ለ 10ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኞች በሙሉ
በቀላሉ ውጤቶን ለማየት የሚያስችል አዲስ ቦት @neaea_neaea_bot ተሰራ ፣ ቀላል ፣ ቀልጣፋ እና ታአማኒ ያለምንም የሰው ጣልቃ ገበነት 24/7 የሚሰራ ።
የእርሶን እና የጓደኞዎቾ እንዲሁም፣ኢንተርኔት ዝግ ለሚልባቸው ቦታዎች ሁሉ መፍትሔ የሚሆን @neaea_neaea_bot ።
(ለ10ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ ውጤት ልክ ሲወጣ የማሳወቂያ መልእክት እንልካለን።)
12 ኛ ምድብ ምት ጠብ ቁም እዚሁ bot ላይ ታገኙታላችሁ
@getem
@getem
በቀላሉ ውጤቶን ለማየት የሚያስችል አዲስ ቦት @neaea_neaea_bot ተሰራ ፣ ቀላል ፣ ቀልጣፋ እና ታአማኒ ያለምንም የሰው ጣልቃ ገበነት 24/7 የሚሰራ ።
የእርሶን እና የጓደኞዎቾ እንዲሁም፣ኢንተርኔት ዝግ ለሚልባቸው ቦታዎች ሁሉ መፍትሔ የሚሆን @neaea_neaea_bot ።
(ለ10ኛ ክፍል ተፈታኞች በሙሉ ውጤት ልክ ሲወጣ የማሳወቂያ መልእክት እንልካለን።)
12 ኛ ምድብ ምት ጠብ ቁም እዚሁ bot ላይ ታገኙታላችሁ
@getem
@getem
ከመሸ ለምስጋና ብቅ ብለናል !
🙏
#የቻናላችን ቤተሰቦች የላካቹን በሙሉ በጣም እናመሰግናለን 🙏🙏🙏
እውነት እጅግ ብዙ ብዙ መልክቶች ናቸው የተላከልን የሁላችሁንም መልክቶች ማቅረብ አልቻልንም ለዚህም ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን የላክናቸው ይበቃል ከማለት ነው የላካችሁሉን በሙሉ ግን ትልቅ አክብሮት አለን 🙏!!!
ሁላችሁም ሀሳባቹ በነፃነት ስለገለፃቹልን ደስ ብሎናል እናመሰግናለን !!
#አብዛኞቻችሁ ማለት እችላለሁ ልዩነቶቻችን ትንሽ ናቸው አንድ የሚያደርገን ግን ብዙ እንደሆነ ገብቶኛል ያ ደግሞ አስደስቶኛል እኛ የተለያየ ምርጫዎች ፣ ፍላጎቶች ይኖሩናል ይሄ የሚጠበቅ ነው የሚያስገርምም አይደለም .....
ሁላችንም ኢትዮጵያ በተለያየ ምልከታዎች ልንመለከታት እንችላለን ይሄ ሸጋ ነገር ነው !!መነሻችንም መድረሻችንም ግን እሷ ናት !! ሁላችንም ሀገራችን እንወዳለን የተሻለች እንድትሆን እንፈልጋለን ሀገራችን ብዙ መልካም ነገሮች እንድትሆን እንፈልጋለን አይደል.? ስለዚህ የምንፈልገውን ነገር ከመፈለግ ባሻገር ከኛ የሚጠበቀውን ማንኛውንም መልካም ነገር እናድርግላት ከመንገድ ላይ የሙዝ ልጣጭ (ቆሻሻን ) ማንሳትም ጀምሮ መፈለግ ብቻውን ለውጥ አያመጣምና !!
#በመጨረሻም ኢትዮጵያ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን !! በሃይል የምወደውን የልቤን ሰው #የነብይ መኮንን ግጥም ጀባ ብያቹ ወደ አልጋዬ
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር💚💛❤️ አሜን!!!
------------------------------------------------
///ነብይ መኮንን///
በዚህ ዓመት
ሳንጣላ መታረቂያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሰደጃ፡፡
ምንለበት ፤
ለምናልባት ብንተውለት !!
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል ፣ ከልባችን ደግ በኩል፡፡
ለአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
" ምናልባት " የምንልበት፡፡
ልክ እንዳምና ፣ ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰርያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ፡፡
ጥግ ድረስ የለም ስራ ፣ ጥግ ድረስ የለም ፋታ፡፡
በልባችን ደግ በኩል ፣ እንፈልግ ባዶ ቦታ፡፡
የጳጉሜ ዓይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ !!
((( ደግ ለሚያስቡ ))))💚💛❤️
@balmbaras
@getem
🙏
#የቻናላችን ቤተሰቦች የላካቹን በሙሉ በጣም እናመሰግናለን 🙏🙏🙏
እውነት እጅግ ብዙ ብዙ መልክቶች ናቸው የተላከልን የሁላችሁንም መልክቶች ማቅረብ አልቻልንም ለዚህም ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን የላክናቸው ይበቃል ከማለት ነው የላካችሁሉን በሙሉ ግን ትልቅ አክብሮት አለን 🙏!!!
ሁላችሁም ሀሳባቹ በነፃነት ስለገለፃቹልን ደስ ብሎናል እናመሰግናለን !!
#አብዛኞቻችሁ ማለት እችላለሁ ልዩነቶቻችን ትንሽ ናቸው አንድ የሚያደርገን ግን ብዙ እንደሆነ ገብቶኛል ያ ደግሞ አስደስቶኛል እኛ የተለያየ ምርጫዎች ፣ ፍላጎቶች ይኖሩናል ይሄ የሚጠበቅ ነው የሚያስገርምም አይደለም .....
ሁላችንም ኢትዮጵያ በተለያየ ምልከታዎች ልንመለከታት እንችላለን ይሄ ሸጋ ነገር ነው !!መነሻችንም መድረሻችንም ግን እሷ ናት !! ሁላችንም ሀገራችን እንወዳለን የተሻለች እንድትሆን እንፈልጋለን ሀገራችን ብዙ መልካም ነገሮች እንድትሆን እንፈልጋለን አይደል.? ስለዚህ የምንፈልገውን ነገር ከመፈለግ ባሻገር ከኛ የሚጠበቀውን ማንኛውንም መልካም ነገር እናድርግላት ከመንገድ ላይ የሙዝ ልጣጭ (ቆሻሻን ) ማንሳትም ጀምሮ መፈለግ ብቻውን ለውጥ አያመጣምና !!
#በመጨረሻም ኢትዮጵያ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን !! በሃይል የምወደውን የልቤን ሰው #የነብይ መኮንን ግጥም ጀባ ብያቹ ወደ አልጋዬ
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር💚💛❤️ አሜን!!!
------------------------------------------------
///ነብይ መኮንን///
በዚህ ዓመት
ሳንጣላ መታረቂያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሰደጃ፡፡
ምንለበት ፤
ለምናልባት ብንተውለት !!
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል ፣ ከልባችን ደግ በኩል፡፡
ለአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
" ምናልባት " የምንልበት፡፡
ልክ እንዳምና ፣ ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰርያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ፡፡
ጥግ ድረስ የለም ስራ ፣ ጥግ ድረስ የለም ፋታ፡፡
በልባችን ደግ በኩል ፣ እንፈልግ ባዶ ቦታ፡፡
የጳጉሜ ዓይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ !!
((( ደግ ለሚያስቡ ))))💚💛❤️
@balmbaras
@getem
ገጣሚ #በርናባስ_ከበደ ከላይ ያሉትን አጭሬ ግጥሞች ከፎቶዎቻቸው ጋር ስላደረስከን አክባሪህ ነን ከልብ እናመሰግናለን 🙏🙏🙏
እንደዚህ አይነት አጭር ግጥሞችን ከፎቶ ጋር በመፃፍ መላክ ትችላላችሁ
@gebriel_19
💚💛❤️
@getem
@getem
@gebriel_19
እንደዚህ አይነት አጭር ግጥሞችን ከፎቶ ጋር በመፃፍ መላክ ትችላላችሁ
@gebriel_19
💚💛❤️
@getem
@getem
@gebriel_19
👍2
ለሀገሬ ለዕንቁጣጣሽ የተላከ ደብዳቤ
እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንደምነሽ ኢትዮጵ
እኔ አለው በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃሽ ድነሽ ተነሺና
እንደው ግን ሀገሬ ኑሮ እንዴት ይዞሻል
ድሮም እንዳሁኑ ይበጠብጡሻል
በፊት እንደዛሬ ብርሀን ናፍቆሽ ያውቃል
ሁሌ ብርሃን ነበር ወይስ ነው ጨለማ
ራቅ ላለ ሀገር ደምቆ የሚሰማ
ሀሳብ ነበረሽ ወይ ህዝብ ኖሮሽ ያውቃል
ይሄን ግን መጠየቅ እጅግ ያሳፍራል
ቢሆንም ቢሆንም ግድ የለም መልሺ
ወሎ አድሮ ደግሞ ከሌሎቹ ጋራ እኔን ከምቶቅሺ
ገድ የለም መልሺ
ዳቦ በሌለበት የኩራት ጎህ ብለሽ ቀን ትሰይሚያለሽ
ሰላም በሌለበት የሰላም ቀን እያልሽ ትደሰኩሪያለሽ
በወደቀች ሀገር የብልፅግና ቀን ታስከብሪናለሽ
ፍቅር በጠፋበት የፍቅር ቀን አያልሽ ታስጎመጂናለሽ
ፍትህ ባልኖረበት የፍትህ ዕለት ብለሽ ታስቀጥፊናለሽ
ሁሉም ቀናቶችሽ በሌሉ ነገሮች እየተሰየሙ
ልብን ያደማሉ ሀሳብ ያጠፋሉ ደዌ ያፈጥናሉ
ለኑሮ ታጋዩን ተስፋ ያሳጣሉ
እምነት ያስክዳሉ ውሸት አስወድደው ግፍ ያስለምዳሉ
አና እንዴት ነሽልሽ
ጤና እንዴት ይዞሻል
ዛሬም እንዳማረርሽ ይመሻል ይነጋል
እኔ ግን የምልሽ
መሪ ግን አለሽ ወይ
መሪው እንኳን ተይ
አትንገሪኝ በቃ ፓለቲካ ብለው እንዳይጠፈንጉኝ
አይኔን ባይኔ ሳላይ ዘሬን እንዳይቀሙኝ
ስለ መሪ ማጣት ተይው እንዳትነግሪኝ
አነማ
አነማ ነው ያልሽው
አንቺ ምን አለብሽ ኔትወርኩ ነው መሰል መረጃ አይደርስሽ
ኢሜልሽ አይሰራ ያስቸግራል ስልክሽ
ኦላይን የለሽም ችግር ላለመስማት
ፌስብክ ላይ አትኖሪ ሰውን ላለማማት
ታዲያ እንዴት ልንገርሽ
እኔ ግን ሀገሬ በጣም ስላዘንኩኝ
ነፍሴን የሚያሳጣ ሚስጥሬን ልነግርሽ ሰሞኑን ወሰንኩኝ
ምን መሠለሽ እሱ
በአሁኑ ሰአት ላይ የሚመራሽ የለም
መሪ የሚባል እንጂ መሪ ልጅ የለሽም
ሳትሞቺ ተስካርሽ በቁምሽ ሲበላ
ለሰማኒያሽ እንጃ ለአርባሽ መቶ ሰው በቁሙ ሲቀላ
ወዳንቺ እያየው አለሁኝ ከኀላ
ምክንያቱም
እንደ ሀገሬ ሰው እሬሳን አልወቅስም በሚለው በሀሉ
ለወዳጁም ሆነ ለመሠሪው ጎዱ እንሚለው ሁሉ
ሀገሬ ጥሩ ናት ሞትማ ቀደማት
ለስንቱ መዳኒት ለስንቱ ሸማ ናት
ብዬ ልፅፍልሽ ኀላሽ ሆኛለው
ህዝብሽን ስኮንን አቺን ደሞ ስረግም ይኸው እኖራለው
ሀገሬ አንደምነሽ
ህመሙ እንዴት ነው ዛሬስ ተሽሎሻል
ወይስ እንደ ድሮው ያቅለሸልሽሻል
ሆስፒታሉ እንዴት ነው
የህዝቦችሽ ጋር ነሽ ወይስ የግል ነው
እንደዛ ከሆነ
ዶክተሮቹ አሉ
በሰርጀሪ ግዜ ድንጋይ ኮብልስቶን ሆድሽ ውስጥ አረሱም
ለራስ ምታት ህመም ሽንት እና ሰገራ ምርመራ አልጠየቁም
ደምሽን ለመቅዳት ሀያ ስምንት ግዜ ደግመው አሎጉሽም
የውልሻ እኔ የልብ አውቃ ልጅሽ እንዲ ነኝ እወቂ
ህዝብሽ ይሰቃያል እንትና ይጨፍራል አንቺ ስትማቅቂ
እኔ ግን የምልሽ
ሽንት ቤቱ እንዴት ነው
ዛሬም እንደድሮው እንደነበረ ነው
የትም አትሂጂ ህዝብሽን ለማየት
መፀዳጃ ይበቃል ምሁር ለመለየት
እሱን ተይውና
ነርሶቹ እንዴት ናቸው
እንዴት አየሻቸው
ከዶክተሩ ናቸው ልባቸው ከማነው
ወይስ ካንቺ አሉ እንዴት ገመትሻቸው
አረ ሳልጠይቅሽ
እንዴት ልትገቢ ቻልሽ ዘበኛውን አልፈሽ
ወይስ እንደ ሰው ጉቦ መስጠት ለመድሽ
ጉቦ ይሰጣል ወይ
ህዝብሽ ተበሻቅጦ ያለ እጅ መንሻ የተሰራለት ለት
ስራውን አያምንም ጉቦ ካልሰጠበት
እንደው ግን እምዬ
አልጋ ከየት አገኘሽ
ወይስ እንደነሱ አንዱ ላይ ተደረብሽ
ወይስ እንደነዛ በጉልበት አስለቀቅሽ
ወንበር ላይ ነኝ አልሽኝ
ምነው እናት አለም የሚረዳሽ የለም
ዘመድ አልባ ነሽ ወይ ዘበኛው ዘመድሽ ይህንን አላየም
አሱ ምን ያረጋል ምንስ አቅም አለው
ምስኪን ተቀጣሪ ደህና ገንዘብ የለው
እሱን እንኳን ተይው
ከዳክተሩ በላይ ሆስፒታሉን የያዘው እሱ ነው ሚመስለው
ስትደመር ሚስቱ ያቺ ፅዳቱዋ ልጅ
ከተጣሉሽማ እንኳንስ ወንበሯን አትገቢም ከደጅ
እንዴት ነሽ አለሜ
እኔ አለው በጤና
ያው ታምሜም ቢሆን እግዜር ይመስገን ነው እኖራለው ደህና
የሸክላ በርበሬ በጀሶ እንጀራ አጥቅሼ
ዲታ የሆንኩ ቀን አህያ ቀምሼ
ባለ ብሩን ዳቦ አምስት ብር ገዝቼ
በ ሶስት ሺህ ብሬ ነጭ ጤፍ ሸምቼ
አለውኝ በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃኝ ድነሽ ተነሽና
እስከዛው ግን ቆይኝ
በአዲስ አመት ዜማ ባደይ ተንቆጥቁጠሽ
አዲስ ሳይፈጠር እድሜሽ ላይ ጨምረሽ
ግቡን የማይመታ ልጥጥ ስራ አቅደሽ
ልጆችሽን ማሰር ትውልድሽን መቅበር በደንብ ተምረሽ
ከብረሽ ቆይኝ ከብረሽ
✍✍ናብሊስ
መልካም እንቁጣጣሽ
ለ አስተያየቶ @kINGOFMORIYAM
@getem
@getem
@getem
እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንደምነሽ ኢትዮጵ
እኔ አለው በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃሽ ድነሽ ተነሺና
እንደው ግን ሀገሬ ኑሮ እንዴት ይዞሻል
ድሮም እንዳሁኑ ይበጠብጡሻል
በፊት እንደዛሬ ብርሀን ናፍቆሽ ያውቃል
ሁሌ ብርሃን ነበር ወይስ ነው ጨለማ
ራቅ ላለ ሀገር ደምቆ የሚሰማ
ሀሳብ ነበረሽ ወይ ህዝብ ኖሮሽ ያውቃል
ይሄን ግን መጠየቅ እጅግ ያሳፍራል
ቢሆንም ቢሆንም ግድ የለም መልሺ
ወሎ አድሮ ደግሞ ከሌሎቹ ጋራ እኔን ከምቶቅሺ
ገድ የለም መልሺ
ዳቦ በሌለበት የኩራት ጎህ ብለሽ ቀን ትሰይሚያለሽ
ሰላም በሌለበት የሰላም ቀን እያልሽ ትደሰኩሪያለሽ
በወደቀች ሀገር የብልፅግና ቀን ታስከብሪናለሽ
ፍቅር በጠፋበት የፍቅር ቀን አያልሽ ታስጎመጂናለሽ
ፍትህ ባልኖረበት የፍትህ ዕለት ብለሽ ታስቀጥፊናለሽ
ሁሉም ቀናቶችሽ በሌሉ ነገሮች እየተሰየሙ
ልብን ያደማሉ ሀሳብ ያጠፋሉ ደዌ ያፈጥናሉ
ለኑሮ ታጋዩን ተስፋ ያሳጣሉ
እምነት ያስክዳሉ ውሸት አስወድደው ግፍ ያስለምዳሉ
አና እንዴት ነሽልሽ
ጤና እንዴት ይዞሻል
ዛሬም እንዳማረርሽ ይመሻል ይነጋል
እኔ ግን የምልሽ
መሪ ግን አለሽ ወይ
መሪው እንኳን ተይ
አትንገሪኝ በቃ ፓለቲካ ብለው እንዳይጠፈንጉኝ
አይኔን ባይኔ ሳላይ ዘሬን እንዳይቀሙኝ
ስለ መሪ ማጣት ተይው እንዳትነግሪኝ
አነማ
አነማ ነው ያልሽው
አንቺ ምን አለብሽ ኔትወርኩ ነው መሰል መረጃ አይደርስሽ
ኢሜልሽ አይሰራ ያስቸግራል ስልክሽ
ኦላይን የለሽም ችግር ላለመስማት
ፌስብክ ላይ አትኖሪ ሰውን ላለማማት
ታዲያ እንዴት ልንገርሽ
እኔ ግን ሀገሬ በጣም ስላዘንኩኝ
ነፍሴን የሚያሳጣ ሚስጥሬን ልነግርሽ ሰሞኑን ወሰንኩኝ
ምን መሠለሽ እሱ
በአሁኑ ሰአት ላይ የሚመራሽ የለም
መሪ የሚባል እንጂ መሪ ልጅ የለሽም
ሳትሞቺ ተስካርሽ በቁምሽ ሲበላ
ለሰማኒያሽ እንጃ ለአርባሽ መቶ ሰው በቁሙ ሲቀላ
ወዳንቺ እያየው አለሁኝ ከኀላ
ምክንያቱም
እንደ ሀገሬ ሰው እሬሳን አልወቅስም በሚለው በሀሉ
ለወዳጁም ሆነ ለመሠሪው ጎዱ እንሚለው ሁሉ
ሀገሬ ጥሩ ናት ሞትማ ቀደማት
ለስንቱ መዳኒት ለስንቱ ሸማ ናት
ብዬ ልፅፍልሽ ኀላሽ ሆኛለው
ህዝብሽን ስኮንን አቺን ደሞ ስረግም ይኸው እኖራለው
ሀገሬ አንደምነሽ
ህመሙ እንዴት ነው ዛሬስ ተሽሎሻል
ወይስ እንደ ድሮው ያቅለሸልሽሻል
ሆስፒታሉ እንዴት ነው
የህዝቦችሽ ጋር ነሽ ወይስ የግል ነው
እንደዛ ከሆነ
ዶክተሮቹ አሉ
በሰርጀሪ ግዜ ድንጋይ ኮብልስቶን ሆድሽ ውስጥ አረሱም
ለራስ ምታት ህመም ሽንት እና ሰገራ ምርመራ አልጠየቁም
ደምሽን ለመቅዳት ሀያ ስምንት ግዜ ደግመው አሎጉሽም
የውልሻ እኔ የልብ አውቃ ልጅሽ እንዲ ነኝ እወቂ
ህዝብሽ ይሰቃያል እንትና ይጨፍራል አንቺ ስትማቅቂ
እኔ ግን የምልሽ
ሽንት ቤቱ እንዴት ነው
ዛሬም እንደድሮው እንደነበረ ነው
የትም አትሂጂ ህዝብሽን ለማየት
መፀዳጃ ይበቃል ምሁር ለመለየት
እሱን ተይውና
ነርሶቹ እንዴት ናቸው
እንዴት አየሻቸው
ከዶክተሩ ናቸው ልባቸው ከማነው
ወይስ ካንቺ አሉ እንዴት ገመትሻቸው
አረ ሳልጠይቅሽ
እንዴት ልትገቢ ቻልሽ ዘበኛውን አልፈሽ
ወይስ እንደ ሰው ጉቦ መስጠት ለመድሽ
ጉቦ ይሰጣል ወይ
ህዝብሽ ተበሻቅጦ ያለ እጅ መንሻ የተሰራለት ለት
ስራውን አያምንም ጉቦ ካልሰጠበት
እንደው ግን እምዬ
አልጋ ከየት አገኘሽ
ወይስ እንደነሱ አንዱ ላይ ተደረብሽ
ወይስ እንደነዛ በጉልበት አስለቀቅሽ
ወንበር ላይ ነኝ አልሽኝ
ምነው እናት አለም የሚረዳሽ የለም
ዘመድ አልባ ነሽ ወይ ዘበኛው ዘመድሽ ይህንን አላየም
አሱ ምን ያረጋል ምንስ አቅም አለው
ምስኪን ተቀጣሪ ደህና ገንዘብ የለው
እሱን እንኳን ተይው
ከዳክተሩ በላይ ሆስፒታሉን የያዘው እሱ ነው ሚመስለው
ስትደመር ሚስቱ ያቺ ፅዳቱዋ ልጅ
ከተጣሉሽማ እንኳንስ ወንበሯን አትገቢም ከደጅ
እንዴት ነሽ አለሜ
እኔ አለው በጤና
ያው ታምሜም ቢሆን እግዜር ይመስገን ነው እኖራለው ደህና
የሸክላ በርበሬ በጀሶ እንጀራ አጥቅሼ
ዲታ የሆንኩ ቀን አህያ ቀምሼ
ባለ ብሩን ዳቦ አምስት ብር ገዝቼ
በ ሶስት ሺህ ብሬ ነጭ ጤፍ ሸምቼ
አለውኝ በደህና
ጤና ብትነሺኝም ሰላም ይስጥሽና
ለወቀሳ ያብቃኝ ድነሽ ተነሽና
እስከዛው ግን ቆይኝ
በአዲስ አመት ዜማ ባደይ ተንቆጥቁጠሽ
አዲስ ሳይፈጠር እድሜሽ ላይ ጨምረሽ
ግቡን የማይመታ ልጥጥ ስራ አቅደሽ
ልጆችሽን ማሰር ትውልድሽን መቅበር በደንብ ተምረሽ
ከብረሽ ቆይኝ ከብረሽ
✍✍ናብሊስ
መልካም እንቁጣጣሽ
ለ አስተያየቶ @kINGOFMORIYAM
@getem
@getem
@getem
👍2
"ከአያት ቅድም አያቴ ፣ ሞያ እንጂ ቁምነገር
ቀልድን አልተማርኩም ፣ በእምነት እና በሀገር
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ጠብመንጃን ፣ቆንጨራን ፣ ገጀራን ፣ ዱላን፣ የፈላ ውሃን ፣ ዛቻን እና ስድብን ስለምን ከዚህ ሰልፍ ትፈልጋላችሁ? መሥቀል እና ዝማሬ እንጂ ሌላው በዚህ የለም!!!
#መሥከረም_አራት!!!
።።።
""ወይ መካ ላይ ልምጣ ፣ ወይ ነይ ጎሎጎታ
ፍቅር የትም አለ ፣ ሳይወስነው ቦታ !!!"
።።።።
💚💛❤️
ለሀገራችን ሠላም ለህዝቧም ፍቅር ይብዛ!!!
@getem
@getem
@getem
ቀልድን አልተማርኩም ፣ በእምነት እና በሀገር
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ጠብመንጃን ፣ቆንጨራን ፣ ገጀራን ፣ ዱላን፣ የፈላ ውሃን ፣ ዛቻን እና ስድብን ስለምን ከዚህ ሰልፍ ትፈልጋላችሁ? መሥቀል እና ዝማሬ እንጂ ሌላው በዚህ የለም!!!
#መሥከረም_አራት!!!
።።።
""ወይ መካ ላይ ልምጣ ፣ ወይ ነይ ጎሎጎታ
ፍቅር የትም አለ ፣ ሳይወስነው ቦታ !!!"
።።።።
💚💛❤️
ለሀገራችን ሠላም ለህዝቧም ፍቅር ይብዛ!!!
@getem
@getem
@getem
🔥1
እንቁ ዕጣሽ ጣጣሽ
^^^^¿^^^^^¿^^^^^^
ድሮ … ጥንት
ጥሩ መሬት እህል የሚያፈራ
ብርቱ አራሽ ዘር የሚዘራ
አማኝ ምዕመን አምላኩን ሚፈራ
አስተዋይ መሪ ህዝቡን የሚመራ
በነበረሽ ጊዜ
ረሀብ ኮስሶ ጥጋብ ተኮፍሶ
የጎረቤት ጓዳ
የራስ እስኪመስል ሰቆቃ ተደርምሶ
በአብሮ መብላት ባህል
በመተሳሰብ ብሂል ክብርሽ ታድሷል
ዕጣሽ ሰምሮ ፍቅር ነግሷል
ዛሬ …
ክረምት ገብቶ
ከቤትህ ስትወጣ እህል ልትዘራ
ሲለፈፍ ትሰማለህ ስለህዝብ ቆጠራ
ግንቦት ደርሶልህ
ክንድህን አበርትተህ ሞፈር ስታነሳ
ማረሻ ማፈሻ
አርማ ይሆናል ለምርጫ ቅስቀሳ
ምትመርጠውን ሳታውቅ
የተመራጭ ብዛት ከብሔር ይበልጣል
በዚህ ስትወዛገብ
ክረምቱ ጠልቆ ፀደይ ይወጣል
ለሀገር ሲታሰብ
ማረስ ተረስቶ ጓሮ ይሳሳል
የኑሮ ውድነት ጣሪያ ይደርሳል
የት ተሂዶ
አቤት ይባላል ማንስ ይከሰሳል
በሚል ጥያቄ
የመረረው ልጅሽ በቁጭት ይታመሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲላሽቅ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
ኢትዮጵያዬ …
ተባረኪ ሲልሽ
እጆችሽን እንድትዘረጊ አምላክ ይፈቅዳል
የሰንደቅሽን አርማ
በማርያም መቀነት ሰማይ ላይ ይወልዳል
ዕጣሽን ሲያሳምር
የፍቅር ማማ ላይ ጎህ ይቀዳል
በብርሀን ፋና ህዝብሽን አጥምቆ
በእምነት ዘውድ ሰላምሽን አድምቆ
ያኖረሽ አምላክ ዕጣሽን ሲያጠፋ
ለማስመሰል ያጨሽው ዕጣንሽ ከረፋ
የአንድነትሽ ቅዳሴ ልዩነቱ ሰፋ
በዚህም በዚያም መጥፊያሽን ሚያስሱ
የግላቸውን ቤተ ክህነት ሊያቋቁሙ ተነሱ
ሀገሬ …
ጥፊ ያለሽ ጊዜ እምነትሽ ይፈርሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከዳሽ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
በፊት …
ለሰው ልጅ
ክብር ይሰጣል ከሁሉም ልቆ
ሁሉን ከዋኝ
ሁሉን አድራጊ መሆኑ ታውቆ
ዛሬ …
ለልማት ተብሎ ቤት ይፈርሳል
የሰው ልጅ ታንቆ ከተማ ይታደሳል
መጠለያ ያጣ
የዋህ ወገኔ ጎዳና ይፈሳል
የከተማን ውበት
አጠለሸ ተብሎ ተጋፎ ይነሳል
ሚዲያ ይለፍፋል
ለአረንጓዴ ልማት ተሰማራ ብሎ
በውሃ ናፍቆት ህዝብን በጥም ገሎ
ይታለፍ ይመስል
ከችግር አረንቋ ችግኝ ተጠልሎ
እምዬ …
ብዙ ነው ፈታኝሽ
ከባድ ነው ፈተናሽ
ብዙ ነው መካሪሽ
ከባድ ነው መከራሽ
ብዙ ነው ጣይˆሽ
ብሩህ ነው ፀሀይሽ
ብዙ ነው ጨማቂሽ
ጣፋጭ ነው ጭማቂሽ
ያውም … ካልመረረ
… ካልናረ
ሀገሬ …
ተተኪሽን ተኪ
የትምህርት ስርዓትሽ ፍኖቱ ተጣሟል
መርቆ ሸኝ እንጅ
የተመረቀ ተቀባይ እጅ ከስሟል
ፈተና ይሰረቃል
ውጤት ይሰረዛል
የሰው ህይወት ለቁማር ይረከዛል
ይኼውልሽ …
የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኝ
በማሽን ስህተት ውጤቱ ሲናኝ
ስህተትን ለማረም
የትምህርት አይነት ተለይቶ ይቀነሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከስም
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
የኳስሽ እድገት ቁልቁል ይፈሳል
የክለብሽ ስም
የክልል ካባ በላዩ ለብሷል
ደጋፊሽ ሁሌ
ክለቡን ወግኖ ለጥል ይነሳል
ይኸውልሽ …
በቱርክ ወረራ ህዝባችን መክኖ
በኳስ ቁማር ልቡ በግኖ … ስራ አቁሞ
ያለፋበትን ገንዘብ እያሳደደ
በከንቱ ተስፋ
ጨጓራውን ልጦ ህመም ወለደ
መከረኛው ልጅሽ
ለውድቀት ክብር ይኸው ተዘጋጅቷል
እንቁ ዕጣሽን ትቶ
እንቁ ጣጣሽን ይጠብቃል
@getem
@getem
@getem
^^^^¿^^^^^¿^^^^^^
ድሮ … ጥንት
ጥሩ መሬት እህል የሚያፈራ
ብርቱ አራሽ ዘር የሚዘራ
አማኝ ምዕመን አምላኩን ሚፈራ
አስተዋይ መሪ ህዝቡን የሚመራ
በነበረሽ ጊዜ
ረሀብ ኮስሶ ጥጋብ ተኮፍሶ
የጎረቤት ጓዳ
የራስ እስኪመስል ሰቆቃ ተደርምሶ
በአብሮ መብላት ባህል
በመተሳሰብ ብሂል ክብርሽ ታድሷል
ዕጣሽ ሰምሮ ፍቅር ነግሷል
ዛሬ …
ክረምት ገብቶ
ከቤትህ ስትወጣ እህል ልትዘራ
ሲለፈፍ ትሰማለህ ስለህዝብ ቆጠራ
ግንቦት ደርሶልህ
ክንድህን አበርትተህ ሞፈር ስታነሳ
ማረሻ ማፈሻ
አርማ ይሆናል ለምርጫ ቅስቀሳ
ምትመርጠውን ሳታውቅ
የተመራጭ ብዛት ከብሔር ይበልጣል
በዚህ ስትወዛገብ
ክረምቱ ጠልቆ ፀደይ ይወጣል
ለሀገር ሲታሰብ
ማረስ ተረስቶ ጓሮ ይሳሳል
የኑሮ ውድነት ጣሪያ ይደርሳል
የት ተሂዶ
አቤት ይባላል ማንስ ይከሰሳል
በሚል ጥያቄ
የመረረው ልጅሽ በቁጭት ይታመሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲላሽቅ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
ኢትዮጵያዬ …
ተባረኪ ሲልሽ
እጆችሽን እንድትዘረጊ አምላክ ይፈቅዳል
የሰንደቅሽን አርማ
በማርያም መቀነት ሰማይ ላይ ይወልዳል
ዕጣሽን ሲያሳምር
የፍቅር ማማ ላይ ጎህ ይቀዳል
በብርሀን ፋና ህዝብሽን አጥምቆ
በእምነት ዘውድ ሰላምሽን አድምቆ
ያኖረሽ አምላክ ዕጣሽን ሲያጠፋ
ለማስመሰል ያጨሽው ዕጣንሽ ከረፋ
የአንድነትሽ ቅዳሴ ልዩነቱ ሰፋ
በዚህም በዚያም መጥፊያሽን ሚያስሱ
የግላቸውን ቤተ ክህነት ሊያቋቁሙ ተነሱ
ሀገሬ …
ጥፊ ያለሽ ጊዜ እምነትሽ ይፈርሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከዳሽ
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
በፊት …
ለሰው ልጅ
ክብር ይሰጣል ከሁሉም ልቆ
ሁሉን ከዋኝ
ሁሉን አድራጊ መሆኑ ታውቆ
ዛሬ …
ለልማት ተብሎ ቤት ይፈርሳል
የሰው ልጅ ታንቆ ከተማ ይታደሳል
መጠለያ ያጣ
የዋህ ወገኔ ጎዳና ይፈሳል
የከተማን ውበት
አጠለሸ ተብሎ ተጋፎ ይነሳል
ሚዲያ ይለፍፋል
ለአረንጓዴ ልማት ተሰማራ ብሎ
በውሃ ናፍቆት ህዝብን በጥም ገሎ
ይታለፍ ይመስል
ከችግር አረንቋ ችግኝ ተጠልሎ
እምዬ …
ብዙ ነው ፈታኝሽ
ከባድ ነው ፈተናሽ
ብዙ ነው መካሪሽ
ከባድ ነው መከራሽ
ብዙ ነው ጣይˆሽ
ብሩህ ነው ፀሀይሽ
ብዙ ነው ጨማቂሽ
ጣፋጭ ነው ጭማቂሽ
ያውም … ካልመረረ
… ካልናረ
ሀገሬ …
ተተኪሽን ተኪ
የትምህርት ስርዓትሽ ፍኖቱ ተጣሟል
መርቆ ሸኝ እንጅ
የተመረቀ ተቀባይ እጅ ከስሟል
ፈተና ይሰረቃል
ውጤት ይሰረዛል
የሰው ህይወት ለቁማር ይረከዛል
ይኼውልሽ …
የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ተፈታኝ
በማሽን ስህተት ውጤቱ ሲናኝ
ስህተትን ለማረም
የትምህርት አይነት ተለይቶ ይቀነሳል
እንቁ ዕጣሽ ሲከስም
እንቁ ጣጣሽ ይነግሳል
የኳስሽ እድገት ቁልቁል ይፈሳል
የክለብሽ ስም
የክልል ካባ በላዩ ለብሷል
ደጋፊሽ ሁሌ
ክለቡን ወግኖ ለጥል ይነሳል
ይኸውልሽ …
በቱርክ ወረራ ህዝባችን መክኖ
በኳስ ቁማር ልቡ በግኖ … ስራ አቁሞ
ያለፋበትን ገንዘብ እያሳደደ
በከንቱ ተስፋ
ጨጓራውን ልጦ ህመም ወለደ
መከረኛው ልጅሽ
ለውድቀት ክብር ይኸው ተዘጋጅቷል
እንቁ ዕጣሽን ትቶ
እንቁ ጣጣሽን ይጠብቃል
@getem
@getem
@getem
❤1
ግጥም እንደዚህ ሲሆን እንዴት የልብ ያደርሳል❤️ለነፍስም ይቀርባል.... ግጥሙ ውስጥ ያለው ፍልስፍናው ሲጣፍጥ ፣ ያገማሽራልም ባነበው ባነው አልጠገብኩትም ....ማሜዋ በረካ ሁን አቦ!!!
( እልል አሮጌ ዓመት)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሃበሻ እና ዘመን
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በሃበሻ ምድር
ከኑባሬ አዳም እስከዛሬ ድረስ
ያደስንውን ዓመት ውሉን ስናጤነው ።
በዘመን አዙሪት የአድስ አመት መምጣት
ሲገባኝ ተፍሲሩ ፍቹን ስተምነው፣
ከአምና የተረፈ የልጅነት ወዝን የኛነትን እሸት
ለተራበው አዲስ ወስዶ መገበር ነው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም ይገርማል ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ አደይ አበባ ኑረቱ ሳይፈካ
በፈኩ ወራቶች ታደስኩኝ ይልሃል፣
በእግረ መንገድ ኑሮ ቀናቶች ሸምነው
አመት ሆነህ ሲሉት እልልታ ያቀልጣል፣
ዳግም ለሚመጣ ለዘመን ቋጠሮ
ድጋሜ እማይመጣ እራሱን ይሰዋል፣
ከእድሜው ተቀንሶ የተወራረደ
የእድሜውን ጎደሎ በፌሽታ ያውጃል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዋህ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዘመን ሩጫ ከትላንት አባሮ ለማያውቀው
ነገ ለመጪው ዘንድሮ ሲድረው ጎትቶ፣
ባድስ አመት ብስራት ማርጀት ይሉት ሸማ
ወዶ መደረቡን መልበሱን ዘንግቶ።
እ
ል
ል
አድስ ዓመት
እ
ል
ል
እንቁጣጣሽ
ማለት ይቀናዋል፣
በአድስ አመት ጀርባ እርጅናና ሞቱን
በእልልታ እያጀበ ያወራርደዋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሞኝ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ተመለስ ብትለው ለማይሰማ ዘመን
እንኳን መጣህ ብሎ ድግስ ያሰናዳል፣
ያልተደካን ዘመን ቁጥር ለመጨመር
የዘመኑን ድካ እድሜውን ይንዳል።
ይሄው እስከዛሬ
ሃበሻና እልልታ በያድስ አመቱ
ቀጠሮ እየያዙ እኩል ቢታደሱም፣
ከአንዱ እየቀነሱ በተቀናሽ ሂሳብ
አንዱን ከማፈርጠም ተሻግረው አያውቁም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሃበሻን ኑረት ከፍታ እሚያሳየን
ፍካት የሚያስዋጀን ቅፅበት እስኪመጣ፣
የዘመን ትከሻ አየገፈተረኝ እድሜየን ገብሬ
ከኖርኩበት ዘመን ከአሮጌው ስወጣ።
ባዶ እጁን ለመጣ ላልኖርኩበት አድስ
አሮጌውና አምና አላማውምና፣
ከአድስነቱ ጋር አድስ እስኪያመጣ
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
እንኳን ኖርኩኝ አምና።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት!!!!!!!!!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሙሃመድ ሰኢድ💚💛❤️
ጷግሜ 5/13/2011
@getem
@getem
@balmbaras
( እልል አሮጌ ዓመት)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሃበሻ እና ዘመን
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በሃበሻ ምድር
ከኑባሬ አዳም እስከዛሬ ድረስ
ያደስንውን ዓመት ውሉን ስናጤነው ።
በዘመን አዙሪት የአድስ አመት መምጣት
ሲገባኝ ተፍሲሩ ፍቹን ስተምነው፣
ከአምና የተረፈ የልጅነት ወዝን የኛነትን እሸት
ለተራበው አዲስ ወስዶ መገበር ነው።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም ይገርማል ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እንደ አደይ አበባ ኑረቱ ሳይፈካ
በፈኩ ወራቶች ታደስኩኝ ይልሃል፣
በእግረ መንገድ ኑሮ ቀናቶች ሸምነው
አመት ሆነህ ሲሉት እልልታ ያቀልጣል፣
ዳግም ለሚመጣ ለዘመን ቋጠሮ
ድጋሜ እማይመጣ እራሱን ይሰዋል፣
ከእድሜው ተቀንሶ የተወራረደ
የእድሜውን ጎደሎ በፌሽታ ያውጃል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዋህ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዘመን ሩጫ ከትላንት አባሮ ለማያውቀው
ነገ ለመጪው ዘንድሮ ሲድረው ጎትቶ፣
ባድስ አመት ብስራት ማርጀት ይሉት ሸማ
ወዶ መደረቡን መልበሱን ዘንግቶ።
እ
ል
ል
አድስ ዓመት
እ
ል
ል
እንቁጣጣሽ
ማለት ይቀናዋል፣
በአድስ አመት ጀርባ እርጅናና ሞቱን
በእልልታ እያጀበ ያወራርደዋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሞኝ ነው ሃበሻ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ተመለስ ብትለው ለማይሰማ ዘመን
እንኳን መጣህ ብሎ ድግስ ያሰናዳል፣
ያልተደካን ዘመን ቁጥር ለመጨመር
የዘመኑን ድካ እድሜውን ይንዳል።
ይሄው እስከዛሬ
ሃበሻና እልልታ በያድስ አመቱ
ቀጠሮ እየያዙ እኩል ቢታደሱም፣
ከአንዱ እየቀነሱ በተቀናሽ ሂሳብ
አንዱን ከማፈርጠም ተሻግረው አያውቁም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እናም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሃበሻን ኑረት ከፍታ እሚያሳየን
ፍካት የሚያስዋጀን ቅፅበት እስኪመጣ፣
የዘመን ትከሻ አየገፈተረኝ እድሜየን ገብሬ
ከኖርኩበት ዘመን ከአሮጌው ስወጣ።
ባዶ እጁን ለመጣ ላልኖርኩበት አድስ
አሮጌውና አምና አላማውምና፣
ከአድስነቱ ጋር አድስ እስኪያመጣ
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት
እንኳን ኖርኩኝ አምና።
እ
ል
ል
አሮጌ ዓመት!!!!!!!!!!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሙሃመድ ሰኢድ💚💛❤️
ጷግሜ 5/13/2011
@getem
@getem
@balmbaras