ግጥም ብቻ 📘
64.3K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
በውዴታ የማትገኝ ጥበብ
___________

ጥበብን ላዋራት
ቀርቤያት ከሁዋላ..
እርሷ ግን ሸሸችኝ
አልፈልግም ብላ።
አቦ ስታስጠላ
ንቀት አይሉት ኩራት
እኔ እዚህ ቁጭ ብዬ
የሩቅ ሰው አማራት ።
አላወቅኩም ለካ....

እየተሯሯጥኩኝ
ነይ ወደ እኔ ስላት...
ለካ እኔ ማላውቀው
ሌላ ጓደኛ አላት።

ዮሐንስ ገርማሜ

@getem
@getem
@getem
ለ 10ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኞች በሙሉ
በቀላሉ ውጤቶን ለማየት የሚያስችል አዲስ ቦት @neaea_neaea_bot ተሰራ ፣ ቀላል ፣ ቀልጣፋ እና ታአማኒ ያለምንም የሰው ጣልቃ ገበነት 24/7 የሚሰራ ።
የእርሶን እና የጓደኞዎቾ እንዲሁም፣ኢንተርኔት ዝግ ለሚልባቸው ቦታዎች ሁሉ መፍትሔ የሚሆን @neaea_neaea_bot
(ለ10ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ ውጤት ልክ ሲወጣ የማሳወቂያ መልእክት እንልካለን።)

12 ኛ ምድብ ምት ጠብ ቁም እዚሁ bot ላይ ታገኙታላችሁ

@getem
@getem
አትንኩን!!..(ልዑል ኃይሌ)

ማተቤን አትንኩት ውሰዱት አንገቴን፤
ላይ ሌላ ነፍስ አለኝ አልፈራውም ሞቴን፤
ምግባሬ ቢቀልልም ከመስቀሉ ሚዛን፤
በእሳት አትሸጡትም በደም የተገዛን፤
እረፉ!

ጳጉሜ ፬፡ ፳፻፲፩ ዓ.ም.
💚💛❤️
@getem
@getem
@getem
ከመሸ ለምስጋና ብቅ ብለናል !
🙏

#የቻናላችን ቤተሰቦች የላካቹን በሙሉ በጣም እናመሰግናለን 🙏🙏🙏

እውነት እጅግ ብዙ ብዙ መልክቶች ናቸው የተላከልን የሁላችሁንም መልክቶች ማቅረብ አልቻልንም ለዚህም ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን የላክናቸው ይበቃል ከማለት ነው የላካችሁሉን በሙሉ ግን ትልቅ አክብሮት አለን 🙏!!!

ሁላችሁም ሀሳባቹ በነፃነት ስለገለፃቹልን ደስ ብሎናል እናመሰግናለን !!

#አብዛኞቻችሁ ማለት እችላለሁ ልዩነቶቻችን ትንሽ ናቸው አንድ የሚያደርገን ግን ብዙ እንደሆነ ገብቶኛል ያ ደግሞ አስደስቶኛል እኛ የተለያየ ምርጫዎች ፣ ፍላጎቶች ይኖሩናል ይሄ የሚጠበቅ ነው የሚያስገርምም አይደለም .....

ሁላችንም ኢትዮጵያ በተለያየ ምልከታዎች ልንመለከታት እንችላለን ይሄ ሸጋ ነገር ነው !!መነሻችንም መድረሻችንም ግን እሷ ናት !! ሁላችንም ሀገራችን እንወዳለን የተሻለች እንድትሆን እንፈልጋለን ሀገራችን ብዙ መልካም ነገሮች እንድትሆን እንፈልጋለን አይደል.? ስለዚህ የምንፈልገውን ነገር ከመፈለግ ባሻገር ከኛ የሚጠበቀውን ማንኛውንም መልካም ነገር እናድርግላት ከመንገድ ላይ የሙዝ ልጣጭ (ቆሻሻን ) ማንሳትም ጀምሮ መፈለግ ብቻውን ለውጥ አያመጣምና !!

#በመጨረሻም ኢትዮጵያ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን !! በሃይል የምወደውን የልቤን ሰው #የነብይ መኮንን ግጥም ጀባ ብያቹ ወደ አልጋዬ

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር💚💛❤️ አሜን!!!

------------------------------------------------


///ነብይ መኮንን///

በዚህ ዓመት
ሳንጣላ መታረቂያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሰደጃ፡፡
ምንለበት ፤
ለምናልባት ብንተውለት !!
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል ፣ ከልባችን ደግ በኩል፡፡
ለአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
" ምናልባት " የምንልበት፡፡
ልክ እንዳምና ፣ ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰርያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ፡፡
ጥግ ድረስ የለም ስራ ፣ ጥግ ድረስ የለም ፋታ፡፡
በልባችን ደግ በኩል ፣ እንፈልግ ባዶ ቦታ፡፡
የጳጉሜ ዓይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ !!

((( ደግ ለሚያስቡ ))))💚💛❤️



@balmbaras
@getem
-
አትኩራም አትፈር በምድር ኳኳታ
ይልቅ ከፍ ብለህ እረፍ በእርጋታ!


#በርናባስ_ከበደ

@getem
@getem
ታግሼ ጠብቄው
ቀና ብዬ ሳየው ፥ ሰማይ ቢሆን ወና
እነሆኝ አበጀሁ
, በልኬ ሰፋሁት ፥ የራሴን ደመና!!

#በርናባስ_ከበደ

@getem
@getem
@getem
" ..
ያገሬ ልጅ ሳቂ! ሳቂ ግድ የለሽም
እውነት እና ንጋት - እያደር አይሸሽም!"
(ሰለሞን ሳህለ)

@getem
@getem
@getem
<< ይማርክ ነበረ ሰበዝ እና አለላው
የሰፋነው ሁሉ ሆነ እንጂ ለሌላው!!>>

(ኃይለኢየሱስ ግርማ)

@getem
@getem
@gebriel_19
ቂም ቋጥሬ ነበር ፥ ወዜን መልኬን ያጣሁ
በይቅርታ ፀበል ፥ አዲስ ሆኜ መጣሁ!!!

(በርናባስ ከበደ)

@getem
@getem
@gebriel_19
ምስጋና ለምጣድ ፥ ሊጦች ነን እኛማ
እሳት እየላሰው ፥ ላረገን አይናማ!!

(በርናባስ ከበደ)

@getem
@getem
@gebriel_19
-
ክፉውም መልካሙም - አብሮን ፈገግ ይላል
ምናል ማየት ቢቻል - ሰውን እንደ እንቁላል!

(በርናባስ ከበደ)

@getem
@getem
@gebriel_19
ገጣሚ #በርናባስ_ከበደ ከላይ ያሉትን አጭሬ ግጥሞች ከፎቶዎቻቸው ጋር ስላደረስከን አክባሪህ ነን ከልብ እናመሰግናለን 🙏🙏🙏


እንደዚህ አይነት አጭር ግጥሞችን ከፎቶ ጋር በመፃፍ መላክ ትችላላችሁ
@gebriel_19
💚💛❤️

@getem
@getem
@gebriel_19
👍2
አልፈጠረው ኖሮ ፣ ለእስኪብርቶ ጣቴ፣
ሲጋራ አንቄያለሁ ፣ በህፃንነቴ።

በ ዳሀ,49 ተፃፈ

@getem
@getem
@getem
የአባቶቹን ጥበብ በእሳት ካቃጠለ
የከሸፈው ትውልድ ማለት እሄ አይደለ?
ስልጡን ሊያስገብረው ደንገት የመጣ ዕለት
እውቀት ንቋልና ጥበብ ክዷልና ይህ ትውልድ ወዮለት!
ወዮለት!

ተክሉ#

@getem
@getem
አይለጠፍ እንጂ በሰፊው ግንባር ላይ፣
ህሊናውን ለቆ ሞልቷል የሚያከራይ፣

((ሳሙኤል አለሙ))
@Sazi5

@getem
@getem
@getem
ለሀገሬ ለዕንቁጣጣሽ የተላከ ደብዳቤ

እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንደምነሽ ኢትዮጵ
እኔ አለው በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃሽ ድነሽ ተነሺና
እንደው ግን ሀገሬ ኑሮ እንዴት ይዞሻል
ድሮም እንዳሁኑ ይበጠብጡሻል
በፊት እንደዛሬ ብርሀን ናፍቆሽ ያውቃል
ሁሌ ብርሃን ነበር ወይስ ነው ጨለማ
ራቅ ላለ ሀገር ደምቆ የሚሰማ
ሀሳብ ነበረሽ ወይ ህዝብ ኖሮሽ ያውቃል
ይሄን ግን መጠየቅ እጅግ ያሳፍራል

ቢሆንም ቢሆንም ግድ የለም መልሺ
ወሎ አድሮ ደግሞ ከሌሎቹ ጋራ እኔን ከምቶቅሺ
ገድ የለም መልሺ
ዳቦ በሌለበት የኩራት ጎህ ብለሽ ቀን ትሰይሚያለሽ
ሰላም በሌለበት የሰላም ቀን እያልሽ ትደሰኩሪያለሽ
በወደቀች ሀገር የብልፅግና ቀን ታስከብሪናለሽ
ፍቅር በጠፋበት የፍቅር ቀን አያልሽ ታስጎመጂናለሽ
ፍትህ ባልኖረበት የፍትህ ዕለት ብለሽ ታስቀጥፊናለሽ

ሁሉም ቀናቶችሽ በሌሉ ነገሮች እየተሰየሙ
ልብን ያደማሉ ሀሳብ ያጠፋሉ ደዌ ያፈጥናሉ
ለኑሮ ታጋዩን ተስፋ ያሳጣሉ
እምነት ያስክዳሉ ውሸት አስወድደው ግፍ ያስለምዳሉ

አና እንዴት ነሽልሽ
ጤና እንዴት ይዞሻል
ዛሬም እንዳማረርሽ ይመሻል ይነጋል
እኔ ግን የምልሽ
መሪ ግን አለሽ ወይ
መሪው እንኳን ተይ
አትንገሪኝ በቃ ፓለቲካ ብለው እንዳይጠፈንጉኝ
አይኔን ባይኔ ሳላይ ዘሬን እንዳይቀሙኝ
ስለ መሪ ማጣት ተይው እንዳትነግሪኝ

አነማ

አነማ ነው ያልሽው
አንቺ ምን አለብሽ ኔትወርኩ ነው መሰል መረጃ አይደርስሽ
ኢሜልሽ አይሰራ ያስቸግራል ስልክሽ
ኦላይን የለሽም ችግር ላለመስማት
ፌስብክ ላይ አትኖሪ ሰውን ላለማማት
ታዲያ እንዴት ልንገርሽ
እኔ ግን ሀገሬ በጣም ስላዘንኩኝ
ነፍሴን የሚያሳጣ ሚስጥሬን ልነግርሽ ሰሞኑን ወሰንኩኝ

ምን መሠለሽ እሱ
በአሁኑ ሰአት ላይ የሚመራሽ የለም
መሪ የሚባል እንጂ መሪ ልጅ የለሽም
ሳትሞቺ ተስካርሽ በቁምሽ ሲበላ
ለሰማኒያሽ እንጃ ለአርባሽ መቶ ሰው በቁሙ ሲቀላ
ወዳንቺ እያየው አለሁኝ ከኀላ
ምክንያቱም
እንደ ሀገሬ ሰው እሬሳን አልወቅስም በሚለው በሀሉ
ለወዳጁም ሆነ ለመሠሪው ጎዱ እንሚለው ሁሉ
ሀገሬ ጥሩ ናት ሞትማ ቀደማት
ለስንቱ መዳኒት ለስንቱ ሸማ ናት
ብዬ ልፅፍልሽ ኀላሽ ሆኛለው
ህዝብሽን ስኮንን አቺን ደሞ ስረግም ይኸው እኖራለው

ሀገሬ አንደምነሽ
ህመሙ እንዴት ነው ዛሬስ ተሽሎሻል
ወይስ እንደ ድሮው ያቅለሸልሽሻል
ሆስፒታሉ እንዴት ነው
የህዝቦችሽ ጋር ነሽ ወይስ የግል ነው

እንደዛ ከሆነ

ዶክተሮቹ አሉ
በሰርጀሪ ግዜ ድንጋይ ኮብልስቶን ሆድሽ ውስጥ አረሱም
ለራስ ምታት ህመም ሽንት እና ሰገራ ምርመራ አልጠየቁም
ደምሽን ለመቅዳት ሀያ ስምንት ግዜ ደግመው አሎጉሽም

የውልሻ እኔ የልብ አውቃ ልጅሽ እንዲ ነኝ እወቂ
ህዝብሽ ይሰቃያል እንትና ይጨፍራል አንቺ ስትማቅቂ

እኔ ግን የምልሽ
ሽንት ቤቱ እንዴት ነው
ዛሬም እንደድሮው እንደነበረ ነው
የትም አትሂጂ ህዝብሽን ለማየት
መፀዳጃ ይበቃል ምሁር ለመለየት

እሱን ተይውና
ነርሶቹ እንዴት ናቸው
እንዴት አየሻቸው
ከዶክተሩ ናቸው ልባቸው ከማነው
ወይስ ካንቺ አሉ እንዴት ገመትሻቸው


አረ ሳልጠይቅሽ
እንዴት ልትገቢ ቻልሽ ዘበኛውን አልፈሽ
ወይስ እንደ ሰው ጉቦ መስጠት ለመድሽ

ጉቦ ይሰጣል ወይ

ህዝብሽ ተበሻቅጦ ያለ እጅ መንሻ የተሰራለት ለት
ስራውን አያምንም ጉቦ ካልሰጠበት

እንደው ግን እምዬ
አልጋ ከየት አገኘሽ
ወይስ እንደነሱ አንዱ ላይ ተደረብሽ
ወይስ እንደነዛ በጉልበት አስለቀቅሽ

ወንበር ላይ ነኝ አልሽኝ

ምነው እናት አለም የሚረዳሽ የለም
ዘመድ አልባ ነሽ ወይ ዘበኛው ዘመድሽ ይህንን አላየም

አሱ ምን ያረጋል ምንስ አቅም አለው
ምስኪን ተቀጣሪ ደህና ገንዘብ የለው

እሱን እንኳን ተይው
ከዳክተሩ በላይ ሆስፒታሉን የያዘው እሱ ነው ሚመስለው
ስትደመር ሚስቱ ያቺ ፅዳቱዋ ልጅ
ከተጣሉሽማ እንኳንስ ወንበሯን አትገቢም ከደጅ

እንዴት ነሽ አለሜ
እኔ አለው በጤና
ያው ታምሜም ቢሆን እግዜር ይመስገን ነው እኖራለው ደህና
የሸክላ በርበሬ በጀሶ እንጀራ አጥቅሼ
ዲታ የሆንኩ ቀን አህያ ቀምሼ
ባለ ብሩን ዳቦ አምስት ብር ገዝቼ
በ ሶስት ሺህ ብሬ ነጭ ጤፍ ሸምቼ
አለውኝ በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃኝ ድነሽ ተነሽና
እስከዛው ግን ቆይኝ
በአዲስ አመት ዜማ ባደይ ተንቆጥቁጠሽ
አዲስ ሳይፈጠር እድሜሽ ላይ ጨምረሽ
ግቡን የማይመታ ልጥጥ ስራ አቅደሽ
ልጆችሽን ማሰር ትውልድሽን መቅበር በደንብ ተምረሽ
ከብረሽ ቆይኝ ከብረሽ

ናብሊስ
መልካም እንቁጣጣሽ
ለ አስተያየቶ @kINGOFMORIYAM

@getem
@getem
@getem
👍2
የእንፋሎት መቀነት
----------©ሲራክ-------
እህህ ብቻ ነው ዘውትር ለኔ ቀኑ
ቁራ ሰርገኛ ነው በቤቴ ክዳኑ
@siraaq

@getem
@getem
"ከአያት ቅድም አያቴ ፣ ሞያ እንጂ ቁምነገር
ቀልድን አልተማርኩም ፣ በእምነት እና በሀገር
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ጠብመንጃን ፣ቆንጨራን ፣ ገጀራን ፣ ዱላን፣ የፈላ ውሃን ፣ ዛቻን እና ስድብን ስለምን ከዚህ ሰልፍ ትፈልጋላችሁ? መሥቀል እና ዝማሬ እንጂ ሌላው በዚህ የለም!!!
#መሥከረም_አራት!!!
።።።
""ወይ መካ ላይ ልምጣ ፣ ወይ ነይ ጎሎጎታ
ፍቅር የትም አለ ፣ ሳይወስነው ቦታ !!!"
።።።።
💚💛❤️
ለሀገራችን ሠላም ለህዝቧም ፍቅር ይብዛ!!!

@getem
@getem
@getem
🔥1
ባክህ ቶሎ አትምጣ...
"አዮብ ዘ ማርያም"
-
ጥሩ እንዳደረጉ እንደ ሰሩ ደህና
ብለው ይፀልያሉ ጌታ ሆይ ቶሎ ና
እኔ ግን ምስኪኑ ሀጢያተኛ ልጅህ
ይችን ፀሎት ፀለይኩ ወድቄ ከደጅህ
አምላኬ፣
ካለሁበት ሀጢያት ነብሴን ሳላወጣ
በንስሀ ፀፀት እራሴን ሳልቀጣ
ባክህ ቶሎ አትምጣ!
"
@getem
@getem
@getem
እንቁ ዕጣሽ ጣጣሽ
^^^^¿^^^^^¿^^^^^^

ድሮ … ጥንት
ጥሩ መሬት እህል የሚያፈራ
ብርቱ አራሽ ዘር የሚዘራ
አማኝ ምዕመን አምላኩን ሚፈራ
አስተዋይ መሪ ህዝቡን የሚመራ
በነበረሽ ጊዜ
ረሀብ ኮስሶ ጥጋብ ተኮፍሶ
የጎረቤት ጓዳ
የራስ እስኪመስል ሰቆቃ ተደርምሶ
በአብሮ መብላት ባህል
በመተሳሰብ ብሂል ክብርሽ ታድሷል
ዕጣሽ ሰምሮ ፍቅር ነግሷል
ዛሬ …
ክረምት ገብቶ
ከቤትህ ስትወጣ እህል ልትዘራ
ሲለፈፍ ትሰማለህ ስለህዝብ ቆጠራ
ግንቦት ደርሶልህ
ክንድህን አበርትተህ ሞፈር ስታነሳ
ማረሻ ማፈሻ
አርማ ይሆናል ለምርጫ ቅስቀሳ
ምትመርጠውን ሳታውቅ
የተመራጭ ብዛት ከብሔር ይበልጣል
በዚህ ስትወዛገብ
ክረምቱ ጠልቆ ፀደይ ይወጣል
ለሀገር ሲታሰብ
ማረስ ተረስቶ ጓሮ ይሳሳል
የኑሮ ውድነት ጣሪያ ይደርሳል
የት ተሂዶ
አቤት ይባላል ማንስ ይከሰሳል
በሚል ጥያቄ
የመረረው ልጅሽ በቁጭት ይታመሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲላሽቅ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
ኢትዮጵያዬ …
ተባረኪ ሲልሽ
እጆችሽን እንድትዘረጊ አምላክ ይፈቅዳል
የሰንደቅሽን አርማ
በማርያም መቀነት ሰማይ ላይ ይወልዳል
ዕጣሽን ሲያሳምር
የፍቅር ማማ ላይ ጎህ ይቀዳል
በብርሀን ፋና ህዝብሽን አጥምቆ
በእምነት ዘውድ ሰላምሽን አድምቆ
ያኖረሽ አምላክ ዕጣሽን ሲያጠፋ
ለማስመሰል ያጨሽው ዕጣንሽ ከረፋ
የአንድነትሽ ቅዳሴ ልዩነቱ ሰፋ
በዚህም በዚያም መጥፊያሽን ሚያስሱ
የግላቸውን ቤተ ክህነት ሊያቋቁሙ ተነሱ
ሀገሬ …
ጥፊ ያለሽ ጊዜ እምነትሽ ይፈርሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከዳሽ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
በፊት …
ለሰው ልጅ
ክብር ይሰጣል ከሁሉም ልቆ
ሁሉን ከዋኝ
ሁሉን አድራጊ መሆኑ ታውቆ
ዛሬ …
ለልማት ተብሎ ቤት ይፈርሳል
የሰው ልጅ ታንቆ ከተማ ይታደሳል
መጠለያ ያጣ
የዋህ ወገኔ ጎዳና ይፈሳል
የከተማን ውበት
አጠለሸ ተብሎ ተጋፎ ይነሳል
ሚዲያ ይለፍፋል
ለአረንጓዴ ልማት ተሰማራ ብሎ
በውሃ ናፍቆት ህዝብን በጥም ገሎ
ይታለፍ ይመስል
ከችግር አረንቋ ችግኝ ተጠልሎ
እምዬ …
ብዙ ነው ፈታኝሽ
ከባድ ነው ፈተናሽ
ብዙ ነው መካሪሽ
ከባድ ነው መከራሽ
ብዙ ነው ጣይˆሽ
ብሩህ ነው ፀሀይሽ
ብዙ ነው ጨማቂሽ
ጣፋጭ ነው ጭማቂሽ
ያውም … ካልመረረ
… ካልናረ
ሀገሬ …
ተተኪሽን ተኪ
የትምህርት ስርዓትሽ ፍኖቱ ተጣሟል
መርቆ ሸኝ እንጅ
የተመረቀ ተቀባይ እጅ ከስሟል
ፈተና ይሰረቃል
ውጤት ይሰረዛል
የሰው ህይወት ለቁማር ይረከዛል
ይኼውልሽ …
የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኝ
በማሽን ስህተት ውጤቱ ሲናኝ
ስህተትን ለማረም
የትምህርት አይነት ተለይቶ ይቀነሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከስም
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
የኳስሽ እድገት ቁልቁል ይፈሳል
የክለብሽ ስም
የክልል ካባ በላዩ ለብሷል
ደጋፊሽ ሁሌ
ክለቡን ወግኖ ለጥል ይነሳል
ይኸውልሽ …
በቱርክ ወረራ ህዝባችን መክኖ
በኳስ ቁማር ልቡ በግኖ … ስራ አቁሞ
ያለፋበትን ገንዘብ እያሳደደ
በከንቱ ተስፋ
ጨጓራውን ልጦ ህመም ወለደ
መከረኛው ልጅሽ
ለውድቀት ክብር ይኸው ተዘጋጅቷል
እንቁ ዕጣሽን ትቶ
እንቁ ጣጣሽን ይጠብቃል

@getem
@getem
@getem
1
ግጥም እንደዚህ ሲሆን እንዴት የልብ ያደርሳል❤️ለነፍስም ይቀርባል.... ግጥሙ ውስጥ ያለው ፍልስፍናው ሲጣፍጥ ፣ ያገማሽራልም ባነበው ባነው አልጠገብኩትም ....ማሜዋ በረካ ሁን አቦ!!!

( እልል አሮጌ ዓመት)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሃበሻ እና ዘመን
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በሃበሻ ምድር
ከኑባሬ አዳም እስከዛሬ ድረስ
ያደስንውን ዓመት ውሉን ስናጤነው ።
በዘመን አዙሪት የአድስ አመት መምጣት
ሲገባኝ ተፍሲሩ ፍቹን ስተምነው፣
ከአምና የተረፈ የልጅነት ወዝን የኛነትን እሸት
ለተራበው አዲስ ወስዶ መገበር ነው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም ይገርማል ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ አደይ አበባ ኑረቱ ሳይፈካ
በፈኩ ወራቶች ታደስኩኝ ይልሃል፣
በእግረ መንገድ ኑሮ ቀናቶች ሸምነው
አመት ሆነህ ሲሉት እልልታ ያቀልጣል፣
ዳግም ለሚመጣ ለዘመን ቋጠሮ
ድጋሜ እማይመጣ እራሱን ይሰዋል፣
ከእድሜው ተቀንሶ የተወራረደ
የእድሜውን ጎደሎ በፌሽታ ያውጃል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዋህ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዘመን ሩጫ ከትላንት አባሮ ለማያውቀው
ነገ ለመጪው ዘንድሮ ሲድረው ጎትቶ፣
ባድስ አመት ብስራት ማርጀት ይሉት ሸማ
ወዶ መደረቡን መልበሱን ዘንግቶ።



አድስ ዓመት



እንቁጣጣሽ
ማለት ይቀናዋል፣
በአድስ አመት ጀርባ እርጅናና ሞቱን
በእልልታ እያጀበ ያወራርደዋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሞኝ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ተመለስ ብትለው ለማይሰማ ዘመን
እንኳን መጣህ ብሎ ድግስ ያሰናዳል፣
ያልተደካን ዘመን ቁጥር ለመጨመር
የዘመኑን ድካ እድሜውን ይንዳል።
ይሄው እስከዛሬ
ሃበሻና እልልታ በያድስ አመቱ
ቀጠሮ እየያዙ እኩል ቢታደሱም፣
ከአንዱ እየቀነሱ በተቀናሽ ሂሳብ
አንዱን ከማፈርጠም ተሻግረው አያውቁም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።



አሮጌ ዓመት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሃበሻን ኑረት ከፍታ እሚያሳየን
ፍካት የሚያስዋጀን ቅፅበት እስኪመጣ፣
የዘመን ትከሻ አየገፈተረኝ እድሜየን ገብሬ
ከኖርኩበት ዘመን ከአሮጌው ስወጣ።
ባዶ እጁን ለመጣ ላልኖርኩበት አድስ
አሮጌውና አምና አላማውምና፣
ከአድስነቱ ጋር አድስ እስኪያመጣ



አሮጌ ዓመት
እንኳን ኖርኩኝ አምና።



አሮጌ ዓመት!!!!!!!!!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሙሃመድ ሰኢድ💚💛❤️
ጷግሜ 5/13/2011

@getem
@getem
@balmbaras