኝታ ጠፍቶበት በአጀብ በሆሆታ ሲሄዴ ተግተልትሎ፤
ወንድሙን እንደ በግ፤
ሆ ብሎ በደቦ ዛፍ ላይ አንጠልጥሎ፤
በመንጋ ጉባኤ፤ ንፁሃንን ሰቅሎ፤
የገዛ ወገኑን በድንጋይ ውርጅብኝ በአደባባይ ወግሮ፤
በሜንጫ በዱላ ምስኪኖቹን ቀብሮ፤
መኪና እያስቆመ ፤
የገዛ ወገኑን ንብረት እየቀማ በሽፍትነት አድሮ፤
ዘሎ እየዘረፈ የሰው ድንኳን ሰብሮ፤
ወንድሙን ሲያደማ ሙቅ ውሃ እየደፋ ጀበና ወርውሮ፤
እንዴት መንጋ ይክፋው ፤
ግጥም ሲፃፍበት መንጋ ነህ ተብሎ???
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
@getem
@getem
@balmbaras
ሚሌ ወዲህ ሃራ መጋሌ ስመራ፤
ኩርሚንጋፎ ቆቦ ዳዩ መንደፈራ፤
አቧራው ጨሰ አሉ፤
ከመሆኒ ጨርጨር ፤ ከዋጃ እስከ ጉራ ፤
መቼም ራያ ላይ፤
ወትሮም በሽበሽ ነው ልብና ተራራ።
ያች የራያ ልጅ ባለ ጥርቅ ጫማ ባለመልጎሚቱ ፤
ባለ ኩሌ ከንፈር ባለወተቲቱ ፤
የአባቶቿ ድንበር፤
ከዳዩ እስከ ራማ፤
ከኢቦ እስከ አላውሃ ፤ ታይቷት ምልክቱ፤
ራያ ነኝ ብላ ስመራ ስመራ ስመራ ልጅቱ ፤
ቦፌዋን ታቅፋ ፤
ጎንቢሶዋን ይዛ ለቀየው ተረፈች እንኳን ለማጀቱ።
ይኸ የራያ ሰው ፤
ይኸ የጨርጨር ሰው፤ ሁለትና ሶስቱ ፤
ድብ ይደረምሳል ፤
ሺ ቡከን ቢሰለፍ አይታጠፍ ፊቱ፤
ራቁት ያስኬዳል ደርሰው ከመጡበት በርስቱ በሚስቱ።
እንካ ልበስማ ፤
ማይ ማዩን ደርበው ጎንቢሶውን ታጠቅ፤
ለእነዚያ ሆዳሞች፤
ብለህ ንገርልኝ ፤
እዳው ለልጅ ልጅ ነው ራያን መዳፈር ማንነቱን መስረቅ።
ይህን ሸጋ ቦፌ፤
ይህንን ጎንቢሶ ታጠቅ በወገብህ፤ ዱላም ጨምርበት፤
ይኸው ነው ሰንደቁ፤
ይኸው ነው ባንዲራው የራያ ነፃነት የሚታወጅበት!!
አላ ዝናብ ባይጥል፤ ጎሊና ጅረቱ ቢሞላ ባይሞላ፤
አትጠራጠረኝ፤
ራያ ወሎ እንጅ፤ ራያ ራያ እንጅ አይደለም የሌላ።
ሃበከው !!!!ሃበከው!!!! ሃበከው !!!!!
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
እምወድሽዋ እንኳን መጣሽልኝ ❤️ ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!❤️
በነገራችን ላይ ዛሬ ከ 7:00 ጀምሮ ሸገር ሬድዮ ብትሰሙ ጋዜጠኛ መኣዛ ብሩ ከጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያደረገችው ቃለመጠይቅ ትሰማላቹ ...ሁሌም ቅዳሜ ከሰዓታችን ገምሸርሸር የሚያደርግልን #ሸገር ሬድዮ ነው !! ይኸው ነው!!
@getem
@getem
@balmbaras
ኩርሚንጋፎ ቆቦ ዳዩ መንደፈራ፤
አቧራው ጨሰ አሉ፤
ከመሆኒ ጨርጨር ፤ ከዋጃ እስከ ጉራ ፤
መቼም ራያ ላይ፤
ወትሮም በሽበሽ ነው ልብና ተራራ።
ያች የራያ ልጅ ባለ ጥርቅ ጫማ ባለመልጎሚቱ ፤
ባለ ኩሌ ከንፈር ባለወተቲቱ ፤
የአባቶቿ ድንበር፤
ከዳዩ እስከ ራማ፤
ከኢቦ እስከ አላውሃ ፤ ታይቷት ምልክቱ፤
ራያ ነኝ ብላ ስመራ ስመራ ስመራ ልጅቱ ፤
ቦፌዋን ታቅፋ ፤
ጎንቢሶዋን ይዛ ለቀየው ተረፈች እንኳን ለማጀቱ።
ይኸ የራያ ሰው ፤
ይኸ የጨርጨር ሰው፤ ሁለትና ሶስቱ ፤
ድብ ይደረምሳል ፤
ሺ ቡከን ቢሰለፍ አይታጠፍ ፊቱ፤
ራቁት ያስኬዳል ደርሰው ከመጡበት በርስቱ በሚስቱ።
እንካ ልበስማ ፤
ማይ ማዩን ደርበው ጎንቢሶውን ታጠቅ፤
ለእነዚያ ሆዳሞች፤
ብለህ ንገርልኝ ፤
እዳው ለልጅ ልጅ ነው ራያን መዳፈር ማንነቱን መስረቅ።
ይህን ሸጋ ቦፌ፤
ይህንን ጎንቢሶ ታጠቅ በወገብህ፤ ዱላም ጨምርበት፤
ይኸው ነው ሰንደቁ፤
ይኸው ነው ባንዲራው የራያ ነፃነት የሚታወጅበት!!
አላ ዝናብ ባይጥል፤ ጎሊና ጅረቱ ቢሞላ ባይሞላ፤
አትጠራጠረኝ፤
ራያ ወሎ እንጅ፤ ራያ ራያ እንጅ አይደለም የሌላ።
ሃበከው !!!!ሃበከው!!!! ሃበከው !!!!!
((( ጃ ኖ ))💚💛❤️
እምወድሽዋ እንኳን መጣሽልኝ ❤️ ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!❤️
በነገራችን ላይ ዛሬ ከ 7:00 ጀምሮ ሸገር ሬድዮ ብትሰሙ ጋዜጠኛ መኣዛ ብሩ ከጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ያደረገችው ቃለመጠይቅ ትሰማላቹ ...ሁሌም ቅዳሜ ከሰዓታችን ገምሸርሸር የሚያደርግልን #ሸገር ሬድዮ ነው !! ይኸው ነው!!
@getem
@getem
@balmbaras
ሲነጋ ልንገርሽ
።።።።።።።።።።።
(ከድር መሀመድ)
ገለጥ ሲልልኝ
ድርብርቡ አፈና፤ጨለማው ተገፎ፤
ሽኩቻ ለትግል
እንቅልፍ ሲነሳ፤በሀገሩ ለፍፎ፤
ምንም አትበይ
ዛሬ ቃላት አጥተሽ፤አፍሽ ቢቀየድም፤
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸ፤መንጋቱ አይቀርም፤
እንደነቃሁ ገና
ሲነጋ ልነግርሽ ፤ከንፈሬን ላልሼ ቃላት ፈልግና፤
ሳስብ እፈራለው
ሚስጥር እንዳይሾልከኝ፤ቃል እንዳላዛባ ሳላስብሆነና፤
ምን አልባት
በነገርሽ መሃል ሌላን፤ብተነፍስ ከመሀል ቆይቼ፤
ቃል ግቢልኝ!
አዝልቀሽ ላትሰጪኝ ላሳደኳቸው ነፍስ ወስደሽ ለጅቦቼ፤
በነገርሽ መሀል?
አትስጊ ግዴለም!
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም፤
ይሄው ነው
በጅ ያሳደጉት ጅብ አጉራሽ እጁን ቢነክስ መልሶ፤
ዘመኑ ይሆናል!
ወላጁን ሰዉቶ ተሹሞ የሚኖር መንጎችን ገርስሶ፤
ይሁና ከሆነ?
በመገርሰስ መሀል ራስ ሆኖ ከኖረ፤
መስማቱን ዘንግቶ
ወራጅ አለ እያሉት ዘግቶ ከበረረ፤
ለምን እንዳትይ?
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም።
@getem
@getem
@kedir
።።።።።።።።።።።
(ከድር መሀመድ)
ገለጥ ሲልልኝ
ድርብርቡ አፈና፤ጨለማው ተገፎ፤
ሽኩቻ ለትግል
እንቅልፍ ሲነሳ፤በሀገሩ ለፍፎ፤
ምንም አትበይ
ዛሬ ቃላት አጥተሽ፤አፍሽ ቢቀየድም፤
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸ፤መንጋቱ አይቀርም፤
እንደነቃሁ ገና
ሲነጋ ልነግርሽ ፤ከንፈሬን ላልሼ ቃላት ፈልግና፤
ሳስብ እፈራለው
ሚስጥር እንዳይሾልከኝ፤ቃል እንዳላዛባ ሳላስብሆነና፤
ምን አልባት
በነገርሽ መሃል ሌላን፤ብተነፍስ ከመሀል ቆይቼ፤
ቃል ግቢልኝ!
አዝልቀሽ ላትሰጪኝ ላሳደኳቸው ነፍስ ወስደሽ ለጅቦቼ፤
በነገርሽ መሀል?
አትስጊ ግዴለም!
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም፤
ይሄው ነው
በጅ ያሳደጉት ጅብ አጉራሽ እጁን ቢነክስ መልሶ፤
ዘመኑ ይሆናል!
ወላጁን ሰዉቶ ተሹሞ የሚኖር መንጎችን ገርስሶ፤
ይሁና ከሆነ?
በመገርሰስ መሀል ራስ ሆኖ ከኖረ፤
መስማቱን ዘንግቶ
ወራጅ አለ እያሉት ዘግቶ ከበረረ፤
ለምን እንዳትይ?
አትስጊ ግዴለም
ዶሮ ጮኸ አልጮኸም መንጋቱ አይቀርም።
@getem
@getem
@kedir
#ጥማት
በኮርማ ፣ በርችት ፣ ከምንቀበለው የዘመን መባቻ
ባርቲ ቡርቲ ወሬ ፥ በወገን ጥላቻ
እንደ ሀገር ኖሮ ፥ መሞት ለየብቻ
ምን አውቅልሽ በዝቶ.....
ውሎ ማደር ፈርተን ፥ በማጀት ጉልቻ
ቀናችንን ሳናምን
ጠጥተን ሳንረካ ፥ ጎርሰን ሳንጠግብ
ዛሬ ሳያከትም ፥ ለነገ ስናስብ
የሰቀቀን ጉርሻ ፥ ደጋግሞ እያነቀን
የኑሮ ውድነት ፥ በጠኔ እየናጠን
ዝም ባለ ሰፈር ፥ በፍርሀት ተጣብቀን
በጠራራ ፀሀይ ፥ ጨለማ አውሮን ፥ ምርኩዝ ተስፋ እያጣን
በልተን እንዳልበላ ፥ ስጋት እያከሳን
ካዲስ አመት በላይ ፥ ሰላም ነው የጠማን።
እንጂ!!
አሻፈረን ብንል ፥ ዘመን መች ይቆማል
ሲሻው የሳት እራት ፥ አልያ ዶሴ ገድል
የምንከትብበት
ባለ ሶስት መቶ ገፅ ፥ ብራና ያበጃል።
#ሰላማችን_ይብዛ
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
በኮርማ ፣ በርችት ፣ ከምንቀበለው የዘመን መባቻ
ባርቲ ቡርቲ ወሬ ፥ በወገን ጥላቻ
እንደ ሀገር ኖሮ ፥ መሞት ለየብቻ
ምን አውቅልሽ በዝቶ.....
ውሎ ማደር ፈርተን ፥ በማጀት ጉልቻ
ቀናችንን ሳናምን
ጠጥተን ሳንረካ ፥ ጎርሰን ሳንጠግብ
ዛሬ ሳያከትም ፥ ለነገ ስናስብ
የሰቀቀን ጉርሻ ፥ ደጋግሞ እያነቀን
የኑሮ ውድነት ፥ በጠኔ እየናጠን
ዝም ባለ ሰፈር ፥ በፍርሀት ተጣብቀን
በጠራራ ፀሀይ ፥ ጨለማ አውሮን ፥ ምርኩዝ ተስፋ እያጣን
በልተን እንዳልበላ ፥ ስጋት እያከሳን
ካዲስ አመት በላይ ፥ ሰላም ነው የጠማን።
እንጂ!!
አሻፈረን ብንል ፥ ዘመን መች ይቆማል
ሲሻው የሳት እራት ፥ አልያ ዶሴ ገድል
የምንከትብበት
ባለ ሶስት መቶ ገፅ ፥ ብራና ያበጃል።
#ሰላማችን_ይብዛ
✍ #አብርሀም_ተክሉ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
#ሳቅና_እንባ😁😭
አትላወስ ፡ ሆዴ
እባክህ ፡ ሁን ፡ ደስተኛ
ዘንድሮ ፡ አልተገኘም
አርፎ ፡ የሚተኛ
አትጭስ ፡ አትብገን
አትላወስ ፡ ሆዴ
ኑሮና ፡ ተራራ
ይገፋል ፡ በዘዴ
ኸረ ፡ ፍቅር ፡ ፍቅር
ፍቅር ፡ ጠፋ ፡ ይላሉ
አፍቃሪ ፡ አይደለም
ጓደኛ ፡ የሆነ ፡ ሁሉ
የዚህ ፡ አለም ፡ ነገር
በጣም ፡ ይገርመኛል
ልሙትልህ ፡ እንዳላለ
ሊገልህ ፡ ይመጣል
በክፉ ፡ ቀን ፡ ጊዜ
ፍቅር ፡ የት ፡ ይገኛል ።
አንድ ፡ ሁለት
እያለ ፡ እያለሳለሰ
ፍቅርም ፡ ጠፋ
ትንቢቱ ፡ ደረሰ
መከራና ፡ ደስታ
ማግኘትና ፡ ማጣት
ሰማይና ፡ ምድር
ጨለማና ፡ ንጋት
ፅድቅና ፡ ኩነኔ
አዝመራና ፡ አበባ
ወትሮም ፡ የነበረ ፡ ነው
ድሮም ፡ ሳቅና ፡ እንባ ።
ግጥም ፡- ኢሳ ፡ ሙሀመድ ፡ (ዳና)
@getem
@getem
@getem
አትላወስ ፡ ሆዴ
እባክህ ፡ ሁን ፡ ደስተኛ
ዘንድሮ ፡ አልተገኘም
አርፎ ፡ የሚተኛ
አትጭስ ፡ አትብገን
አትላወስ ፡ ሆዴ
ኑሮና ፡ ተራራ
ይገፋል ፡ በዘዴ
ኸረ ፡ ፍቅር ፡ ፍቅር
ፍቅር ፡ ጠፋ ፡ ይላሉ
አፍቃሪ ፡ አይደለም
ጓደኛ ፡ የሆነ ፡ ሁሉ
የዚህ ፡ አለም ፡ ነገር
በጣም ፡ ይገርመኛል
ልሙትልህ ፡ እንዳላለ
ሊገልህ ፡ ይመጣል
በክፉ ፡ ቀን ፡ ጊዜ
ፍቅር ፡ የት ፡ ይገኛል ።
አንድ ፡ ሁለት
እያለ ፡ እያለሳለሰ
ፍቅርም ፡ ጠፋ
ትንቢቱ ፡ ደረሰ
መከራና ፡ ደስታ
ማግኘትና ፡ ማጣት
ሰማይና ፡ ምድር
ጨለማና ፡ ንጋት
ፅድቅና ፡ ኩነኔ
አዝመራና ፡ አበባ
ወትሮም ፡ የነበረ ፡ ነው
ድሮም ፡ ሳቅና ፡ እንባ ።
ግጥም ፡- ኢሳ ፡ ሙሀመድ ፡ (ዳና)
@getem
@getem
@getem
👍1
ፎቶ በ ቀለም እንዲሁም በ drawing ለማሳል
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ማዘዝ ይቻላል ።
ሦዕል ለ ስጦታ ጥሩ አማራጭ ነው።
ይህን እድል ይጠቀሙበት!
@seiloch
@seiloch
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ማዘዝ ይቻላል ።
ሦዕል ለ ስጦታ ጥሩ አማራጭ ነው።
ይህን እድል ይጠቀሙበት!
@seiloch
@seiloch
♡ ስሞት አትቅበረኝ ♡♡♡
በሂወት እያለሁ እንባዬን ካልጠረግህ ፣
በእኔ እንባ ማንባት ካላዘነ ልብህ ፣
ሰታመም ዝም ካልህ ፣
እራቤ ካልገባህ ፣
ጭንቀቴም ብሶቴም ከመሰለህ ተራ ፣
ድፍርሱ ሂወቴ በፍቅርህ ካልጠራ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴ በፍቅርህ ካልበራ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬን
ካላሰናዳከዉ ፣
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝከዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ፍቅሬን ካልመራሀዉ ፣
እዉነት እልሃለሁ ዉዴ...
ስሞት አትቅበረኝ ፣
እንባም አታንባልኝ ፣
ፀፀትም አትግባ
ይልቁንስ ፍቅሬ...
እንደ ሻማ ቀልጦ ፍቅሬ ሳያልቅብህ ፣
እጂጉን አምሮ ልቤ ሳይቆርጥብህ ፣
ስታመም አስታመኝ ፣
ሰከፋ አፅናናኝ ፣
ስወድቅ ደግፈኝ ፣
የጭንቀቴን ብሶት
የዉስጤን ተረዳኝ ፣
ድፍርሱን ሂወቴን
በፍቅርህ አጥራልኝ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴን
በፍቅርህ አብራልኝ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬ
ፈጥነህ አሰናዳዉ ፣
የተደላደለ ቦታዉን አሲዘዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ልቤን ይዘሀ ምራዉ ፣
ደስታና ፍቅርን ከልብ አስተምረኝ ፣
ሁል ጊዜ ሳቅልኝ ፣
ይሄ ካልሆነ ግን
ስሞት አትቅበረኝ ::
ምንጭ፦ ወንጌላዊት እሙ
=======================
ለ "ስሞት አትቅበረኝ" ግጥም ምላሽ
ከአያልቅበት ሰለሞን
እሙ በህይወት እስካለሽ እንባሽን አብሼ
ስታለቅሺ ሳይሽ ተንሰቅስቄ አልቅሼ
ስትዝኚ ዕያየሁ እጥፍ ካላዘንኩኝ
ምኑን ሰው ተባልኩኝ
ሢያምሽ ካላመመኝ
እራብሽ ካልራበኝ
ምኑን አፈቀርኩሽ ምኑን ወዳጅ ሆንኩኝ
ጭንቀትሽ ብሶትሽ ከመሰለኝ ተራ
ድፍርሱ ህይወትሽ በፍቅሬ ካልጠራ
ተልካሻው ኑሮሽን ካላሰናዳሁት
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝኩት
ምናል ባልተዋወቅን እላለሁኝ ዕኔ
ለፍቅርሽ መከታ ስላለመሆኔ
ይልቅስ አታስቢ ፍቅሬ
ቃል ልግባልሽ ዛሬ
ስታለቅሺ አልቅሼ ስታዝኝም አዝናለው
ባስለቀሰሽ ጉዳይ ዳኛም እሆናለው
እፋረደዋለው።
ፍቅርሽን ቀንበቀን በፍቅሬ አድሳለው
ምስቅልቅል ህይወትሽን ዘውትር አድሳለው
እታመንሻለው
አይንሽ አያለቅስም
ልብሽ አይቆዝምም
ፈገግታሽ አይፈዝም
የፊትሽም ፀዳል ከቶ አይደብዝዝም
ይኸውልሽ ፍቅሬ ቃል ልግባ ደግሜ
ፍቅርሽ ተሰራጭቷል ባካልና ደሜ
ሲያምሽ ያምመኛል ሥታዝኚም አዝናለው
ስታለቅሺ አልቅሼ ስትስቂም ስቃለው
በፊትሽ ብርሐን እኔም እደምቃለው
ነገርግን ፍቅሬ ሆይ ስሚኝ በጽሞና
ምናልባት ሚሆነውን አላውቀውምና
አድምጭ እንደገና
ምናልባት ይህ ቃሌን መጠበቅ ቢያቅተኝ
ለፍቅርሽ መከታ መሖን ቢያታክተኝ
ህይወትሽን ማቃናት ባልችል በስንፍና
ይሄ ወዳጅነት ከቶ አይሆንምና
አድምጭ እንደገና
በፍቅሬ ፍቅርሽን መፈውስ ቢሳነኝ
ሀዘንሽን ማዘን ከቶ ባይቻለኝ
ዕንባሽን አብሼ
ባንቺ ፈንታ አልቅሼ
ሀዘንሽን አዝኜ
ሥታባክኝ ባክኜ
ካልተገኝኁ እኔ
ስትሞች አላለቅስም
ለቅሶ አልቀመጥም
በሞትሽ አላዝንም
ይልቅስ አድምጭ ነግርሻለው
ስትሞቺ ሞታለው
እከተልሻለው
እዚሕ በበደልኩሽ ላይ ቤት እክስሻለው
እመኝኝ ቃሌ ነው።
ምንጭ፦ አያልቅበት ሰለሞን
@getem
@getem
@getem
በሂወት እያለሁ እንባዬን ካልጠረግህ ፣
በእኔ እንባ ማንባት ካላዘነ ልብህ ፣
ሰታመም ዝም ካልህ ፣
እራቤ ካልገባህ ፣
ጭንቀቴም ብሶቴም ከመሰለህ ተራ ፣
ድፍርሱ ሂወቴ በፍቅርህ ካልጠራ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴ በፍቅርህ ካልበራ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬን
ካላሰናዳከዉ ፣
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝከዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ፍቅሬን ካልመራሀዉ ፣
እዉነት እልሃለሁ ዉዴ...
ስሞት አትቅበረኝ ፣
እንባም አታንባልኝ ፣
ፀፀትም አትግባ
ይልቁንስ ፍቅሬ...
እንደ ሻማ ቀልጦ ፍቅሬ ሳያልቅብህ ፣
እጂጉን አምሮ ልቤ ሳይቆርጥብህ ፣
ስታመም አስታመኝ ፣
ሰከፋ አፅናናኝ ፣
ስወድቅ ደግፈኝ ፣
የጭንቀቴን ብሶት
የዉስጤን ተረዳኝ ፣
ድፍርሱን ሂወቴን
በፍቅርህ አጥራልኝ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴን
በፍቅርህ አብራልኝ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬ
ፈጥነህ አሰናዳዉ ፣
የተደላደለ ቦታዉን አሲዘዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ልቤን ይዘሀ ምራዉ ፣
ደስታና ፍቅርን ከልብ አስተምረኝ ፣
ሁል ጊዜ ሳቅልኝ ፣
ይሄ ካልሆነ ግን
ስሞት አትቅበረኝ ::
ምንጭ፦ ወንጌላዊት እሙ
=======================
ለ "ስሞት አትቅበረኝ" ግጥም ምላሽ
ከአያልቅበት ሰለሞን
እሙ በህይወት እስካለሽ እንባሽን አብሼ
ስታለቅሺ ሳይሽ ተንሰቅስቄ አልቅሼ
ስትዝኚ ዕያየሁ እጥፍ ካላዘንኩኝ
ምኑን ሰው ተባልኩኝ
ሢያምሽ ካላመመኝ
እራብሽ ካልራበኝ
ምኑን አፈቀርኩሽ ምኑን ወዳጅ ሆንኩኝ
ጭንቀትሽ ብሶትሽ ከመሰለኝ ተራ
ድፍርሱ ህይወትሽ በፍቅሬ ካልጠራ
ተልካሻው ኑሮሽን ካላሰናዳሁት
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝኩት
ምናል ባልተዋወቅን እላለሁኝ ዕኔ
ለፍቅርሽ መከታ ስላለመሆኔ
ይልቅስ አታስቢ ፍቅሬ
ቃል ልግባልሽ ዛሬ
ስታለቅሺ አልቅሼ ስታዝኝም አዝናለው
ባስለቀሰሽ ጉዳይ ዳኛም እሆናለው
እፋረደዋለው።
ፍቅርሽን ቀንበቀን በፍቅሬ አድሳለው
ምስቅልቅል ህይወትሽን ዘውትር አድሳለው
እታመንሻለው
አይንሽ አያለቅስም
ልብሽ አይቆዝምም
ፈገግታሽ አይፈዝም
የፊትሽም ፀዳል ከቶ አይደብዝዝም
ይኸውልሽ ፍቅሬ ቃል ልግባ ደግሜ
ፍቅርሽ ተሰራጭቷል ባካልና ደሜ
ሲያምሽ ያምመኛል ሥታዝኚም አዝናለው
ስታለቅሺ አልቅሼ ስትስቂም ስቃለው
በፊትሽ ብርሐን እኔም እደምቃለው
ነገርግን ፍቅሬ ሆይ ስሚኝ በጽሞና
ምናልባት ሚሆነውን አላውቀውምና
አድምጭ እንደገና
ምናልባት ይህ ቃሌን መጠበቅ ቢያቅተኝ
ለፍቅርሽ መከታ መሖን ቢያታክተኝ
ህይወትሽን ማቃናት ባልችል በስንፍና
ይሄ ወዳጅነት ከቶ አይሆንምና
አድምጭ እንደገና
በፍቅሬ ፍቅርሽን መፈውስ ቢሳነኝ
ሀዘንሽን ማዘን ከቶ ባይቻለኝ
ዕንባሽን አብሼ
ባንቺ ፈንታ አልቅሼ
ሀዘንሽን አዝኜ
ሥታባክኝ ባክኜ
ካልተገኝኁ እኔ
ስትሞች አላለቅስም
ለቅሶ አልቀመጥም
በሞትሽ አላዝንም
ይልቅስ አድምጭ ነግርሻለው
ስትሞቺ ሞታለው
እከተልሻለው
እዚሕ በበደልኩሽ ላይ ቤት እክስሻለው
እመኝኝ ቃሌ ነው።
ምንጭ፦ አያልቅበት ሰለሞን
@getem
@getem
@getem
❤1
ድምፃዊ #ሙሉአለም_ተክሌ ወንድማችን ነው። ከጎን ለመቆም ሁላችንም ጊዜ አንጠብቅ
ዛሬ አሁን ለምንወደው ድምፃዊ እገዛችንን እናድርግ !
ሙሌ #በኩላሊት ህመም #ዲያልሲስ ጀምሯል
ለጥያቄ እና ለመርዳት
ስልክ:- +251911572276
ንግድ ባንክ (CBE)
mulualem takele
1000182044184
ከጎን ሆናችሁ ሀሳብ ለመስጠት ይሄን
group ተጠቀሙ https://t.me/joinchat/JSJyPhNcOTNP5V8x4LOXOw
ዛሬ አሁን ለምንወደው ድምፃዊ እገዛችንን እናድርግ !
ሙሌ #በኩላሊት ህመም #ዲያልሲስ ጀምሯል
ለጥያቄ እና ለመርዳት
ስልክ:- +251911572276
ንግድ ባንክ (CBE)
mulualem takele
1000182044184
ከጎን ሆናችሁ ሀሳብ ለመስጠት ይሄን
group ተጠቀሙ https://t.me/joinchat/JSJyPhNcOTNP5V8x4LOXOw
ተወዳጁ ሙዚቀኛ ሙሌ ሐመልማሎ በተለይም ከኤፍሬም አማረጋ "ተሸንፊያለሁ" በሚለው ስራው በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ሙሉአለም በደረሰበት የኩላሊት ህመም ዲያሊሲስ እንዲያደርግ በሀኪሞች ተነግሮታል። እንደሚታወቀው ይህ ሂደት ከፍተኛ ገንዘብን የሚጠይቅ ሲሆን በአርቲስቱ አቅም ደግሞ እስከ መጨረሻው መግፋት የማይቻል በመሆኑ ሁሉም ሰው ድጋፉን ያሳየው ዘንድ በፈጣሪ ስም እንጠይቃለን..
ይህ ወጣት አርቲስት ብዙ የሚጠበቅበት ገና ሙዚቃን ጀመርኳት እያለ እሩቅ በሚያስብበት በዚህ ሰዓት እንዲህ ባለው አደጋ ተደናቅፎ እንዳይቀር ሁላችንም በመረባረብ የበኩላችንን ማድረግ ይኖርብናል። አርቲስት የህዝብ ሀብት ነው። ህይወቱን እና ጊዜውን ለህዝብ ሰቶ የሚሰራ ጥበበኛ መጠለያው መሸሸጊያው ይኼው ያገለገለው ህዝብ ነውና ሁላችን ወደ ህዝብ እንጮሃለን..? ድጋፋችሁን ሽተን ደጃቹን የምንረግጥ ድርጅቶችም ትተባበሩን ዘንድ በዙሁ አጋጣሚ ለመጠየቅ እንገደዳለን።
ከፀሎት ጀምሮ ሁላችንም በምንችለው አቅም ከአርቲስቱ ጎን በመሆን እንርዳው.. #ጓደኞቹ
mulualem takele
1000182044184
ንግድ ባንክ
ከጎን ሆናችሁ ሀሳብ ለመስጠት ይሄን group ተጠቀሙ
https://t.me/joinchat/JSJyPhNcOTNP5V8x4LOXOw
ይህ ወጣት አርቲስት ብዙ የሚጠበቅበት ገና ሙዚቃን ጀመርኳት እያለ እሩቅ በሚያስብበት በዚህ ሰዓት እንዲህ ባለው አደጋ ተደናቅፎ እንዳይቀር ሁላችንም በመረባረብ የበኩላችንን ማድረግ ይኖርብናል። አርቲስት የህዝብ ሀብት ነው። ህይወቱን እና ጊዜውን ለህዝብ ሰቶ የሚሰራ ጥበበኛ መጠለያው መሸሸጊያው ይኼው ያገለገለው ህዝብ ነውና ሁላችን ወደ ህዝብ እንጮሃለን..? ድጋፋችሁን ሽተን ደጃቹን የምንረግጥ ድርጅቶችም ትተባበሩን ዘንድ በዙሁ አጋጣሚ ለመጠየቅ እንገደዳለን።
ከፀሎት ጀምሮ ሁላችንም በምንችለው አቅም ከአርቲስቱ ጎን በመሆን እንርዳው.. #ጓደኞቹ
mulualem takele
1000182044184
ንግድ ባንክ
ከጎን ሆናችሁ ሀሳብ ለመስጠት ይሄን group ተጠቀሙ
https://t.me/joinchat/JSJyPhNcOTNP5V8x4LOXOw
ትዝታና ተስፋ(ልዑል ሀይሌ)
ያኔ ባዲስ ዓመት
በጥበብ ሳገኝሽ
ቅኔዬንም ባጣ
የሰው ስዘርፍልሽ
በልቤ የቋጠርኩት
ጅምር ስንኝ ይዤ
ወዳንቺ ስመጣ
ይታወቀኝ ነበር
ባንቺ መድፊያ ፍቅር
ውብ ግጥም ሲወጣ
..
.
ያ ውብ ጅምር ግጥም...
.
የኔ ጅምር ስንኝ
ያንቺ ውብ መድፊያዎች
ዘላለም ሊያቆዩን
ቃላት ሲያማምሉን
እልፍ መሃላዎች
..
ታዲያ ምን ያደርጋል
.
.
አዲስ ያልነው ዓመት
እርጅና ተጭኖት
ያን ውብ ግጥማችንን
አንድ አፍራሽ ቃል ሰብሮት
ከጅምር ስንኜ ጥለሺኝ ስትሄጂ
ቤት ደፊስ አልጠፋም
አንቺ ቀረሽ እንጂ
..
.
ዛሬ
.
በጳጉሜ ላይ ሆኜ
የትናንት ና ነገ
መስከረም ሳያቸው
ትዝታና ተስፋ
እኩል መዝኛቸው
ካለፈ ትዝታ ተስፋ በልጦብኛል
ካምናው መስከረምሽ
የነገው ናፍቆኛል
..
.
በጊዜ ሂደት ውስጥ...
...
.
ያንድ ኑሮ ግጥም
ርዝመት አውቄያለሁ
ግጥሜን ልቀጥል
ጅምር ስንኝ ይዤ
መድፊያው ጋ ሄጃለሁ
4-13-2008
@getem
@getem
Share it.... @getem
ያኔ ባዲስ ዓመት
በጥበብ ሳገኝሽ
ቅኔዬንም ባጣ
የሰው ስዘርፍልሽ
በልቤ የቋጠርኩት
ጅምር ስንኝ ይዤ
ወዳንቺ ስመጣ
ይታወቀኝ ነበር
ባንቺ መድፊያ ፍቅር
ውብ ግጥም ሲወጣ
..
.
ያ ውብ ጅምር ግጥም...
.
የኔ ጅምር ስንኝ
ያንቺ ውብ መድፊያዎች
ዘላለም ሊያቆዩን
ቃላት ሲያማምሉን
እልፍ መሃላዎች
..
ታዲያ ምን ያደርጋል
.
.
አዲስ ያልነው ዓመት
እርጅና ተጭኖት
ያን ውብ ግጥማችንን
አንድ አፍራሽ ቃል ሰብሮት
ከጅምር ስንኜ ጥለሺኝ ስትሄጂ
ቤት ደፊስ አልጠፋም
አንቺ ቀረሽ እንጂ
..
.
ዛሬ
.
በጳጉሜ ላይ ሆኜ
የትናንት ና ነገ
መስከረም ሳያቸው
ትዝታና ተስፋ
እኩል መዝኛቸው
ካለፈ ትዝታ ተስፋ በልጦብኛል
ካምናው መስከረምሽ
የነገው ናፍቆኛል
..
.
በጊዜ ሂደት ውስጥ...
...
.
ያንድ ኑሮ ግጥም
ርዝመት አውቄያለሁ
ግጥሜን ልቀጥል
ጅምር ስንኝ ይዤ
መድፊያው ጋ ሄጃለሁ
4-13-2008
@getem
@getem
Share it.... @getem
👍1
ኢትዮጲያ በሚሏት የሚስኪኖች ሀገር
ሁሉም ሰው እረስቷት እኔ ብቻ ብቀር
መቼም አላቆምም እሷን ብቻ ማፍቀር።
(ልብ አልባው ገጣሚ )
@getem
@getem
@gebriel_19
ሁሉም ሰው እረስቷት እኔ ብቻ ብቀር
መቼም አላቆምም እሷን ብቻ ማፍቀር።
(ልብ አልባው ገጣሚ )
@getem
@getem
@gebriel_19
ያስተሰርያል ቁጥር ሁለት " ፈገግ ብላችሁ እደሩ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ወያኔነታቸው ከዚህ ሰረገላ
ስልጣን ሀክ ተደርገው ፣ ሲተኩ በሌላ
በአፈሙዞች ራስ ፣ ያስወጣችው ጠብሳ
ጋብዛ አስገባችው ፣ መቀሌ ላይ ምሳ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
አስራ ሰባት መርፌው ፣ ወጋግቶን ሲወጣ
አስራ ሰባት ባንኮች ፣ የሚዘርፈው መጣ
ይህን ሁሉ እያየ ፣ ከአፉ ቃል ያልወጣ
አንዲት ቅኔ ብዘርፍ ፣ ቆይ ለምን ተቆጣ?
ይቅር በለውና ፣ ከፋፋዩን ወቅሰህ
አንድ የነበረን ህዝብ ፣ አንድ አርገው መልሰህ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ኢትዮጵያ
እማማ አቢሲኒያ
ኢትዮጵያ ስሚ
እማማ አቢሲኒያ
ቂም በቀል ክፉ ነው ፣ከአምላክ ያለያያል
በቀለን በማሰር ፣ የህዋት ፅድቅ ይታያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ዘፅአት በኢትዮጵያ ፣ ወደ ለውጥ ጉዞ
ኩሬውን ሚያሻግር፣ ባህር ሀሳብ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅ ፣ የኢትዮጵያ ቀን መውጫ
ባንድነት ከጣልን ፣ ዱላ ክላሽ ሜንጫ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ፍቅር አጥተን እንጂ ፣ በርሀብ የተቀጣን
ጭማሪ ጥላቻ ፣ ሚሰጠን መች አጣን
ኦሲሳ ኦሲሳ ፣ ኦሲሳ ማንደላው
ይቅርታን አያውቅም ፣ ክላሽ እና ዱላው
በተስፋዋ መሬት ፣ እንዲፈፀም ቃሉ
መሥጅት ቤተስኪያኑን ፣ አትናዱ አታቃጥሉ
እማማ ኤሎሔ አላሔ
እማማ አትሰማኝ ወይ በይው
እማማ ማማዬ እማማ
ይሔም በክፉ ቃል ፣ ይሄንን ሲወቅሰው
ይህም በጥላቻ ፣ ይሄንን ሲከሰው
ህዝቦች እመሐል ቤት ፣ የምንቧቀሰው
መለየት አቅቶን ነው ፣ ሚበጀውን ሰው
ኦኦኦኦ ያስተሰርያል
ጃ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ማለት ፈጣሪ ፣ መሰረይ ይቅርታ
እኛ ሳንስማማ ፣ እንዴት ይስማን ጌታ
ኤሎሔ አላሔ
እማማ ማማዬ እማማ
እስቲ ተደመሩ ፣ እርስ በእርሳችሁ
እናንተን እያየ ፣ ህዝብ ይማርባችሁ
አንድ ሀገር አድኑ ፣ በልዩነታችሁ
አለበለዚያማ
በምን ያስታውቃል ፣ እኛን መውደዳችሁ?
።።።
አቤት ስቃይ ፣ አቤት ጠኔ
ኡንዱ ኬኛ ፣ ሁሉ የኔ
አልቅሰን ሳናባራ ፣ በወያኔ
እዚ ደግሞ ፣ ሌላ ትኩሳት
ሳይጠሩት አቤት ፣ ብሎ መነሳት
ወዲህ አፈናቃይ ፣ ወዲያ እድሳት
ወገኔ አለቀ ፣ በዘረኛ እሳት
እሳት
እሳት
እሳት
ኧረ አይነጋም ወይ
ኧረ አይነጋም ወይ ኢትዮጵያዬ
@getem
@getem
@gebriel_19
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ወያኔነታቸው ከዚህ ሰረገላ
ስልጣን ሀክ ተደርገው ፣ ሲተኩ በሌላ
በአፈሙዞች ራስ ፣ ያስወጣችው ጠብሳ
ጋብዛ አስገባችው ፣ መቀሌ ላይ ምሳ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
አስራ ሰባት መርፌው ፣ ወጋግቶን ሲወጣ
አስራ ሰባት ባንኮች ፣ የሚዘርፈው መጣ
ይህን ሁሉ እያየ ፣ ከአፉ ቃል ያልወጣ
አንዲት ቅኔ ብዘርፍ ፣ ቆይ ለምን ተቆጣ?
ይቅር በለውና ፣ ከፋፋዩን ወቅሰህ
አንድ የነበረን ህዝብ ፣ አንድ አርገው መልሰህ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ኢትዮጵያ
እማማ አቢሲኒያ
ኢትዮጵያ ስሚ
እማማ አቢሲኒያ
ቂም በቀል ክፉ ነው ፣ከአምላክ ያለያያል
በቀለን በማሰር ፣ የህዋት ፅድቅ ይታያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ዘፅአት በኢትዮጵያ ፣ ወደ ለውጥ ጉዞ
ኩሬውን ሚያሻግር፣ ባህር ሀሳብ ይዞ
ቅርብ ነው አይርቅ ፣ የኢትዮጵያ ቀን መውጫ
ባንድነት ከጣልን ፣ ዱላ ክላሽ ሜንጫ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ፍቅር አጥተን እንጂ ፣ በርሀብ የተቀጣን
ጭማሪ ጥላቻ ፣ ሚሰጠን መች አጣን
ኦሲሳ ኦሲሳ ፣ ኦሲሳ ማንደላው
ይቅርታን አያውቅም ፣ ክላሽ እና ዱላው
በተስፋዋ መሬት ፣ እንዲፈፀም ቃሉ
መሥጅት ቤተስኪያኑን ፣ አትናዱ አታቃጥሉ
እማማ ኤሎሔ አላሔ
እማማ አትሰማኝ ወይ በይው
እማማ ማማዬ እማማ
ይሔም በክፉ ቃል ፣ ይሄንን ሲወቅሰው
ይህም በጥላቻ ፣ ይሄንን ሲከሰው
ህዝቦች እመሐል ቤት ፣ የምንቧቀሰው
መለየት አቅቶን ነው ፣ ሚበጀውን ሰው
ኦኦኦኦ ያስተሰርያል
ጃ
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ያስተሰርያል
ጃ ማለት ፈጣሪ ፣ መሰረይ ይቅርታ
እኛ ሳንስማማ ፣ እንዴት ይስማን ጌታ
ኤሎሔ አላሔ
እማማ ማማዬ እማማ
እስቲ ተደመሩ ፣ እርስ በእርሳችሁ
እናንተን እያየ ፣ ህዝብ ይማርባችሁ
አንድ ሀገር አድኑ ፣ በልዩነታችሁ
አለበለዚያማ
በምን ያስታውቃል ፣ እኛን መውደዳችሁ?
።።።
አቤት ስቃይ ፣ አቤት ጠኔ
ኡንዱ ኬኛ ፣ ሁሉ የኔ
አልቅሰን ሳናባራ ፣ በወያኔ
እዚ ደግሞ ፣ ሌላ ትኩሳት
ሳይጠሩት አቤት ፣ ብሎ መነሳት
ወዲህ አፈናቃይ ፣ ወዲያ እድሳት
ወገኔ አለቀ ፣ በዘረኛ እሳት
እሳት
እሳት
እሳት
ኧረ አይነጋም ወይ
ኧረ አይነጋም ወይ ኢትዮጵያዬ
@getem
@getem
@gebriel_19
❤1👍1
የማጀት ሥር ወንጌል
(ህሊና ደሳለኝ)
ሙያተኛ ሀገሬ ከማጥገብ ጎደለ በረከት እራቀው የገበታሽ ለዛ፣
ተሻምቶ ለመጉረስ ከበላነው ይልቅ የደፋነው በዛ፡፡
ሙያሽ ባያስደፍር አጀብ ቢሰኙበት፣
ማዕዱ ቢሙላላ ዓይነቱ ቢያምርበት፣
አበዛዙ አይደለም አበላሉ ላይ ነው የገበታሽ ውበት፡፡
እየተማመንን! የፉክክር ቅሚያ በርሃብ እየናጥን፣
ከደፋነው ጠግቦ ውሻችን በለጠን፡፡
ከምርት አላነስን፣
ጎተራችን ሙሉ ጀግና አራሽ መች አጥተን፣
ማሰብ የጎደለው አያያዛችን ነው ገደል የከተተን፡፡
ይልቅ ግዴለሽም! ከምግባር ምጣድ ላይ ሳንበስል አንጋግተሸ ከማዕድ አትምሪን፣
ገበታሽ እንዲያምር ከእግዜር የሚያስታርቅ ፍቅር አስተምሪን፡፡
ገበታ ዕድሜ ነው ባለ ማሰብ መክነን፣
ሳንፀነስ ጃጀን፣
ሳንጣድ አረርን፣
ከዘመን ገበታ ከፊደል አቅድመን ዘር እየቆጠርን፡፡
ገበታ ሀቅ ነው በክፋት ሊጥ ጋግረው ያሻገቱት እውነት፣
በሆዳም እስክስታ ረግጠው ያፈኑት የምስኪናን ጩኸት፡፡
እስከ ልጠይቅሽ በጥም ደዌ ደቆ የረሃብ ጠኔ ደፍቶት እልፍ ትውልድ ያልፋል፣
ቢራ ለመጥመቂያ ሚበተን ገብስ ግን ከሀገር መች ይጠፋል፡፡
ከሆድ በማይሻገር የማጀት ቤት ዕውቀት አጥብበሽ አትለኪን፣
እስቲ መኖር ይግባን ከማስተዋል መቅደስ ሰው መሆን ስበኪን፡፡
ዘመን ካልገበረው ከችጋር ተራራ ከሲኦል ዳር ኑሮ፣
እንዴት ነው መሻገር ከመርፌ ቀዳዳ በጠበበ አይምሮ፡፡
ከምስኪን ዘመን ላይ የማይኖሩበትን ዕድሜ መበዳደር፣
ለአንዲት ማምሻ ደስታ በአያት እስትንፋስ ላይ ቁማር መደራደር፣
ያሳፍራል አይደል?
እያደጉ ማነስ እያነሱ መዝቀጥ፣
አጎንብሶ ያፀናን የድሃ እናት ጉልበት በጭካኔ መርገጥ፣
ያሳምማል አይደል?
መንገስ ከሚያባላስ መጥገብ ከሚያቃቅር ማግኘት ከሚያጎለን፣
ማጣት ውሎ ይግባ ባርነት ይሰንብት ድህነት ይግደለን፡፡
ከረፈደ ፀፀት ደረት እየደቁ ከእግዜር ቢዋቀሱ፣
ትርጉሙ ምንድነው ሲኖር ተቃቅሮ ሲሞት መላቀሱ፡፡
በእናታችን አድባር በፍቅሯ ይሁንብን፣
መድመቅ ካጋደለን ቆሽሸን ይመርብን፡፡
በመጠማት ሲቃ እስትንፋስ እስኪያንቃት ነፍሳችን ትርበትበት፣
ብቻህን ከመጥገብ አብሮ መራብህ ነው ሰው የመሆን ውበት፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ከመንጋነት ሚያግድ እረኛ አያሻህም ከህሊናህ በላይ፣
ስታስብ መሪ ነህ በብስለት ከፍታ በማስተዋል ሰማይ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን የጎጥ አረም ነቅለህ በአንድነት መስክ ላይ ፍቅር ትዘራለህ፣
በወረወሩብህ የጥላቻ ድንጋይ ትውልድ የሚያፋቅር ድልድይ ታበጃለህ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ዝምታህ ኃያል ነው ጀግና የሚያንበረክክ፣
ከፈሪ ቀረርቶ ከባዶ ሰው ጩኀት፣
ሀገር ላምስ ከሚል በመንደር አጀንዳ በአሽኮለሌ ተረት፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ነጻ ነህ እያሉህ መታሰር ያምርሃል፣
መቀመቅ መበስበስ፡፡
የኖርክለት እውነት ሀገር እስኪፈታ፣
በሀቁ እስኪመዘን ስለ በርባን ክብር የቆሸሸው ፍቅር የታሰረው ጌታ፣
ከድል ታሪክ ሰማይ ከሥልጣኔ ዳር ከጥበብ ከፍታ፣
እንሻገራለን ህዝብነትን ትተን ሰው የሆንን ለታ፡፡
በትረ ጥበበ ቢካን ዓለም ሊያንቀጠቅጥ ድል ሥልጣን ቢሰጠው፣
ጀግና መሪ አይደለም ብርቱ ተመሪ ነው ሀገር ሚለውጠው፡፡
አስተውል ወዳጄ ጠልተን ላንጣላ ችለን ላንጋደል ነደን ላንፋጀው፣
የኛው ትርምስ ነው በልቶ ለሚያባላ ጠላት ሚበጀው፡፡
ስጋና ደም እንጂ የአንድነታችን ውል የፍቅራችን ቀለም፣
ያሰመርነው ክልል የታጠርንበት ዘር ቋንቋችን አይደለም፡፡
ከመዋሃድ መቅደስ ትውልድ እናስተምር፣
ዘመን ይመርቀን ፍቅራችን ምን ጎድሎት ደማችን ያስታርቀን፡፡
በልጆቿ አጥንት በደም ኪዳን ምለን የገባንላት ቃል፣
ከጩኀት ያለፈ ዘመን የሚሻገር ተግባር ይጠይቃል፡፡
በአንድ ሃሳብ ተጋምደን በድል ድር እናብር ውድቀታችን ያንቃን፣
ሠርተን እናሳምን ሆነን ድል እንንሳ የአፍ ጀግንነት ይብቃን፡፡
ምስኪኒቷ እናቴ! በሞላ ጎዳና ባልጠበበ ድንበር በዘር ገመድ ታግዳ፣
ነጻ ነኝ ትላለች መንጋነት ያሰረው ባሪያ ትውልድ ወልዳ፡፡
የጀግንነት እብሪት ልባችንን ደፍኖት ማሰብ እየከዳን፣
እንዴት ነው ነጻነት እንዳበደ ፈረስ ስሜት እየነዳን፡፡
ገድሎ የመንገስ ጥማት ጩኀት ላገነነ አመጽ ላጀገነው፣
ለዚህ ምስኪን ትውልድ በጅምላ እየነዱት፣
በመንጋ እያሰበ ነጻነት እንዴት ነው?
ነጻነት ምርጫ ነው አምሮ ቢደላደል ጥፋት ያመነነው የመንጋዎች መንገድ፣
እንቅፋቱን ወዶ ለኖሩለት እውነት ለብቻ መራመድ፡፡
ነጻነት ማመን ነው ቀን ወዶ ቢያጀግን ቀን ጠልቶ ቢከዳም፣
ቢቆሽሹም ቢደምቁም እራስን መቀበል ራስን መምሰል ነው የነጻነት ገዳም፡፡
ነጻነት ማሰብ ነው በአንድነት መለምለም የኔነትን አረም ከህሊና ማጥፋት፣
ዘር ሆኖ ከማነስ ሀገር ሆኖ ማበብ ዓለም ሆኖ መስፋት፡፡
ንገሯት ለሀገሬ በጀግኖቿ ትግል ድንበር ባታስደፍር ከእጀ ገዥ ብትወጣ፣
ነጻ ነኝ እንዳትል በገዛ ልጆቿ በእጅ አዙር ተሸጣ ፡፡
ስሩን ካልሸመነው በመዋሃድ ጥለት በማስተዋል ሸማ፣
ታሪክ አናደምቅም በጭብጨባ ድግስ በሆይ ሆይታ ዜማ፡፡
ምን ብናቀነቅን በየሰልፉ ሜዳ ወኔ ብንደግስም፣
በፈረሰ አይምሮ በደቀቀ አንድነት ሀገር አናድስም፡፡
በጭፍን ከመሮጥ አስቦ ማዝገም ነው የመራመድ ውሉ፣
ሁሉም እንቅፋቶች እስኪጥሉን ድረስ ምርኩዝ ይመስላሉ፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
ከእግዜር ልንወዳጅ ለምህረቱ ጥላ እምባ ብንደግስም፣
ልብን ሳይመልሱ ለንስሃ መሮጥ ከጽድቅ አያደርስም፡፡
ውብ ነገን እናውርስ ትላንትን አክመን በይቅርታ ፀበል፣
ትውልድ ይጨርሳል ያረገዝነው እምባ የቋጠርነው በቀል፣
ከመስጠት አንጉደል ከቀማኞች ገደል ተረግጠን ብንጣል፣
ካሸከሙን በቀል ምናወርሰው ፍቅር ሀገር ይለውጣል፡፡
ከዕድሏ ጣሪያ ላይ ዘር የቀዳደው ሽንቁሯ ቢበዛም፣
ያ ከንቱ ፎካሪ ባፈጀ ቀረርቶ ሺህ ጉራ ቢነዛም፣
ሚሊዮን ዘር ቢሸጥ አንድ ሀገር አይገዛም፡፡
ኢዮጵያዊነት ነው የትርታችን ልክ የነፍሳችን ግጥም፣
መልስ ቤት በራቀው በከረመ ፀሎት ሰርክ ብታንጋጥም
አጎንብሳ ድሃ ባፀናችው ጉልበት ብትረጋገጥም
ነፍሷን አደህይታ ባሻረችው ቁስል ብትገሸለጥም፣
ሀገር ሆና ገዝፋ በየ ጎጣጎጡ አትርመጠመጥም፡፡
የዘመን እውነት ነን ከደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን፣
ትዕግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን፡፡
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል፣
ከሀገር ክብር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል፡፡
ንገሩት ለዛ ሰው ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ ኃይል እንደ ተራራ ገዝፎ ቢከመርም፣
ክንዱን አፈርጥሞ እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰድርም፣
ዓለም የሞተበት የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም፣
በአንድ ዓይናችን ሰላም በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም!!!
©ሕሊና ደሳለኝ
ኅሊና_ደሳለኝ በአዲስ ዓመት ዋዜማ በቤተ መንግስት
ካቀረበችው ግጥም
@getem
@getem
@getem
(ህሊና ደሳለኝ)
ሙያተኛ ሀገሬ ከማጥገብ ጎደለ በረከት እራቀው የገበታሽ ለዛ፣
ተሻምቶ ለመጉረስ ከበላነው ይልቅ የደፋነው በዛ፡፡
ሙያሽ ባያስደፍር አጀብ ቢሰኙበት፣
ማዕዱ ቢሙላላ ዓይነቱ ቢያምርበት፣
አበዛዙ አይደለም አበላሉ ላይ ነው የገበታሽ ውበት፡፡
እየተማመንን! የፉክክር ቅሚያ በርሃብ እየናጥን፣
ከደፋነው ጠግቦ ውሻችን በለጠን፡፡
ከምርት አላነስን፣
ጎተራችን ሙሉ ጀግና አራሽ መች አጥተን፣
ማሰብ የጎደለው አያያዛችን ነው ገደል የከተተን፡፡
ይልቅ ግዴለሽም! ከምግባር ምጣድ ላይ ሳንበስል አንጋግተሸ ከማዕድ አትምሪን፣
ገበታሽ እንዲያምር ከእግዜር የሚያስታርቅ ፍቅር አስተምሪን፡፡
ገበታ ዕድሜ ነው ባለ ማሰብ መክነን፣
ሳንፀነስ ጃጀን፣
ሳንጣድ አረርን፣
ከዘመን ገበታ ከፊደል አቅድመን ዘር እየቆጠርን፡፡
ገበታ ሀቅ ነው በክፋት ሊጥ ጋግረው ያሻገቱት እውነት፣
በሆዳም እስክስታ ረግጠው ያፈኑት የምስኪናን ጩኸት፡፡
እስከ ልጠይቅሽ በጥም ደዌ ደቆ የረሃብ ጠኔ ደፍቶት እልፍ ትውልድ ያልፋል፣
ቢራ ለመጥመቂያ ሚበተን ገብስ ግን ከሀገር መች ይጠፋል፡፡
ከሆድ በማይሻገር የማጀት ቤት ዕውቀት አጥብበሽ አትለኪን፣
እስቲ መኖር ይግባን ከማስተዋል መቅደስ ሰው መሆን ስበኪን፡፡
ዘመን ካልገበረው ከችጋር ተራራ ከሲኦል ዳር ኑሮ፣
እንዴት ነው መሻገር ከመርፌ ቀዳዳ በጠበበ አይምሮ፡፡
ከምስኪን ዘመን ላይ የማይኖሩበትን ዕድሜ መበዳደር፣
ለአንዲት ማምሻ ደስታ በአያት እስትንፋስ ላይ ቁማር መደራደር፣
ያሳፍራል አይደል?
እያደጉ ማነስ እያነሱ መዝቀጥ፣
አጎንብሶ ያፀናን የድሃ እናት ጉልበት በጭካኔ መርገጥ፣
ያሳምማል አይደል?
መንገስ ከሚያባላስ መጥገብ ከሚያቃቅር ማግኘት ከሚያጎለን፣
ማጣት ውሎ ይግባ ባርነት ይሰንብት ድህነት ይግደለን፡፡
ከረፈደ ፀፀት ደረት እየደቁ ከእግዜር ቢዋቀሱ፣
ትርጉሙ ምንድነው ሲኖር ተቃቅሮ ሲሞት መላቀሱ፡፡
በእናታችን አድባር በፍቅሯ ይሁንብን፣
መድመቅ ካጋደለን ቆሽሸን ይመርብን፡፡
በመጠማት ሲቃ እስትንፋስ እስኪያንቃት ነፍሳችን ትርበትበት፣
ብቻህን ከመጥገብ አብሮ መራብህ ነው ሰው የመሆን ውበት፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ከመንጋነት ሚያግድ እረኛ አያሻህም ከህሊናህ በላይ፣
ስታስብ መሪ ነህ በብስለት ከፍታ በማስተዋል ሰማይ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን የጎጥ አረም ነቅለህ በአንድነት መስክ ላይ ፍቅር ትዘራለህ፣
በወረወሩብህ የጥላቻ ድንጋይ ትውልድ የሚያፋቅር ድልድይ ታበጃለህ፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ዝምታህ ኃያል ነው ጀግና የሚያንበረክክ፣
ከፈሪ ቀረርቶ ከባዶ ሰው ጩኀት፣
ሀገር ላምስ ከሚል በመንደር አጀንዳ በአሽኮለሌ ተረት፡፡
አየህ! ሰው ስትሆን ነጻ ነህ እያሉህ መታሰር ያምርሃል፣
መቀመቅ መበስበስ፡፡
የኖርክለት እውነት ሀገር እስኪፈታ፣
በሀቁ እስኪመዘን ስለ በርባን ክብር የቆሸሸው ፍቅር የታሰረው ጌታ፣
ከድል ታሪክ ሰማይ ከሥልጣኔ ዳር ከጥበብ ከፍታ፣
እንሻገራለን ህዝብነትን ትተን ሰው የሆንን ለታ፡፡
በትረ ጥበበ ቢካን ዓለም ሊያንቀጠቅጥ ድል ሥልጣን ቢሰጠው፣
ጀግና መሪ አይደለም ብርቱ ተመሪ ነው ሀገር ሚለውጠው፡፡
አስተውል ወዳጄ ጠልተን ላንጣላ ችለን ላንጋደል ነደን ላንፋጀው፣
የኛው ትርምስ ነው በልቶ ለሚያባላ ጠላት ሚበጀው፡፡
ስጋና ደም እንጂ የአንድነታችን ውል የፍቅራችን ቀለም፣
ያሰመርነው ክልል የታጠርንበት ዘር ቋንቋችን አይደለም፡፡
ከመዋሃድ መቅደስ ትውልድ እናስተምር፣
ዘመን ይመርቀን ፍቅራችን ምን ጎድሎት ደማችን ያስታርቀን፡፡
በልጆቿ አጥንት በደም ኪዳን ምለን የገባንላት ቃል፣
ከጩኀት ያለፈ ዘመን የሚሻገር ተግባር ይጠይቃል፡፡
በአንድ ሃሳብ ተጋምደን በድል ድር እናብር ውድቀታችን ያንቃን፣
ሠርተን እናሳምን ሆነን ድል እንንሳ የአፍ ጀግንነት ይብቃን፡፡
ምስኪኒቷ እናቴ! በሞላ ጎዳና ባልጠበበ ድንበር በዘር ገመድ ታግዳ፣
ነጻ ነኝ ትላለች መንጋነት ያሰረው ባሪያ ትውልድ ወልዳ፡፡
የጀግንነት እብሪት ልባችንን ደፍኖት ማሰብ እየከዳን፣
እንዴት ነው ነጻነት እንዳበደ ፈረስ ስሜት እየነዳን፡፡
ገድሎ የመንገስ ጥማት ጩኀት ላገነነ አመጽ ላጀገነው፣
ለዚህ ምስኪን ትውልድ በጅምላ እየነዱት፣
በመንጋ እያሰበ ነጻነት እንዴት ነው?
ነጻነት ምርጫ ነው አምሮ ቢደላደል ጥፋት ያመነነው የመንጋዎች መንገድ፣
እንቅፋቱን ወዶ ለኖሩለት እውነት ለብቻ መራመድ፡፡
ነጻነት ማመን ነው ቀን ወዶ ቢያጀግን ቀን ጠልቶ ቢከዳም፣
ቢቆሽሹም ቢደምቁም እራስን መቀበል ራስን መምሰል ነው የነጻነት ገዳም፡፡
ነጻነት ማሰብ ነው በአንድነት መለምለም የኔነትን አረም ከህሊና ማጥፋት፣
ዘር ሆኖ ከማነስ ሀገር ሆኖ ማበብ ዓለም ሆኖ መስፋት፡፡
ንገሯት ለሀገሬ በጀግኖቿ ትግል ድንበር ባታስደፍር ከእጀ ገዥ ብትወጣ፣
ነጻ ነኝ እንዳትል በገዛ ልጆቿ በእጅ አዙር ተሸጣ ፡፡
ስሩን ካልሸመነው በመዋሃድ ጥለት በማስተዋል ሸማ፣
ታሪክ አናደምቅም በጭብጨባ ድግስ በሆይ ሆይታ ዜማ፡፡
ምን ብናቀነቅን በየሰልፉ ሜዳ ወኔ ብንደግስም፣
በፈረሰ አይምሮ በደቀቀ አንድነት ሀገር አናድስም፡፡
በጭፍን ከመሮጥ አስቦ ማዝገም ነው የመራመድ ውሉ፣
ሁሉም እንቅፋቶች እስኪጥሉን ድረስ ምርኩዝ ይመስላሉ፡፡
በድፍን ግልብ እሚያጋድል ህዝብ የመሆን መንጋ አይንዳን፣
በማሰብ ስር እንፈወስ በሰውነት ፀበል እንዳን፡፡
ከእግዜር ልንወዳጅ ለምህረቱ ጥላ እምባ ብንደግስም፣
ልብን ሳይመልሱ ለንስሃ መሮጥ ከጽድቅ አያደርስም፡፡
ውብ ነገን እናውርስ ትላንትን አክመን በይቅርታ ፀበል፣
ትውልድ ይጨርሳል ያረገዝነው እምባ የቋጠርነው በቀል፣
ከመስጠት አንጉደል ከቀማኞች ገደል ተረግጠን ብንጣል፣
ካሸከሙን በቀል ምናወርሰው ፍቅር ሀገር ይለውጣል፡፡
ከዕድሏ ጣሪያ ላይ ዘር የቀዳደው ሽንቁሯ ቢበዛም፣
ያ ከንቱ ፎካሪ ባፈጀ ቀረርቶ ሺህ ጉራ ቢነዛም፣
ሚሊዮን ዘር ቢሸጥ አንድ ሀገር አይገዛም፡፡
ኢዮጵያዊነት ነው የትርታችን ልክ የነፍሳችን ግጥም፣
መልስ ቤት በራቀው በከረመ ፀሎት ሰርክ ብታንጋጥም
አጎንብሳ ድሃ ባፀናችው ጉልበት ብትረጋገጥም
ነፍሷን አደህይታ ባሻረችው ቁስል ብትገሸለጥም፣
ሀገር ሆና ገዝፋ በየ ጎጣጎጡ አትርመጠመጥም፡፡
የዘመን እውነት ነን ከደግነት ሰማይ በጥበብ የኖርን፣
ትዕግስትም ልክ አለው ፈርተን እንዳይመስለው ስላቀረቀርን፡፡
ማተብ አስሮን እንጂ ተጣልተን እንዳንቀር በክፍፍል ገደል፣
ከሀገር ክብር በልጦ ሞት ብርቃችን አይደል፡፡
ንገሩት ለዛ ሰው ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ ኃይል እንደ ተራራ ገዝፎ ቢከመርም፣
ክንዱን አፈርጥሞ እልፍ የሰገደለት ጀግና ቢሰድርም፣
ዓለም የሞተበት የጠላት ማርከሻ ጦር ቢደረድርም፣
በአንድ ዓይናችን ሰላም በኢትዮጵያችን ክብር አንደራደርም!!!
©ሕሊና ደሳለኝ
ኅሊና_ደሳለኝ በአዲስ ዓመት ዋዜማ በቤተ መንግስት
ካቀረበችው ግጥም
@getem
@getem
@getem
❤1