ግጥም ብቻ 📘
64.3K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
©

ህልሜ ከ'ኔ ሸሽቶ
በአንቺ እንቅልፍ ውስጥ
ማድባት ከጀመረ፣
(እመኚኝ ልንገርሽ)
የስጋዬ ሳይሆን
የነፍሴ ቁልፍ ነው
ካንቺ ዘንድ የኖረ፣

(ምክንያቱም)
ህልሜ ነው መኖሬ
በሌሊት አለም ውስጥ
አንቺን የሚያሳየኝ፣
ከስጋዬ አልፎ
ነፍሴን ሚጎበኘኝ...
(ለዚህ ነው)
...///...
ሻሸመኔ

@getem
@getem
👍1
መዋደድ መፋቀር፣ ከንቱነት ነው ብላ
ጨዋ-ነኝ ባይዋ ሴት፣ ቀረች በነጠላ፡፡

(ሲታዛዚን ;P )

@getem
@getem
*ያችን ልጅ ንገርዋት*
(ሠለሞን ሣህለ)

እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልከ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በሉዋት

አወ እንዳገሬ ነዉ…
እንደ ምንጩ ጣእም እንደ አፈሩ ሽታ
ልጎንጭሽ የምላት…
ልዳብስሽ የምላት ጠዋትና ማታ
ለብሻት የምኖር…
እንደ ቀዩ ጃኖ እንደ ነጩ ኩታ
ጋቢዋ ነኝ እኔ…

ጠላት የተኮሰዉ ንፋስ እንዳይነካት
ሁለት ግዜ ዙሬ…
ወገቡዋ ላይ ያደርኩ የማርያም መቀነት

እንደ አገር አርጅታ…
እንደ አገር አዉግታ ደግሞ ተበሳጭታ
እድሜዉ ይሁን ንዴት ጸጉርዋን አሸብታ
አፋፉ ላይ ቁማ…ብቻዋን ቆዝማ
ድንገት ብታገኝዋት…

እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልክ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በልዋት
ንገሩልኝ ዘመድ ንገሩልኝ ወገን
እኔ በሱዋ ፍቅር እንዴት እንደምሆን

እንደተዋለበት ጤናዉን እንዳጣ
በጠላ አስተናግር በጥብጦ እንደጠጣ
ያስለፈልፈኛል ጩህ ጩህ ያሰኘኛል
የቀኑ ሳይበቃዉ ሌሊት ያስዞረኛል

ጎርፉን እጠጣለሁ አፈር እቅማለሁ
ጎርፉን እየጠጣሁ….ሃገሬን እላለሁ
ጨለጥኩዋት እላለሁ
አፈሩን እየቃምኩ….ሃገሬን እላለሁ
በላሁዋት እላለሁ
ጸጉሬን እነጫለሁ ልብሴን እቀዳለሁ
እንዳይሆን እንዳይሆን እንዳይሆን ሁኛለሁ ፤

እናም ያች የኔ…
የምጠብቃት ሴት የመጣች እንደሆን
መስከረምን አልፋ…
ጥቅምትን ተሸግራ ህዳሩ ሲታጠን

ገላየ ቆሽሾ አካላቴ ዝሎ
ገጼ ተጎሳቅሎ
ድንገት አልፋኝ ብትሄድ…
ፍቅሬ ተዘንግትዋት…
ማንነቴ ጠፍትዋት…

እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
እንዳገሩ ነበር የሚወድሽ በልዋት፡፡

@getem
@getem
@lula_al_greekO
እኔ እንዳልጠራ
(ለእዮብ ዘማርያም ለስምረት እና ለመጨረሻው ገጣሚ)

አልልህም ነገር ቶሎ ና፡ ቶሎ ና
አልሠራሁምና አንዲት ነገር ደህና
ቅርም አልልህም
ወዜና ጥረቴ ሁሉም ቢደመርም
የልፋቴ ዋጋ ደሞዝ ቢታሠብም
ዕዳዬን አይከፍልም
ግና ግን ጌታዬ ይቺ ነዳይ ነፍሴ ስጋ የበደላት
ካንተ ፍቅር በቀር የለም የሚክሣት
የፈተናው ገመድ ግዜ ያከረረው
ዘመን ያደለበው
አንተ ስትመጣልን ብጣሽ ነው ሚሆነው

ያን ግዜ ነው መፍራት
ስጋ ከነፍስ ጋር በአንድ እንዳልተሠፋ
አላቅም ይላታል ጥግ እየተጋፋ

አንተም ትመጣና
እርቃን የቀረችው ቅንጣቢ ነፍሴን
ገላልጣ ብታየው ሀፍረቴን ሀጥአቴን
ክርፋቴ ገፋፍቶህ ጥለህ ትሄዳለህ
ለፀዓዳ ቤቴ አትመጥንም ብለህ

ባትመጣ ደሞ
ይህቺ ምስኪን ነፍሴ አለም የበደላት
ዝንት አለም ልትኖር ነው ስጋዬ ሲገዛት
ስጋዬ ሲወቅጣት

የቱ ነው ሚሻለው
የቱ ነው ሚበጀው?

ብትመጣ
በህግ ያልተገዛ ባንተ ያልታመነ
ነፍሴ ተኮነነ
ብትቀር
ዘመን የጠበቀ ዘመን የዋለለ
ይመጣል እያለ
ሁልግዜ ሊኖር ነው ነፍስ እያቃጠለ

ወዳጄ
መምጣትህ ቅጣት ነው
መቅረትህም ሞት ነው
እኛ ማለት ላንተ በደረቱ ሚድህ እንፉቅቅ ልጅ ነንና
ውስጡ ያልበሰለ ጉልበቱ ያልጠና
መምጣትህም መልካም መቅረትህም ደህና
ፍቃድህ ነንና፡፡

ግና ግን ጌታዬ የሀጥአቴን ጭቃ በእንባ ሳላጠራ
እኔ እንዳልጠራ፡፡

አንተ እንደፈለክ


@getem
@getem
@inluvwidart
--የሴት ልጅ ያሉኛል አዎ የሴት ልጅ ነኝ--

አዎ የሴት ልጅ ነኝ የውዲቷ እናቴ
ከግማሽ አካልዋ ተቆርጦዋል እትብቴ

አዎ የሴት ልጅ ነኝ የኔ አንድ ውዲቷ
ጡት የምታጠባ በታጠፈ አንጀቷ

ያንስብኛል እንዴ የሴት ልጅ ለመባል
የአንድ ቀን ጭነቅዋ ምጧ አኮ ያበቃል

እንዴት አልጠራ አልባል የሴት ልጂ
ውርደት አኮ አያደለም ክብር ቢሆን እንጂ

እንደሻማ ቀልታ ብርሀን ለሆነች
የሷን ኑሮ ትታ ለኔ እየኖረች
እኔን ለማቃናት እሷ አየጎበጠች

ለራሷ ታርዛ እኔን ያለበዘች
እርጥቡ ደረቁ ለ፡ሁሉ ሲነድባት
ዋጥ አድርጋ ችላ ሰው እንድሆንላት

ለዚህ ያበቃችኝ እንድዉል ከሰው ተራ
ክብር ማንነቴ ናት በስሟ ልጠራ


ምንጭ: የግጥም አምባ
@getem
@getem
✧✧✧ ብዙ ተባዙ

የእናትነት እጣ፣ ያባትነት ውርሱን
የፍጥረትን ምስጢር፣ የቤተሰብ ቅርሱን
የትውልድ አደራ፣ የብዙ ተባዙን፤
ለአእምሮህ ሳይሆን ባሻው ለሚከንፈው
ለልቦናሽ ሳይሆን ስርአት ለሚገድፈው
ለፈቃድህ ሳይሆን እብደት ለሚለክፈው
ለህሊናሽ ሳይሆን ዓለም ለሚያጎድፈው፤
ሰጠው ለሽፍደትህ ጦር ለማይመልሰው
ለመግነጢስ ገላሽ ጾም ለሚያስፈርሰው
ጻፈው በገበናሽ በጉያሽ ትኩሳት
በማትሟገተው የጭንህ ዲን እሳት፤
በሰጣችሁ ርስት በወጉ አንድትረቡ
በሴስ አቆራኝቶ በወሲብ ቀለቡ
ምድርን በሰው ሞላት በኪነጥበቡ።

ፋሲል ይትባረክ

@getem
@getem
@getem
የሰማይ ቤት ግሮሰሪ
(አሱ እንደፃፈዉ)
.
.
"ጨረቃ" ምንላት
ግሮሰሪ ቤት ናት!!!
"ሰማይ" ለምንለው ፣ ቀውጢ ከተማ
ሥራ ምትጀምረው ፣ሲሆን ነው ጨለማ!!!
..................................................
በር እንደከፈተች ፣ አብረው የሚወጡ
ከዋክብት ደሞ...
ሰካራሞች ናቸው ፣ እሷ ጋ ሚጠጡ!!!
*********************
በጣም የሰከረው...
ከሰማይ ፈጥፍጦ ፣ ራሱን ሲገድል
"ተወርዋሪ ኮከብ" ..
ማለት ነው የኛ እድል!!!
********************
ተወርዋሪ ጠርሙስ ሊሆንም ይችላል!
ማን ያውቃል?

@getem
1
👆👆👆 ገጣሚ (በላይ በቀለ ወያ)
❀ግጥም እና ግጣም ...

ኣውቃለሁ
የግጥምሽ መድፊያ ፣ የቅኔሽ መጣጣም
ስምረቱ ድንቅ ነው ፣ ቀልብ ይቀማል በጣም፡፡
#እኔን_የገረመኝ ...
ስንኝ ለመቋጠር ፣ የደረደሩት ቃል
ቤትና አጥር ዘሎ ፣ እንዴት ልብ ይመታል
Ezana Mesfin

@getem
@getem
@lula_al_greeko
ይህ ጠቅላይ ሚኒስቴር ፣ ፍቅሩ ያሸንፋል
እሰሩት ራሱን !!!
የመለስን ራዕይ ፣ ለምን ያንሻፍፋል

Belay Bekele Weya

@getem
@getem
@getem
ተኛ አትበዪኝ ፣ አልተኛም እንብየው
የስተዛሬ ህልሜን
አብይ ሲያስፈታው ፣ ነቅቼ ሳላየው

(በላይ በቀለ ወያ)

@getem
@getem
👍1
የፍቅር ቃል
(ዳጊ)

ድሮም አረማመድ አካሃድ አትችል፣

ታየች በጎዳና ወልቸም ወልቸም ስትል...

መሸከም ቢከብዳት አንዲት የፍቅር ቃል።




@getem
@getem
@lula_al_greeko
..ዝምታዮ..

ጉርምርምታው ሲፋተግ
ነፋሱ ሲያፋሽክ
ለመርዶ ነጋሪ
ለጧሪ ቀባሪ
ያሰኘው እሪታ
ፀሀይ ያለወትሮ በስተምዕራብ ወጥታ
በግማሽ ተገምሶ
ጨረቃ ደም ለብሶ
የሰማዩ መብረቅ
ጎሚ እንዳለው መልህቅ
ላንዴ ተወርውሮ ከምድር ሲጣበቅ
ደመናው ተቀዶ ዝናም ሲጥለቀለቅ
ውሽንፍሩ አይሎ ነፍሴ ስትል ጭንቅ
ጣራዮ አፍስሶ
ኮርኒሴ እርሶ
ጠብ ጠብ የሚለው
ከወለሉ ሲደርስ ጧ ብሎ ሚወድቀው
ላለቅሰው ፈልጌ ስመኘው ያጣሁት
የኔ እምባ መሰለኝ
ሰዉ ያልተረዳልኝ
ዝምታ ሸፍኖት ስቅ ስቅ የሚለኝ
.ዝ
.ም
.ም
.ም
ህመሜ በርትቶ ሳላገግም በልክ
ይማርህ የሚል ሰው ኩርማን እንኳ ሚልክ
በሌለበት መንደር ጩኸት ይሰማኛል
አውቀው የመሰለኝ ድምጹ ይጠራኛል
መልስ ችዮ እንዳልሰጥ ሰቅዞ ይዞኛል
በውሸት ድንበር ላይ ለእውነት መታገል
ወንጀለኛነት ነው ያስከትላል ገድል
እንደተነቀለ ስሩ እንደጠፋ ዛፍ
ዝምታ ይሻላል ተኝቶ መንዘፍዘፍ



ቅጥ የሌለው እበለት
ወዲያ ሲበሸከት
አላስችልህ ብሎ ለማረቅ የቃጣኝ
የእውነት አስተኔው መደማመጥ መስሎኝ
በነሱ አረዳድ ክፋት ሆኖ ቢገኝ
ልሟገታቸው ስል.......
ህመሙ ጠናና ቆበሬ ደፈቀኝ
ሞት አፋፍ ላይ ሆኘ ከሩቅ ለሚጠራኝ
ዝምታዮ በዝቶ ይሄው አስገመተኝ
ለንቶፈንቶ ወሬ አፉ የማያርፈው
ለዝምታ ጊዜ ሁሉም ምክንያት አለው
ብላችሁ ንገሩት ቢረዳልኝ ቢያውቀው



(ማሜ)


ግጥም ለማላክም ሆነ ለ አስታየት
👉@Getem_sourcebot

@getem
@getem
@lula_al_greeko
የ ገራፊ ምሬት


እንግዲህ አንተ ፍረድ
ገርፋችሁ ረገጣችሁ ፣ ኑሩ ያልከን ጌታ
ምን ሰርተን እንብላ
እኛ ያሰርነውን ፣ አብይ እየፈታ
።።።።።።
በላይ በቀለ ወያ

ለአስታየት @getem_sourcebot

@getem
@getem
ጠ-ረ*ጠ-ር*-ኩ-ሽ(ልዑል ሀይሌ)

ንፋሱ ገልቦሻል
ምን አስለምደሽው?
ፀሐዩን ስታዪ
ለምን ነው ልብስሽን ቶሎ ያወለቅሽው?
ምነው መራቆትሽ
ለወጪ ወራጁ ላማተረሽ ሁሉ
አሁን ጠረጠርኩሽ
የወጡ የገቡ አስወለቅናት ሲሉ

15-09-10

ለመላክ: @getem_sourcebot

@getem
@getem
"ጥጋብ እና ሚዛን"
እዛ ማዶ ጋራ፣
ምን ይንኮሻኮሻል፣
ፍየል ተደብቆ፣
ያንን ቦርጩን ያሻል፣
እዚህ ማዶ ዋሻ፣
ዝምታው በርትቷል፣
በጉ ተደብቆ፣
ምራቁን ይውጣል፣
የሚለውን ቀመር፣
የበጉን ረሀብ፣
የፍየሉን ሲሳይ፣
ይሄኛው ልዩነት፣
ለምን መጣ ብለን፣
መነሻውን ስናይ፣
ፍየል ማለት ተግባር፣
ጎርሶ አጣጥሞ፣
ጠግቦ የሚያገሳ፣
በግ ማለት አባባል፣
ለህሊናው ብሎ፣
ሆዱን የሚረሳ፣
የሚል ተረት ይዘን፣
ለከሰረ ውጤት፣
ነፍስን ከስጋ ጋር፣
ከምናወዳድር፣
እስኪ ምን አለበት፣
ህሊናም ቅን ሆኖ፣
ሆድም ጠግቦ ቢያድር፣
ብለን ስንጠይቅ፣
የሚሰራው ጠፍቶ፣
የተፈጥሮን ሒሳብ፣
በግ በደግነቱ፣
ለህሊናው ብሎ፣
ሆዱን እየረሳ፣
ምግብ ትቶ ሲራብ፣
ቆጡን እያሳዩ፣
ፍየሎች ወሰዱት፣
የብብቱን ጥጋብ፡፡

መርዕድ ተስፋዬ

03/06/2008ዓ.ም

👉👉@getem_sourcebot

@getem
@getem
👍1
አንቆቅልሽ?

ሙሉ ናት ሙሉ ናት ፡ ስትባል የኖረች
ሁሉም የሚወዷት ፡ አንድ አካል ነበረች

እንቆቅልሽ? ብላ ፊቷን ታዞርና፡
ምን አውቅልሽ ስላት፡
ጥላኝ ትሄዳለች ፡ መልሳ እንደገና

እንዲሁ ብትሄድ ፡ መልካም በነበረ
ዙሩን አጠማዛው ፡ ሆኗል የከረረ፡፡

ደግሞ ወዳጅ አላት ፡ የምትለው ጊዜ
ቦታና ሁኔታን ፡ የያዘው አባዜ

አነኚህ ፍጥረቶች ፡ አብረው ካልገጠሙ
ሀገር ስትሰጣት ፡ ቆመው ካልታደሙ፡

የሰጠሃትን ሀገር ፡ ብታስገባ ከእጇ፡
ሁሉንም በእጇ ፡ ብታደርግ በደጇ፡

መልስ የለውም ብላ ፡ ስትሰጥ ቀጠሮ
ጊዜና ሁኔታ ቦታም እስኪመጣ ትጠብቃታለህ፡
ሁለተኛ ዞሮ፡፡

By SaMaL Afrique


@getem
@getem
@samalafrique
'ካንሰር' ፍቅር(ልዑል ሀይሌ)

አጭር ነኝ አጭር ነሽ
ቁመት የምንለምን በነጋ በጠባ
ቀጭን ነኝ ቀጭን ነሽ
ስጋ የናፈቀን ካጥንት የሚጠጋ
.
ዓይን የለኝ ዓይን የለሽ
ህልሜንም አታይው ህልምሽንም አላይ
ጥርስ የለኝ ጥርስ የለሽ
ደስታዬን ማትቀጂ
ማልቀዳ ደስታሽን ከአንቺነትሽ ሰማይ
.
እግር የለኝ እግር የለሽ
የሚራመድ ላንቺ የሚራመድ ለኔ
እጅ የለኝ እጅ የለሽ
ስላንቺ የሚፅፍ
ስለኔ የሚዘርፍ ነፍስ የሞላው ቅኔ
.
መለያየት 'ካንሰር'
እጅ እግሬን ጥርስ ዓይኔን
ሰውነቴን ሁሉ እየቆራረጠ
ስላንቺ ያኖርኩት
ግዝፈ-አካሌን ወስዶ ለሌላ እየሰጠ
.
ይኸው ቀሪ ዕድሜዬን
እየቆጠርኩኝ ነው ነይ አብረን እንቁጠር
ወትሮም አንድ አይደለን
ለ -የ-ቅል ፍቅር ነው እኛ ስንፈጠር

23-09-10

@getem
@getem
#መስታወት_ልግዛልሽ
:
:
መቼስ በዚች ዓለም
አምናለው አልክድም
የሰው ፍፁም የለም።


ሰው ስህተት ይሰራል
ከዚያም ይታረማል
ከስ'ተቱ ይማራል።


ያንቺ ግን ፍቅርዬ መሳሳትሽ ወዛ
በ'ኔና አንቺ መሀል ምንም ሰው ሳይበዛ
እራስሽ የጣድሺው ጎመንም ጠነዛ።


ከሰራሺው ስህተት ትማሪያለሽ ብዬ...
...በተስፋ ስጠብቅ ወይ ዛሬ ወይ ነገ
እንኳን ልትማሪ ጥፋትሽ ስር ሰዶ...
ቅርንጫፍ አውጥቶ ይባሱን አደገ።


እናምልሽ ፍቅሬ...
ትናንት በመቅረዜ ደቂቅ ተስፋን ይዤ
ሁሉን ለ አምላክ ጥዬ እሱን ተመርኩዤ
አጣጥቤ ልኬሽ ጨቅይተሽ ስትመጪ
ፍቅርሽ እንዳይርቀኝ ከልቤ እንዳትወጪ
መውደድ አስገድዶኝ ዳግም እንደገና
አምጥቼልሽ ነበር ውሀና ሳሙና።


ዛሬ ግን ታከተኝ ዛሬማ በቅቶኛል
ጭቃሽን ለማንፃት ውሀ ምቀዳበት...
ጉልበቴም ከድቶኛል።


እናም ካሁን ወዲህ ለኔም እንዲቀለኝ...
...ላንቺም እንዲበጅሽ
በሳሙና ፈንታ ጭቃሽን እንድታይ...
...መስታወት ልግዛልሽ።

#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ @Henokbirhanu

@getem
@getem
አፍቄሜሌፅ (የፍቅር ቃል እድሜ)
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ፍቅርን ያህል ነገር
ተሸክሜ ስኖር ፣ በልቤ ትከሻ
"ቃል አጠረኝ" የሚል
ቃል ካፌ አይወጣም ፣ ላወድስሽ ስሻ።
እንደውም ሳፈቅር ፣ ቃል ነው የሚተርፈኝ
እንኳንስ ቃል ሊያጥረኝ
ሁሉ ያጥርብኛል
በልብሽ ቅርፅ ውስጥ ፣ መውደድሽ ሲያገዝፈኝ
ቃልም ነው በመንፈስ
ልሳን እየሰጠ ፣ የሚያስለፈልፈኝ ።
ሻምጵራ ቅራንጳ
ወዘ ትሩሩጳ
አፍረንትረን ደስቴ
ፄፃቱ ጳፃቴ
ወኡዝ ሀአሪከ
አዝወረ ነባከ
ፊፀአ ነአቱ
ጀነወ ርዕቱ
ናፃ ፄላሟሜ
እናልሽ አለሜ
አዲስ ፊደል ባልቀርፅ ፣ አዲስ ቃል ቀምሜ
ትርጉሙ እንዲገባሽ
የልሳን ቃሎቼን ፣ በአንዲት ቃል ተርጉሜ
"አፍቄሜሌፅ" አልኩሽ!
አፍቄሜሌፅ ማለት ፣ በኔ ትርጓሜ
ሁሉ ያጥራል እንጂ
አያጥርም ማለት ነው ፣ የፍቅር ቃል እድሜ።
።።።።።።።
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ሰፊ ያልሁት አለም ፣ ባንድ እርምጃ አለቀ
ሳልሄደው ሚደክመኝ...
ተራራና ጋራው ፣ ከግሬ ስር ጠለቀ።
"ሩቅ" ያልሁት ሰማይ..
ሩቅ የሚመስለኝ ፣ ነካሁት በስንዝር
ጨረቃና ፀሀይ....
ከኮከብ ያንሳሉ ፣ ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር።
.......................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
ንጉስን ከዙፋን ፣ ማርከው የሚያወርዱ
የሀያላንን አቅም ፣ በጥቅሻ ሚያርዱ
ቆነጃጅት ሴቶች ...
"ቃል አጠረኝ" በሚል ቃላት የተሞሉ
ከፍቅርሽ ግዝፈት ስር..
ቃል ተገኝቶላቸው ፣ "ፋንጋዎች" ተባሉ።
.........................................
ሳፈቅርሽ ይህ ሆነ...
"ቃል አጠረኝ "በሚል...
ባፍቃሪ አንደበት ፣ ቃል ተትረፈረፈ
ሁሉን አሳንሶ...
በልቡ ቅርፅ ውስጥ ፣ ፍቅሩን አገዘፈ
አለሙን ሰርዞ ፣ ፍቅሩን ብቻ ፃፈ!!!
..........................................
ሳፈቅርሽ ይህን አልኩ...
ፍቅርን ተሸክሞ ፣ የሚኖር ልቦና
ሁሉም ከፍቅርሽ ስር ፣ መሆኑን አውቅና
አንቺን ለማወደስ .፣..እኔም ቃል ያጥረኛል
"ቃል አጠረኝ "ማለት...
ቃል እንደሆነ ግን ፣ ፍቅርሽ ይነግረኛል!!!
ሻምጵራ ቅራንጳ
ወዘ ትሩሩጳ
አፍረንትረን ደስቴ
ፄፃቱ ጳፃቴ
ወኡዝ ሀአሪከ
አዝወረ ነባከ
ፊፀአ ነአቱ
ጀነወ ርዕቱ
ናፃ ፄላሟሜ
እናልሽ አለሜ
አንደበት ዝም ቢል
ዝም አይልም አይኔ ፣ ዝም አይልም ጥርሴ
ቃል አለው ጆሮዬ ፣ ዝም ቢል ምላሴ።
ዝም አይልም እጄ ፣ ዝም አይልም እግሬ
እኔ ቃል ቢያጥረኝም
ሰማይና ምድሩ
ፈጣሪና ፍጡሩ
ለፍቅር ቃል አለው ፣ ይናገራል ፍቅሬ።
።።።።።
ትርጉም ብንሰጠው
ጥላቻ በራሱ ፣ ለፍቅር አለው ቋንቋ
"አፍቄሜሌፅ" አልኩሽ
የፍቅር ቃል እድሜ
ከዘላለም የሚያልፍ ፣ ዘላለም ነው በቃ።
ሀዘሩ ጣሪቃ
ሉፋሴ ጰኑቃ
ሪድዋ ሸዛጨ
አገቀ ጠየጨ

@getem
@getem
@lula_al_greeko
1
​​ጠቅላይ ሚኒስቴሩ የፃፉት ግጥም
(በላይ በቀለ ወያ)።።።።።

እነ ሀምሳ ብሮች...
እነ መቶ ብሮች ፣ ከኪሴ ሲጠፉ
እነ አስር ብሮች...
የማያልቅ ሰፌድ ፣ ዘላለም ሲሰፉ
እነ አምስት ብሮች...
ቡና እየለቀሙ ፣ ነግደው ሲያተርፉ
አንድ ብር ይስቃል!!!
።።።፣፣፣፣፣።።።፣፣፣፣፣፣፣፣፣።።።፣።።
የማያባራ ሳቅ ፣ የሚኖር ፈገግታ
እኔም ላይ ይታያል ፣ ያንድ ብር ሁኔታ
እንዲህ ያደርገኛል...
ያደጉ ካድሬዎች
ኢትዮጵያ አድጋለች ፣ ብለው ያሉኝ ለታ
የታሰሩን ብሮች?
የታሰሩን ሰዎች? እኔ ስንቱን ልፍታ?

@getem
@getem
👍21