*ያችን ልጅ ንገርዋት*
(ሠለሞን ሣህለ)
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልከ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በሉዋት
አወ እንዳገሬ ነዉ…
እንደ ምንጩ ጣእም እንደ አፈሩ ሽታ
ልጎንጭሽ የምላት…
ልዳብስሽ የምላት ጠዋትና ማታ
ለብሻት የምኖር…
እንደ ቀዩ ጃኖ እንደ ነጩ ኩታ
ጋቢዋ ነኝ እኔ…
ጠላት የተኮሰዉ ንፋስ እንዳይነካት
ሁለት ግዜ ዙሬ…
ወገቡዋ ላይ ያደርኩ የማርያም መቀነት
እንደ አገር አርጅታ…
እንደ አገር አዉግታ ደግሞ ተበሳጭታ
እድሜዉ ይሁን ንዴት ጸጉርዋን አሸብታ
አፋፉ ላይ ቁማ…ብቻዋን ቆዝማ
ድንገት ብታገኝዋት…
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልክ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በልዋት
ንገሩልኝ ዘመድ ንገሩልኝ ወገን
እኔ በሱዋ ፍቅር እንዴት እንደምሆን
እንደተዋለበት ጤናዉን እንዳጣ
በጠላ አስተናግር በጥብጦ እንደጠጣ
ያስለፈልፈኛል ጩህ ጩህ ያሰኘኛል
የቀኑ ሳይበቃዉ ሌሊት ያስዞረኛል
ጎርፉን እጠጣለሁ አፈር እቅማለሁ
ጎርፉን እየጠጣሁ….ሃገሬን እላለሁ
ጨለጥኩዋት እላለሁ
አፈሩን እየቃምኩ….ሃገሬን እላለሁ
በላሁዋት እላለሁ
ጸጉሬን እነጫለሁ ልብሴን እቀዳለሁ
እንዳይሆን እንዳይሆን እንዳይሆን ሁኛለሁ ፤
እናም ያች የኔ…
የምጠብቃት ሴት የመጣች እንደሆን
መስከረምን አልፋ…
ጥቅምትን ተሸግራ ህዳሩ ሲታጠን
ገላየ ቆሽሾ አካላቴ ዝሎ
ገጼ ተጎሳቅሎ
ድንገት አልፋኝ ብትሄድ…
ፍቅሬ ተዘንግትዋት…
ማንነቴ ጠፍትዋት…
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
እንዳገሩ ነበር የሚወድሽ በልዋት፡፡
@getem
@getem
@lula_al_greekO
(ሠለሞን ሣህለ)
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልከ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በሉዋት
አወ እንዳገሬ ነዉ…
እንደ ምንጩ ጣእም እንደ አፈሩ ሽታ
ልጎንጭሽ የምላት…
ልዳብስሽ የምላት ጠዋትና ማታ
ለብሻት የምኖር…
እንደ ቀዩ ጃኖ እንደ ነጩ ኩታ
ጋቢዋ ነኝ እኔ…
ጠላት የተኮሰዉ ንፋስ እንዳይነካት
ሁለት ግዜ ዙሬ…
ወገቡዋ ላይ ያደርኩ የማርያም መቀነት
እንደ አገር አርጅታ…
እንደ አገር አዉግታ ደግሞ ተበሳጭታ
እድሜዉ ይሁን ንዴት ጸጉርዋን አሸብታ
አፋፉ ላይ ቁማ…ብቻዋን ቆዝማ
ድንገት ብታገኝዋት…
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
ልክ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በልዋት
ንገሩልኝ ዘመድ ንገሩልኝ ወገን
እኔ በሱዋ ፍቅር እንዴት እንደምሆን
እንደተዋለበት ጤናዉን እንዳጣ
በጠላ አስተናግር በጥብጦ እንደጠጣ
ያስለፈልፈኛል ጩህ ጩህ ያሰኘኛል
የቀኑ ሳይበቃዉ ሌሊት ያስዞረኛል
ጎርፉን እጠጣለሁ አፈር እቅማለሁ
ጎርፉን እየጠጣሁ….ሃገሬን እላለሁ
ጨለጥኩዋት እላለሁ
አፈሩን እየቃምኩ….ሃገሬን እላለሁ
በላሁዋት እላለሁ
ጸጉሬን እነጫለሁ ልብሴን እቀዳለሁ
እንዳይሆን እንዳይሆን እንዳይሆን ሁኛለሁ ፤
እናም ያች የኔ…
የምጠብቃት ሴት የመጣች እንደሆን
መስከረምን አልፋ…
ጥቅምትን ተሸግራ ህዳሩ ሲታጠን
ገላየ ቆሽሾ አካላቴ ዝሎ
ገጼ ተጎሳቅሎ
ድንገት አልፋኝ ብትሄድ…
ፍቅሬ ተዘንግትዋት…
ማንነቴ ጠፍትዋት…
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያችን ልጅ ንገርዋት
እንዳገሩ ነበር የሚወድሽ በልዋት፡፡
@getem
@getem
@lula_al_greekO
እኔ እንዳልጠራ
(ለእዮብ ዘማርያም ለስምረት እና ለመጨረሻው ገጣሚ)
አልልህም ነገር ቶሎ ና፡ ቶሎ ና
አልሠራሁምና አንዲት ነገር ደህና
ቅርም አልልህም
ወዜና ጥረቴ ሁሉም ቢደመርም
የልፋቴ ዋጋ ደሞዝ ቢታሠብም
ዕዳዬን አይከፍልም
ግና ግን ጌታዬ ይቺ ነዳይ ነፍሴ ስጋ የበደላት
ካንተ ፍቅር በቀር የለም የሚክሣት
የፈተናው ገመድ ግዜ ያከረረው
ዘመን ያደለበው
አንተ ስትመጣልን ብጣሽ ነው ሚሆነው
ያን ግዜ ነው መፍራት
ስጋ ከነፍስ ጋር በአንድ እንዳልተሠፋ
አላቅም ይላታል ጥግ እየተጋፋ
አንተም ትመጣና
እርቃን የቀረችው ቅንጣቢ ነፍሴን
ገላልጣ ብታየው ሀፍረቴን ሀጥአቴን
ክርፋቴ ገፋፍቶህ ጥለህ ትሄዳለህ
ለፀዓዳ ቤቴ አትመጥንም ብለህ
ባትመጣ ደሞ
ይህቺ ምስኪን ነፍሴ አለም የበደላት
ዝንት አለም ልትኖር ነው ስጋዬ ሲገዛት
ስጋዬ ሲወቅጣት
የቱ ነው ሚሻለው
የቱ ነው ሚበጀው?
ብትመጣ
በህግ ያልተገዛ ባንተ ያልታመነ
ነፍሴ ተኮነነ
ብትቀር
ዘመን የጠበቀ ዘመን የዋለለ
ይመጣል እያለ
ሁልግዜ ሊኖር ነው ነፍስ እያቃጠለ
ወዳጄ
መምጣትህ ቅጣት ነው
መቅረትህም ሞት ነው
እኛ ማለት ላንተ በደረቱ ሚድህ እንፉቅቅ ልጅ ነንና
ውስጡ ያልበሰለ ጉልበቱ ያልጠና
መምጣትህም መልካም መቅረትህም ደህና
ፍቃድህ ነንና፡፡
ግና ግን ጌታዬ የሀጥአቴን ጭቃ በእንባ ሳላጠራ
እኔ እንዳልጠራ፡፡
አንተ እንደፈለክ
@getem
@getem
@inluvwidart
(ለእዮብ ዘማርያም ለስምረት እና ለመጨረሻው ገጣሚ)
አልልህም ነገር ቶሎ ና፡ ቶሎ ና
አልሠራሁምና አንዲት ነገር ደህና
ቅርም አልልህም
ወዜና ጥረቴ ሁሉም ቢደመርም
የልፋቴ ዋጋ ደሞዝ ቢታሠብም
ዕዳዬን አይከፍልም
ግና ግን ጌታዬ ይቺ ነዳይ ነፍሴ ስጋ የበደላት
ካንተ ፍቅር በቀር የለም የሚክሣት
የፈተናው ገመድ ግዜ ያከረረው
ዘመን ያደለበው
አንተ ስትመጣልን ብጣሽ ነው ሚሆነው
ያን ግዜ ነው መፍራት
ስጋ ከነፍስ ጋር በአንድ እንዳልተሠፋ
አላቅም ይላታል ጥግ እየተጋፋ
አንተም ትመጣና
እርቃን የቀረችው ቅንጣቢ ነፍሴን
ገላልጣ ብታየው ሀፍረቴን ሀጥአቴን
ክርፋቴ ገፋፍቶህ ጥለህ ትሄዳለህ
ለፀዓዳ ቤቴ አትመጥንም ብለህ
ባትመጣ ደሞ
ይህቺ ምስኪን ነፍሴ አለም የበደላት
ዝንት አለም ልትኖር ነው ስጋዬ ሲገዛት
ስጋዬ ሲወቅጣት
የቱ ነው ሚሻለው
የቱ ነው ሚበጀው?
ብትመጣ
በህግ ያልተገዛ ባንተ ያልታመነ
ነፍሴ ተኮነነ
ብትቀር
ዘመን የጠበቀ ዘመን የዋለለ
ይመጣል እያለ
ሁልግዜ ሊኖር ነው ነፍስ እያቃጠለ
ወዳጄ
መምጣትህ ቅጣት ነው
መቅረትህም ሞት ነው
እኛ ማለት ላንተ በደረቱ ሚድህ እንፉቅቅ ልጅ ነንና
ውስጡ ያልበሰለ ጉልበቱ ያልጠና
መምጣትህም መልካም መቅረትህም ደህና
ፍቃድህ ነንና፡፡
ግና ግን ጌታዬ የሀጥአቴን ጭቃ በእንባ ሳላጠራ
እኔ እንዳልጠራ፡፡
አንተ እንደፈለክ
@getem
@getem
@inluvwidart
--የሴት ልጅ ያሉኛል አዎ የሴት ልጅ ነኝ--
አዎ የሴት ልጅ ነኝ የውዲቷ እናቴ
ከግማሽ አካልዋ ተቆርጦዋል እትብቴ
አዎ የሴት ልጅ ነኝ የኔ አንድ ውዲቷ
ጡት የምታጠባ በታጠፈ አንጀቷ
ያንስብኛል እንዴ የሴት ልጅ ለመባል
የአንድ ቀን ጭነቅዋ ምጧ አኮ ያበቃል
እንዴት አልጠራ አልባል የሴት ልጂ
ውርደት አኮ አያደለም ክብር ቢሆን እንጂ
እንደሻማ ቀልታ ብርሀን ለሆነች
የሷን ኑሮ ትታ ለኔ እየኖረች
እኔን ለማቃናት እሷ አየጎበጠች
ለራሷ ታርዛ እኔን ያለበዘች
እርጥቡ ደረቁ ለ፡ሁሉ ሲነድባት
ዋጥ አድርጋ ችላ ሰው እንድሆንላት
ለዚህ ያበቃችኝ እንድዉል ከሰው ተራ
ክብር ማንነቴ ናት በስሟ ልጠራ
ምንጭ: የግጥም አምባ
@getem
@getem
አዎ የሴት ልጅ ነኝ የውዲቷ እናቴ
ከግማሽ አካልዋ ተቆርጦዋል እትብቴ
አዎ የሴት ልጅ ነኝ የኔ አንድ ውዲቷ
ጡት የምታጠባ በታጠፈ አንጀቷ
ያንስብኛል እንዴ የሴት ልጅ ለመባል
የአንድ ቀን ጭነቅዋ ምጧ አኮ ያበቃል
እንዴት አልጠራ አልባል የሴት ልጂ
ውርደት አኮ አያደለም ክብር ቢሆን እንጂ
እንደሻማ ቀልታ ብርሀን ለሆነች
የሷን ኑሮ ትታ ለኔ እየኖረች
እኔን ለማቃናት እሷ አየጎበጠች
ለራሷ ታርዛ እኔን ያለበዘች
እርጥቡ ደረቁ ለ፡ሁሉ ሲነድባት
ዋጥ አድርጋ ችላ ሰው እንድሆንላት
ለዚህ ያበቃችኝ እንድዉል ከሰው ተራ
ክብር ማንነቴ ናት በስሟ ልጠራ
ምንጭ: የግጥም አምባ
@getem
@getem
✧✧✧ ብዙ ተባዙ ☺
የእናትነት እጣ፣ ያባትነት ውርሱን
የፍጥረትን ምስጢር፣ የቤተሰብ ቅርሱን
የትውልድ አደራ፣ የብዙ ተባዙን፤
ለአእምሮህ ሳይሆን ባሻው ለሚከንፈው
ለልቦናሽ ሳይሆን ስርአት ለሚገድፈው
ለፈቃድህ ሳይሆን እብደት ለሚለክፈው
ለህሊናሽ ሳይሆን ዓለም ለሚያጎድፈው፤
ሰጠው ለሽፍደትህ ጦር ለማይመልሰው
ለመግነጢስ ገላሽ ጾም ለሚያስፈርሰው
ጻፈው በገበናሽ በጉያሽ ትኩሳት
በማትሟገተው የጭንህ ዲን እሳት፤
በሰጣችሁ ርስት በወጉ አንድትረቡ
በሴስ አቆራኝቶ በወሲብ ቀለቡ
ምድርን በሰው ሞላት በኪነጥበቡ።
✍ ፋሲል ይትባረክ ✍
@getem
@getem
@getem
የእናትነት እጣ፣ ያባትነት ውርሱን
የፍጥረትን ምስጢር፣ የቤተሰብ ቅርሱን
የትውልድ አደራ፣ የብዙ ተባዙን፤
ለአእምሮህ ሳይሆን ባሻው ለሚከንፈው
ለልቦናሽ ሳይሆን ስርአት ለሚገድፈው
ለፈቃድህ ሳይሆን እብደት ለሚለክፈው
ለህሊናሽ ሳይሆን ዓለም ለሚያጎድፈው፤
ሰጠው ለሽፍደትህ ጦር ለማይመልሰው
ለመግነጢስ ገላሽ ጾም ለሚያስፈርሰው
ጻፈው በገበናሽ በጉያሽ ትኩሳት
በማትሟገተው የጭንህ ዲን እሳት፤
በሰጣችሁ ርስት በወጉ አንድትረቡ
በሴስ አቆራኝቶ በወሲብ ቀለቡ
ምድርን በሰው ሞላት በኪነጥበቡ።
✍ ፋሲል ይትባረክ ✍
@getem
@getem
@getem
የሰማይ ቤት ግሮሰሪ
(አሱ እንደፃፈዉ)
.
.
"ጨረቃ" ምንላት
ግሮሰሪ ቤት ናት!!!
"ሰማይ" ለምንለው ፣ ቀውጢ ከተማ
ሥራ ምትጀምረው ፣ሲሆን ነው ጨለማ!!!
..................................................
በር እንደከፈተች ፣ አብረው የሚወጡ
ከዋክብት ደሞ...
ሰካራሞች ናቸው ፣ እሷ ጋ ሚጠጡ!!!
*********************
በጣም የሰከረው...
ከሰማይ ፈጥፍጦ ፣ ራሱን ሲገድል
"ተወርዋሪ ኮከብ" ..
ማለት ነው የኛ እድል!!!
********************
ተወርዋሪ ጠርሙስ ሊሆንም ይችላል!
ማን ያውቃል?
@getem
(አሱ እንደፃፈዉ)
.
.
"ጨረቃ" ምንላት
ግሮሰሪ ቤት ናት!!!
"ሰማይ" ለምንለው ፣ ቀውጢ ከተማ
ሥራ ምትጀምረው ፣ሲሆን ነው ጨለማ!!!
..................................................
በር እንደከፈተች ፣ አብረው የሚወጡ
ከዋክብት ደሞ...
ሰካራሞች ናቸው ፣ እሷ ጋ ሚጠጡ!!!
*********************
በጣም የሰከረው...
ከሰማይ ፈጥፍጦ ፣ ራሱን ሲገድል
"ተወርዋሪ ኮከብ" ..
ማለት ነው የኛ እድል!!!
********************
ተወርዋሪ ጠርሙስ ሊሆንም ይችላል!
ማን ያውቃል?
@getem
❤1
❀ግጥም እና ግጣም ...
፡
ኣውቃለሁ
የግጥምሽ መድፊያ ፣ የቅኔሽ መጣጣም
ስምረቱ ድንቅ ነው ፣ ቀልብ ይቀማል በጣም፡፡
#እኔን_የገረመኝ ...
ስንኝ ለመቋጠር ፣ የደረደሩት ቃል
ቤትና አጥር ዘሎ ፣ እንዴት ልብ ይመታል
Ezana Mesfin
@getem
@getem
@lula_al_greeko
፡
ኣውቃለሁ
የግጥምሽ መድፊያ ፣ የቅኔሽ መጣጣም
ስምረቱ ድንቅ ነው ፣ ቀልብ ይቀማል በጣም፡፡
#እኔን_የገረመኝ ...
ስንኝ ለመቋጠር ፣ የደረደሩት ቃል
ቤትና አጥር ዘሎ ፣ እንዴት ልብ ይመታል
Ezana Mesfin
@getem
@getem
@lula_al_greeko
..ዝምታዮ..
ጉርምርምታው ሲፋተግ
ነፋሱ ሲያፋሽክ
ለመርዶ ነጋሪ
ለጧሪ ቀባሪ
ያሰኘው እሪታ
ፀሀይ ያለወትሮ በስተምዕራብ ወጥታ
በግማሽ ተገምሶ
ጨረቃ ደም ለብሶ
የሰማዩ መብረቅ
ጎሚ እንዳለው መልህቅ
ላንዴ ተወርውሮ ከምድር ሲጣበቅ
ደመናው ተቀዶ ዝናም ሲጥለቀለቅ
ውሽንፍሩ አይሎ ነፍሴ ስትል ጭንቅ
ጣራዮ አፍስሶ
ኮርኒሴ እርሶ
ጠብ ጠብ የሚለው
ከወለሉ ሲደርስ ጧ ብሎ ሚወድቀው
ላለቅሰው ፈልጌ ስመኘው ያጣሁት
የኔ እምባ መሰለኝ
ሰዉ ያልተረዳልኝ
ዝምታ ሸፍኖት ስቅ ስቅ የሚለኝ
.ዝ
.ም
.ም
.ም
ህመሜ በርትቶ ሳላገግም በልክ
ይማርህ የሚል ሰው ኩርማን እንኳ ሚልክ
በሌለበት መንደር ጩኸት ይሰማኛል
አውቀው የመሰለኝ ድምጹ ይጠራኛል
መልስ ችዮ እንዳልሰጥ ሰቅዞ ይዞኛል
በውሸት ድንበር ላይ ለእውነት መታገል
ወንጀለኛነት ነው ያስከትላል ገድል
እንደተነቀለ ስሩ እንደጠፋ ዛፍ
ዝምታ ይሻላል ተኝቶ መንዘፍዘፍ
ዝ
ም
ም
ቅጥ የሌለው እበለት
ወዲያ ሲበሸከት
አላስችልህ ብሎ ለማረቅ የቃጣኝ
የእውነት አስተኔው መደማመጥ መስሎኝ
በነሱ አረዳድ ክፋት ሆኖ ቢገኝ
ልሟገታቸው ስል.......
ህመሙ ጠናና ቆበሬ ደፈቀኝ
ሞት አፋፍ ላይ ሆኘ ከሩቅ ለሚጠራኝ
ዝምታዮ በዝቶ ይሄው አስገመተኝ
ለንቶፈንቶ ወሬ አፉ የማያርፈው
ለዝምታ ጊዜ ሁሉም ምክንያት አለው
ብላችሁ ንገሩት ቢረዳልኝ ቢያውቀው
ዝ
ም
(ማሜ)
✅ግጥም ለማላክም ሆነ ለ አስታየት
👉@Getem_sourcebot
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ጉርምርምታው ሲፋተግ
ነፋሱ ሲያፋሽክ
ለመርዶ ነጋሪ
ለጧሪ ቀባሪ
ያሰኘው እሪታ
ፀሀይ ያለወትሮ በስተምዕራብ ወጥታ
በግማሽ ተገምሶ
ጨረቃ ደም ለብሶ
የሰማዩ መብረቅ
ጎሚ እንዳለው መልህቅ
ላንዴ ተወርውሮ ከምድር ሲጣበቅ
ደመናው ተቀዶ ዝናም ሲጥለቀለቅ
ውሽንፍሩ አይሎ ነፍሴ ስትል ጭንቅ
ጣራዮ አፍስሶ
ኮርኒሴ እርሶ
ጠብ ጠብ የሚለው
ከወለሉ ሲደርስ ጧ ብሎ ሚወድቀው
ላለቅሰው ፈልጌ ስመኘው ያጣሁት
የኔ እምባ መሰለኝ
ሰዉ ያልተረዳልኝ
ዝምታ ሸፍኖት ስቅ ስቅ የሚለኝ
.ዝ
.ም
.ም
.ም
ህመሜ በርትቶ ሳላገግም በልክ
ይማርህ የሚል ሰው ኩርማን እንኳ ሚልክ
በሌለበት መንደር ጩኸት ይሰማኛል
አውቀው የመሰለኝ ድምጹ ይጠራኛል
መልስ ችዮ እንዳልሰጥ ሰቅዞ ይዞኛል
በውሸት ድንበር ላይ ለእውነት መታገል
ወንጀለኛነት ነው ያስከትላል ገድል
እንደተነቀለ ስሩ እንደጠፋ ዛፍ
ዝምታ ይሻላል ተኝቶ መንዘፍዘፍ
ዝ
ም
ም
ቅጥ የሌለው እበለት
ወዲያ ሲበሸከት
አላስችልህ ብሎ ለማረቅ የቃጣኝ
የእውነት አስተኔው መደማመጥ መስሎኝ
በነሱ አረዳድ ክፋት ሆኖ ቢገኝ
ልሟገታቸው ስል.......
ህመሙ ጠናና ቆበሬ ደፈቀኝ
ሞት አፋፍ ላይ ሆኘ ከሩቅ ለሚጠራኝ
ዝምታዮ በዝቶ ይሄው አስገመተኝ
ለንቶፈንቶ ወሬ አፉ የማያርፈው
ለዝምታ ጊዜ ሁሉም ምክንያት አለው
ብላችሁ ንገሩት ቢረዳልኝ ቢያውቀው
ዝ
ም
(ማሜ)
✅ግጥም ለማላክም ሆነ ለ አስታየት
👉@Getem_sourcebot
@getem
@getem
@lula_al_greeko
"ጥጋብ እና ሚዛን"
እዛ ማዶ ጋራ፣
ምን ይንኮሻኮሻል፣
ፍየል ተደብቆ፣
ያንን ቦርጩን ያሻል፣
እዚህ ማዶ ዋሻ፣
ዝምታው በርትቷል፣
በጉ ተደብቆ፣
ምራቁን ይውጣል፣
የሚለውን ቀመር፣
የበጉን ረሀብ፣
የፍየሉን ሲሳይ፣
ይሄኛው ልዩነት፣
ለምን መጣ ብለን፣
መነሻውን ስናይ፣
ፍየል ማለት ተግባር፣
ጎርሶ አጣጥሞ፣
ጠግቦ የሚያገሳ፣
በግ ማለት አባባል፣
ለህሊናው ብሎ፣
ሆዱን የሚረሳ፣
የሚል ተረት ይዘን፣
ለከሰረ ውጤት፣
ነፍስን ከስጋ ጋር፣
ከምናወዳድር፣
እስኪ ምን አለበት፣
ህሊናም ቅን ሆኖ፣
ሆድም ጠግቦ ቢያድር፣
ብለን ስንጠይቅ፣
የሚሰራው ጠፍቶ፣
የተፈጥሮን ሒሳብ፣
በግ በደግነቱ፣
ለህሊናው ብሎ፣
ሆዱን እየረሳ፣
ምግብ ትቶ ሲራብ፣
ቆጡን እያሳዩ፣
ፍየሎች ወሰዱት፣
የብብቱን ጥጋብ፡፡
መርዕድ ተስፋዬ
03/06/2008ዓ.ም
👉👉@getem_sourcebot
@getem
@getem
እዛ ማዶ ጋራ፣
ምን ይንኮሻኮሻል፣
ፍየል ተደብቆ፣
ያንን ቦርጩን ያሻል፣
እዚህ ማዶ ዋሻ፣
ዝምታው በርትቷል፣
በጉ ተደብቆ፣
ምራቁን ይውጣል፣
የሚለውን ቀመር፣
የበጉን ረሀብ፣
የፍየሉን ሲሳይ፣
ይሄኛው ልዩነት፣
ለምን መጣ ብለን፣
መነሻውን ስናይ፣
ፍየል ማለት ተግባር፣
ጎርሶ አጣጥሞ፣
ጠግቦ የሚያገሳ፣
በግ ማለት አባባል፣
ለህሊናው ብሎ፣
ሆዱን የሚረሳ፣
የሚል ተረት ይዘን፣
ለከሰረ ውጤት፣
ነፍስን ከስጋ ጋር፣
ከምናወዳድር፣
እስኪ ምን አለበት፣
ህሊናም ቅን ሆኖ፣
ሆድም ጠግቦ ቢያድር፣
ብለን ስንጠይቅ፣
የሚሰራው ጠፍቶ፣
የተፈጥሮን ሒሳብ፣
በግ በደግነቱ፣
ለህሊናው ብሎ፣
ሆዱን እየረሳ፣
ምግብ ትቶ ሲራብ፣
ቆጡን እያሳዩ፣
ፍየሎች ወሰዱት፣
የብብቱን ጥጋብ፡፡
መርዕድ ተስፋዬ
03/06/2008ዓ.ም
👉👉@getem_sourcebot
@getem
@getem
👍1
አንቆቅልሽ?
ሙሉ ናት ሙሉ ናት ፡ ስትባል የኖረች
ሁሉም የሚወዷት ፡ አንድ አካል ነበረች
እንቆቅልሽ? ብላ ፊቷን ታዞርና፡
ምን አውቅልሽ ስላት፡
ጥላኝ ትሄዳለች ፡ መልሳ እንደገና
እንዲሁ ብትሄድ ፡ መልካም በነበረ
ዙሩን አጠማዛው ፡ ሆኗል የከረረ፡፡
ደግሞ ወዳጅ አላት ፡ የምትለው ጊዜ
ቦታና ሁኔታን ፡ የያዘው አባዜ
አነኚህ ፍጥረቶች ፡ አብረው ካልገጠሙ
ሀገር ስትሰጣት ፡ ቆመው ካልታደሙ፡
የሰጠሃትን ሀገር ፡ ብታስገባ ከእጇ፡
ሁሉንም በእጇ ፡ ብታደርግ በደጇ፡
መልስ የለውም ብላ ፡ ስትሰጥ ቀጠሮ
ጊዜና ሁኔታ ቦታም እስኪመጣ ትጠብቃታለህ፡
ሁለተኛ ዞሮ፡፡
By SaMaL Afrique
@getem
@getem
@samalafrique
ሙሉ ናት ሙሉ ናት ፡ ስትባል የኖረች
ሁሉም የሚወዷት ፡ አንድ አካል ነበረች
እንቆቅልሽ? ብላ ፊቷን ታዞርና፡
ምን አውቅልሽ ስላት፡
ጥላኝ ትሄዳለች ፡ መልሳ እንደገና
እንዲሁ ብትሄድ ፡ መልካም በነበረ
ዙሩን አጠማዛው ፡ ሆኗል የከረረ፡፡
ደግሞ ወዳጅ አላት ፡ የምትለው ጊዜ
ቦታና ሁኔታን ፡ የያዘው አባዜ
አነኚህ ፍጥረቶች ፡ አብረው ካልገጠሙ
ሀገር ስትሰጣት ፡ ቆመው ካልታደሙ፡
የሰጠሃትን ሀገር ፡ ብታስገባ ከእጇ፡
ሁሉንም በእጇ ፡ ብታደርግ በደጇ፡
መልስ የለውም ብላ ፡ ስትሰጥ ቀጠሮ
ጊዜና ሁኔታ ቦታም እስኪመጣ ትጠብቃታለህ፡
ሁለተኛ ዞሮ፡፡
By SaMaL Afrique
@getem
@getem
@samalafrique
'ካንሰር' ፍቅር(ልዑል ሀይሌ)
አጭር ነኝ አጭር ነሽ
ቁመት የምንለምን በነጋ በጠባ
ቀጭን ነኝ ቀጭን ነሽ
ስጋ የናፈቀን ካጥንት የሚጠጋ
.
ዓይን የለኝ ዓይን የለሽ
ህልሜንም አታይው ህልምሽንም አላይ
ጥርስ የለኝ ጥርስ የለሽ
ደስታዬን ማትቀጂ
ማልቀዳ ደስታሽን ከአንቺነትሽ ሰማይ
.
እግር የለኝ እግር የለሽ
የሚራመድ ላንቺ የሚራመድ ለኔ
እጅ የለኝ እጅ የለሽ
ስላንቺ የሚፅፍ
ስለኔ የሚዘርፍ ነፍስ የሞላው ቅኔ
.
መለያየት 'ካንሰር'
እጅ እግሬን ጥርስ ዓይኔን
ሰውነቴን ሁሉ እየቆራረጠ
ስላንቺ ያኖርኩት
ግዝፈ-አካሌን ወስዶ ለሌላ እየሰጠ
.
ይኸው ቀሪ ዕድሜዬን
እየቆጠርኩኝ ነው ነይ አብረን እንቁጠር
ወትሮም አንድ አይደለን
ለ -የ-ቅል ፍቅር ነው እኛ ስንፈጠር
23-09-10
@getem
@getem
አጭር ነኝ አጭር ነሽ
ቁመት የምንለምን በነጋ በጠባ
ቀጭን ነኝ ቀጭን ነሽ
ስጋ የናፈቀን ካጥንት የሚጠጋ
.
ዓይን የለኝ ዓይን የለሽ
ህልሜንም አታይው ህልምሽንም አላይ
ጥርስ የለኝ ጥርስ የለሽ
ደስታዬን ማትቀጂ
ማልቀዳ ደስታሽን ከአንቺነትሽ ሰማይ
.
እግር የለኝ እግር የለሽ
የሚራመድ ላንቺ የሚራመድ ለኔ
እጅ የለኝ እጅ የለሽ
ስላንቺ የሚፅፍ
ስለኔ የሚዘርፍ ነፍስ የሞላው ቅኔ
.
መለያየት 'ካንሰር'
እጅ እግሬን ጥርስ ዓይኔን
ሰውነቴን ሁሉ እየቆራረጠ
ስላንቺ ያኖርኩት
ግዝፈ-አካሌን ወስዶ ለሌላ እየሰጠ
.
ይኸው ቀሪ ዕድሜዬን
እየቆጠርኩኝ ነው ነይ አብረን እንቁጠር
ወትሮም አንድ አይደለን
ለ -የ-ቅል ፍቅር ነው እኛ ስንፈጠር
23-09-10
@getem
@getem
#መስታወት_ልግዛልሽ
:
:
መቼስ በዚች ዓለም
አምናለው አልክድም
የሰው ፍፁም የለም።
፡
፡
ሰው ስህተት ይሰራል
ከዚያም ይታረማል
ከስ'ተቱ ይማራል።
፡
፡
ያንቺ ግን ፍቅርዬ መሳሳትሽ ወዛ
በ'ኔና አንቺ መሀል ምንም ሰው ሳይበዛ
እራስሽ የጣድሺው ጎመንም ጠነዛ።
፡
፡
ከሰራሺው ስህተት ትማሪያለሽ ብዬ...
...በተስፋ ስጠብቅ ወይ ዛሬ ወይ ነገ
እንኳን ልትማሪ ጥፋትሽ ስር ሰዶ...
ቅርንጫፍ አውጥቶ ይባሱን አደገ።
፡
፡
እናምልሽ ፍቅሬ...
ትናንት በመቅረዜ ደቂቅ ተስፋን ይዤ
ሁሉን ለ አምላክ ጥዬ እሱን ተመርኩዤ
አጣጥቤ ልኬሽ ጨቅይተሽ ስትመጪ
ፍቅርሽ እንዳይርቀኝ ከልቤ እንዳትወጪ
መውደድ አስገድዶኝ ዳግም እንደገና
አምጥቼልሽ ነበር ውሀና ሳሙና።
፡
፡
ዛሬ ግን ታከተኝ ዛሬማ በቅቶኛል
ጭቃሽን ለማንፃት ውሀ ምቀዳበት...
ጉልበቴም ከድቶኛል።
፡
፡
እናም ካሁን ወዲህ ለኔም እንዲቀለኝ...
...ላንቺም እንዲበጅሽ
በሳሙና ፈንታ ጭቃሽን እንድታይ...
...መስታወት ልግዛልሽ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ @Henokbirhanu
@getem
@getem
:
:
መቼስ በዚች ዓለም
አምናለው አልክድም
የሰው ፍፁም የለም።
፡
፡
ሰው ስህተት ይሰራል
ከዚያም ይታረማል
ከስ'ተቱ ይማራል።
፡
፡
ያንቺ ግን ፍቅርዬ መሳሳትሽ ወዛ
በ'ኔና አንቺ መሀል ምንም ሰው ሳይበዛ
እራስሽ የጣድሺው ጎመንም ጠነዛ።
፡
፡
ከሰራሺው ስህተት ትማሪያለሽ ብዬ...
...በተስፋ ስጠብቅ ወይ ዛሬ ወይ ነገ
እንኳን ልትማሪ ጥፋትሽ ስር ሰዶ...
ቅርንጫፍ አውጥቶ ይባሱን አደገ።
፡
፡
እናምልሽ ፍቅሬ...
ትናንት በመቅረዜ ደቂቅ ተስፋን ይዤ
ሁሉን ለ አምላክ ጥዬ እሱን ተመርኩዤ
አጣጥቤ ልኬሽ ጨቅይተሽ ስትመጪ
ፍቅርሽ እንዳይርቀኝ ከልቤ እንዳትወጪ
መውደድ አስገድዶኝ ዳግም እንደገና
አምጥቼልሽ ነበር ውሀና ሳሙና።
፡
፡
ዛሬ ግን ታከተኝ ዛሬማ በቅቶኛል
ጭቃሽን ለማንፃት ውሀ ምቀዳበት...
ጉልበቴም ከድቶኛል።
፡
፡
እናም ካሁን ወዲህ ለኔም እንዲቀለኝ...
...ላንቺም እንዲበጅሽ
በሳሙና ፈንታ ጭቃሽን እንድታይ...
...መስታወት ልግዛልሽ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ @Henokbirhanu
@getem
@getem