ለሀገሬ ለዕንቁጣጣሽ የተላከ ደብዳቤ
እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንደምነሽ ኢትዮጵ
እኔ አለው በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃሽ ድነሽ ተነሺና
እንደው ግን ሀገሬ ኑሮ እንዴት ይዞሻል
ድሮም እንዳሁኑ ይበጠብጡሻል
በፊት እንደዛሬ ብርሀን ናፍቆሽ ያውቃል
ሁሌ ብርሃን ነበር ወይስ ነው ጨለማ
ራቅ ላለ ሀገር ደምቆ የሚሰማ
ሀሳብ ነበረሽ ወይ ህዝብ ኖሮሽ ያውቃል
ይሄን ግን መጠየቅ እጅግ ያሳፍራል
ቢሆንም ቢሆንም ግድ የለም መልሺ
ወሎ አድሮ ደግሞ ከሌሎቹ ጋራ እኔን ከምቶቅሺ
ገድ የለም መልሺ
ዳቦ በሌለበት የኩራት ጎህ ብለሽ ቀን ትሰይሚያለሽ
ሰላም በሌለበት የሰላም ቀን እያልሽ ትደሰኩሪያለሽ
በወደቀች ሀገር የብልፅግና ቀን ታስከብሪናለሽ
ፍቅር በጠፋበት የፍቅር ቀን አያልሽ ታስጎመጂናለሽ
ፍትህ ባልኖረበት የፍትህ ዕለት ብለሽ ታስቀጥፊናለሽ
ሁሉም ቀናቶችሽ በሌሉ ነገሮች እየተሰየሙ
ልብን ያደማሉ ሀሳብ ያጠፋሉ ደዌ ያፈጥናሉ
ለኑሮ ታጋዩን ተስፋ ያሳጣሉ
እምነት ያስክዳሉ ውሸት አስወድደው ግፍ ያስለምዳሉ
አና እንዴት ነሽልሽ
ጤና እንዴት ይዞሻል
ዛሬም እንዳማረርሽ ይመሻል ይነጋል
እኔ ግን የምልሽ
መሪ ግን አለሽ ወይ
መሪው እንኳን ተይ
አትንገሪኝ በቃ ፓለቲካ ብለው እንዳይጠፈንጉኝ
አይኔን ባይኔ ሳላይ ዘሬን እንዳይቀሙኝ
ስለ መሪ ማጣት ተይው እንዳትነግሪኝ
አነማ
አነማ ነው ያልሽው
አንቺ ምን አለብሽ ኔትወርኩ ነው መሰል መረጃ አይደርስሽ
ኢሜልሽ አይሰራ ያስቸግራል ስልክሽ
ኦላይን የለሽም ችግር ላለመስማት
ፌስብክ ላይ አትኖሪ ሰውን ላለማማት
ታዲያ እንዴት ልንገርሽ
እኔ ግን ሀገሬ በጣም ስላዘንኩኝ
ነፍሴን የሚያሳጣ ሚስጥሬን ልነግርሽ ሰሞኑን ወሰንኩኝ
ምን መሠለሽ እሱ
በአሁኑ ሰአት ላይ የሚመራሽ የለም
መሪ የሚባል እንጂ መሪ ልጅ የለሽም
ሳትሞቺ ተስካርሽ በቁምሽ ሲበላ
ለሰማኒያሽ እንጃ ለአርባሽ መቶ ሰው በቁሙ ሲቀላ
ወዳንቺ እያየው አለሁኝ ከኀላ
ምክንያቱም
እንደ ሀገሬ ሰው እሬሳን አልወቅስም በሚለው በሀሉ
ለወዳጁም ሆነ ለመሠሪው ጎዱ እንሚለው ሁሉ
ሀገሬ ጥሩ ናት ሞትማ ቀደማት
ለስንቱ መዳኒት ለስንቱ ሸማ ናት
ብዬ ልፅፍልሽ ኀላሽ ሆኛለው
ህዝብሽን ስኮንን አቺን ደሞ ስረግም ይኸው እኖራለው
ሀገሬ አንደምነሽ
ህመሙ እንዴት ነው ዛሬስ ተሽሎሻል
ወይስ እንደ ድሮው ያቅለሸልሽሻል
ሆስፒታሉ እንዴት ነው
የህዝቦችሽ ጋር ነሽ ወይስ የግል ነው
እንደዛ ከሆነ
ዶክተሮቹ አሉ
በሰርጀሪ ግዜ ድንጋይ ኮብልስቶን ሆድሽ ውስጥ አረሱም
ለራስ ምታት ህመም ሽንት እና ሰገራ ምርመራ አልጠየቁም
ደምሽን ለመቅዳት ሀያ ስምንት ግዜ ደግመው አሎጉሽም
የውልሻ እኔ የልብ አውቃ ልጅሽ እንዲ ነኝ እወቂ
ህዝብሽ ይሰቃያል እንትና ይጨፍራል አንቺ ስትማቅቂ
እኔ ግን የምልሽ
ሽንት ቤቱ እንዴት ነው
ዛሬም እንደድሮው እንደነበረ ነው
የትም አትሂጂ ህዝብሽን ለማየት
መፀዳጃ ይበቃል ምሁር ለመለየት
እሱን ተይውና
ነርሶቹ እንዴት ናቸው
እንዴት አየሻቸው
ከዶክተሩ ናቸው ልባቸው ከማነው
ወይስ ካንቺ አሉ እንዴት ገመትሻቸው
አረ ሳልጠይቅሽ
እንዴት ልትገቢ ቻልሽ ዘበኛውን አልፈሽ
ወይስ እንደ ሰው ጉቦ መስጠት ለመድሽ
ጉቦ ይሰጣል ወይ
ህዝብሽ ተበሻቅጦ ያለ እጅ መንሻ የተሰራለት ለት
ስራውን አያምንም ጉቦ ካልሰጠበት
እንደው ግን እምዬ
አልጋ ከየት አገኘሽ
ወይስ እንደነሱ አንዱ ላይ ተደረብሽ
ወይስ እንደነዛ በጉልበት አስለቀቅሽ
ወንበር ላይ ነኝ አልሽኝ
ምነው እናት አለም የሚረዳሽ የለም
ዘመድ አልባ ነሽ ወይ ዘበኛው ዘመድሽ ይህንን አላየም
አሱ ምን ያረጋል ምንስ አቅም አለው
ምስኪን ተቀጣሪ ደህና ገንዘብ የለው
እሱን እንኳን ተይው
ከዳክተሩ በላይ ሆስፒታሉን የያዘው እሱ ነው ሚመስለው
ስትደመር ሚስቱ ያቺ ፅዳቱዋ ልጅ
ከተጣሉሽማ እንኳንስ ወንበሯን አትገቢም ከደጅ
እንዴት ነሽ አለሜ
እኔ አለው በጤና
ያው ታምሜም ቢሆን እግዜር ይመስገን ነው እኖራለው ደህና
የሸክላ በርበሬ በጀሶ እንጀራ አጥቅሼ
ዲታ የሆንኩ ቀን አህያ ቀምሼ
ባለ ብሩን ዳቦ አምስት ብር ገዝቼ
በ ሶስት ሺህ ብሬ ነጭ ጤፍ ሸምቼ
አለውኝ በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃኝ ድነሽ ተነሽና
እስከዛው ግን ቆይኝ
በአዲስ አመት ዜማ ባደይ ተንቆጥቁጠሽ
አዲስ ሳይፈጠር እድሜሽ ላይ ጨምረሽ
ግቡን የማይመታ ልጥጥ ስራ አቅደሽ
ልጆችሽን ማሰር ትውልድሽን መቅበር በደንብ ተምረሽ
ከብረሽ ቆይኝ ከብረሽ
✍✍ናብሊስ
መልካም እንቁጣጣሽ
ለ አስተያየቶ @kINGOFMORIYAM
@getem
@getem
@getem
እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንደምነሽ ኢትዮጵ
እኔ አለው በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃሽ ድነሽ ተነሺና
እንደው ግን ሀገሬ ኑሮ እንዴት ይዞሻል
ድሮም እንዳሁኑ ይበጠብጡሻል
በፊት እንደዛሬ ብርሀን ናፍቆሽ ያውቃል
ሁሌ ብርሃን ነበር ወይስ ነው ጨለማ
ራቅ ላለ ሀገር ደምቆ የሚሰማ
ሀሳብ ነበረሽ ወይ ህዝብ ኖሮሽ ያውቃል
ይሄን ግን መጠየቅ እጅግ ያሳፍራል
ቢሆንም ቢሆንም ግድ የለም መልሺ
ወሎ አድሮ ደግሞ ከሌሎቹ ጋራ እኔን ከምቶቅሺ
ገድ የለም መልሺ
ዳቦ በሌለበት የኩራት ጎህ ብለሽ ቀን ትሰይሚያለሽ
ሰላም በሌለበት የሰላም ቀን እያልሽ ትደሰኩሪያለሽ
በወደቀች ሀገር የብልፅግና ቀን ታስከብሪናለሽ
ፍቅር በጠፋበት የፍቅር ቀን አያልሽ ታስጎመጂናለሽ
ፍትህ ባልኖረበት የፍትህ ዕለት ብለሽ ታስቀጥፊናለሽ
ሁሉም ቀናቶችሽ በሌሉ ነገሮች እየተሰየሙ
ልብን ያደማሉ ሀሳብ ያጠፋሉ ደዌ ያፈጥናሉ
ለኑሮ ታጋዩን ተስፋ ያሳጣሉ
እምነት ያስክዳሉ ውሸት አስወድደው ግፍ ያስለምዳሉ
አና እንዴት ነሽልሽ
ጤና እንዴት ይዞሻል
ዛሬም እንዳማረርሽ ይመሻል ይነጋል
እኔ ግን የምልሽ
መሪ ግን አለሽ ወይ
መሪው እንኳን ተይ
አትንገሪኝ በቃ ፓለቲካ ብለው እንዳይጠፈንጉኝ
አይኔን ባይኔ ሳላይ ዘሬን እንዳይቀሙኝ
ስለ መሪ ማጣት ተይው እንዳትነግሪኝ
አነማ
አነማ ነው ያልሽው
አንቺ ምን አለብሽ ኔትወርኩ ነው መሰል መረጃ አይደርስሽ
ኢሜልሽ አይሰራ ያስቸግራል ስልክሽ
ኦላይን የለሽም ችግር ላለመስማት
ፌስብክ ላይ አትኖሪ ሰውን ላለማማት
ታዲያ እንዴት ልንገርሽ
እኔ ግን ሀገሬ በጣም ስላዘንኩኝ
ነፍሴን የሚያሳጣ ሚስጥሬን ልነግርሽ ሰሞኑን ወሰንኩኝ
ምን መሠለሽ እሱ
በአሁኑ ሰአት ላይ የሚመራሽ የለም
መሪ የሚባል እንጂ መሪ ልጅ የለሽም
ሳትሞቺ ተስካርሽ በቁምሽ ሲበላ
ለሰማኒያሽ እንጃ ለአርባሽ መቶ ሰው በቁሙ ሲቀላ
ወዳንቺ እያየው አለሁኝ ከኀላ
ምክንያቱም
እንደ ሀገሬ ሰው እሬሳን አልወቅስም በሚለው በሀሉ
ለወዳጁም ሆነ ለመሠሪው ጎዱ እንሚለው ሁሉ
ሀገሬ ጥሩ ናት ሞትማ ቀደማት
ለስንቱ መዳኒት ለስንቱ ሸማ ናት
ብዬ ልፅፍልሽ ኀላሽ ሆኛለው
ህዝብሽን ስኮንን አቺን ደሞ ስረግም ይኸው እኖራለው
ሀገሬ አንደምነሽ
ህመሙ እንዴት ነው ዛሬስ ተሽሎሻል
ወይስ እንደ ድሮው ያቅለሸልሽሻል
ሆስፒታሉ እንዴት ነው
የህዝቦችሽ ጋር ነሽ ወይስ የግል ነው
እንደዛ ከሆነ
ዶክተሮቹ አሉ
በሰርጀሪ ግዜ ድንጋይ ኮብልስቶን ሆድሽ ውስጥ አረሱም
ለራስ ምታት ህመም ሽንት እና ሰገራ ምርመራ አልጠየቁም
ደምሽን ለመቅዳት ሀያ ስምንት ግዜ ደግመው አሎጉሽም
የውልሻ እኔ የልብ አውቃ ልጅሽ እንዲ ነኝ እወቂ
ህዝብሽ ይሰቃያል እንትና ይጨፍራል አንቺ ስትማቅቂ
እኔ ግን የምልሽ
ሽንት ቤቱ እንዴት ነው
ዛሬም እንደድሮው እንደነበረ ነው
የትም አትሂጂ ህዝብሽን ለማየት
መፀዳጃ ይበቃል ምሁር ለመለየት
እሱን ተይውና
ነርሶቹ እንዴት ናቸው
እንዴት አየሻቸው
ከዶክተሩ ናቸው ልባቸው ከማነው
ወይስ ካንቺ አሉ እንዴት ገመትሻቸው
አረ ሳልጠይቅሽ
እንዴት ልትገቢ ቻልሽ ዘበኛውን አልፈሽ
ወይስ እንደ ሰው ጉቦ መስጠት ለመድሽ
ጉቦ ይሰጣል ወይ
ህዝብሽ ተበሻቅጦ ያለ እጅ መንሻ የተሰራለት ለት
ስራውን አያምንም ጉቦ ካልሰጠበት
እንደው ግን እምዬ
አልጋ ከየት አገኘሽ
ወይስ እንደነሱ አንዱ ላይ ተደረብሽ
ወይስ እንደነዛ በጉልበት አስለቀቅሽ
ወንበር ላይ ነኝ አልሽኝ
ምነው እናት አለም የሚረዳሽ የለም
ዘመድ አልባ ነሽ ወይ ዘበኛው ዘመድሽ ይህንን አላየም
አሱ ምን ያረጋል ምንስ አቅም አለው
ምስኪን ተቀጣሪ ደህና ገንዘብ የለው
እሱን እንኳን ተይው
ከዳክተሩ በላይ ሆስፒታሉን የያዘው እሱ ነው ሚመስለው
ስትደመር ሚስቱ ያቺ ፅዳቱዋ ልጅ
ከተጣሉሽማ እንኳንስ ወንበሯን አትገቢም ከደጅ
እንዴት ነሽ አለሜ
እኔ አለው በጤና
ያው ታምሜም ቢሆን እግዜር ይመስገን ነው እኖራለው ደህና
የሸክላ በርበሬ በጀሶ እንጀራ አጥቅሼ
ዲታ የሆንኩ ቀን አህያ ቀምሼ
ባለ ብሩን ዳቦ አምስት ብር ገዝቼ
በ ሶስት ሺህ ብሬ ነጭ ጤፍ ሸምቼ
አለውኝ በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃኝ ድነሽ ተነሽና
እስከዛው ግን ቆይኝ
በአዲስ አመት ዜማ ባደይ ተንቆጥቁጠሽ
አዲስ ሳይፈጠር እድሜሽ ላይ ጨምረሽ
ግቡን የማይመታ ልጥጥ ስራ አቅደሽ
ልጆችሽን ማሰር ትውልድሽን መቅበር በደንብ ተምረሽ
ከብረሽ ቆይኝ ከብረሽ
✍✍ናብሊስ
መልካም እንቁጣጣሽ
ለ አስተያየቶ @kINGOFMORIYAM
@getem
@getem
@getem
👍2
"ከአያት ቅድም አያቴ ፣ ሞያ እንጂ ቁምነገር
ቀልድን አልተማርኩም ፣ በእምነት እና በሀገር
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ጠብመንጃን ፣ቆንጨራን ፣ ገጀራን ፣ ዱላን፣ የፈላ ውሃን ፣ ዛቻን እና ስድብን ስለምን ከዚህ ሰልፍ ትፈልጋላችሁ? መሥቀል እና ዝማሬ እንጂ ሌላው በዚህ የለም!!!
#መሥከረም_አራት!!!
።።።
""ወይ መካ ላይ ልምጣ ፣ ወይ ነይ ጎሎጎታ
ፍቅር የትም አለ ፣ ሳይወስነው ቦታ !!!"
።።።።
💚💛❤️
ለሀገራችን ሠላም ለህዝቧም ፍቅር ይብዛ!!!
@getem
@getem
@getem
ቀልድን አልተማርኩም ፣ በእምነት እና በሀገር
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ጠብመንጃን ፣ቆንጨራን ፣ ገጀራን ፣ ዱላን፣ የፈላ ውሃን ፣ ዛቻን እና ስድብን ስለምን ከዚህ ሰልፍ ትፈልጋላችሁ? መሥቀል እና ዝማሬ እንጂ ሌላው በዚህ የለም!!!
#መሥከረም_አራት!!!
።።።
""ወይ መካ ላይ ልምጣ ፣ ወይ ነይ ጎሎጎታ
ፍቅር የትም አለ ፣ ሳይወስነው ቦታ !!!"
።።።።
💚💛❤️
ለሀገራችን ሠላም ለህዝቧም ፍቅር ይብዛ!!!
@getem
@getem
@getem
🔥1
እንቁ ዕጣሽ ጣጣሽ
^^^^¿^^^^^¿^^^^^^
ድሮ … ጥንት
ጥሩ መሬት እህል የሚያፈራ
ብርቱ አራሽ ዘር የሚዘራ
አማኝ ምዕመን አምላኩን ሚፈራ
አስተዋይ መሪ ህዝቡን የሚመራ
በነበረሽ ጊዜ
ረሀብ ኮስሶ ጥጋብ ተኮፍሶ
የጎረቤት ጓዳ
የራስ እስኪመስል ሰቆቃ ተደርምሶ
በአብሮ መብላት ባህል
በመተሳሰብ ብሂል ክብርሽ ታድሷል
ዕጣሽ ሰምሮ ፍቅር ነግሷል
ዛሬ …
ክረምት ገብቶ
ከቤትህ ስትወጣ እህል ልትዘራ
ሲለፈፍ ትሰማለህ ስለህዝብ ቆጠራ
ግንቦት ደርሶልህ
ክንድህን አበርትተህ ሞፈር ስታነሳ
ማረሻ ማፈሻ
አርማ ይሆናል ለምርጫ ቅስቀሳ
ምትመርጠውን ሳታውቅ
የተመራጭ ብዛት ከብሔር ይበልጣል
በዚህ ስትወዛገብ
ክረምቱ ጠልቆ ፀደይ ይወጣል
ለሀገር ሲታሰብ
ማረስ ተረስቶ ጓሮ ይሳሳል
የኑሮ ውድነት ጣሪያ ይደርሳል
የት ተሂዶ
አቤት ይባላል ማንስ ይከሰሳል
በሚል ጥያቄ
የመረረው ልጅሽ በቁጭት ይታመሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲላሽቅ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
ኢትዮጵያዬ …
ተባረኪ ሲልሽ
እጆችሽን እንድትዘረጊ አምላክ ይፈቅዳል
የሰንደቅሽን አርማ
በማርያም መቀነት ሰማይ ላይ ይወልዳል
ዕጣሽን ሲያሳምር
የፍቅር ማማ ላይ ጎህ ይቀዳል
በብርሀን ፋና ህዝብሽን አጥምቆ
በእምነት ዘውድ ሰላምሽን አድምቆ
ያኖረሽ አምላክ ዕጣሽን ሲያጠፋ
ለማስመሰል ያጨሽው ዕጣንሽ ከረፋ
የአንድነትሽ ቅዳሴ ልዩነቱ ሰፋ
በዚህም በዚያም መጥፊያሽን ሚያስሱ
የግላቸውን ቤተ ክህነት ሊያቋቁሙ ተነሱ
ሀገሬ …
ጥፊ ያለሽ ጊዜ እምነትሽ ይፈርሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከዳሽ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
በፊት …
ለሰው ልጅ
ክብር ይሰጣል ከሁሉም ልቆ
ሁሉን ከዋኝ
ሁሉን አድራጊ መሆኑ ታውቆ
ዛሬ …
ለልማት ተብሎ ቤት ይፈርሳል
የሰው ልጅ ታንቆ ከተማ ይታደሳል
መጠለያ ያጣ
የዋህ ወገኔ ጎዳና ይፈሳል
የከተማን ውበት
አጠለሸ ተብሎ ተጋፎ ይነሳል
ሚዲያ ይለፍፋል
ለአረንጓዴ ልማት ተሰማራ ብሎ
በውሃ ናፍቆት ህዝብን በጥም ገሎ
ይታለፍ ይመስል
ከችግር አረንቋ ችግኝ ተጠልሎ
እምዬ …
ብዙ ነው ፈታኝሽ
ከባድ ነው ፈተናሽ
ብዙ ነው መካሪሽ
ከባድ ነው መከራሽ
ብዙ ነው ጣይˆሽ
ብሩህ ነው ፀሀይሽ
ብዙ ነው ጨማቂሽ
ጣፋጭ ነው ጭማቂሽ
ያውም … ካልመረረ
… ካልናረ
ሀገሬ …
ተተኪሽን ተኪ
የትምህርት ስርዓትሽ ፍኖቱ ተጣሟል
መርቆ ሸኝ እንጅ
የተመረቀ ተቀባይ እጅ ከስሟል
ፈተና ይሰረቃል
ውጤት ይሰረዛል
የሰው ህይወት ለቁማር ይረከዛል
ይኼውልሽ …
የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኝ
በማሽን ስህተት ውጤቱ ሲናኝ
ስህተትን ለማረም
የትምህርት አይነት ተለይቶ ይቀነሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከስም
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
የኳስሽ እድገት ቁልቁል ይፈሳል
የክለብሽ ስም
የክልል ካባ በላዩ ለብሷል
ደጋፊሽ ሁሌ
ክለቡን ወግኖ ለጥል ይነሳል
ይኸውልሽ …
በቱርክ ወረራ ህዝባችን መክኖ
በኳስ ቁማር ልቡ በግኖ … ስራ አቁሞ
ያለፋበትን ገንዘብ እያሳደደ
በከንቱ ተስፋ
ጨጓራውን ልጦ ህመም ወለደ
መከረኛው ልጅሽ
ለውድቀት ክብር ይኸው ተዘጋጅቷል
እንቁ ዕጣሽን ትቶ
እንቁ ጣጣሽን ይጠብቃል
@getem
@getem
@getem
^^^^¿^^^^^¿^^^^^^
ድሮ … ጥንት
ጥሩ መሬት እህል የሚያፈራ
ብርቱ አራሽ ዘር የሚዘራ
አማኝ ምዕመን አምላኩን ሚፈራ
አስተዋይ መሪ ህዝቡን የሚመራ
በነበረሽ ጊዜ
ረሀብ ኮስሶ ጥጋብ ተኮፍሶ
የጎረቤት ጓዳ
የራስ እስኪመስል ሰቆቃ ተደርምሶ
በአብሮ መብላት ባህል
በመተሳሰብ ብሂል ክብርሽ ታድሷል
ዕጣሽ ሰምሮ ፍቅር ነግሷል
ዛሬ …
ክረምት ገብቶ
ከቤትህ ስትወጣ እህል ልትዘራ
ሲለፈፍ ትሰማለህ ስለህዝብ ቆጠራ
ግንቦት ደርሶልህ
ክንድህን አበርትተህ ሞፈር ስታነሳ
ማረሻ ማፈሻ
አርማ ይሆናል ለምርጫ ቅስቀሳ
ምትመርጠውን ሳታውቅ
የተመራጭ ብዛት ከብሔር ይበልጣል
በዚህ ስትወዛገብ
ክረምቱ ጠልቆ ፀደይ ይወጣል
ለሀገር ሲታሰብ
ማረስ ተረስቶ ጓሮ ይሳሳል
የኑሮ ውድነት ጣሪያ ይደርሳል
የት ተሂዶ
አቤት ይባላል ማንስ ይከሰሳል
በሚል ጥያቄ
የመረረው ልጅሽ በቁጭት ይታመሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲላሽቅ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
ኢትዮጵያዬ …
ተባረኪ ሲልሽ
እጆችሽን እንድትዘረጊ አምላክ ይፈቅዳል
የሰንደቅሽን አርማ
በማርያም መቀነት ሰማይ ላይ ይወልዳል
ዕጣሽን ሲያሳምር
የፍቅር ማማ ላይ ጎህ ይቀዳል
በብርሀን ፋና ህዝብሽን አጥምቆ
በእምነት ዘውድ ሰላምሽን አድምቆ
ያኖረሽ አምላክ ዕጣሽን ሲያጠፋ
ለማስመሰል ያጨሽው ዕጣንሽ ከረፋ
የአንድነትሽ ቅዳሴ ልዩነቱ ሰፋ
በዚህም በዚያም መጥፊያሽን ሚያስሱ
የግላቸውን ቤተ ክህነት ሊያቋቁሙ ተነሱ
ሀገሬ …
ጥፊ ያለሽ ጊዜ እምነትሽ ይፈርሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከዳሽ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
በፊት …
ለሰው ልጅ
ክብር ይሰጣል ከሁሉም ልቆ
ሁሉን ከዋኝ
ሁሉን አድራጊ መሆኑ ታውቆ
ዛሬ …
ለልማት ተብሎ ቤት ይፈርሳል
የሰው ልጅ ታንቆ ከተማ ይታደሳል
መጠለያ ያጣ
የዋህ ወገኔ ጎዳና ይፈሳል
የከተማን ውበት
አጠለሸ ተብሎ ተጋፎ ይነሳል
ሚዲያ ይለፍፋል
ለአረንጓዴ ልማት ተሰማራ ብሎ
በውሃ ናፍቆት ህዝብን በጥም ገሎ
ይታለፍ ይመስል
ከችግር አረንቋ ችግኝ ተጠልሎ
እምዬ …
ብዙ ነው ፈታኝሽ
ከባድ ነው ፈተናሽ
ብዙ ነው መካሪሽ
ከባድ ነው መከራሽ
ብዙ ነው ጣይˆሽ
ብሩህ ነው ፀሀይሽ
ብዙ ነው ጨማቂሽ
ጣፋጭ ነው ጭማቂሽ
ያውም … ካልመረረ
… ካልናረ
ሀገሬ …
ተተኪሽን ተኪ
የትምህርት ስርዓትሽ ፍኖቱ ተጣሟል
መርቆ ሸኝ እንጅ
የተመረቀ ተቀባይ እጅ ከስሟል
ፈተና ይሰረቃል
ውጤት ይሰረዛል
የሰው ህይወት ለቁማር ይረከዛል
ይኼውልሽ …
የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኝ
በማሽን ስህተት ውጤቱ ሲናኝ
ስህተትን ለማረም
የትምህርት አይነት ተለይቶ ይቀነሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከስም
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
የኳስሽ እድገት ቁልቁል ይፈሳል
የክለብሽ ስም
የክልል ካባ በላዩ ለብሷል
ደጋፊሽ ሁሌ
ክለቡን ወግኖ ለጥል ይነሳል
ይኸውልሽ …
በቱርክ ወረራ ህዝባችን መክኖ
በኳስ ቁማር ልቡ በግኖ … ስራ አቁሞ
ያለፋበትን ገንዘብ እያሳደደ
በከንቱ ተስፋ
ጨጓራውን ልጦ ህመም ወለደ
መከረኛው ልጅሽ
ለውድቀት ክብር ይኸው ተዘጋጅቷል
እንቁ ዕጣሽን ትቶ
እንቁ ጣጣሽን ይጠብቃል
@getem
@getem
@getem
❤1
ግጥም እንደዚህ ሲሆን እንዴት የልብ ያደርሳል❤️ለነፍስም ይቀርባል.... ግጥሙ ውስጥ ያለው ፍልስፍናው ሲጣፍጥ ፣ ያገማሽራልም ባነበው ባነው አልጠገብኩትም ....ማሜዋ በረካ ሁን አቦ!!!
( እልል አሮጌ ዓመት)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሃበሻ እና ዘመን
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በሃበሻ ምድር
ከኑባሬ አዳም እስከዛሬ ድረስ
ያደስንውን ዓመት ውሉን ስናጤነው ።
በዘመን አዙሪት የአድስ አመት መምጣት
ሲገባኝ ተፍሲሩ ፍቹን ስተምነው፣
ከአምና የተረፈ የልጅነት ወዝን የኛነትን እሸት
ለተራበው አዲስ ወስዶ መገበር ነው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም ይገርማል ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ አደይ አበባ ኑረቱ ሳይፈካ
በፈኩ ወራቶች ታደስኩኝ ይልሃል፣
በእግረ መንገድ ኑሮ ቀናቶች ሸምነው
አመት ሆነህ ሲሉት እልልታ ያቀልጣል፣
ዳግም ለሚመጣ ለዘመን ቋጠሮ
ድጋሜ እማይመጣ እራሱን ይሰዋል፣
ከእድሜው ተቀንሶ የተወራረደ
የእድሜውን ጎደሎ በፌሽታ ያውጃል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዋህ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዘመን ሩጫ ከትላንት አባሮ ለማያውቀው
ነገ ለመጪው ዘንድሮ ሲድረው ጎትቶ፣
ባድስ አመት ብስራት ማርጀት ይሉት ሸማ
ወዶ መደረቡን መልበሱን ዘንግቶ።
እ
ል
ል
አድስ ዓመት
እ
ል
ል
እንቁጣጣሽ
ማለት ይቀናዋል፣
በአድስ አመት ጀርባ እርጅናና ሞቱን
በእልልታ እያጀበ ያወራርደዋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሞኝ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ተመለስ ብትለው ለማይሰማ ዘመን
እንኳን መጣህ ብሎ ድግስ ያሰናዳል፣
ያልተደካን ዘመን ቁጥር ለመጨመር
የዘመኑን ድካ እድሜውን ይንዳል።
ይሄው እስከዛሬ
ሃበሻና እልልታ በያድስ አመቱ
ቀጠሮ እየያዙ እኩል ቢታደሱም፣
ከአንዱ እየቀነሱ በተቀናሽ ሂሳብ
አንዱን ከማፈርጠም ተሻግረው አያውቁም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሃበሻን ኑረት ከፍታ እሚያሳየን
ፍካት የሚያስዋጀን ቅፅበት እስኪመጣ፣
የዘመን ትከሻ አየገፈተረኝ እድሜየን ገብሬ
ከኖርኩበት ዘመን ከአሮጌው ስወጣ።
ባዶ እጁን ለመጣ ላልኖርኩበት አድስ
አሮጌውና አምና አላማውምና፣
ከአድስነቱ ጋር አድስ እስኪያመጣ
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
እንኳን ኖርኩኝ አምና።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት!!!!!!!!!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሙሃመድ ሰኢድ💚💛❤️
ጷግሜ 5/13/2011
@getem
@getem
@balmbaras
( እልል አሮጌ ዓመት)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሃበሻ እና ዘመን
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በሃበሻ ምድር
ከኑባሬ አዳም እስከዛሬ ድረስ
ያደስንውን ዓመት ውሉን ስናጤነው ።
በዘመን አዙሪት የአድስ አመት መምጣት
ሲገባኝ ተፍሲሩ ፍቹን ስተምነው፣
ከአምና የተረፈ የልጅነት ወዝን የኛነትን እሸት
ለተራበው አዲስ ወስዶ መገበር ነው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም ይገርማል ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ አደይ አበባ ኑረቱ ሳይፈካ
በፈኩ ወራቶች ታደስኩኝ ይልሃል፣
በእግረ መንገድ ኑሮ ቀናቶች ሸምነው
አመት ሆነህ ሲሉት እልልታ ያቀልጣል፣
ዳግም ለሚመጣ ለዘመን ቋጠሮ
ድጋሜ እማይመጣ እራሱን ይሰዋል፣
ከእድሜው ተቀንሶ የተወራረደ
የእድሜውን ጎደሎ በፌሽታ ያውጃል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዋህ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዘመን ሩጫ ከትላንት አባሮ ለማያውቀው
ነገ ለመጪው ዘንድሮ ሲድረው ጎትቶ፣
ባድስ አመት ብስራት ማርጀት ይሉት ሸማ
ወዶ መደረቡን መልበሱን ዘንግቶ።
እ
ል
ል
አድስ ዓመት
እ
ል
ል
እንቁጣጣሽ
ማለት ይቀናዋል፣
በአድስ አመት ጀርባ እርጅናና ሞቱን
በእልልታ እያጀበ ያወራርደዋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሞኝ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ተመለስ ብትለው ለማይሰማ ዘመን
እንኳን መጣህ ብሎ ድግስ ያሰናዳል፣
ያልተደካን ዘመን ቁጥር ለመጨመር
የዘመኑን ድካ እድሜውን ይንዳል።
ይሄው እስከዛሬ
ሃበሻና እልልታ በያድስ አመቱ
ቀጠሮ እየያዙ እኩል ቢታደሱም፣
ከአንዱ እየቀነሱ በተቀናሽ ሂሳብ
አንዱን ከማፈርጠም ተሻግረው አያውቁም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሃበሻን ኑረት ከፍታ እሚያሳየን
ፍካት የሚያስዋጀን ቅፅበት እስኪመጣ፣
የዘመን ትከሻ አየገፈተረኝ እድሜየን ገብሬ
ከኖርኩበት ዘመን ከአሮጌው ስወጣ።
ባዶ እጁን ለመጣ ላልኖርኩበት አድስ
አሮጌውና አምና አላማውምና፣
ከአድስነቱ ጋር አድስ እስኪያመጣ
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
እንኳን ኖርኩኝ አምና።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት!!!!!!!!!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሙሃመድ ሰኢድ💚💛❤️
ጷግሜ 5/13/2011
@getem
@getem
@balmbaras
ግጥም ብቻ 📘
Photo
የተረት መሠረት
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
አባቶች እናቶች
በፍቅር ተጋግዘው ፣ ያቆሙልን እውነት
በዘመን ጠልሽቶ...
ለእኛ ለልጆች ፣ ይመስለናል ተረት፡፡
።።።።።።
የኛ ትልቅ ችግር ፣ የኛ ትልቅ ህመም
መሰረት ሳንይዝ.
"የመሰረት" ብሎ ፣" እሺ" እያሉ ማዝገም፡፡
።።።።።።፣
ተረት ተረት
"የመሰረት"
አንድ ሀገር ነበረች
"እሺ"
እምነትን ከፍቅር ፣ ገምዳ ያስተማረች፡፡
"እሺ"
አናም በዚች ሀገር...
ሙስሊሞች በእምነት ፣ መስጅድ ሲገነቡ
ክርስቲያኖች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ምሶሶ ሲያቀርቡ፡፡
"እሺ"
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም በዚች ሀገር...
ክርስቲያኖች በምነት ፣ ቤተስኪያን ሲያንፁ
ሙስሊሞች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ጉልላት ሲቀርፁ፡፡
"እሺ"
እናም በዚ መልኩ ፣ ሲኖሩ ሰኖሩ
እንደተዋደዱ እንደተፋቀሩ
እንደተጋገዙ እንደተባበሩ
መሰረት እንድናይ...
አንዋር ከራጉኤል ፣ ተጎራብተው ቀሩ
"እሺ"
"እሺ" ማለት ጥሩ
መሰረት ሳይዙ ...
የመሰረት ብሎ ፣ መኖር ነው ችግሩ!!!
።።።።።
።።።።።
በኮልፌ ጠሮ የሚገኝ የኡስማን በስጅድ እና የስላሴ ቤተ ክርስቲያን ጉርብትና።
#ሼር ለሁሉም!!!
@getem
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
አባቶች እናቶች
በፍቅር ተጋግዘው ፣ ያቆሙልን እውነት
በዘመን ጠልሽቶ...
ለእኛ ለልጆች ፣ ይመስለናል ተረት፡፡
።።።።።።
የኛ ትልቅ ችግር ፣ የኛ ትልቅ ህመም
መሰረት ሳንይዝ.
"የመሰረት" ብሎ ፣" እሺ" እያሉ ማዝገም፡፡
።።።።።።፣
ተረት ተረት
"የመሰረት"
አንድ ሀገር ነበረች
"እሺ"
እምነትን ከፍቅር ፣ ገምዳ ያስተማረች፡፡
"እሺ"
አናም በዚች ሀገር...
ሙስሊሞች በእምነት ፣ መስጅድ ሲገነቡ
ክርስቲያኖች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ምሶሶ ሲያቀርቡ፡፡
"እሺ"
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም በዚች ሀገር...
ክርስቲያኖች በምነት ፣ ቤተስኪያን ሲያንፁ
ሙስሊሞች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ጉልላት ሲቀርፁ፡፡
"እሺ"
እናም በዚ መልኩ ፣ ሲኖሩ ሰኖሩ
እንደተዋደዱ እንደተፋቀሩ
እንደተጋገዙ እንደተባበሩ
መሰረት እንድናይ...
አንዋር ከራጉኤል ፣ ተጎራብተው ቀሩ
"እሺ"
"እሺ" ማለት ጥሩ
መሰረት ሳይዙ ...
የመሰረት ብሎ ፣ መኖር ነው ችግሩ!!!
።።።።።
።።።።።
በኮልፌ ጠሮ የሚገኝ የኡስማን በስጅድ እና የስላሴ ቤተ ክርስቲያን ጉርብትና።
#ሼር ለሁሉም!!!
@getem
@getem
@getem
=== ጓደኛዬ እምለው ====
ወረትን አርቆ ከእኔ ተጎዳኝቶ፣
የጀርባ ሹክሹክታን እርግፍ እድርጎ ትቶ፤
ብከፋ ጠይቆ ብሳሳት አርሞ፣
እንደ እናት እንደ አባት ገስጾ ኮርኩሞ፤
የሚያቃናኝን ነው፣
ጓደኛዬ እምለው።
አስተዋይ አሳቢ ክፋት የሌለበት፣
ዝብርቅርቅ ባህሪ የማይታይበት፤
ዛሬም ነገም ፍፁም የማይቀያየር፣
ቁልፉን ያልደበቀ የልቦናውን በር፤
መንፈሰ ጠንካራ የፀና አቋም ያለው፣
ይህ ነው ጓደኛዬ ምርጫዬ ማደርገው፤
ርኅሩኅ አዛኝ ተፈጥሮን አፍቃሪ፣
በእውነት ተመርኩዞ እውነት ተናጋሪ፤
ደስታም ሆነ ሀዘን ቢፈራረቅብኝ፣
አለሁህ የሚለኝ በጣም የማይርቀኝ፤
እምነቱና እምነቴ ልዩነትን ፍቀው፣
የሚሄድ ከሆነ በአንድነት ተሳስረው፣
እስከ እለቴ ሞቴ ጓደኛዬ እሱ ነው።
@getem
@getem
@getem
ወረትን አርቆ ከእኔ ተጎዳኝቶ፣
የጀርባ ሹክሹክታን እርግፍ እድርጎ ትቶ፤
ብከፋ ጠይቆ ብሳሳት አርሞ፣
እንደ እናት እንደ አባት ገስጾ ኮርኩሞ፤
የሚያቃናኝን ነው፣
ጓደኛዬ እምለው።
አስተዋይ አሳቢ ክፋት የሌለበት፣
ዝብርቅርቅ ባህሪ የማይታይበት፤
ዛሬም ነገም ፍፁም የማይቀያየር፣
ቁልፉን ያልደበቀ የልቦናውን በር፤
መንፈሰ ጠንካራ የፀና አቋም ያለው፣
ይህ ነው ጓደኛዬ ምርጫዬ ማደርገው፤
ርኅሩኅ አዛኝ ተፈጥሮን አፍቃሪ፣
በእውነት ተመርኩዞ እውነት ተናጋሪ፤
ደስታም ሆነ ሀዘን ቢፈራረቅብኝ፣
አለሁህ የሚለኝ በጣም የማይርቀኝ፤
እምነቱና እምነቴ ልዩነትን ፍቀው፣
የሚሄድ ከሆነ በአንድነት ተሳስረው፣
እስከ እለቴ ሞቴ ጓደኛዬ እሱ ነው።
@getem
@getem
@getem
አገር ዕንቁጣጣሽ!
(በዕውቀቱ ሥዩም)
..
የ’ዳ ክንድሽ አቅፎኝ
ያሳር ክንፍሽ አቅፎኝ
እንቁሽን ስመኘው
ጣጣሽ ብቻ ተርፎኝ
መኖርን ስፈራ - መሞትም ስፈራ
ካየር ንብረት በቀር - ንብረት ሳላፈራ
ወሩ ተጠራቅሞ - አንድ ደርዘን ሞልቶ
እንደባለጌ ልጅ - በሩን በግሩ ከፍቶ
አዲስ ዘመን ገባ
አዲስ አመት ገባ
ያለ መስቀል ወፎች... ያለ አደይ አበባ።
በግዜር ሰራሽ ማማ፣
ቁራ ብቻ ሰፍሯል
የመስቀል ወፍማ፣
ወይ አገር ለውጧል
ወይ ልብሱን ቀይሯል።
.
አዲስ አመት ገባ...
በቄጤማ ምትክ - ቡልኬት ጎዝጉዞ
በቅፍ አደይ ምትክ -ጉንጉን ሽቦ ይዞ
በሉባንጃ ምትክ- አቡዋራ እያጤሰ
በፈንድሻ ምትክ - ጠጠር እያፈሰ።
.
አዲስ አመት ገባ...
አዲስ እንዲህ ዋዛ
ተፈጥሮ በውበት - መንፈሴን ሳይገዛ
በመአዛው ሳይዋጅ፣
መስከረም መግባቱን - በሬድዮ ልስማው?
እንደ መንግስት አዋጅ።
@getem
@getem
@getem
(በዕውቀቱ ሥዩም)
..
የ’ዳ ክንድሽ አቅፎኝ
ያሳር ክንፍሽ አቅፎኝ
እንቁሽን ስመኘው
ጣጣሽ ብቻ ተርፎኝ
መኖርን ስፈራ - መሞትም ስፈራ
ካየር ንብረት በቀር - ንብረት ሳላፈራ
ወሩ ተጠራቅሞ - አንድ ደርዘን ሞልቶ
እንደባለጌ ልጅ - በሩን በግሩ ከፍቶ
አዲስ ዘመን ገባ
አዲስ አመት ገባ
ያለ መስቀል ወፎች... ያለ አደይ አበባ።
በግዜር ሰራሽ ማማ፣
ቁራ ብቻ ሰፍሯል
የመስቀል ወፍማ፣
ወይ አገር ለውጧል
ወይ ልብሱን ቀይሯል።
.
አዲስ አመት ገባ...
በቄጤማ ምትክ - ቡልኬት ጎዝጉዞ
በቅፍ አደይ ምትክ -ጉንጉን ሽቦ ይዞ
በሉባንጃ ምትክ- አቡዋራ እያጤሰ
በፈንድሻ ምትክ - ጠጠር እያፈሰ።
.
አዲስ አመት ገባ...
አዲስ እንዲህ ዋዛ
ተፈጥሮ በውበት - መንፈሴን ሳይገዛ
በመአዛው ሳይዋጅ፣
መስከረም መግባቱን - በሬድዮ ልስማው?
እንደ መንግስት አዋጅ።
@getem
@getem
@getem
አበባና ዘመን!!!!! ዘመንና አበባ! !!!!
አበባ ለዘመን፣ ቀለም እያዋሰ፣
ዘመን ለመስኩ ዳር፣የእንቁጣጣሽ ጥሎሽ ፣ ጃኖ እያለበሰ፣
የመስከረም አደይ፤ በመልካው ከንፈር ላይ ሳቅ እየደገሰ፤
ታዲያ በዚህ መሃል ፥
እቴ ለምን ይሆን??
"ጠብቅ እመጣለሁ!!!!"
የሚለው ያ ቃልሽ፣
መልሶ መላልሶ መልሶ ፈረሰ???
ደማቃው መስከረም፣
ሸብራቃው መስከረም፤
ይዘልቀው ይሆን ወይ????
ይቻለው ይሆን ወይ????
የከረመን ፍቅር ፣
የሻገተን መውደድ፣
አዚሙን ገላልጦ፣በብርሃን ፀዳል ማንቃት እንደገና፣
ይሆንለት ይሆን፣
ገጥሞ መቀጣጥል፣የፈረሰውን ቃል፣ የእምነቱን ቁመና????
ይህ አበባ ማለት፣
የመስክ ላይ ቆሎ፣
ፍክትክት ፣ፍንድቅድቅ ፣ ፍልቅልቅ አለሳ???
አዝመራና እሸቱ፤
ሜዳው ላይ ሲያሽቃርር ፣
እንደ እምቦሳ ጥጃ፣ እንደ ደንገላሳ፣
ደግሞ በእርሻየ ላይ፤
የከረመ መውደድ፣
የከሰረ ናፍቆት፣
እንደ እንግጫ በዝቶ አለሁኝ እያለ፣ ሆ ብሎ ይነሳ???
በከረመው ሰማይ፣ በሃምሌ ደመና፣
አደይ አበባየ ልምጣ አልምጣ እያለች በጉም ተሸፍና ፤
ነይልኝ እያልኳት፣
ጳጉሜ ዝናብ ጥሏል ፤ጎርፍ ነው አለችኝ መንገዷም አልቀና፤
ብየ አልቅሼ ነበር፤
ምነው በኔ መንደር፤
ዝናብ አልሆን አለ ፤ አይኔ ላይ ያበጠው የናፍቆት ደመና??
በናፍቆት ሲጠሩት፤
ወይ!!!!! ያላለ መውደድ፣
እሽ እማይል መንገድ፣ያላከመው ናፍቆት፣ ያላደለው ገላ፣
ቢስሙት አይድንም፣
ቢጠሩት አይሰማም፣ ጳጉሜ ከበረረ ከተሸኘ ዃላ።
ሃኒ የኔ ቆንጆ !!!!
የሚለውን ተረት፣ ተይው ገደል ይግባ፣
ምን በወጣኝ ዛሬ፣
በእንቁጣጣሽ ማጀት፣በሃኒ ቁልምጫ፣ ሆዴ የሚባባ??
ይልቅ፣
ያ ደማሙ ፍቅርሽ፣
ያ ጌጠኛው ሳቅሽ፣አይኔን የሚያሽረው፣ ካንጀቴ እሚገባ፣
ይህ ከርታታው ልቤ፣አልመጣችም ብሎ፣ ቂም የማይጋባ፣
ስትልኪልኝ ነው፣
የመስኩን ላይ እሸት፣
አደይ እንጉዳዩን፣ የአድባሩን ቀዘባ፣
ውብ አንች ሳቅሽን ፣ ውብ አደይ አበባ።
አበባና ዘመን፣ዘመንና ተስፋ፣ ከተሸባረቁ፣
በመስኩ ገላ ላይ፤ እቅፍቅፍ ብለው ፍቅር ከወደቁ፣
ናፍቆት ላሰከረው፣
መውደድ ላተኮሰው፣ በእንቁጣጣሽ ሰሞን፣
ለካስ መድሃኒት ነው፣እንቁጣጣሽ ብሎ፣ በአበባ ማሽሞንሞን።
ይኸውልሽ ማሬ፣
ጳጉሜ ተፋሰሰ፣ እንቁጣጣሽ ገባ፣
ቀንሽና ቀኔ፣
አለ እንደተራበ፣ አለ እንደተዛባ፣
ወይ መውደዴ አልሻረ፣ ወይ እግርሽ አልገባ፣
አይዞህ ይለኛል፣
የማዶ አገር ፍቅርሽ፣
በጄ እያስታቀፈኝ፣በስእል ያማረ ፤ ናፍቆትና አበባ።
እናም፣
ከምናምን ከንፈር፣ ከተደሟሞሰ፣
ከሽፍንፍን ገላ፣ ቂም ከተለወሰ፣
ከእመጣለሁ ተስፋ፣ ከተልፈሰፈሰ፣
ከጠብቀኝ ምኞት፣ ከተልከሰከሰ፣
ይቅርብሽ እቴ ሆይ፣
ምኞት ምን ሊፈይድ፣ ቅዠት ምን ሊረባ፣
ያን የለመድኩትን፣
ችፍርግ አበባሽን፣
እንቁጣጣሽ ብለሽ ላኪው ቤቴ ይግባ።
አየሽ፣
አገኝሽ ይሆናል፣
ትመጭ ይሆናል፣
በመስከረም ሰማይ፣
ምድር እንዳማረች፣ቄጤማ ነስንሳ፣ እንግጫ ደርባ፣
ግን እስከዚያው ድረስ፣
መጣሁኝ እያለ፣ጳጉሜ ሲያረገርግ፣ መስከረም ሲገባ፣
ትልኪው አታጭም፣ሳቅና ሆይ ላሌ፣ ሆየና ወሸባ፣
መላክ አይሰለችሽ፣
ያንኑ ፖስት ካርድ ፤
ከላዮ ያለበት ፤እንግጫና ናፍቆት፣ አደይና አበባ።
((( ጃ ኖ ))💚🌼💛🌼❤️🌼
@getem
@getem
@balmbaras
አበባ ለዘመን፣ ቀለም እያዋሰ፣
ዘመን ለመስኩ ዳር፣የእንቁጣጣሽ ጥሎሽ ፣ ጃኖ እያለበሰ፣
የመስከረም አደይ፤ በመልካው ከንፈር ላይ ሳቅ እየደገሰ፤
ታዲያ በዚህ መሃል ፥
እቴ ለምን ይሆን??
"ጠብቅ እመጣለሁ!!!!"
የሚለው ያ ቃልሽ፣
መልሶ መላልሶ መልሶ ፈረሰ???
ደማቃው መስከረም፣
ሸብራቃው መስከረም፤
ይዘልቀው ይሆን ወይ????
ይቻለው ይሆን ወይ????
የከረመን ፍቅር ፣
የሻገተን መውደድ፣
አዚሙን ገላልጦ፣በብርሃን ፀዳል ማንቃት እንደገና፣
ይሆንለት ይሆን፣
ገጥሞ መቀጣጥል፣የፈረሰውን ቃል፣ የእምነቱን ቁመና????
ይህ አበባ ማለት፣
የመስክ ላይ ቆሎ፣
ፍክትክት ፣ፍንድቅድቅ ፣ ፍልቅልቅ አለሳ???
አዝመራና እሸቱ፤
ሜዳው ላይ ሲያሽቃርር ፣
እንደ እምቦሳ ጥጃ፣ እንደ ደንገላሳ፣
ደግሞ በእርሻየ ላይ፤
የከረመ መውደድ፣
የከሰረ ናፍቆት፣
እንደ እንግጫ በዝቶ አለሁኝ እያለ፣ ሆ ብሎ ይነሳ???
በከረመው ሰማይ፣ በሃምሌ ደመና፣
አደይ አበባየ ልምጣ አልምጣ እያለች በጉም ተሸፍና ፤
ነይልኝ እያልኳት፣
ጳጉሜ ዝናብ ጥሏል ፤ጎርፍ ነው አለችኝ መንገዷም አልቀና፤
ብየ አልቅሼ ነበር፤
ምነው በኔ መንደር፤
ዝናብ አልሆን አለ ፤ አይኔ ላይ ያበጠው የናፍቆት ደመና??
በናፍቆት ሲጠሩት፤
ወይ!!!!! ያላለ መውደድ፣
እሽ እማይል መንገድ፣ያላከመው ናፍቆት፣ ያላደለው ገላ፣
ቢስሙት አይድንም፣
ቢጠሩት አይሰማም፣ ጳጉሜ ከበረረ ከተሸኘ ዃላ።
ሃኒ የኔ ቆንጆ !!!!
የሚለውን ተረት፣ ተይው ገደል ይግባ፣
ምን በወጣኝ ዛሬ፣
በእንቁጣጣሽ ማጀት፣በሃኒ ቁልምጫ፣ ሆዴ የሚባባ??
ይልቅ፣
ያ ደማሙ ፍቅርሽ፣
ያ ጌጠኛው ሳቅሽ፣አይኔን የሚያሽረው፣ ካንጀቴ እሚገባ፣
ይህ ከርታታው ልቤ፣አልመጣችም ብሎ፣ ቂም የማይጋባ፣
ስትልኪልኝ ነው፣
የመስኩን ላይ እሸት፣
አደይ እንጉዳዩን፣ የአድባሩን ቀዘባ፣
ውብ አንች ሳቅሽን ፣ ውብ አደይ አበባ።
አበባና ዘመን፣ዘመንና ተስፋ፣ ከተሸባረቁ፣
በመስኩ ገላ ላይ፤ እቅፍቅፍ ብለው ፍቅር ከወደቁ፣
ናፍቆት ላሰከረው፣
መውደድ ላተኮሰው፣ በእንቁጣጣሽ ሰሞን፣
ለካስ መድሃኒት ነው፣እንቁጣጣሽ ብሎ፣ በአበባ ማሽሞንሞን።
ይኸውልሽ ማሬ፣
ጳጉሜ ተፋሰሰ፣ እንቁጣጣሽ ገባ፣
ቀንሽና ቀኔ፣
አለ እንደተራበ፣ አለ እንደተዛባ፣
ወይ መውደዴ አልሻረ፣ ወይ እግርሽ አልገባ፣
አይዞህ ይለኛል፣
የማዶ አገር ፍቅርሽ፣
በጄ እያስታቀፈኝ፣በስእል ያማረ ፤ ናፍቆትና አበባ።
እናም፣
ከምናምን ከንፈር፣ ከተደሟሞሰ፣
ከሽፍንፍን ገላ፣ ቂም ከተለወሰ፣
ከእመጣለሁ ተስፋ፣ ከተልፈሰፈሰ፣
ከጠብቀኝ ምኞት፣ ከተልከሰከሰ፣
ይቅርብሽ እቴ ሆይ፣
ምኞት ምን ሊፈይድ፣ ቅዠት ምን ሊረባ፣
ያን የለመድኩትን፣
ችፍርግ አበባሽን፣
እንቁጣጣሽ ብለሽ ላኪው ቤቴ ይግባ።
አየሽ፣
አገኝሽ ይሆናል፣
ትመጭ ይሆናል፣
በመስከረም ሰማይ፣
ምድር እንዳማረች፣ቄጤማ ነስንሳ፣ እንግጫ ደርባ፣
ግን እስከዚያው ድረስ፣
መጣሁኝ እያለ፣ጳጉሜ ሲያረገርግ፣ መስከረም ሲገባ፣
ትልኪው አታጭም፣ሳቅና ሆይ ላሌ፣ ሆየና ወሸባ፣
መላክ አይሰለችሽ፣
ያንኑ ፖስት ካርድ ፤
ከላዮ ያለበት ፤እንግጫና ናፍቆት፣ አደይና አበባ።
((( ጃ ኖ ))💚🌼💛🌼❤️🌼
@getem
@getem
@balmbaras
ግጥም ብቻ 📘
Photo
በአንድነት እንዘምን
______
🌼🌼🌼🌼🌼
አሮጌዋን አመት
ቆፈኑን ተሻግረን
ክረምቷን አጀብናት፣
በውርጩ ዘለቅናት
የሰማይ ዶፍ አልፈን፣
ውሃው ላይ ተንሳፈን፣
የሀምሌን ነጎድጓድ
ምጡን ተቋቁመን፣
ይኸው ተገናኘን፣
ዳግም በአዲስ ዘመን።🌼
አደይ ሽሙንሙኗ፣
ሲነጉድ ዘመኗ፣
በመስከረም ነፍሷ፣
ከተፍ ትላለች
ከተራሮች አናት፣
በቢጫ ቀሚሷ።
ጀምበር ሳቅ ስትል፣🌼
በአዲሷ መስከረም፣
ተነቅሎ ይወገድ፣
የጥላቻው አረም።
መስከረም ስታጌጥ፣
የዘር ፍቅር እሳት፣
ውሃ ይደፋበት፣
አስክሮ የሚጥል፣🌼
የብሔር አረቄ፣
ሀይሉ ይድከምበት።
በአንድነት ሰማይ ላይ፣
ከ ሰላም ደመና ፣
ጠማማ የነበረው፣
ዳግም እንዲቃና፣
የጥላቻው በርኖስ፣
ይውደቅ ከገሀነብ፣
ለስኬቱ ጣሪያ፣
የሰላም ዶፍ ይዝነብ።
አሮጌው አመት አልፎ፣🌼
አዲሱ ሲገባ፣
ለምልማ ያጌጠች፣
አዲሲቷ ኢትዮጵያ፣
እንድትገነባ፣
የደረቀው ሰላም፣🌼
በፍቅር እንዲርስ፣
አንቆ የሚያስቀረውን ፣
የጥሉን ግድግዳ፣
በአንድነት እናፍርስ።🌼
በአደይ አበቦች፣
መሐል ላይ ተከበን፣
ያቺ የመስቀል ወፍ፣
እንዳትታዘበን፣🌼
ለእድገት ከፍታ፣
ተስፋን እያለምን፣
ከአዲሱ ዘመን ጋር፣
በአንድነት እንዘምን።
መልካም አዲስ አመት!!!
✍
ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
______
🌼🌼🌼🌼🌼
አሮጌዋን አመት
ቆፈኑን ተሻግረን
ክረምቷን አጀብናት፣
በውርጩ ዘለቅናት
የሰማይ ዶፍ አልፈን፣
ውሃው ላይ ተንሳፈን፣
የሀምሌን ነጎድጓድ
ምጡን ተቋቁመን፣
ይኸው ተገናኘን፣
ዳግም በአዲስ ዘመን።🌼
አደይ ሽሙንሙኗ፣
ሲነጉድ ዘመኗ፣
በመስከረም ነፍሷ፣
ከተፍ ትላለች
ከተራሮች አናት፣
በቢጫ ቀሚሷ።
ጀምበር ሳቅ ስትል፣🌼
በአዲሷ መስከረም፣
ተነቅሎ ይወገድ፣
የጥላቻው አረም።
መስከረም ስታጌጥ፣
የዘር ፍቅር እሳት፣
ውሃ ይደፋበት፣
አስክሮ የሚጥል፣🌼
የብሔር አረቄ፣
ሀይሉ ይድከምበት።
በአንድነት ሰማይ ላይ፣
ከ ሰላም ደመና ፣
ጠማማ የነበረው፣
ዳግም እንዲቃና፣
የጥላቻው በርኖስ፣
ይውደቅ ከገሀነብ፣
ለስኬቱ ጣሪያ፣
የሰላም ዶፍ ይዝነብ።
አሮጌው አመት አልፎ፣🌼
አዲሱ ሲገባ፣
ለምልማ ያጌጠች፣
አዲሲቷ ኢትዮጵያ፣
እንድትገነባ፣
የደረቀው ሰላም፣🌼
በፍቅር እንዲርስ፣
አንቆ የሚያስቀረውን ፣
የጥሉን ግድግዳ፣
በአንድነት እናፍርስ።🌼
በአደይ አበቦች፣
መሐል ላይ ተከበን፣
ያቺ የመስቀል ወፍ፣
እንዳትታዘበን፣🌼
ለእድገት ከፍታ፣
ተስፋን እያለምን፣
ከአዲሱ ዘመን ጋር፣
በአንድነት እንዘምን።
መልካም አዲስ አመት!!!
✍
ዮሐንስ ገርማሜ
@getem
@getem
@getem
👍2
ደስ ይላል መስከረም
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በግርሻ'ጣይ ሰርዶ ነቅሎ በሚያዚያንሽ ተርበጥብጦ ...
በግንቦት ሐሩር ተቀቅሎ ... በፀሐይ አብስሎ በዝናብ አብቅሎ
ከወዳጅ ከዘመድ ተቀላቅሎ ...
ባዝራን ከአህያ አዳቅሎ ...
በባለበርሸት ሽልም በቅሎ ...
ተፈናጦ አብሮ ገስግሶ ...
ጅራፍ ግርፊያ ሆያ ሆዬ ...ቡሄ በሉ ተጫውቶ ...
ኪዳነ ምሕረትን አንግሶ ... ደግሞ በወሩ ለአስተሮዬው..
ግሼን ማሪያም እማአርያም ... ደጀሰላም ደርሶ ለመሳለም..
" እዮሃ አበባዬ መስከረም ጠባዬ ..
ዐደይ ለምለም ለኔ እንዳንቺ የለም..."
እያሉ ንጥቂያ ...
ከጀንበር መፍለቂያ እሥከ ጀንበር መጥለቂያ
አለላ ነቅሎ ባሕር እንጉዳይ ...
ጀግና ሰውገዳይ...
አካል እንጉዳይ...
እያሉ ሲያንጎራጉሩ
ደስ ይላል መስከረም !
.
ቡቃያው ጣል ከንበል ሲስ ...
ሽሩባዋ ወርዶ እንዲያ ሲዘናፈል ...
ልቤ እንደበቆሎ ያድራል ሲፈለፈል...
በቀጭን ተሰርታ ሥትል ዘንከት ዘንከት ...
ጃሎ ሲል ሊያነጋ አገር በመለከት ...
ለመስቀል ጠንስሶ ... በማድጋ ገንቦ ለእንግዳ ቀንሶ ...
በሞቴ አፈር ስሆን እያለ ሲያጋፍር ...
ጥርስ እንጎቻ አስፍቶ አሞጭ በመሰለው እርጎ ፍርፍር ...
እንኳን ሳቅ ጨዋታው ድብድቡ ልፊያው ...
ድገሙኝ ያሰኛል ሰፈፍ የለሽ ሞገድ መደዶ ዘር ዜማ ሲቆረቆር ክትፊያው..
ደስ ይላል መስከረም !
.
የሽንብራ ሸት እየጠረጠሩ ...
የልጅነት ሚዜ 'ኧረ አይዋ ክንዴ' እያሉ እየጠሩ ..
አብሮ ወፍ ጥበቃ ማማ ላይ ተሰቅሎ ...
ካፊያውን በገሳ በአንድ ተጠልሎ...
እሳት አቀጣጥሎ በቆሎ ጠባብሶ ...
አየሁ አላየሁም...ሰማሁ አልሰማሁም ...
በላልቶ አፍ አብሶ ...
ለስለሶ አስፈትሎ የ'ናት ኩታ ለብሶ ...
ላዋቂ ተልኮ ለልጅ ተጎናብሶ ...
ደስ ይላል መስከረም !
.
እንደቢራ ቢሮ አበባ ለአበባ ዐደይ እንቡር እንቡር ...
በፍቅር ለመክረም ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ወፉ ከነ ጎጆው እሥከ መናጆው ...
ንቡ ከነ ቀፎው መረባ ከነ እርፎው ...
በዐደይ ለምለም ክብር ለመስከረም ክብር ...
ቅዱስ ! ቅዱስ ! ቅዱስ !
የዓመት አሥራት ሊያፈስ ...
ሊያስገባለት ግብር ...
በዝማሬ ሲያብር ...
አንጄት ሲበረብር ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ተዋዶ ወዶ ተወሕዶ ... ያንጀት ተፈቃቅዶ ...
ባንድ አብሮ ለመክረም ...
ደስ ይላል መስከረም !
ለቅኔ ዘረፋው ጠፈፍ ሲል ፈፋው ...
የቆሎ ተማሪ ያ ተመራማሪ ...
የወላዲት አምላክ የድንግል አዝማሪ ...
ያ ደበሎ ለባሽ .... !
በእግዚትነ ማሪያም ...እባካቹህ እባሽ እባካቹህ ቁራሽ..
እያለ ሲለምን ...
ከጥንቅሹ ቅንጥሽ ማሩቴ ባይሰጠው ...
አይቀር መደንገጡ አራሽ አባ ወራሽ ማብላት ያሰለጠው..!
የማይለወጠው..!
በዐይኑ እየመዘነ በልቡ እማይመርጠው ...
ገሩ ባላገሩ...!
ያ ባለሞፈሩ ያ ባለዘገሩ ...,!
በሞቴ ነው ቋንቋው ስሞት ነው ነገሩ...!
ደስ ይላል መስከረም !
.
ወዶ ተወሕዶ ያንጀት ተፈቃቅዶ ...!
አንድ ልብ አቅዶ...!
አንድ ላይ ለመክረም...!
ደስ ይላል መስከረም !
...
ጥቅምትና ኅዳር ቢያዋውል ምንጭ ዳር ...
ታኅሳስና ጥር ዐውድማ አስለቅልቆ ጥሪት እሚያስቋጥር..
የካቲት መጋቢት መኸር አስከትቶ ቢያበስል እንደ ዐቃቢት..
ሚያዚያና ግንቦቱ ተርቲበኛው ቀርቦ ወርዶ ራከቦቱ...
የላም ልጅ በዋንጫ ቢቀርብ ሥልባቦቱ...
ሰኔ ሐምሌ ነሐሴ እንደ ቄስ ምናሴ...
እያረበረበ ደግሞ እየወረበ...
ሰማይ በበረቀ ታርሶርሶ ሲስረቀረቅ...
ከራሱ እስኪታረቅ...!
ሁሉም እንደ ግብሩ..
ሁሉም እንደ ሙያው...!
አሥራ ሁለቱም ወር ...
እዮሃ አበባዬ መስከረም ሲጠባ..
ያኔ ነው ገቢያ..
ያኔ ነው መታያው ...
ያኔ ነው ማባያው ...
ደስ ይላል መስከረም ! ! !
.
( ሙሉ ጌታ ተስፋዬ )💚🌼💛🌼❤️🌼
… እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
ገ/ክርስቶስ ደስታ
(እንደገና)🌼🌼🌼
…በይ ብር በይ ቢራ ቢሮ፣ ክረምት ላንቺ
ብቻ አለፈ
ሌላው በጎርፍ ጎረፈ
ሞተ፣ በተኛበት ረጋ…
ፀደይ ላንቺ ብቻ ነጋ
ሽር ብለሽ መንቆጥቆጥ ነው፤ ከዚያም፤
ከዚያም፤ ከዚያም ሰምሮ
አወቅሁብሽ፤ ነቃሁብሽ፤ አንቺ ሕይወት
ቢራ ቢሮ…
ቀናሁ መሰል አንች ወላዋይ?
ነይ ብር በይ እንወያይ
አንቺ የዕፅዋት አዋዋይ
ከፀደይ ጋር ፀደይ መሳይ
ከአበባም አበባ መሳይ…
ምን አለበት ላንዲት ሰሞን
ቢራ ቢሮ እኔ አንቺን ብሆን?
ፀጋዬ ገ/መድህን
(ሕይወት ቢራቢሮ)🌼🌼🌼
… ወፎች ሲዘምሩ ሰማይ ደማስ መስሎ፣
ሐሴት ገባ ልቤ በውበት ተኩሎ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ወፎች በተጥለግለግ - 1955 ዓ.ም)
* * *
…ነበረች አበባ፣
በሾህ ተቀንብባ፣
መዓዛዋ ዘምቶ፣
ተወርዋሪን ኮከብ አቀረበው ጠርቶ፡፡
በውበት ብትልቅ ይህች የዋህ አበባ፣
ረብ የሰው ዘየ በሾህ ተቀንብባ፣
እሾህ አያስደርስ፣ ቆንጥሩ አያስጠጋ፣ የዘመን
ጋሬጣ አድርጓት ሰለባ፣
በእጦት መቃጠል ነው መዓዛዋ ሲያውድ
ከልብ እየገባ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ተወርዋሪ ኮከብ)🌼🌼🌼
የተስፋዬ ዛፉ
ሊከረከም ቅርንጫፉ፣
ሥሩ ሲነቃቀል
ሲበጠስ ሲፈነገል፤
ጭላንጭል ስትዳፈን
ብርሀን ዐይኑ ሲከደን፣
አንጥፌ ደርቤ ማቄን
ዘንግቻት እንቁጣጣሽን
ፀደይ አበባ ዐደዬን፣
በድቅድቅ ተቀመጥሁኝ
ላለማሰብ እያሰብሁኝ፣
የልቤን ልበ ባሻነት ገሰጽኩኝ
ተስፋ መቁረጥን ተስፋ አረኩኝ፡፡
ደበበ ሰይፉ
(የተስፋዬ ዛፉ)🌼🌼🌼
@getem
@getem
@balmbaras
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በግርሻ'ጣይ ሰርዶ ነቅሎ በሚያዚያንሽ ተርበጥብጦ ...
በግንቦት ሐሩር ተቀቅሎ ... በፀሐይ አብስሎ በዝናብ አብቅሎ
ከወዳጅ ከዘመድ ተቀላቅሎ ...
ባዝራን ከአህያ አዳቅሎ ...
በባለበርሸት ሽልም በቅሎ ...
ተፈናጦ አብሮ ገስግሶ ...
ጅራፍ ግርፊያ ሆያ ሆዬ ...ቡሄ በሉ ተጫውቶ ...
ኪዳነ ምሕረትን አንግሶ ... ደግሞ በወሩ ለአስተሮዬው..
ግሼን ማሪያም እማአርያም ... ደጀሰላም ደርሶ ለመሳለም..
" እዮሃ አበባዬ መስከረም ጠባዬ ..
ዐደይ ለምለም ለኔ እንዳንቺ የለም..."
እያሉ ንጥቂያ ...
ከጀንበር መፍለቂያ እሥከ ጀንበር መጥለቂያ
አለላ ነቅሎ ባሕር እንጉዳይ ...
ጀግና ሰውገዳይ...
አካል እንጉዳይ...
እያሉ ሲያንጎራጉሩ
ደስ ይላል መስከረም !
.
ቡቃያው ጣል ከንበል ሲስ ...
ሽሩባዋ ወርዶ እንዲያ ሲዘናፈል ...
ልቤ እንደበቆሎ ያድራል ሲፈለፈል...
በቀጭን ተሰርታ ሥትል ዘንከት ዘንከት ...
ጃሎ ሲል ሊያነጋ አገር በመለከት ...
ለመስቀል ጠንስሶ ... በማድጋ ገንቦ ለእንግዳ ቀንሶ ...
በሞቴ አፈር ስሆን እያለ ሲያጋፍር ...
ጥርስ እንጎቻ አስፍቶ አሞጭ በመሰለው እርጎ ፍርፍር ...
እንኳን ሳቅ ጨዋታው ድብድቡ ልፊያው ...
ድገሙኝ ያሰኛል ሰፈፍ የለሽ ሞገድ መደዶ ዘር ዜማ ሲቆረቆር ክትፊያው..
ደስ ይላል መስከረም !
.
የሽንብራ ሸት እየጠረጠሩ ...
የልጅነት ሚዜ 'ኧረ አይዋ ክንዴ' እያሉ እየጠሩ ..
አብሮ ወፍ ጥበቃ ማማ ላይ ተሰቅሎ ...
ካፊያውን በገሳ በአንድ ተጠልሎ...
እሳት አቀጣጥሎ በቆሎ ጠባብሶ ...
አየሁ አላየሁም...ሰማሁ አልሰማሁም ...
በላልቶ አፍ አብሶ ...
ለስለሶ አስፈትሎ የ'ናት ኩታ ለብሶ ...
ላዋቂ ተልኮ ለልጅ ተጎናብሶ ...
ደስ ይላል መስከረም !
.
እንደቢራ ቢሮ አበባ ለአበባ ዐደይ እንቡር እንቡር ...
በፍቅር ለመክረም ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ወፉ ከነ ጎጆው እሥከ መናጆው ...
ንቡ ከነ ቀፎው መረባ ከነ እርፎው ...
በዐደይ ለምለም ክብር ለመስከረም ክብር ...
ቅዱስ ! ቅዱስ ! ቅዱስ !
የዓመት አሥራት ሊያፈስ ...
ሊያስገባለት ግብር ...
በዝማሬ ሲያብር ...
አንጄት ሲበረብር ... !
ደስ ይላል መስከረም !
ተዋዶ ወዶ ተወሕዶ ... ያንጀት ተፈቃቅዶ ...
ባንድ አብሮ ለመክረም ...
ደስ ይላል መስከረም !
ለቅኔ ዘረፋው ጠፈፍ ሲል ፈፋው ...
የቆሎ ተማሪ ያ ተመራማሪ ...
የወላዲት አምላክ የድንግል አዝማሪ ...
ያ ደበሎ ለባሽ .... !
በእግዚትነ ማሪያም ...እባካቹህ እባሽ እባካቹህ ቁራሽ..
እያለ ሲለምን ...
ከጥንቅሹ ቅንጥሽ ማሩቴ ባይሰጠው ...
አይቀር መደንገጡ አራሽ አባ ወራሽ ማብላት ያሰለጠው..!
የማይለወጠው..!
በዐይኑ እየመዘነ በልቡ እማይመርጠው ...
ገሩ ባላገሩ...!
ያ ባለሞፈሩ ያ ባለዘገሩ ...,!
በሞቴ ነው ቋንቋው ስሞት ነው ነገሩ...!
ደስ ይላል መስከረም !
.
ወዶ ተወሕዶ ያንጀት ተፈቃቅዶ ...!
አንድ ልብ አቅዶ...!
አንድ ላይ ለመክረም...!
ደስ ይላል መስከረም !
...
ጥቅምትና ኅዳር ቢያዋውል ምንጭ ዳር ...
ታኅሳስና ጥር ዐውድማ አስለቅልቆ ጥሪት እሚያስቋጥር..
የካቲት መጋቢት መኸር አስከትቶ ቢያበስል እንደ ዐቃቢት..
ሚያዚያና ግንቦቱ ተርቲበኛው ቀርቦ ወርዶ ራከቦቱ...
የላም ልጅ በዋንጫ ቢቀርብ ሥልባቦቱ...
ሰኔ ሐምሌ ነሐሴ እንደ ቄስ ምናሴ...
እያረበረበ ደግሞ እየወረበ...
ሰማይ በበረቀ ታርሶርሶ ሲስረቀረቅ...
ከራሱ እስኪታረቅ...!
ሁሉም እንደ ግብሩ..
ሁሉም እንደ ሙያው...!
አሥራ ሁለቱም ወር ...
እዮሃ አበባዬ መስከረም ሲጠባ..
ያኔ ነው ገቢያ..
ያኔ ነው መታያው ...
ያኔ ነው ማባያው ...
ደስ ይላል መስከረም ! ! !
.
( ሙሉ ጌታ ተስፋዬ )💚🌼💛🌼❤️🌼
… እንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር
ሌላም… ደግሞ ሌላ
አለብኝ ትዝታ!
ዘመዶቼ ሳሙኝ
ጓደኞቼም ጋብዙኝ
ሊስትሮ ጨብጠኝ
ባለጋሪ ንዳ መንገዴን አሳየኝ
ያገሬ ልጅ ቆንጆ ‹‹ቤት ለእንግዳ›› በይኝ
አለብኝ ትዝታ…
ገ/ክርስቶስ ደስታ
(እንደገና)🌼🌼🌼
…በይ ብር በይ ቢራ ቢሮ፣ ክረምት ላንቺ
ብቻ አለፈ
ሌላው በጎርፍ ጎረፈ
ሞተ፣ በተኛበት ረጋ…
ፀደይ ላንቺ ብቻ ነጋ
ሽር ብለሽ መንቆጥቆጥ ነው፤ ከዚያም፤
ከዚያም፤ ከዚያም ሰምሮ
አወቅሁብሽ፤ ነቃሁብሽ፤ አንቺ ሕይወት
ቢራ ቢሮ…
ቀናሁ መሰል አንች ወላዋይ?
ነይ ብር በይ እንወያይ
አንቺ የዕፅዋት አዋዋይ
ከፀደይ ጋር ፀደይ መሳይ
ከአበባም አበባ መሳይ…
ምን አለበት ላንዲት ሰሞን
ቢራ ቢሮ እኔ አንቺን ብሆን?
ፀጋዬ ገ/መድህን
(ሕይወት ቢራቢሮ)🌼🌼🌼
… ወፎች ሲዘምሩ ሰማይ ደማስ መስሎ፣
ሐሴት ገባ ልቤ በውበት ተኩሎ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ወፎች በተጥለግለግ - 1955 ዓ.ም)
* * *
…ነበረች አበባ፣
በሾህ ተቀንብባ፣
መዓዛዋ ዘምቶ፣
ተወርዋሪን ኮከብ አቀረበው ጠርቶ፡፡
በውበት ብትልቅ ይህች የዋህ አበባ፣
ረብ የሰው ዘየ በሾህ ተቀንብባ፣
እሾህ አያስደርስ፣ ቆንጥሩ አያስጠጋ፣ የዘመን
ጋሬጣ አድርጓት ሰለባ፣
በእጦት መቃጠል ነው መዓዛዋ ሲያውድ
ከልብ እየገባ፡፡
ዮሐንስ አድማሱ
(ተወርዋሪ ኮከብ)🌼🌼🌼
የተስፋዬ ዛፉ
ሊከረከም ቅርንጫፉ፣
ሥሩ ሲነቃቀል
ሲበጠስ ሲፈነገል፤
ጭላንጭል ስትዳፈን
ብርሀን ዐይኑ ሲከደን፣
አንጥፌ ደርቤ ማቄን
ዘንግቻት እንቁጣጣሽን
ፀደይ አበባ ዐደዬን፣
በድቅድቅ ተቀመጥሁኝ
ላለማሰብ እያሰብሁኝ፣
የልቤን ልበ ባሻነት ገሰጽኩኝ
ተስፋ መቁረጥን ተስፋ አረኩኝ፡፡
ደበበ ሰይፉ
(የተስፋዬ ዛፉ)🌼🌼🌼
@getem
@getem
@balmbaras
❤1👍1