'ካንሰር' ፍቅር(ልዑል ሀይሌ)
አጭር ነኝ አጭር ነሽ
ቁመት የምንለምን በነጋ በጠባ
ቀጭን ነኝ ቀጭን ነሽ
ስጋ የናፈቀን ካጥንት የሚጠጋ
.
ዓይን የለኝ ዓይን የለሽ
ህልሜንም አታይው ህልምሽንም አላይ
ጥርስ የለኝ ጥርስ የለሽ
ደስታዬን ማትቀጂ
ማልቀዳ ደስታሽን ከአንቺነትሽ ሰማይ
.
እግር የለኝ እግር የለሽ
የሚራመድ ላንቺ የሚራመድ ለኔ
እጅ የለኝ እጅ የለሽ
ስላንቺ የሚፅፍ
ስለኔ የሚዘርፍ ነፍስ የሞላው ቅኔ
.
መለያየት 'ካንሰር'
እጅ እግሬን ጥርስ ዓይኔን
ሰውነቴን ሁሉ እየቆራረጠ
ስላንቺ ያኖርኩት
ግዝፈ-አካሌን ወስዶ ለሌላ እየሰጠ
.
ይኸው ቀሪ ዕድሜዬን
እየቆጠርኩኝ ነው ነይ አብረን እንቁጠር
ወትሮም አንድ አይደለን
ለ -የ-ቅል ፍቅር ነው እኛ ስንፈጠር
23-09-10
@getem
@getem
አጭር ነኝ አጭር ነሽ
ቁመት የምንለምን በነጋ በጠባ
ቀጭን ነኝ ቀጭን ነሽ
ስጋ የናፈቀን ካጥንት የሚጠጋ
.
ዓይን የለኝ ዓይን የለሽ
ህልሜንም አታይው ህልምሽንም አላይ
ጥርስ የለኝ ጥርስ የለሽ
ደስታዬን ማትቀጂ
ማልቀዳ ደስታሽን ከአንቺነትሽ ሰማይ
.
እግር የለኝ እግር የለሽ
የሚራመድ ላንቺ የሚራመድ ለኔ
እጅ የለኝ እጅ የለሽ
ስላንቺ የሚፅፍ
ስለኔ የሚዘርፍ ነፍስ የሞላው ቅኔ
.
መለያየት 'ካንሰር'
እጅ እግሬን ጥርስ ዓይኔን
ሰውነቴን ሁሉ እየቆራረጠ
ስላንቺ ያኖርኩት
ግዝፈ-አካሌን ወስዶ ለሌላ እየሰጠ
.
ይኸው ቀሪ ዕድሜዬን
እየቆጠርኩኝ ነው ነይ አብረን እንቁጠር
ወትሮም አንድ አይደለን
ለ -የ-ቅል ፍቅር ነው እኛ ስንፈጠር
23-09-10
@getem
@getem
#መስታወት_ልግዛልሽ
:
:
መቼስ በዚች ዓለም
አምናለው አልክድም
የሰው ፍፁም የለም።
፡
፡
ሰው ስህተት ይሰራል
ከዚያም ይታረማል
ከስ'ተቱ ይማራል።
፡
፡
ያንቺ ግን ፍቅርዬ መሳሳትሽ ወዛ
በ'ኔና አንቺ መሀል ምንም ሰው ሳይበዛ
እራስሽ የጣድሺው ጎመንም ጠነዛ።
፡
፡
ከሰራሺው ስህተት ትማሪያለሽ ብዬ...
...በተስፋ ስጠብቅ ወይ ዛሬ ወይ ነገ
እንኳን ልትማሪ ጥፋትሽ ስር ሰዶ...
ቅርንጫፍ አውጥቶ ይባሱን አደገ።
፡
፡
እናምልሽ ፍቅሬ...
ትናንት በመቅረዜ ደቂቅ ተስፋን ይዤ
ሁሉን ለ አምላክ ጥዬ እሱን ተመርኩዤ
አጣጥቤ ልኬሽ ጨቅይተሽ ስትመጪ
ፍቅርሽ እንዳይርቀኝ ከልቤ እንዳትወጪ
መውደድ አስገድዶኝ ዳግም እንደገና
አምጥቼልሽ ነበር ውሀና ሳሙና።
፡
፡
ዛሬ ግን ታከተኝ ዛሬማ በቅቶኛል
ጭቃሽን ለማንፃት ውሀ ምቀዳበት...
ጉልበቴም ከድቶኛል።
፡
፡
እናም ካሁን ወዲህ ለኔም እንዲቀለኝ...
...ላንቺም እንዲበጅሽ
በሳሙና ፈንታ ጭቃሽን እንድታይ...
...መስታወት ልግዛልሽ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ @Henokbirhanu
@getem
@getem
:
:
መቼስ በዚች ዓለም
አምናለው አልክድም
የሰው ፍፁም የለም።
፡
፡
ሰው ስህተት ይሰራል
ከዚያም ይታረማል
ከስ'ተቱ ይማራል።
፡
፡
ያንቺ ግን ፍቅርዬ መሳሳትሽ ወዛ
በ'ኔና አንቺ መሀል ምንም ሰው ሳይበዛ
እራስሽ የጣድሺው ጎመንም ጠነዛ።
፡
፡
ከሰራሺው ስህተት ትማሪያለሽ ብዬ...
...በተስፋ ስጠብቅ ወይ ዛሬ ወይ ነገ
እንኳን ልትማሪ ጥፋትሽ ስር ሰዶ...
ቅርንጫፍ አውጥቶ ይባሱን አደገ።
፡
፡
እናምልሽ ፍቅሬ...
ትናንት በመቅረዜ ደቂቅ ተስፋን ይዤ
ሁሉን ለ አምላክ ጥዬ እሱን ተመርኩዤ
አጣጥቤ ልኬሽ ጨቅይተሽ ስትመጪ
ፍቅርሽ እንዳይርቀኝ ከልቤ እንዳትወጪ
መውደድ አስገድዶኝ ዳግም እንደገና
አምጥቼልሽ ነበር ውሀና ሳሙና።
፡
፡
ዛሬ ግን ታከተኝ ዛሬማ በቅቶኛል
ጭቃሽን ለማንፃት ውሀ ምቀዳበት...
ጉልበቴም ከድቶኛል።
፡
፡
እናም ካሁን ወዲህ ለኔም እንዲቀለኝ...
...ላንቺም እንዲበጅሽ
በሳሙና ፈንታ ጭቃሽን እንድታይ...
...መስታወት ልግዛልሽ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ @Henokbirhanu
@getem
@getem
አፍቄሜሌፅ (የፍቅር ቃል እድሜ)
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ፍቅርን ያህል ነገር
ተሸክሜ ስኖር ፣ በልቤ ትከሻ
"ቃል አጠረኝ" የሚል
ቃል ካፌ አይወጣም ፣ ላወድስሽ ስሻ።
እንደውም ሳፈቅር ፣ ቃል ነው የሚተርፈኝ
እንኳንስ ቃል ሊያጥረኝ
ሁሉ ያጥርብኛል
በልብሽ ቅርፅ ውስጥ ፣ መውደድሽ ሲያገዝፈኝ
ቃልም ነው በመንፈስ
ልሳን እየሰጠ ፣ የሚያስለፈልፈኝ ።
ሻምጵራ ቅራንጳ
ወዘ ትሩሩጳ
አፍረንትረን ደስቴ
ፄፃቱ ጳፃቴ
ወኡዝ ሀአሪከ
አዝወረ ነባከ
ፊፀአ ነአቱ
ጀነወ ርዕቱ
ናፃ ፄላሟሜ
እናልሽ አለሜ
አዲስ ፊደል ባልቀርፅ ፣ አዲስ ቃል ቀምሜ
ትርጉሙ እንዲገባሽ
የልሳን ቃሎቼን ፣ በአንዲት ቃል ተርጉሜ
"አፍቄሜሌፅ" አልኩሽ!
አፍቄሜሌፅ ማለት ፣ በኔ ትርጓሜ
ሁሉ ያጥራል እንጂ
አያጥርም ማለት ነው ፣ የፍቅር ቃል እድሜ።
።።።።።።።
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ሰፊ ያልሁት አለም ፣ ባንድ እርምጃ አለቀ
ሳልሄደው ሚደክመኝ...
ተራራና ጋራው ፣ ከግሬ ስር ጠለቀ።
"ሩቅ" ያልሁት ሰማይ..
ሩቅ የሚመስለኝ ፣ ነካሁት በስንዝር
ጨረቃና ፀሀይ....
ከኮከብ ያንሳሉ ፣ ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር።
.......................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ንጉስን ከዙፋን ፣ ማርከው የሚያወርዱ
የሀያላንን አቅም ፣ በጥቅሻ ሚያርዱ
ቆነጃጅት ሴቶች ...
"ቃል አጠረኝ" በሚል ቃላት የተሞሉ
ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር..
ቃል ተገኝቶላቸው ፣ "ፋንጋዎች" ተባሉ።
.........................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
"ቃል አጠረኝ "በሚል...
ባፍቃሪ አንደበት ፣ ቃል ተትረፈረፈ
ሁሉን አሳንሶ...
በልቡ ቅርፅ ውስጥ ፣ ፍቅሩን አገዘፈ
አለሙን ሰርዞ ፣ ፍቅሩን ብቻ ፃፈ!!!
..........................................
ሳፈቅርሽ ይህን አልኩ...
ፍቅርን ተሸክሞ ፣ የሚኖር ልቦና
ሁሉም ከፍቅርሽ ስር ፣ መሆኑን አውቅና
አንቺን ለማወደስ .፣..እኔም ቃል ያጥረኛል
"ቃል አጠረኝ "ማለት...
ቃል እንደሆነ ግን ፣ ፍቅርሽ ይነግረኛል!!!
ሻምጵራ ቅራንጳ
ወዘ ትሩሩጳ
አፍረንትረን ደስቴ
ፄፃቱ ጳፃቴ
ወኡዝ ሀአሪከ
አዝወረ ነባከ
ፊፀአ ነአቱ
ጀነወ ርዕቱ
ናፃ ፄላሟሜ
እናልሽ አለሜ
አንደበት ዝም ቢል
ዝም አይልም አይኔ ፣ ዝም አይልም ጥርሴ
ቃል አለው ጆሮዬ ፣ ዝም ቢል ምላሴ።
ዝም አይልም እጄ ፣ ዝም አይልም እግሬ
እኔ ቃል ቢያጥረኝም
ሰማይና ምድሩ
ፈጣሪና ፍጡሩ
ለፍቅር ቃል አለው ፣ ይናገራል ፍቅሬ።
።።።።።
ትርጉም ብንሰጠው
ጥላቻ በራሱ ፣ ለፍቅር አለው ቋንቋ
"አፍቄሜሌፅ" አልኩሽ
የፍቅር ቃል እድሜ
ከዘላለም የሚያልፍ ፣ ዘላለም ነው በቃ።
ሀዘሩ ጣሪቃ
ሉፋሴ ጰኑቃ
ሪድዋ ሸዛጨ
አገቀ ጠየጨ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ፍቅርን ያህል ነገር
ተሸክሜ ስኖር ፣ በልቤ ትከሻ
"ቃል አጠረኝ" የሚል
ቃል ካፌ አይወጣም ፣ ላወድስሽ ስሻ።
እንደውም ሳፈቅር ፣ ቃል ነው የሚተርፈኝ
እንኳንስ ቃል ሊያጥረኝ
ሁሉ ያጥርብኛል
በልብሽ ቅርፅ ውስጥ ፣ መውደድሽ ሲያገዝፈኝ
ቃልም ነው በመንፈስ
ልሳን እየሰጠ ፣ የሚያስለፈልፈኝ ።
ሻምጵራ ቅራንጳ
ወዘ ትሩሩጳ
አፍረንትረን ደስቴ
ፄፃቱ ጳፃቴ
ወኡዝ ሀአሪከ
አዝወረ ነባከ
ፊፀአ ነአቱ
ጀነወ ርዕቱ
ናፃ ፄላሟሜ
እናልሽ አለሜ
አዲስ ፊደል ባልቀርፅ ፣ አዲስ ቃል ቀምሜ
ትርጉሙ እንዲገባሽ
የልሳን ቃሎቼን ፣ በአንዲት ቃል ተርጉሜ
"አፍቄሜሌፅ" አልኩሽ!
አፍቄሜሌፅ ማለት ፣ በኔ ትርጓሜ
ሁሉ ያጥራል እንጂ
አያጥርም ማለት ነው ፣ የፍቅር ቃል እድሜ።
።።።።።።።
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ሰፊ ያልሁት አለም ፣ ባንድ እርምጃ አለቀ
ሳልሄደው ሚደክመኝ...
ተራራና ጋራው ፣ ከግሬ ስር ጠለቀ።
"ሩቅ" ያልሁት ሰማይ..
ሩቅ የሚመስለኝ ፣ ነካሁት በስንዝር
ጨረቃና ፀሀይ....
ከኮከብ ያንሳሉ ፣ ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር።
.......................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ንጉስን ከዙፋን ፣ ማርከው የሚያወርዱ
የሀያላንን አቅም ፣ በጥቅሻ ሚያርዱ
ቆነጃጅት ሴቶች ...
"ቃል አጠረኝ" በሚል ቃላት የተሞሉ
ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር..
ቃል ተገኝቶላቸው ፣ "ፋንጋዎች" ተባሉ።
.........................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
"ቃል አጠረኝ "በሚል...
ባፍቃሪ አንደበት ፣ ቃል ተትረፈረፈ
ሁሉን አሳንሶ...
በልቡ ቅርፅ ውስጥ ፣ ፍቅሩን አገዘፈ
አለሙን ሰርዞ ፣ ፍቅሩን ብቻ ፃፈ!!!
..........................................
ሳፈቅርሽ ይህን አልኩ...
ፍቅርን ተሸክሞ ፣ የሚኖር ልቦና
ሁሉም ከፍቅርሽ ስር ፣ መሆኑን አውቅና
አንቺን ለማወደስ .፣..እኔም ቃል ያጥረኛል
"ቃል አጠረኝ "ማለት...
ቃል እንደሆነ ግን ፣ ፍቅርሽ ይነግረኛል!!!
ሻምጵራ ቅራንጳ
ወዘ ትሩሩጳ
አፍረንትረን ደስቴ
ፄፃቱ ጳፃቴ
ወኡዝ ሀአሪከ
አዝወረ ነባከ
ፊፀአ ነአቱ
ጀነወ ርዕቱ
ናፃ ፄላሟሜ
እናልሽ አለሜ
አንደበት ዝም ቢል
ዝም አይልም አይኔ ፣ ዝም አይልም ጥርሴ
ቃል አለው ጆሮዬ ፣ ዝም ቢል ምላሴ።
ዝም አይልም እጄ ፣ ዝም አይልም እግሬ
እኔ ቃል ቢያጥረኝም
ሰማይና ምድሩ
ፈጣሪና ፍጡሩ
ለፍቅር ቃል አለው ፣ ይናገራል ፍቅሬ።
።።።።።
ትርጉም ብንሰጠው
ጥላቻ በራሱ ፣ ለፍቅር አለው ቋንቋ
"አፍቄሜሌፅ" አልኩሽ
የፍቅር ቃል እድሜ
ከዘላለም የሚያልፍ ፣ ዘላለም ነው በቃ።
ሀዘሩ ጣሪቃ
ሉፋሴ ጰኑቃ
ሪድዋ ሸዛጨ
አገቀ ጠየጨ
@getem
@getem
@lula_al_greeko
❤1
ጠቅላይ ሚኒስቴሩ የፃፉት ግጥም
(በላይ በቀለ ወያ)።።።።።
እነ ሀምሳ ብሮች...
እነ መቶ ብሮች ፣ ከኪሴ ሲጠፉ
እነ አስር ብሮች...
የማያልቅ ሰፌድ ፣ ዘላለም ሲሰፉ
እነ አምስት ብሮች...
ቡና እየለቀሙ ፣ ነግደው ሲያተርፉ
አንድ ብር ይስቃል!!!
።።።፣፣፣፣፣።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣።።።፣።።
የማያባራ ሳቅ ፣ የሚኖር ፈገግታ
እኔም ላይ ይታያል ፣ ያንድ ብር ሁኔታ
እንዲህ ያደርገኛል...
ያደጉ ካድሬዎች
ኢትዮጵያ አድጋለች ፣ ብለው ያሉኝ ለታ
የታሰሩን ብሮች?
የታሰሩን ሰዎች? እኔ ስንቱን ልፍታ?
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)።።።።።
እነ ሀምሳ ብሮች...
እነ መቶ ብሮች ፣ ከኪሴ ሲጠፉ
እነ አስር ብሮች...
የማያልቅ ሰፌድ ፣ ዘላለም ሲሰፉ
እነ አምስት ብሮች...
ቡና እየለቀሙ ፣ ነግደው ሲያተርፉ
አንድ ብር ይስቃል!!!
።።።፣፣፣፣፣።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣።።።፣።።
የማያባራ ሳቅ ፣ የሚኖር ፈገግታ
እኔም ላይ ይታያል ፣ ያንድ ብር ሁኔታ
እንዲህ ያደርገኛል...
ያደጉ ካድሬዎች
ኢትዮጵያ አድጋለች ፣ ብለው ያሉኝ ለታ
የታሰሩን ብሮች?
የታሰሩን ሰዎች? እኔ ስንቱን ልፍታ?
@getem
@getem
👍2❤1
ሟች እና ቀባሪ
(ፍፄ ሎሬት )
ከሩቅ ይሰማኛል የመንደር ጡረምባ
ቀጠሮ እያስያዘ ሰፈሩን ሊያስነባ
ጡሩምባ ለፋፊ ያ ሙጢ ምለሱ ካፎቱ
እንደወጣ
ዳናዉ ይሰማኛል ወደ እኔ ሲመጣ
አወይ... አንት ፈጣሪ
አወይ... አንት ጠሪ
አንዱ ጊዜው ከድቶት ወዳንተ ሲጠራ
አንድ ጡሩምባ ነፊ ይበላል እንጀራ
አሁንም ተሰማኝ ያ ጡሩምባ ነፊ
የሞት ዜና አዋጅ የህልፈት ለፋፊ
ሞተ አዎ ሞተ ያ ልጅ እንዲያ እንደዋተተ
ለሰዉ በሽተኛ ለራሱ ጤነኛ እንደሆነ ሞተ
የቱ...ያ ወፈፌዉ ያ ጅላጅል እብዱ
አትበሉ ባካችሁ ነገር ሳትረዱ
ካፎቱ እንደወጣ የሰላ ጎራዴ
ሊያንቅ እንደሚዳዳዉ የአንገት ግማዴ
ምላሳችሁ ሰልቶ ልቡን እንዳደማ
ጡረምባ ለፋፊ መሞቱን ሲያሰማ
እብድ ነዉ ብላችሁ ሳያብድ እንዳበደ
በሞቱ ለማፌዝ አፋችሁ ወደደ
ቢሆንማ ኖሮ....
የቃላት ጦር ሰብቆ ለገደለ ገዳይ
ሸንጎ ባይኖር እንጂ ፍርድ ችሎት አስቻይ
የምን ፍታብሄር ወንጀለኛ መቅጫ
ህገ-ኦሪት ነበር በደልን መወጫ።
@getem
@getem
(ፍፄ ሎሬት )
ከሩቅ ይሰማኛል የመንደር ጡረምባ
ቀጠሮ እያስያዘ ሰፈሩን ሊያስነባ
ጡሩምባ ለፋፊ ያ ሙጢ ምለሱ ካፎቱ
እንደወጣ
ዳናዉ ይሰማኛል ወደ እኔ ሲመጣ
አወይ... አንት ፈጣሪ
አወይ... አንት ጠሪ
አንዱ ጊዜው ከድቶት ወዳንተ ሲጠራ
አንድ ጡሩምባ ነፊ ይበላል እንጀራ
አሁንም ተሰማኝ ያ ጡሩምባ ነፊ
የሞት ዜና አዋጅ የህልፈት ለፋፊ
ሞተ አዎ ሞተ ያ ልጅ እንዲያ እንደዋተተ
ለሰዉ በሽተኛ ለራሱ ጤነኛ እንደሆነ ሞተ
የቱ...ያ ወፈፌዉ ያ ጅላጅል እብዱ
አትበሉ ባካችሁ ነገር ሳትረዱ
ካፎቱ እንደወጣ የሰላ ጎራዴ
ሊያንቅ እንደሚዳዳዉ የአንገት ግማዴ
ምላሳችሁ ሰልቶ ልቡን እንዳደማ
ጡረምባ ለፋፊ መሞቱን ሲያሰማ
እብድ ነዉ ብላችሁ ሳያብድ እንዳበደ
በሞቱ ለማፌዝ አፋችሁ ወደደ
ቢሆንማ ኖሮ....
የቃላት ጦር ሰብቆ ለገደለ ገዳይ
ሸንጎ ባይኖር እንጂ ፍርድ ችሎት አስቻይ
የምን ፍታብሄር ወንጀለኛ መቅጫ
ህገ-ኦሪት ነበር በደልን መወጫ።
@getem
@getem
"ውሰጅ"
:
ሀሳቤንም ውሰጅ
ግጥሜንም ውሰጅ
ወንድነቴን ውሰጅ
እኔነቴን ውሰጅ
ሚጠቅምሽን ብቻ፣ ውሰጅ ውሰጅና
አንቺም ተቀላቀይ፣ ከዝነኞች ዝና
ደግሞም ንገሪያቸው፣ መድረክ ላይ ስትቆሚ
"አፍቃሪ ነበረኝ፣ ፍቅሩ እጅግ ገራሚ
ህይወቱን ዘንግቶ፣ እኔን አለምላሚ"
ይሄን እየሰማ፣ ጉድ ይበል ታዳሚ
ብቻ ምለምንሽ...
ህይወቴ እንዲሞላ፣ ኑሮዬ እንዲቃና
ማፍቀሬን ተይልኝ፣ አይጥቅምሽምና...
:
(((...ባባ...)))
ግጥም ለመላክ @getem_sourcebot
@getem
@getem
:
ሀሳቤንም ውሰጅ
ግጥሜንም ውሰጅ
ወንድነቴን ውሰጅ
እኔነቴን ውሰጅ
ሚጠቅምሽን ብቻ፣ ውሰጅ ውሰጅና
አንቺም ተቀላቀይ፣ ከዝነኞች ዝና
ደግሞም ንገሪያቸው፣ መድረክ ላይ ስትቆሚ
"አፍቃሪ ነበረኝ፣ ፍቅሩ እጅግ ገራሚ
ህይወቱን ዘንግቶ፣ እኔን አለምላሚ"
ይሄን እየሰማ፣ ጉድ ይበል ታዳሚ
ብቻ ምለምንሽ...
ህይወቴ እንዲሞላ፣ ኑሮዬ እንዲቃና
ማፍቀሬን ተይልኝ፣ አይጥቅምሽምና...
:
(((...ባባ...)))
ግጥም ለመላክ @getem_sourcebot
@getem
@getem
👍1
ያፈቀረ ታጣቂ የሚፅፈው ግጥም
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
እንዴት ብዬ ልርሳሽ ፣ እንደምን አድርጌ
ልተውሽ አልቻልኩም ፣ ልረሳሽ ፈልጌ፡፡
፡፡፡፡፡፡
ይኸው በቀደም ለት...
ባንዳንድ ጠባቦች ፣ ረብሻ ተነስቶ
"እርምጃ ውሰዱ"
የሚል ቀጭን ትእዛዝ ፣ ከላይ አካል ወጥቶ
እርምጃ ለመውሰድ...
እየተራመድኩኝ ፣ አመፁን ላበርደው
እርምጃሽ ትዝ አለኝ ፣ እርምጃ ሚወስደው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ይኸው ከዛ ወዲህ...
ከመንግስት እርምጃ ፣ እርምጃሽ አይሎ
ትዝታሽን ይዞ ፣ መጣ ተግተልትሎ
በእርምጃዬ ቁጥር...
እርምጃሽ ይመጣል ፣ ናፍቆትሽን አዝሎ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንዴት ነው እርምጃሽ ፣ የማያራምደው
እንዴት ነው ጠረንሽ ፣
እንደ አስለቃሽ ጭስ ፣ ደርሶ ሚያሳውረው
እንደምነው አይንሽ ፣ ነጥቶ የጠቆረው
እንደ እሬንጀር ልብስ ፣ የሚያስደነብረው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነው ጡትሽ
ልክ እንደመርማሪ ፣ ትክ ብሎ ሚያፈጠው
እንደምነው ዳሌሽ...
እንትኑን ተመቶ ፣
እንደወደቀ ሰው ፣ የሚንፈራገጠው፡
፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነው ጭንሽ ፣ ካፈሙዝ ሚሞቀው
እንዴት ነው ያ ነገር...
እንደከስክስ ጫማ ፣ ቢረግጡት ማያልቀው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነው ጥርስሽ...
እንደ አድማ በታኝ ፣ የተደረደረው
እንዴት ነው አፍንጫሽ...
እንደተቃዋሚ ፣ ባጭሩ የቀረው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንዴት ነው ከንፈርሽ ፣ ከስልጣን ሚጥመው
እንዴት ነው ወገብሽ...
እንደ ክፉ ነገር ፣ የሚጠመጠመው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምን ነው ፀጉርሽ
እንደሀገሬ ሰንደቅ ፣ በቁጥር የበዛው
እንደምነው ጉንጭሽ...
ጥፊ እንደተመታ ፣ ቀልቶ የሚወዛው
እንደምነሽ አንቺስ ፣ በናፍቆት ምትቀጪ
እንደ ሀገሬ ታሪክ
ባለፈ ጠባሳ ፣ ቁስል ይዘሽ ምትመጪ።
Share
👇👇👇
@getem
@getem
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
እንዴት ብዬ ልርሳሽ ፣ እንደምን አድርጌ
ልተውሽ አልቻልኩም ፣ ልረሳሽ ፈልጌ፡፡
፡፡፡፡፡፡
ይኸው በቀደም ለት...
ባንዳንድ ጠባቦች ፣ ረብሻ ተነስቶ
"እርምጃ ውሰዱ"
የሚል ቀጭን ትእዛዝ ፣ ከላይ አካል ወጥቶ
እርምጃ ለመውሰድ...
እየተራመድኩኝ ፣ አመፁን ላበርደው
እርምጃሽ ትዝ አለኝ ፣ እርምጃ ሚወስደው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ይኸው ከዛ ወዲህ...
ከመንግስት እርምጃ ፣ እርምጃሽ አይሎ
ትዝታሽን ይዞ ፣ መጣ ተግተልትሎ
በእርምጃዬ ቁጥር...
እርምጃሽ ይመጣል ፣ ናፍቆትሽን አዝሎ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንዴት ነው እርምጃሽ ፣ የማያራምደው
እንዴት ነው ጠረንሽ ፣
እንደ አስለቃሽ ጭስ ፣ ደርሶ ሚያሳውረው
እንደምነው አይንሽ ፣ ነጥቶ የጠቆረው
እንደ እሬንጀር ልብስ ፣ የሚያስደነብረው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነው ጡትሽ
ልክ እንደመርማሪ ፣ ትክ ብሎ ሚያፈጠው
እንደምነው ዳሌሽ...
እንትኑን ተመቶ ፣
እንደወደቀ ሰው ፣ የሚንፈራገጠው፡
፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነው ጭንሽ ፣ ካፈሙዝ ሚሞቀው
እንዴት ነው ያ ነገር...
እንደከስክስ ጫማ ፣ ቢረግጡት ማያልቀው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነው ጥርስሽ...
እንደ አድማ በታኝ ፣ የተደረደረው
እንዴት ነው አፍንጫሽ...
እንደተቃዋሚ ፣ ባጭሩ የቀረው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንዴት ነው ከንፈርሽ ፣ ከስልጣን ሚጥመው
እንዴት ነው ወገብሽ...
እንደ ክፉ ነገር ፣ የሚጠመጠመው
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምን ነው ፀጉርሽ
እንደሀገሬ ሰንደቅ ፣ በቁጥር የበዛው
እንደምነው ጉንጭሽ...
ጥፊ እንደተመታ ፣ ቀልቶ የሚወዛው
እንደምነሽ አንቺስ ፣ በናፍቆት ምትቀጪ
እንደ ሀገሬ ታሪክ
ባለፈ ጠባሳ ፣ ቁስል ይዘሽ ምትመጪ።
Share
👇👇👇
@getem
@getem
<<ጭንሽ ነው ምሽጌ>>
ከግርግዳው ጀርባ ድምጹ ይሰማኛል
ቡና እየጠጣችሁ እናትሽ ያሙኛል
ስጋየ ሲበላ ቁጭ ብየ እሰማለሁ
ጎኔን ሲቦጭቁት አህህ እላለሁ
አንዲህ ሲሉ ሰማሁ
እኚያ እናትሽ
ምክር አስመስለው እኔን ሲያሙልሽ
ፍቅረኛሽ መሆኔን መች አወቁልሽ
ስሚኝማ ልጄ,,,,,,
ይሄ ቀድረ ቀላል
ከጎናችን ያለው ማንነበረ ስሙ?
ተይው አትንገሪኝ
ብቻ እምነግርሽን አስረግጠሽ ስሚኝ
እያሉ ነገሩሽ ቀጣፊ መሆኔን
በቃሌ እማልገኝ ብኩን ሰውነቴን
ሲያሰኘኝ ሌባ በል ሲለኝ ቀማኛ
ነው አሉሽ ጉበኛ
ዛሬ አንዷን አድሬ ነግ ደሞ ሌላዋን
እንደምቀያይር ሴቶችን እንደ አሸን
አግብቼ መፍታቴን ጨምረው ነገሩሽ
እልልታው ቀርቶብኝ ጥላቻ እንዲወርስሽ
ሲጋራ ያጨሳል
ጫቱንም ይቅማል
ሲጠጣ ደ'ሞ አይጣል
ሰፈሩ በሙሉ በሱ ተበጥብጧል
ብለው አሰፉልሽ
ቱ ብለው ሲተፉት የስጋየን ልማጭ
ሰማሁና ከውጭ
እንዳይበሉት ሰጋሁ ያጥንቴን ቅጥቃጭ
ይሄን ሰማሽና........
ስትከንፊ መጣሽ እንደ ጉድ ደነፋሽ
ያሉኝን በሙሉ ነገርሽኝ ጨማምረሽ
ላስረዳሽ ሞክርኩኝ ልናዘዝ ሁሉንም
ግና ምን ያደርጋል
መታደል ነው እንጂ አይታገሉትም
ፍጥረትሽ ነውና መስማት አልታደልሺም
እውነቱ ግን ይህ ነው
አዎ እቅማለሁ..................
ስገርብሽ ውየ በዛው አመሻለሁ
በምርቃናዯ ውስጥ አንችን አይሻለሁ
አዎ ሰካራም ነኝ................
ሳጥን ተረግጬ
ቤቱን አዘግቼ
ጠጥቼ ጠጥቼ
ጨርቅ ሆኘ ሰክሬ
ወጥቶ ድንብርብሬ
እየተንገዳገድኩ
ተሳስሮ እጅ እግሬ
ስገባ እቤቴ ስምሽን ከሩቁ ጮኼ ጠራዋለሁ
ኩልትፍትፍ አድርጌ አሳምረዋለሁ
አዎ አጨሳለሁ................
በከንፈሬ መሃል አምጌሽ ወደውስጥ
ልቤን ያቆስለዋል የፍቅርሽ ረመጥ
ከዛም አንጋጥጬ ወደውጭ ሳወጣሽ
በሲጋራዮ ጭስ ይታየኛል መልክሽ
የጀመርኩት ሳያልቅ ሌላ ለኩሳለሁ
ደስ የሚል ስቃዩን እኔ ወደዋለሁ
የምን ሳምባ መቁሰል
የምን ከንፈር መጥቆር
አቦለው ይዣለሁ እያልኩ የኔፍቅር
ስሚኝማ ውዴ,,,,,,
ንዝንዙን እርሺው ንትርኩም ይቅር
መተሽ እንደሰት በምናውቀው ሃገር
ከእናትሽ ሃሜት
ከምርቃናው ህልሜ
ከመጠጡ አጎበር
ከጭሱ ህመሜ
ከለቅሶየ ድባቅ
ቶሎ እንድላቀቅ
ነይና ደብቂኝ ከጭንሽ ስር ልውደቅ
@getem
@getem
@lula_al_GREEKO
ከግርግዳው ጀርባ ድምጹ ይሰማኛል
ቡና እየጠጣችሁ እናትሽ ያሙኛል
ስጋየ ሲበላ ቁጭ ብየ እሰማለሁ
ጎኔን ሲቦጭቁት አህህ እላለሁ
አንዲህ ሲሉ ሰማሁ
እኚያ እናትሽ
ምክር አስመስለው እኔን ሲያሙልሽ
ፍቅረኛሽ መሆኔን መች አወቁልሽ
ስሚኝማ ልጄ,,,,,,
ይሄ ቀድረ ቀላል
ከጎናችን ያለው ማንነበረ ስሙ?
ተይው አትንገሪኝ
ብቻ እምነግርሽን አስረግጠሽ ስሚኝ
እያሉ ነገሩሽ ቀጣፊ መሆኔን
በቃሌ እማልገኝ ብኩን ሰውነቴን
ሲያሰኘኝ ሌባ በል ሲለኝ ቀማኛ
ነው አሉሽ ጉበኛ
ዛሬ አንዷን አድሬ ነግ ደሞ ሌላዋን
እንደምቀያይር ሴቶችን እንደ አሸን
አግብቼ መፍታቴን ጨምረው ነገሩሽ
እልልታው ቀርቶብኝ ጥላቻ እንዲወርስሽ
ሲጋራ ያጨሳል
ጫቱንም ይቅማል
ሲጠጣ ደ'ሞ አይጣል
ሰፈሩ በሙሉ በሱ ተበጥብጧል
ብለው አሰፉልሽ
ቱ ብለው ሲተፉት የስጋየን ልማጭ
ሰማሁና ከውጭ
እንዳይበሉት ሰጋሁ ያጥንቴን ቅጥቃጭ
ይሄን ሰማሽና........
ስትከንፊ መጣሽ እንደ ጉድ ደነፋሽ
ያሉኝን በሙሉ ነገርሽኝ ጨማምረሽ
ላስረዳሽ ሞክርኩኝ ልናዘዝ ሁሉንም
ግና ምን ያደርጋል
መታደል ነው እንጂ አይታገሉትም
ፍጥረትሽ ነውና መስማት አልታደልሺም
እውነቱ ግን ይህ ነው
አዎ እቅማለሁ..................
ስገርብሽ ውየ በዛው አመሻለሁ
በምርቃናዯ ውስጥ አንችን አይሻለሁ
አዎ ሰካራም ነኝ................
ሳጥን ተረግጬ
ቤቱን አዘግቼ
ጠጥቼ ጠጥቼ
ጨርቅ ሆኘ ሰክሬ
ወጥቶ ድንብርብሬ
እየተንገዳገድኩ
ተሳስሮ እጅ እግሬ
ስገባ እቤቴ ስምሽን ከሩቁ ጮኼ ጠራዋለሁ
ኩልትፍትፍ አድርጌ አሳምረዋለሁ
አዎ አጨሳለሁ................
በከንፈሬ መሃል አምጌሽ ወደውስጥ
ልቤን ያቆስለዋል የፍቅርሽ ረመጥ
ከዛም አንጋጥጬ ወደውጭ ሳወጣሽ
በሲጋራዮ ጭስ ይታየኛል መልክሽ
የጀመርኩት ሳያልቅ ሌላ ለኩሳለሁ
ደስ የሚል ስቃዩን እኔ ወደዋለሁ
የምን ሳምባ መቁሰል
የምን ከንፈር መጥቆር
አቦለው ይዣለሁ እያልኩ የኔፍቅር
ስሚኝማ ውዴ,,,,,,
ንዝንዙን እርሺው ንትርኩም ይቅር
መተሽ እንደሰት በምናውቀው ሃገር
ከእናትሽ ሃሜት
ከምርቃናው ህልሜ
ከመጠጡ አጎበር
ከጭሱ ህመሜ
ከለቅሶየ ድባቅ
ቶሎ እንድላቀቅ
ነይና ደብቂኝ ከጭንሽ ስር ልውደቅ
@getem
@getem
@lula_al_GREEKO
👍1
#ባላላጠሽ
:
:
ፀጉርሽ ጠልፎ ጣለኝ
ወድቄም ተነሳው
ዐይንሽ ጠቅሶ ጣለኝ
ወድቄም ተነሳው
መነሳቴ እንዳለ በጠጠር ተበሳው።
:
:
እኔም በተራዬ
ካንቺው ተከትዬ
በፀጉሬ እንዳልጥልሽ ፀጉሬ አጭር ነው
በጥቅሻ እንዳልጥልሽ ጥቅሻውን አላቀው።
:
:
ታዲያ በምን አቅሜ እንዴትስ ልጣልሽ
አምላክ በጥበቡ እሱ እንደፈጠረሽ
ጉልበታም አድርጎ በኔ እንዳስጀገነሽ
አሞሽ ከምጨነቅ እጅጉን ተጎድተሽ
በጣሙን ሳይበዛ ትንሽ ከፍ አድርጎሽ
ከዛም ከከፍታው ጥሎ ባላላጠሽ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@Henokbirhabu
@getem
@getem
@getem
:
:
ፀጉርሽ ጠልፎ ጣለኝ
ወድቄም ተነሳው
ዐይንሽ ጠቅሶ ጣለኝ
ወድቄም ተነሳው
መነሳቴ እንዳለ በጠጠር ተበሳው።
:
:
እኔም በተራዬ
ካንቺው ተከትዬ
በፀጉሬ እንዳልጥልሽ ፀጉሬ አጭር ነው
በጥቅሻ እንዳልጥልሽ ጥቅሻውን አላቀው።
:
:
ታዲያ በምን አቅሜ እንዴትስ ልጣልሽ
አምላክ በጥበቡ እሱ እንደፈጠረሽ
ጉልበታም አድርጎ በኔ እንዳስጀገነሽ
አሞሽ ከምጨነቅ እጅጉን ተጎድተሽ
በጣሙን ሳይበዛ ትንሽ ከፍ አድርጎሽ
ከዛም ከከፍታው ጥሎ ባላላጠሽ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
@Henokbirhabu
@getem
@getem
@getem
ምስልሽ ይታየኛል
።።።።።።።።።።።
.
እረግቶ በቆመው
ደሞም በሚፈሰው
በሚንደረደረው
በውሃው ገፅ ላይ ውቤ አንቺን አያለው
በጉም ተበሳጭቶ
በመብረቅ አጓርቶ
ከውብ ገፁ ሸሽቶ
በጠቆረው ሰማይ ገፅሽ ሕብር ሰርቶ
ምስልሽን አያለው
ደሞም እቃኛለው
በቢጫው መስክ ላይ
በአደዩ አድባር በአደዩ ቀላይ
በዞማ ጠጉርሽ ላይ አበባ ሰክተሽ
ይታየኛል ገፅሽ ይታየኛል ምስልሽ
ደሞም በገሞራው በአፍዴራው ንዳድ
በሚንቀለቀለው ኃያል የሳት ሰደድ
ውቤ የኔ አበባ ገፅሽ ይስበኛል
እምዬ ሃገሬ ምስልሽ ይታየኛል!
ተፃፈ በዴቭ(Mr. Trump)
ለመላክ: @getem_sourcebot
@getem
@getem
።።።።።።።።።።።
.
እረግቶ በቆመው
ደሞም በሚፈሰው
በሚንደረደረው
በውሃው ገፅ ላይ ውቤ አንቺን አያለው
በጉም ተበሳጭቶ
በመብረቅ አጓርቶ
ከውብ ገፁ ሸሽቶ
በጠቆረው ሰማይ ገፅሽ ሕብር ሰርቶ
ምስልሽን አያለው
ደሞም እቃኛለው
በቢጫው መስክ ላይ
በአደዩ አድባር በአደዩ ቀላይ
በዞማ ጠጉርሽ ላይ አበባ ሰክተሽ
ይታየኛል ገፅሽ ይታየኛል ምስልሽ
ደሞም በገሞራው በአፍዴራው ንዳድ
በሚንቀለቀለው ኃያል የሳት ሰደድ
ውቤ የኔ አበባ ገፅሽ ይስበኛል
እምዬ ሃገሬ ምስልሽ ይታየኛል!
ተፃፈ በዴቭ(Mr. Trump)
ለመላክ: @getem_sourcebot
@getem
@getem
Dagmawi Dagmawi
በጠዋት...
በመስኮቴ በኩል አጮልቄ አያለሁ...
ከቤቴ ፊትለፊት ~ ባለች በጠባብ መንገድ ~ ሰዎች ይጎርፋሉ
ብዙ ተረከዞች ይመላለሳሉ!
ፍልቅልቅ ሚስቲቱን በክንዱ እንዳቀፈ
አይን አይኗን እያየ ያ ሰውዬ አለፈ!
...
ከቤቱ ተኝቶ ሰአት ያለፈበት ሰነፍ ሰራተኛ...
በጠባቧ መንገድ ሄደ እየከነፈ
ኮቱን አወላግዶ በበሬ ጋ አለፈ!
...
ያቻትና አለፈች...
ሽቶዋ ሰፈሩን ለጉድ የሚያውደው
ወንድ አዳሙ ሁሉ በፍቅሯ የሚያብደው
አለፈች በረረች...
በሩቁ እያየኋት ከአይኔ ተሰወረች!
...
ህፃናት አለፉ እየተሯሯጡ
አዛውቶች ሄዱ በእድሜ የጎበጡ!
...
እኔ እንዳጮለኩኝ ቀኑ ማታ ሆነ...
ጠዋት ያየኋቸው በሌሊት የወጡ
በዛው ጎዳና ላይ ሁሉም ሄደው መጡ!
መምጣት ብቻ አይደለም ወደየቤታቸው ሄደው ተሸሸጉ!
ጎዳናው ፀጥ አለ ~ ሁካታው አለቀ
ከፀጥታው መሀል ~ ጥያቄ እየመጣ ልቤ ላይ ወደቀ!
...
ያየኸው ሰው ሁሉ በዚህ ጎዳና ላይ እንዲህ ሲመላለስ
ሁሉም ከሄደበት ወደየማደሪያው በግዜ ሲመለስ
እሷ ወደየት ቀረች?
እመጣለሁ ብላህ ወደየት ተሰወረች?
...
አጮልቄ እያየሁ በመስኮቴ በኩል
በባዶ መሬት ላይ እርምጃሽን ስስል!
ቀን የነበረው ቀን ጨለማ ወረሰው...
ጎዳናው ፀጥ አለ ~ ሁካታው አለቀ
ከፀጥታው መሀል ~ ጥያቄ እየመጣ ልቤ ላይ ወደቀ!
[Dagmawi Dagmawi]
...
(ጥበብ ጠራችን የሚሉ ሰዎችን አንጋፋም ብለን እንጂ እንግጠም
ካልን እኮ እንገጥማለን )
@getem
@getem
@lula_al_greeko
በጠዋት...
በመስኮቴ በኩል አጮልቄ አያለሁ...
ከቤቴ ፊትለፊት ~ ባለች በጠባብ መንገድ ~ ሰዎች ይጎርፋሉ
ብዙ ተረከዞች ይመላለሳሉ!
ፍልቅልቅ ሚስቲቱን በክንዱ እንዳቀፈ
አይን አይኗን እያየ ያ ሰውዬ አለፈ!
...
ከቤቱ ተኝቶ ሰአት ያለፈበት ሰነፍ ሰራተኛ...
በጠባቧ መንገድ ሄደ እየከነፈ
ኮቱን አወላግዶ በበሬ ጋ አለፈ!
...
ያቻትና አለፈች...
ሽቶዋ ሰፈሩን ለጉድ የሚያውደው
ወንድ አዳሙ ሁሉ በፍቅሯ የሚያብደው
አለፈች በረረች...
በሩቁ እያየኋት ከአይኔ ተሰወረች!
...
ህፃናት አለፉ እየተሯሯጡ
አዛውቶች ሄዱ በእድሜ የጎበጡ!
...
እኔ እንዳጮለኩኝ ቀኑ ማታ ሆነ...
ጠዋት ያየኋቸው በሌሊት የወጡ
በዛው ጎዳና ላይ ሁሉም ሄደው መጡ!
መምጣት ብቻ አይደለም ወደየቤታቸው ሄደው ተሸሸጉ!
ጎዳናው ፀጥ አለ ~ ሁካታው አለቀ
ከፀጥታው መሀል ~ ጥያቄ እየመጣ ልቤ ላይ ወደቀ!
...
ያየኸው ሰው ሁሉ በዚህ ጎዳና ላይ እንዲህ ሲመላለስ
ሁሉም ከሄደበት ወደየማደሪያው በግዜ ሲመለስ
እሷ ወደየት ቀረች?
እመጣለሁ ብላህ ወደየት ተሰወረች?
...
አጮልቄ እያየሁ በመስኮቴ በኩል
በባዶ መሬት ላይ እርምጃሽን ስስል!
ቀን የነበረው ቀን ጨለማ ወረሰው...
ጎዳናው ፀጥ አለ ~ ሁካታው አለቀ
ከፀጥታው መሀል ~ ጥያቄ እየመጣ ልቤ ላይ ወደቀ!
[Dagmawi Dagmawi]
...
(ጥበብ ጠራችን የሚሉ ሰዎችን አንጋፋም ብለን እንጂ እንግጠም
ካልን እኮ እንገጥማለን )
@getem
@getem
@lula_al_greeko
©ዮሴፍ ብርሃን
ስስምሽ ከንፈርሽን
**
የዛን እለት ማታ፣
ከንፈርሽን ስስም፣
የተሰማኝ ደስታ፣
መግለጽ ሁሉ አልችልም፣
በቃላት ጋጋታ፣
ብቻ አልረሳዉም፣
የልቤን ትርታ፣
እና
የሳምኩሽን ቦታ፡፡
በቀኝ እጀ አዉሮፓን፣
በግራየ አፍሪቃን፣
የያዝኩ እስኪመስለኝ፣
በእልፍ አእላፍ ደስታ፣
ሲያራጀኝ ሲያቃጀኝ፣
የዛን እለት ማታ፣
ስስምሽ ከንፈርሽን፣
ጨረቃዋ በርታ፣
ባላሰብኩት ቅጽበት፣
አለሜ ሲሞላ፣
በገሀድ አየሁት፣
ፍቅርሽን ቀመስኩት፣
ከንፈርሽን መጠጥኩት፡፡
የዛን እለት ማታ፣
ከወሬ ያለፈ፣
ማያዉቀዉ ከንፈሬ፣
ከዉብ ከንፈሮችሽ፣
ሳቀርበዉ ደፍሬ፣
ያ ያንቀጠቀጠኝ፣
ብርዱ ከኔ ራቀ፣
መላ አካሌ ሞቀ፣
ፍቅራችን ደመቀ፡፡
የዛን እለት ማታ፣
በቅዱስዋ ምሽት፣
አምላኬን ለመንኩት፣
በግልጽ ባይገባኝም፣
ምን እንደጠየኩት፣
ብቻ ተዐምር ፈጥሮ፣
ሳይጎዳ ማንንም፣
አንቺን የኔ አድርጎሽ፣
ከህመሜ እንዳገግም፡፡
እንደዛ እለት ማታ፣
ከንፈርሽን ስስም፣
ጉንጮችሽን ስስም፣
ግንባርሽን ስስም፣
አንገትሽን ስስም፣
የኔ ብቻ ሆነሽ፣
እንድንኖር ዘላለም፡፡
**
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ስስምሽ ከንፈርሽን
**
የዛን እለት ማታ፣
ከንፈርሽን ስስም፣
የተሰማኝ ደስታ፣
መግለጽ ሁሉ አልችልም፣
በቃላት ጋጋታ፣
ብቻ አልረሳዉም፣
የልቤን ትርታ፣
እና
የሳምኩሽን ቦታ፡፡
በቀኝ እጀ አዉሮፓን፣
በግራየ አፍሪቃን፣
የያዝኩ እስኪመስለኝ፣
በእልፍ አእላፍ ደስታ፣
ሲያራጀኝ ሲያቃጀኝ፣
የዛን እለት ማታ፣
ስስምሽ ከንፈርሽን፣
ጨረቃዋ በርታ፣
ባላሰብኩት ቅጽበት፣
አለሜ ሲሞላ፣
በገሀድ አየሁት፣
ፍቅርሽን ቀመስኩት፣
ከንፈርሽን መጠጥኩት፡፡
የዛን እለት ማታ፣
ከወሬ ያለፈ፣
ማያዉቀዉ ከንፈሬ፣
ከዉብ ከንፈሮችሽ፣
ሳቀርበዉ ደፍሬ፣
ያ ያንቀጠቀጠኝ፣
ብርዱ ከኔ ራቀ፣
መላ አካሌ ሞቀ፣
ፍቅራችን ደመቀ፡፡
የዛን እለት ማታ፣
በቅዱስዋ ምሽት፣
አምላኬን ለመንኩት፣
በግልጽ ባይገባኝም፣
ምን እንደጠየኩት፣
ብቻ ተዐምር ፈጥሮ፣
ሳይጎዳ ማንንም፣
አንቺን የኔ አድርጎሽ፣
ከህመሜ እንዳገግም፡፡
እንደዛ እለት ማታ፣
ከንፈርሽን ስስም፣
ጉንጮችሽን ስስም፣
ግንባርሽን ስስም፣
አንገትሽን ስስም፣
የኔ ብቻ ሆነሽ፣
እንድንኖር ዘላለም፡፡
**
@getem
@getem
@lula_al_greeko
# ኑ_እውሸት_እንስራ !
-
ዘጠኝ ቁና ውሸት
ከአንድ ቁና እውነት
አሙቀን አቅልጠን
ቀይጠን አላቁጠን
በተዋበ ተንኮል በረቀቀ ሴራ
ኑ! እውሸት እንስራ!
-
ቅጥፈት ነው እንዳይሉ፤
የእውነት መአዛ ያውዳል በሩቁ
ሀቅም ነው እንዳይሉ፤
መጠርጠር አይቀርም እያደር ሲነቁ!
-
እስከ ጊዜው ድረስ ...
እስኪተላለቁ እርስ በ'ርስ ተጋጭተው
ወይ እስኪያስተውሉ ከሰመመን ነቅተው ...
-
ከጓዳቸው ገብተን
የቻልነውን በልተን
ቀሪውን ሸክፈን አርገን በስልቻ
እንጓዝ በስውር እንሂድ ለብቻ
በጊዜ እናምልጥ እንምጠቅ እንብረር፤
አሻራ ሳንተው ...
ክንፋቸውን ሰርቀን ፥ ከአይን እንሰወር!
-
-
ዘጠኝ ቁና ውሸት
ከአንድ ቁና እውነት
አሙቀን አቅልጠን
ቀይጠን አላቁጠን
በተዋበ ተንኮል በረቀቀ ሴራ
ኑ! እውሸት እንስራ!!
--------//--------
(✍ በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@lula_al_greeko
-
ዘጠኝ ቁና ውሸት
ከአንድ ቁና እውነት
አሙቀን አቅልጠን
ቀይጠን አላቁጠን
በተዋበ ተንኮል በረቀቀ ሴራ
ኑ! እውሸት እንስራ!
-
ቅጥፈት ነው እንዳይሉ፤
የእውነት መአዛ ያውዳል በሩቁ
ሀቅም ነው እንዳይሉ፤
መጠርጠር አይቀርም እያደር ሲነቁ!
-
እስከ ጊዜው ድረስ ...
እስኪተላለቁ እርስ በ'ርስ ተጋጭተው
ወይ እስኪያስተውሉ ከሰመመን ነቅተው ...
-
ከጓዳቸው ገብተን
የቻልነውን በልተን
ቀሪውን ሸክፈን አርገን በስልቻ
እንጓዝ በስውር እንሂድ ለብቻ
በጊዜ እናምልጥ እንምጠቅ እንብረር፤
አሻራ ሳንተው ...
ክንፋቸውን ሰርቀን ፥ ከአይን እንሰወር!
-
-
ዘጠኝ ቁና ውሸት
ከአንድ ቁና እውነት
አሙቀን አቅልጠን
ቀይጠን አላቁጠን
በተዋበ ተንኮል በረቀቀ ሴራ
ኑ! እውሸት እንስራ!!
--------//--------
(✍ በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ብቸኝነት !
/ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም/
——–
ቀኑ ተሰናብቷል
ጨለማው በርትቷል
ጨረቃ የት ጠፋች?
ምን ሆኑ ኮከቦች?
ጅቦች አይፈነጩ
ውሾች አይንጫጩ፡፡
ጨለማው ፍጹም ነው
ነፋስ ጭራሽ አይነፍስ
ዛፍ አይወዛወዝ አንድ ወፍ አይላወስ
ሁሉም ፀጥ
በያለበት ለጥ፡፡
ሰው ሁሉ ምን ነካው?
ድምፁ እንዲህ የጠፋው?
እኔንስ ምን ነካኝ?
እንቅልፍ የማይወስደኝ?
እኔ ብቻዬን ነኝ በዚህ ደረቅ ውድቅት፤
ልቤ እየቃተተ ጠልቶ ብቸኝነት፡፡
ሰው አለወይ ባገር?
ማረፊያ ለፍቅር?
ፈላጊና፤ ተፈላጊ ሁሉ
ቀናው ወይ በሙሉ?
የቀረ የለም ወይ በዓለም አለኔ
በምኞት ኩነኔ?
እኔ እንደዚህ ስዋኝ ባሳብ በትካዜ
የት ይሆን ያለሽው አንቺ ይህን ግዜ
ምን ታደርጊ ይሆን?
እንገናኝ ይሆን?
መች ይሆን ዕለቱ?
መች ይሆን ሰዓቱ?
የትስ ይሆን ቦታው?
እንዴት ይሆን እውቂያው?
እጠብቅሻለሁ ልቤን እየታዘዝሁ፤
አትቅሪ፤ ፈልጊኝ፤ እፈልግሻለሁ፡፡
@getem
@getem
@Poemempire
———
/ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም/
——–
ቀኑ ተሰናብቷል
ጨለማው በርትቷል
ጨረቃ የት ጠፋች?
ምን ሆኑ ኮከቦች?
ጅቦች አይፈነጩ
ውሾች አይንጫጩ፡፡
ጨለማው ፍጹም ነው
ነፋስ ጭራሽ አይነፍስ
ዛፍ አይወዛወዝ አንድ ወፍ አይላወስ
ሁሉም ፀጥ
በያለበት ለጥ፡፡
ሰው ሁሉ ምን ነካው?
ድምፁ እንዲህ የጠፋው?
እኔንስ ምን ነካኝ?
እንቅልፍ የማይወስደኝ?
እኔ ብቻዬን ነኝ በዚህ ደረቅ ውድቅት፤
ልቤ እየቃተተ ጠልቶ ብቸኝነት፡፡
ሰው አለወይ ባገር?
ማረፊያ ለፍቅር?
ፈላጊና፤ ተፈላጊ ሁሉ
ቀናው ወይ በሙሉ?
የቀረ የለም ወይ በዓለም አለኔ
በምኞት ኩነኔ?
እኔ እንደዚህ ስዋኝ ባሳብ በትካዜ
የት ይሆን ያለሽው አንቺ ይህን ግዜ
ምን ታደርጊ ይሆን?
እንገናኝ ይሆን?
መች ይሆን ዕለቱ?
መች ይሆን ሰዓቱ?
የትስ ይሆን ቦታው?
እንዴት ይሆን እውቂያው?
እጠብቅሻለሁ ልቤን እየታዘዝሁ፤
አትቅሪ፤ ፈልጊኝ፤ እፈልግሻለሁ፡፡
@getem
@getem
@Poemempire
———