ግጥም ብቻ 📘
64.3K subscribers
1.56K photos
31 videos
61 files
178 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ግጥም (Facebook)

የሠቆቃ ጊዜ የሠቆቃ ዘመን፣
ዘንቦ ማያባራ ቢጸለይ ቢለመን።
ሠሚ ያጣ ጬኸት፣
እንቅልፍ አልባ ሌሊት፣
ኗሪ አልባ ወና ቤት፣
ጸደይ የለሽ ክረምት፣
ትንሣኤ አልባ ሥቅለት፣

አምላክ ዛሬ ይብቃን፤ በዝቷል ሠቆቃችን፣
ሥንሥም መነከሥ፤ ወርቅ ሥንሠፍር ጠጠር ሆኗል ምላሻችን።
@getem
@getem
……………ባንገናኝ እንጂ…………
(የአምልዬ)

መውደቅ መነሳትን ከትል የተማረ
ለነፋስ የሚስማማ
ድንቅ ድርሰት ድርሳን ውብ ዜማ አዋቀረ
ሰባት ጊዜ ወድቆ
ሰባቴ የተነሳን የደላው ትል አይተህ
በጥልቅ ተመስጦ
ለሩሕ የረቀቀ ዜማ ማበጀትህ

....…………እጅግ ይደንቀኛል .…………

ሰባት ጊዜ ሳይሆን
ሰባ ሰባት ጊዜ ወድቄ 'ምነሳ
በመነሳት ማግስት
ደሞ ሌላ ውድቀት ሲፈጥረኝ ለአበሳ
ባንገገናኝ እንጂ
ዘመን ባያድልህ ያሬድ ማህሌታይ
መገፋት መውደቄን
በድል ያልተቛጨ የኔን ጉዞ ብታይ
ለትል ያዘነ ልብ ላምሳሉ በደማ
ከዚህም የሚልቅ
በደረስክ ድርሳን ባዋቀርክ ዜማ።

@Bookkstore
@getem
@getem
…ልዩነት…
# በረከት_በላይነህ
.
ብዙዎች
አንደበቱ ባይጥም
ለጆሮ ባይመች ~ ትምህርት አሰጣጡ
“ኤዲያ”
የጋን ውስጥ መብራት
በማለት አድመው ~ ካዳራሹ ወጡ
.
ጥቂቶች
የመምህሩ ዕውቀት
የጋን ውስጥ መብራት ~ መሆኑን ያመኑ
አምነው የተግባቡ
አዳራሹን ትተው ~ ወደ ጋኑ ገቡ

@getem
@getem
እዚህ እና እዚያ

እዚህ ᎐ ᎐ ᎐

ነጋሪት፣ ከበሮ ፡ ሲጎሰም ሲመታ
ጋሻ ጦር ተሰብቆ ፡ ሲነፋ በእምቢልታ
መለከት፣ ጸናጽል፣ አታሞ ሻኩራ
በሕብረ ዝማሬ ፡ በመድፍ እያጓራ …
ሽለላ እየደራ 
ሻማም እየበራ 
ፉከራ ቀረርቶ ፡ ያፈኞች ቱማታ 
እዩልኝ ስሙልኝ ፡ ያድር ባይ ድንፋታ
ያደነቁረናል ፡ ያለ ቅንጣት ፋታ !

ስሟቸው !…
“የምልጃ ታቦቴ 
አድባር ጉልላቴ 
ምልክቴ ጌጤ 
ማተቤ ነህ ፈርጤ…” 
ሲሉ ሲባባሉ
በስም ሲማማሉ
ሲ – ሸ – ነ – ጋ – ገ – ሉ !


. . . ያ
. . . . . . ስ
. . . . . . . . . ጠ
. . . . . . . . . . . . ሉ !!!

እዚያ ᎐ ᎐ ᎐

እዬዬና መርዶ፣ የእድር ጡሩንባ 
ያስለቃሾች ዋሽንት፣ ያላቃሽ አዞ እምባ
ለዛ የለሽ ዜማ፣ ጣዕም የለሽ ንፍሮ 
ቅጥ የለሽ ንፍረቃ፣ ገጽ አልባ እንጉርጉሮ …

ዝርጠጣ፣ ፍርጠጣ 
የስሜት ሽምጠጣ
ልዝቡን ከግልቡ ብረዛ ቅየጣ . . .

ደራሽና ገስጋሽ ፡ ላይሆኑ ዘላቂ 
በጅምላ ሲነዱ ፡ ሕዝቤን አሳቃቂ 
ደግሞም አስጨናቂ 
“ስስ ብርሃን ፈንጣቂ” 
ግርዶሽ አሟሟቂ
ውዥንብር ናፋቂ . . .

ስሟቸው !…
“ተፋጀ ተጣላ 
እርስ በርስ ተባላ
ሞተ ተሰደደ 
ተቃጠለ አበደ …

አትነሳም ወይ አትለውም ጎኑን
ደምህን ታቅፈህ ከምትድህ ዘመኑን”
እያሉ እያስባሉ እሳት እየጫሩ
በስም ላይ ስም ጭነው እየተሞሸሩ…

“አዋቂው … ልሒቁ 
ረቂቁ … ምጡቁ 
ታጋዩ … አርበኛው 
የፍትህ እረኛው
አንተ ብቻ ዳኛው “

“ከኛስ ወዲያ ላሳር – ለሕዝባችን ግርማ
እጃችን ያልነካው – ሁሉም ነው ጨለማ።”
ሲሉ ሲፈርጁ በመንጋ ሲያስቡ 
ጽድቅና ኩነኔን ባንድ ገጽ ሲከትቡ
ሲያረቁ ሲያፀድቁ 
በቃል ሲያስመርቁ 
ሲ – ያ – ጨ – መ – ላ – ል – ቁ !


. . . ያ
. . . . . . በ
. . . . . . . . . ሽ
. . . . . . . . . . . . ቁ !!!

እዚያና እዚህ ሆኖ የህልማችን ጫፉ
ስንፋተግ አለን ቀኖች ሲቀጠፉ
እስኪ እንጠጋጋ ወፎቹ እንዳይረግፉ።

/ አብዲ ሰዒድ /

😊
@getem
@getem
ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
——————
መሸ ደግሞ አምባ ልውጣ!
አምባ ወጥቼ እኩለ-ሌት ፤ ስለት ገብቼ በስሟ
ከርሞ ሰይጣን በሷ አስቶኝ፤ ልገላገል ከህመሟ
ጠበሏ አፋፍ በጨረቃ፤ ደጋግሜ፤ ማህሌት ቆሜ
ሆዴ ቃትቶ ባር ባር ብሎ፤እርቃኔን ከሷ ታድሜ
ደጀ ሰላሟን በአራት እግር፤ ተንበርክኬ ተሳልሜ
በስጋዬ እሚነደውን፤ በጸሎት ላቤ አጣጥሜ
እፎይ ብዬ አመስግኜ፤ ውዳሴዋን ደጋግሜ…
ገና ከደጅዋ እልፍ ሳልል፤ ደሞ ይምጣ የቁም ህልሜ?
ሌት በጥምቀቷ የነጣው፤ ነጋ፤ ደፈረሰ ደሜ።
ለሷ እንጂ ለኔ አልያዘልኝ፤ አዬ የስለት አታምጣ!
በውጣ ውረድ በጠበል፤ ባሣር ወዜ ቢገረጣ
ልክፍቷ እንደሁ አልለቀቀኝ፤ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ!

@getem
@getem
@lula_al_greeko
#እኔና_ቤቴ
.
በእንባ ለማራጨት ፥ ቀልድ መቼ ጠፋ?
ከእሬት የመረረ ፥ ከእናት ሞት የከፋ።
.
እንቀልድ ካልንማ ፥ ብዙ አለ ቁምነገር
በሳቅ አንከትክቶ ፥ ጥሎ 'ሚያንፈራፍር።
.
ጠላው በጋን ሞልቷል፥ ምንጭ ውሃም አላጣን
ይሁን ብለን አለን ፥፥ ቅ..ራ..ሪ እየጠጣን ።፡
--------------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@lula_al_greeko
#ሊያባብ_ነው_መሰለኝ
:
ሳይሰምርልኝ ቀርቶ ሳያፈራም ቢቀር
ከዐመታት በፊት ዘር ዘርቼ ነበር።
:
ለዚያውም ምርጥ ዘር ....
...ከእውነት ፍሬ ማህፀን በእውነት ተረግዞ
...ደርሶ የተወለደ ብዙ ተወዝውዞ።
:
ምንም እንኳ ያኔ እውነት ቢያጅበውም
ከዘራሁት ዘር ግን ፍሬ አላገኘውም።
:
በዚም የተነሳ ስላጣሁት ፍሬ
ውስጤ ደምቶ ነበር እየው እስከዛሬ።
:
ዛሬ ግን ቀን ቆጥሮ ለድካሜ ዋጋ
እውነት ጀንበሪቷን ወደኔ ሊያነጋ
ተስፋ አትቁረጥ ብሎ ቡቃያን አሳየኝ
ያኔ የዘራውት ዘር ሊያብብ ነው መሰለኝ።

#ሄኖክ_ብርሃኑ
አስተያየቶን @Henokbirhanu
@getem
@getem
//ባክህ ቶሎ ይምጣ// (፪)
(ስምረት አበበ)

ልጅ የአባቱን መምጣት ስለምን ይጠላል
ደም ያስተሳሰረው ገመድ መች ይላላል
ከነሀጢያቴ ወዶ ልጁ ካደረገኝ
ምንም ሳልሰራለት ጽድቁን ከሸለመኝ
ሸክላ ሰሪው እርሱ እኔን ሸክላ ወዶ
ሀጢያቴን ካነፃ በመስቀል ጠርቆ
እኔ ማን ሆንኩና እርሱን የማርመው
ሲሳሳት አላውቅም ሁሌም ትክክል ነው
በሱ ጽድቅ ሙሉነት አልጠራጠርም
የኔን ጨምር ብዬ የሱን አላጎድፍም
ጊዜው ቢረዝም ቢያጥር መምጫው የወዳጄ
ሁሌም ናፍቃለው እስካየው በደጄ!
[ማራናታ]
(ለእዮብ እና ማርያማዊት ግጥም የተሰጠ ምላሽ 😍😍)

@getem
@getem
@poemmedia
''አንቺነትሽ''

ያማረ ገላሽ ውብ ፊትሽ
አይደለም ያሸነፈኝ
ያንበረከከኝ ።

ይልቁንም እቴ
በምርጫ የሰራሺው ስብዕናሽ
አመለካከከትሽ እና ምግባርሽ
ትህትናሽ: ቀናነትሽ እና ቁም ነገርሽ

በምከንያት በጥበብ; በጥልቅ መረዳት
የገነባሺው ማንነት ።
ሺ እጥፍ በልጦ ከደማቁ ውበት
ስንቱን ድንቅ ካሰኘ ደም ግባት
አንቺነትሽ ረታኝ
አሸነፈኝ ።

እቴ
የሴትነት ትርጉሙ አንቺ ነሽ
ከዳሌ እና ጡትሽ
ከከንፈር እና ጥርስሸ
ከአይንሽ እና ቅንድቦችሽ
ካማረው ገላሽ
ከውቡ ፊትሽ
.
.
.
.

በልጠሽ የተገኘሸ
ተፃፈ በቴድሮስ ገ.አብዝጊ በላይ

@getem
@getem
የተዘበራረቀን ማዘባረቅ(ልዑል ሀይሌ)
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
ሳልምሽ ሌቱ መሸ
ሳስብሽ ቀኑ ነጋ
ስራብሽ ውሃ አጥቼ
ስጠማሽ ጉርሻ ጠፋ
.
ጆሮዬ ተለጉሞ
ቃል ማውጣት እያቃተው
አፌ መስማቱን ረሳ
ፍቅርሽ አቅሌን እያሳተው
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
ጫማ ቁጥርሽን ከኮቴሽ
ለማንበብ እየተጣጣርኩ
ከርቀት በምታልፊበት
ሀሳብ ህልምሽን እየሳልኩ
የምራብሽ ጥጋበኛ
የምፆምሽ ፆም ገዳፊ
ምናል ደህንነቴን ባትጠይቂኝ
ምናል ብኖርበት ብታርፊ
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ ግን
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
እራቴን በጠራራ ፀሐይ በልቼ
ቀን ላልምሽ ማንቀላፋ
በድቅድቅ ጨለማ ምሳ በልቼ
አንቺን ላገኝ
ከጨረቃ ከዋክብቱ የምጋፋ
.
እኔ እንዲህ ነኝ
.
ነይ
አዘባርቂው ንግግሬን
ነይ
ውሎዬን አበላሺው
.
የተዘባረቀን ማዘባረቅ
ማስተካከል እንደሆነ እንዳትረሺው
.
ነይ!
(እንዴት ነህ ካልሺኝ ግን
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
17-09-10

@getem
@getem
@lula_al_greeko
🔥1
//ምስኪኗ//


ማሬ ነሽ እያለ
ልብ እያማለለ
ማሬ ነሽ ሲያበዛ
በፍቅሩ ደንዝዛ
በምላሱ ፈዝዛ

በሰው አገር ሆና
በሃሳብ መንምና

አገሩ ቁጭ ብሎ
ለሷ ያዘነ መስሎ
መቼ! ትመጫለሽ?
ምን! ትፈልጊያለሽ?
ብሩን ልያዝልሽ
መሬትም ልግዛልሽ
እያለ ሲሞላት
ሃቅ እየመሰላት
ስትልክ ስትሰጠው

እሷ በሰው አገር
በጣም ስትቸገር
ያልፍልኛል ብላ
ሃሳብ በሱ ጥላ

ያላትን ሳትሳሳ
ልካለት ጨርሳ
ጨራርሳ ስትወጣ
ወደአገር ስትመጣ

ያመነችው ወጣት
እሷን የጠበቃት
ለለፋችው ልፋት
ምንም ሳይገዛላት

እቃም ባይገዛላት
ገንዘቧን ባይሰጣት
ታማኝ በሆነላት!

እሱ ሌላ ይዞ
በሱሱ ደንዝዞ
ማሬ መሬት ቀርቶ
እሱ የልቡን ሰርቶ
አሷን አንከራቶ
ባዶ አስቅርቶ።

ምስኪኗ እህታችን!
ይህን ሁሉ ለፍታ
ወደ አገሯ ገብታ

ድካሟን ሳትረሳ
ያለውን አበሳ
ወጣች ተመልሳ

@getem
@getem
@fuadmeansheart
👍1
ምን አይነት ቄስ ናቸው ፣ ምፀት የለመዱ
"አባት ይፍቱኝ" ስል
"አብይ ይፍታህ "ብለው ፣ አሳልመውኝ ሔዱ
።።።።።
ዳሩ እውነት አላቸው ፣ ቀልዳቸው ቢመርም
ምህረት ያውቃልና
እኛ ብናጠፋም ፣ አምላክ ሰው አያስርም።

(( በላይ በቀለ ወያ ))

@getem
@getem
@lula_al_greeko
🔥1
Birhanu Henok:
#ይታየኛል
:
:
ሴት ከሆን ማናግር ስልክ ተደውሎ
አናትሽ ላይ ወቶ የሆነ ዛር ዘሎ
ምትደውለው ማናት?
የት ነውስ ምታውቃት?
ደርሶ ቁጥርክን ለምንስ ሰጠሀት?
አምጣው ስልኩን በቃ!! እንደውም ላዋራት!!
ሁሌ ባልሺኝ ቁጥር አላማርርሽም
አሁንስ ሰለቸሺኝ መቼም አልልሽም።
:
:
ሁለታችን ሆነን ስናቀና መንገድ
በፊት ከማታውቂያት ወይ ወዳጅ ወይ ዘመድ
ድንገት ስንገናኝ ከሁሉ አስቀድመሽ
እኔ ባለቤቱ አንቺ ግን ምኑ ነሽ?
ባልሺም ጊዜ ከቶ አልነደድኩብሽም
ለሰው ይምሰል እንጂ ለኔ ግን በፍፁም ጨቅጫቃ አይደለሽም።
:
:
ስልኬን ስትነካኪ ካየሽ የሴት ፎቶ
ቁጣሽ ግሎ ንሮ ወዲያው ደምሽ ፈልቶ
ባይንሽ ቂጥ እያየሽ የጥያቄ ውርጅብኝ
ገና አንዱን ሳልመልስ ስላዘነብሺብኝ
ጭራሽ አይከፋኝም
አዎንታዊነቱ እኔን አይጠፋኝም።
:
:
እቤታችን ሆነን ተቃቅፈን በደስታ
እየተሳሳቅን ፊልም ያየንም ለታ
አንዲቷን ተዋናይት እንደው ሳላስበው
ያልኩሽ እንደሆነ በጣም ነው ምታምረው
ከባጡም ከቆጡም ሰበቦች ደርድረሽ
እየገላመጥሺኝ ቻናሉን ቀይረሽ
ሌላ ሌላ ነገር ስትከፍቺብኝም
ጨቅጫቃነት መስሎ እኔን አይሰማኝም።
:
:
አንዳች ጉዳይ ገጥሞኝ
ከደጅ ውዬ ማታ እቤቴ ስመጣ
እየቀየጥሺብኝ ሰላምታና ቁጣ
ከማን ጋር የት ገብተክ ከማን ጋር የት ወጣ
ከማን ጋራ ምን በልተ ምንስ ደግሞ ጠጣ
ብለሺኛል ብዬ አልበሳጭ እኔ
የልብሽ ነው እንጂ የአፍሽ ለምኔ።
:
:
የሚገርመው ነገር ...
ዘንድሮ ሰው ሁሉ የት ገባ የት ወጣ ጭቅጭቅ መስሎታል
"ቅናት" ካሉት ቅኔ ሰሙን ብቻ አንግቦ ወርቁን ዘንግቶታል።
:
:
እውነት እውነት ውዴ ...
ገብቶኛል ድብቁ
ጌጥ ሆኖኛል ወርቁ።
:
:
እንዲ አረግሺኝ ብዬ እንዲያም አልሺኝ ብዬ
አላፈገፍግም ፍቅራችንን ጥዬ።
:
:
እንደውም የኔ ውድ
በየቀኑ ቅኚ በየቀኑ በዪኝ እጅግ ደስ ይለኛል
ከቅናትሽ ጀርባ ፍቅርሽ ይታየኛል
"ቅናት" ሚሉት ቅኔ ወርቁ በርቶልኛል።

#ሄኖክ_ብርሃኑ

ለአስተያየቶ
@henokbirhanu

@getem
@getem
@getem
👍1
ከጥንት ጀምሮ ~ስናየው የኖርነው
ሲቃጠል የሚስቅ ~ዘወትር እሳት ነው ።
_____(ገሞራው )__________
"እንደ ማሽላ እየሳቅን ያለበት ሁኔታ ነው እያየን ያለነው "
/እሱባለው /


@getem
@getem
😂😜😜
የግንቦት ሀያ በአል አቀባበር እንዴት ነው?

በሬው
@wegoch
@wegoch
@getem
ለእዮብ ዘማርያም
እና
ስምረት


ብዙ ከዘገየህ ቀርተሀል
ብየ አለምን እንዳላይ፣
ቶሎም መጠህብኝ ፍኖስ ሳላበራ
በጨለመ ሰማይ፣

ከምታስጨንቀኝ ከምታሸብረኝ
ፋኖስን ፍለጋ ከምታራሩጠኝ

እባክህን አምላክ ከዚህ ሁላ ጣጣ
በንስሀ ፀሎት እራሴን ሳልቀጣ
ብዙም እንዳዘገይ ቶሎም እንዳትመጣ።

@getem
@getem
@lula_al_greeko
..

ከፍቶህ ተጎሳቁለህ
እያዩ እንዳላዩህ
ባላየ ዝም እሚሉህ

አልበቃ ሲላቸው.....

እንዲህ ነው እንዲህ ናት
እያሉ በኩራት
በራሳቸው ችሎት
ተከሳሽ በሌለበት
ፍርድ ከመስጠት

ምነው?.....

ያንተን ኑሮ ኖረው
በተጓዙሉህ ጉዞህ
እያንዷንዷ እርምጃህ
የዘወትር ስሜትህ
አድምጠው ተረድተው
አንተን መስለው
አንተን ሆነው
በፈረድብህ ።
...



Tedros g. Belay

@getem
@getem
...እኔ...

ላንች ያለኝ ፍቅር
እንደ ስጋ ምኞት
እንደጌታ ታምር
ሺመሽም ሲነጋም
አድሮ የሚጨምር።

(ግጥም እዎዳለው)

@getem
@getem
#በዕውቀቱ_ሥዩም

ወደ ምንም የሚያደርስው መንገድ

ቸኳይ የሚመስለው
ፈጣን የሚመስለው
በውልውል መኪና
በፋሺን መጫምያ
ወይም በባዶ እግሩ
ሸው እልም የሚለው
ይሄ ሁሉ ምሁር ይሄ ሁሉ ማይም
መንገዱን የሞላው ከታችም ከላይም
ሲመላለስ እንጂ ሲደርስ አይታይም፡፡

@getem
@getem
@lula_al_greeko
               "ውበት እና አፍንጫ"

   የሾለ አፍንጫሽ ውብ ነው የተባለው
   የውበት መለኪያ የአፍንጫ መሰልከክ
   ሆኖ እንዳይመስልሽ
   ይልቅስ ደፍጣጣው ሰልካካ እንድትባይ
      እድል ፈጠረልሽ
 
      ሰልካካ አፍንጫ
    ከደፍጣጣው አንፃር ተመዝኖ የመጣ
    የውበት መግለጫ
    መሆኑን ዘንግተሽ
    ውበት መሰልከክ ነው እያልሽ ባገሩ ትመፃደቂያለሽ

     ረስተሽው አንጂ
     ሰልካካ አፍንጫ
     ደፍጣጣ አፍንጫ
      ምንም ተነፃፅረው (አንዱ ከአንዱ በልጦ)
      ውበትን መለኪያ ማሳያ ቢሆኑ
      ሁለቱም ሲነኩ የሚወጣው ነገር አንድ አይነት መሆኑ
      
        ከ ዮሴፍ ግርማ ወርቅነህ
          @getem
          @Wegoch


  
  
አንችን የሳምኩለት
( © #እሱባለው_ኢትዮጵያዊ )

ገነት እንደገባሁ ~ ልቤ ተደስቶ
ሀጥያተኛ ሲማር ~ ሲኦልም ተከፍቶ
ክዋክብት በሀሴት~ ከሰማይ ሲረግፉ
ተራሮች ተንደው ~ ምድር ሲነጠፉ
ደራሲያን ሁሉ ~ ስላንቺ ሲፅፉ


ስደተኛ ሁሉ ~ እቤት ተመልሶ
ጤና የነሳቸው ~ ሁሉም ተፈውሶ
ስራ ፈላጊዎች ~ አግኝተው እንጀራ
እናት በልጆቿ ~ በልቧ ስትኮራ
በሰልፍ የሰለቹት
ታክሲ ጠባቂዎች ~ መኪና ሲገዙ
አበዳሪ ሀገራት~ እዳ ሲሰርዙ
መንግሥት ያሰረውን ~ በምህረት ሲፈታ
ሀሳብ አሸንፎ ~ ጥይትን ሲረታ
ጎዳና እሚተኛው~ ቪላ ተሸልሞ
ብሄርተኛው ሁሉ~ ባንድነቱ ቆሞ


ፍጡራን በሙሉ
በደስታ ሲሞሉ

በረሃዉ ለምልሞ~ በአበቦች ይደምቃል
አራዊት በፊናው~ በፍቅር ይስቃል
የምመኘው ሁሉ ~ ሆኖ ይታየኛል
አንቺን የሳምኩለት ~ እንዲህ ያደርገኛል ።
______ ዛሬ |2010_______

@getem
@getem
@lula_al_greeko
🤩1