ልሰቀልልሽ?
..
እንዲህ ይመስለኛል
.... ክርስቶስ በምድር
ፍቅር ይገባን ዘንድ
.... ቢመላለስ ቢዞር
በእግሩ ተራምዶ አልገባን ስላለ
"ድንገት ካልታያቸው ከፍ ልበል" ብሎ
...በራሱ አምሳያ...ፍቅርን ሰቀለ።
እኔ እንደሚገባኝ......
ክርስቶስ አይደለም የተቸነከረው
ይታያቸው ብሎ...
ፍቅርን ሰቅሎልን...እሱ ዙፋን ላይ ነው።
..ደጅሽ ብመላለስ ሰርክ ብመጣ
..አንቺ እንደ አይሁድ አልገባሽ ስላል
..እኔ ተሰቅዬ ዙፋኔ ላይ ልውጣ
( ታምራት ሚሊዮን)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
..
እንዲህ ይመስለኛል
.... ክርስቶስ በምድር
ፍቅር ይገባን ዘንድ
.... ቢመላለስ ቢዞር
በእግሩ ተራምዶ አልገባን ስላለ
"ድንገት ካልታያቸው ከፍ ልበል" ብሎ
...በራሱ አምሳያ...ፍቅርን ሰቀለ።
እኔ እንደሚገባኝ......
ክርስቶስ አይደለም የተቸነከረው
ይታያቸው ብሎ...
ፍቅርን ሰቅሎልን...እሱ ዙፋን ላይ ነው።
..ደጅሽ ብመላለስ ሰርክ ብመጣ
..አንቺ እንደ አይሁድ አልገባሽ ስላል
..እኔ ተሰቅዬ ዙፋኔ ላይ ልውጣ
( ታምራት ሚሊዮን)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍1
“እናቴ ትሙት አንላቀቅም!”
፩
“ሰማህ የኔ ውድ . . .
ሳፈቅርህ ከልቤ ባንተ ተረትቼ
ስላንተው ስባክን አቅሌን ነፍሴን ስቼ
በክንድህ እያሟሟህ ባፍህ እያቀለጥከኝ
ከማያውቁት ዓለም ወስደህ እየከተትከኝ
ነፍሴን አስክረሃት በሀሴት ዳንኪራ
እንዳልቆም እንዳልሄድ ያላንተ እንዳልሰራ
አድርገህ ጠፍረህ እንዲህ አሳስረኸኝ
እሄዳለሁ ብትል ከመንገድ ጥለኸኝ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በፍቅር ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።
፪
“እየውልህ ውዴ . . .
እኔማ ስወድህ ሁኚ ያልከኝን ሆኜ
የኔን ዓለም ትቼ ባንተ ዓለም መንኜ
ጠቅልዬ ግብቼ ከገዳምህ ዋሻ
በስምህ ፀልዬ ሃጢያቴን ማስረሻ
እንደሆነ መቼም አንተም ታውቀዋለህ
ከቶ ያልሰጠውህ ኧረ እንደው ምን አለህ
ታዲያ ሁሉን ወስደህ ባዶዬን ቀርቼ
ኑሮዬን በሞላ አንተው ላይ ገንብቼ
ስታውቀው እንዳልኖር አንተን ተለይቼ
እሄዳለሁ ብትል ድንገት አንቺን ትቼ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በህወት ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።
፫
ሰማሽ የኔ እመቤት . . .
እውነት አንቺን ርቄ
እምነትሽን ፍቄ
በፍቅርሽ ቀልጄ
ሌላ ሴት ለምጄ
ምኖር ይመስልሻል ?!
እውነት እውነት እውነት
በእውነት ተሳስተሻል !
ደግሞ ፉከራሽን ዛቻሽን ፈርቼ
እንዳይመስልሽ ውዴ እኔስ ተረትቼ!
ይልቅ እኔም አልኩሽ . . .
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
ካንቺስ ወዲያ ሴት አላውቅም።
___
አብዲ ሰዒድ
2004 E.C
@getem
@getem
፩
“ሰማህ የኔ ውድ . . .
ሳፈቅርህ ከልቤ ባንተ ተረትቼ
ስላንተው ስባክን አቅሌን ነፍሴን ስቼ
በክንድህ እያሟሟህ ባፍህ እያቀለጥከኝ
ከማያውቁት ዓለም ወስደህ እየከተትከኝ
ነፍሴን አስክረሃት በሀሴት ዳንኪራ
እንዳልቆም እንዳልሄድ ያላንተ እንዳልሰራ
አድርገህ ጠፍረህ እንዲህ አሳስረኸኝ
እሄዳለሁ ብትል ከመንገድ ጥለኸኝ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በፍቅር ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።
፪
“እየውልህ ውዴ . . .
እኔማ ስወድህ ሁኚ ያልከኝን ሆኜ
የኔን ዓለም ትቼ ባንተ ዓለም መንኜ
ጠቅልዬ ግብቼ ከገዳምህ ዋሻ
በስምህ ፀልዬ ሃጢያቴን ማስረሻ
እንደሆነ መቼም አንተም ታውቀዋለህ
ከቶ ያልሰጠውህ ኧረ እንደው ምን አለህ
ታዲያ ሁሉን ወስደህ ባዶዬን ቀርቼ
ኑሮዬን በሞላ አንተው ላይ ገንብቼ
ስታውቀው እንዳልኖር አንተን ተለይቼ
እሄዳለሁ ብትል ድንገት አንቺን ትቼ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በህወት ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።
፫
ሰማሽ የኔ እመቤት . . .
እውነት አንቺን ርቄ
እምነትሽን ፍቄ
በፍቅርሽ ቀልጄ
ሌላ ሴት ለምጄ
ምኖር ይመስልሻል ?!
እውነት እውነት እውነት
በእውነት ተሳስተሻል !
ደግሞ ፉከራሽን ዛቻሽን ፈርቼ
እንዳይመስልሽ ውዴ እኔስ ተረትቼ!
ይልቅ እኔም አልኩሽ . . .
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
ካንቺስ ወዲያ ሴት አላውቅም።
___
አብዲ ሰዒድ
2004 E.C
@getem
@getem
~~~ ጌሾና ፍቅር ~~~~
ቃሌን ተቀበይኝ በብቅል በጌሾ
ተጠርጎ እንዲወጣ የቂማችን ቁርሾ
ሰክረው ያስቀየሙት ማግስቱን ይረሳል
በጨብሲ የገነቡት አይዘልቅም ይፈርሳል
ቢሆንም ዛሬን ነይ ነገ እንደሁ ይደርሳል።
ውዴ ሆይ ነይልኝ
በይ ጠጪ እንጠጣ
ሰላምና ፍቅር ባገር እንዲመጣ !
ደግሞ ይሄን ጡትሽን እስቲ ሸፈን አርጊው
የባላገር ነፍሴን ሰው ፊት አታባልጊው።
እናልሽ ዓለሜ . . .
አፈር የሚገፋው ያ ሚስኪን ገበሬ
ተስፋው እየፈጀው ልክ እንደ በርበሬ
አንጀቱን አጥብቆ ወኔውን ሰንቆ
ለዓላማው ፅናት እግሩን ሰነጣጥቆ
በደደረው መዳፍ ላቦቱን ሞዥቆ …
“አንተ ስትደርስልኝ አደርጋለሁ ጫማ
ለክብርህ ለግብሬ ለስምህ ሚስማማ
በል በርታልኝ ልጄ ዝመት ወደ አስኳላ
ቀለም የለየ ነው ደህነኛ ‘ሚበላ!”
ብሎ የሸኘኝን ከዚያ ከገብስ እርሻ
የጀግናው አባቴን ድህነት ማስረሻ
እንዲሆነኝ ፍጠኝ
ነይ ጠጪ እንጠጣ
ችጋር ድንቁርና ካገር እንዲወጣ !
ኧረ ተይ ጭንሽን አንሺው ከፊቴ ላይ
አልታይ ይለኛል ካንቺ ወዲያ ሰማይ።
ደግሞም ብትፈልጊ ግብርና ማጥናቴ
በሰብል ምርምር ጥበብ መገብየቴ
ያባቴን ገብስ እርሻ ላዘምን ላስፋፋ
በጉልበት ሳይደክም በእውቀት ላፋፋ
አልሜ ወጥኜ ግቤን አሰልፌ
ነበር የተማርኩት ከሰው ተጣድፌ
ቀረሁኝ ፒያሳ ቢራዬን ታቅፌ።
ኦሆሆይ ፒያሳ …
አሃይ ቼቺኒያ …
የደፈረሽ ይውደም እናት ኢትዮጵያ!
ዘራፍ ብሎ ገዳይ የጀግና ልጅ ጀግና
ድህነቱን ታቅፎ፣
እውቀቱን ጨንግፎ፣
ሽል ተስፋውም ረግፎ፣ ይጠጣል ያውና!
እኔ ምልሽ ውዴ . . .
ባለፈው ከኮሌጅ የተመረቅሽ ለታ
መንደርተኛው ሁሉ ሲጨፍር በሆታ
እናትሽ በኩራት ኮንጎዋን ተጫምታ
ዘመኗን በዚያች ለት ሹሩባ ተሰርታ
በበለዘ መልኳ በቅን ልቧ ፈክታ …
“ብሞትም አይቆጨኝ አልቀረሁ ለፍቼ
አንቺን መሳይ ሃኪም ለቀበሌ አፍርቼ
የትልቋ እህትሽ የገነት መካሻ
የከሰለ ልቤን ሃዘኔን ማስረሻ
እሷ እንደው ተቀጨች አዋላጅ ነርስ አጥታ
አምላክ ባንቺ ካሰኝ ለወገን መከታ”
ብላ እንደሳመችሽ ባስታወስኩት ጊዜ
ያንዘፍዝፈኛል የያዘኝ አባዜ።
የቀዬው ሰው ሁሉ ዶክተር መጣች ሲሉ
ካዛንችስ ተገኘች ልጅት በመሃሉ
ምነው በሌሊቱ?!
ምነው በውድቅቱ?!
አይሻልሽም ወይ ቀን መርፌ መውጋቱ?!
እያለ እንዳይዝሽ ይህ ነዝናዥ ህሊና
በይ ጨለጥ አርጊበት ደብል አስቀጂና
ውዴ ሆይ በይ ጠጪ
አይዞሽ እንጠጣ
እድገት ብልፅግና ባገር እንዲመጣ !
ኧረ ተይ አንቺ ልጅ …
ባጭር ቀሚስሽ ላይ ፍም ጭንሽ ተጋልጦ
እንደ እናትሽ ቅቤ ጨረሰኝ አቅልጦ።
ኦሆሆይ ካዛንቺስ …
አሃይ ቼቺኒያ …
ደህና ቀን ይውጣልሽ እናት ኢትዮጵያ።
____
አብዲ ሰዒድ
2006 E.C
@getem
@getem
ቃሌን ተቀበይኝ በብቅል በጌሾ
ተጠርጎ እንዲወጣ የቂማችን ቁርሾ
ሰክረው ያስቀየሙት ማግስቱን ይረሳል
በጨብሲ የገነቡት አይዘልቅም ይፈርሳል
ቢሆንም ዛሬን ነይ ነገ እንደሁ ይደርሳል።
ውዴ ሆይ ነይልኝ
በይ ጠጪ እንጠጣ
ሰላምና ፍቅር ባገር እንዲመጣ !
ደግሞ ይሄን ጡትሽን እስቲ ሸፈን አርጊው
የባላገር ነፍሴን ሰው ፊት አታባልጊው።
እናልሽ ዓለሜ . . .
አፈር የሚገፋው ያ ሚስኪን ገበሬ
ተስፋው እየፈጀው ልክ እንደ በርበሬ
አንጀቱን አጥብቆ ወኔውን ሰንቆ
ለዓላማው ፅናት እግሩን ሰነጣጥቆ
በደደረው መዳፍ ላቦቱን ሞዥቆ …
“አንተ ስትደርስልኝ አደርጋለሁ ጫማ
ለክብርህ ለግብሬ ለስምህ ሚስማማ
በል በርታልኝ ልጄ ዝመት ወደ አስኳላ
ቀለም የለየ ነው ደህነኛ ‘ሚበላ!”
ብሎ የሸኘኝን ከዚያ ከገብስ እርሻ
የጀግናው አባቴን ድህነት ማስረሻ
እንዲሆነኝ ፍጠኝ
ነይ ጠጪ እንጠጣ
ችጋር ድንቁርና ካገር እንዲወጣ !
ኧረ ተይ ጭንሽን አንሺው ከፊቴ ላይ
አልታይ ይለኛል ካንቺ ወዲያ ሰማይ።
ደግሞም ብትፈልጊ ግብርና ማጥናቴ
በሰብል ምርምር ጥበብ መገብየቴ
ያባቴን ገብስ እርሻ ላዘምን ላስፋፋ
በጉልበት ሳይደክም በእውቀት ላፋፋ
አልሜ ወጥኜ ግቤን አሰልፌ
ነበር የተማርኩት ከሰው ተጣድፌ
ቀረሁኝ ፒያሳ ቢራዬን ታቅፌ።
ኦሆሆይ ፒያሳ …
አሃይ ቼቺኒያ …
የደፈረሽ ይውደም እናት ኢትዮጵያ!
ዘራፍ ብሎ ገዳይ የጀግና ልጅ ጀግና
ድህነቱን ታቅፎ፣
እውቀቱን ጨንግፎ፣
ሽል ተስፋውም ረግፎ፣ ይጠጣል ያውና!
እኔ ምልሽ ውዴ . . .
ባለፈው ከኮሌጅ የተመረቅሽ ለታ
መንደርተኛው ሁሉ ሲጨፍር በሆታ
እናትሽ በኩራት ኮንጎዋን ተጫምታ
ዘመኗን በዚያች ለት ሹሩባ ተሰርታ
በበለዘ መልኳ በቅን ልቧ ፈክታ …
“ብሞትም አይቆጨኝ አልቀረሁ ለፍቼ
አንቺን መሳይ ሃኪም ለቀበሌ አፍርቼ
የትልቋ እህትሽ የገነት መካሻ
የከሰለ ልቤን ሃዘኔን ማስረሻ
እሷ እንደው ተቀጨች አዋላጅ ነርስ አጥታ
አምላክ ባንቺ ካሰኝ ለወገን መከታ”
ብላ እንደሳመችሽ ባስታወስኩት ጊዜ
ያንዘፍዝፈኛል የያዘኝ አባዜ።
የቀዬው ሰው ሁሉ ዶክተር መጣች ሲሉ
ካዛንችስ ተገኘች ልጅት በመሃሉ
ምነው በሌሊቱ?!
ምነው በውድቅቱ?!
አይሻልሽም ወይ ቀን መርፌ መውጋቱ?!
እያለ እንዳይዝሽ ይህ ነዝናዥ ህሊና
በይ ጨለጥ አርጊበት ደብል አስቀጂና
ውዴ ሆይ በይ ጠጪ
አይዞሽ እንጠጣ
እድገት ብልፅግና ባገር እንዲመጣ !
ኧረ ተይ አንቺ ልጅ …
ባጭር ቀሚስሽ ላይ ፍም ጭንሽ ተጋልጦ
እንደ እናትሽ ቅቤ ጨረሰኝ አቅልጦ።
ኦሆሆይ ካዛንቺስ …
አሃይ ቼቺኒያ …
ደህና ቀን ይውጣልሽ እናት ኢትዮጵያ።
____
አብዲ ሰዒድ
2006 E.C
@getem
@getem
……………ባንገናኝ እንጂ…………
(የአምልዬ)
መውደቅ መነሳትን ከትል የተማረ
ለነፋስ የሚስማማ
ድንቅ ድርሰት ድርሳን ውብ ዜማ አዋቀረ
ሰባት ጊዜ ወድቆ
ሰባቴ የተነሳን የደላው ትል አይተህ
በጥልቅ ተመስጦ
ለሩሕ የረቀቀ ዜማ ማበጀትህ
....…………እጅግ ይደንቀኛል .…………
ሰባት ጊዜ ሳይሆን
ሰባ ሰባት ጊዜ ወድቄ 'ምነሳ
በመነሳት ማግስት
ደሞ ሌላ ውድቀት ሲፈጥረኝ ለአበሳ
ባንገገናኝ እንጂ
ዘመን ባያድልህ ያሬድ ማህሌታይ
መገፋት መውደቄን
በድል ያልተቛጨ የኔን ጉዞ ብታይ
ለትል ያዘነ ልብ ላምሳሉ በደማ
ከዚህም የሚልቅ
በደረስክ ድርሳን ባዋቀርክ ዜማ።
@Bookkstore
@getem
@getem
(የአምልዬ)
መውደቅ መነሳትን ከትል የተማረ
ለነፋስ የሚስማማ
ድንቅ ድርሰት ድርሳን ውብ ዜማ አዋቀረ
ሰባት ጊዜ ወድቆ
ሰባቴ የተነሳን የደላው ትል አይተህ
በጥልቅ ተመስጦ
ለሩሕ የረቀቀ ዜማ ማበጀትህ
....…………እጅግ ይደንቀኛል .…………
ሰባት ጊዜ ሳይሆን
ሰባ ሰባት ጊዜ ወድቄ 'ምነሳ
በመነሳት ማግስት
ደሞ ሌላ ውድቀት ሲፈጥረኝ ለአበሳ
ባንገገናኝ እንጂ
ዘመን ባያድልህ ያሬድ ማህሌታይ
መገፋት መውደቄን
በድል ያልተቛጨ የኔን ጉዞ ብታይ
ለትል ያዘነ ልብ ላምሳሉ በደማ
ከዚህም የሚልቅ
በደረስክ ድርሳን ባዋቀርክ ዜማ።
@Bookkstore
@getem
@getem
እዚህ እና እዚያ
እዚህ ᎐ ᎐ ᎐
ነጋሪት፣ ከበሮ ፡ ሲጎሰም ሲመታ
ጋሻ ጦር ተሰብቆ ፡ ሲነፋ በእምቢልታ
መለከት፣ ጸናጽል፣ አታሞ ሻኩራ
በሕብረ ዝማሬ ፡ በመድፍ እያጓራ …
ሽለላ እየደራ
ሻማም እየበራ
ፉከራ ቀረርቶ ፡ ያፈኞች ቱማታ
እዩልኝ ስሙልኝ ፡ ያድር ባይ ድንፋታ
ያደነቁረናል ፡ ያለ ቅንጣት ፋታ !
ስሟቸው !…
“የምልጃ ታቦቴ
አድባር ጉልላቴ
ምልክቴ ጌጤ
ማተቤ ነህ ፈርጤ…”
ሲሉ ሲባባሉ
በስም ሲማማሉ
ሲ – ሸ – ነ – ጋ – ገ – ሉ !
ሲ
. . . ያ
. . . . . . ስ
. . . . . . . . . ጠ
. . . . . . . . . . . . ሉ !!!
እዚያ ᎐ ᎐ ᎐
እዬዬና መርዶ፣ የእድር ጡሩንባ
ያስለቃሾች ዋሽንት፣ ያላቃሽ አዞ እምባ
ለዛ የለሽ ዜማ፣ ጣዕም የለሽ ንፍሮ
ቅጥ የለሽ ንፍረቃ፣ ገጽ አልባ እንጉርጉሮ …
ዝርጠጣ፣ ፍርጠጣ
የስሜት ሽምጠጣ
ልዝቡን ከግልቡ ብረዛ ቅየጣ . . .
ደራሽና ገስጋሽ ፡ ላይሆኑ ዘላቂ
በጅምላ ሲነዱ ፡ ሕዝቤን አሳቃቂ
ደግሞም አስጨናቂ
“ስስ ብርሃን ፈንጣቂ”
ግርዶሽ አሟሟቂ
ውዥንብር ናፋቂ . . .
ስሟቸው !…
“ተፋጀ ተጣላ
እርስ በርስ ተባላ
ሞተ ተሰደደ
ተቃጠለ አበደ …
አትነሳም ወይ አትለውም ጎኑን
ደምህን ታቅፈህ ከምትድህ ዘመኑን”
እያሉ እያስባሉ እሳት እየጫሩ
በስም ላይ ስም ጭነው እየተሞሸሩ…
“አዋቂው … ልሒቁ
ረቂቁ … ምጡቁ
ታጋዩ … አርበኛው
የፍትህ እረኛው
አንተ ብቻ ዳኛው “
“ከኛስ ወዲያ ላሳር – ለሕዝባችን ግርማ
እጃችን ያልነካው – ሁሉም ነው ጨለማ።”
ሲሉ ሲፈርጁ በመንጋ ሲያስቡ
ጽድቅና ኩነኔን ባንድ ገጽ ሲከትቡ
ሲያረቁ ሲያፀድቁ
በቃል ሲያስመርቁ
ሲ – ያ – ጨ – መ – ላ – ል – ቁ !
ሲ
. . . ያ
. . . . . . በ
. . . . . . . . . ሽ
. . . . . . . . . . . . ቁ !!!
እዚያና እዚህ ሆኖ የህልማችን ጫፉ
ስንፋተግ አለን ቀኖች ሲቀጠፉ
እስኪ እንጠጋጋ ወፎቹ እንዳይረግፉ።
/ አብዲ ሰዒድ /
😊
@getem
@getem
እዚህ ᎐ ᎐ ᎐
ነጋሪት፣ ከበሮ ፡ ሲጎሰም ሲመታ
ጋሻ ጦር ተሰብቆ ፡ ሲነፋ በእምቢልታ
መለከት፣ ጸናጽል፣ አታሞ ሻኩራ
በሕብረ ዝማሬ ፡ በመድፍ እያጓራ …
ሽለላ እየደራ
ሻማም እየበራ
ፉከራ ቀረርቶ ፡ ያፈኞች ቱማታ
እዩልኝ ስሙልኝ ፡ ያድር ባይ ድንፋታ
ያደነቁረናል ፡ ያለ ቅንጣት ፋታ !
ስሟቸው !…
“የምልጃ ታቦቴ
አድባር ጉልላቴ
ምልክቴ ጌጤ
ማተቤ ነህ ፈርጤ…”
ሲሉ ሲባባሉ
በስም ሲማማሉ
ሲ – ሸ – ነ – ጋ – ገ – ሉ !
ሲ
. . . ያ
. . . . . . ስ
. . . . . . . . . ጠ
. . . . . . . . . . . . ሉ !!!
እዚያ ᎐ ᎐ ᎐
እዬዬና መርዶ፣ የእድር ጡሩንባ
ያስለቃሾች ዋሽንት፣ ያላቃሽ አዞ እምባ
ለዛ የለሽ ዜማ፣ ጣዕም የለሽ ንፍሮ
ቅጥ የለሽ ንፍረቃ፣ ገጽ አልባ እንጉርጉሮ …
ዝርጠጣ፣ ፍርጠጣ
የስሜት ሽምጠጣ
ልዝቡን ከግልቡ ብረዛ ቅየጣ . . .
ደራሽና ገስጋሽ ፡ ላይሆኑ ዘላቂ
በጅምላ ሲነዱ ፡ ሕዝቤን አሳቃቂ
ደግሞም አስጨናቂ
“ስስ ብርሃን ፈንጣቂ”
ግርዶሽ አሟሟቂ
ውዥንብር ናፋቂ . . .
ስሟቸው !…
“ተፋጀ ተጣላ
እርስ በርስ ተባላ
ሞተ ተሰደደ
ተቃጠለ አበደ …
አትነሳም ወይ አትለውም ጎኑን
ደምህን ታቅፈህ ከምትድህ ዘመኑን”
እያሉ እያስባሉ እሳት እየጫሩ
በስም ላይ ስም ጭነው እየተሞሸሩ…
“አዋቂው … ልሒቁ
ረቂቁ … ምጡቁ
ታጋዩ … አርበኛው
የፍትህ እረኛው
አንተ ብቻ ዳኛው “
“ከኛስ ወዲያ ላሳር – ለሕዝባችን ግርማ
እጃችን ያልነካው – ሁሉም ነው ጨለማ።”
ሲሉ ሲፈርጁ በመንጋ ሲያስቡ
ጽድቅና ኩነኔን ባንድ ገጽ ሲከትቡ
ሲያረቁ ሲያፀድቁ
በቃል ሲያስመርቁ
ሲ – ያ – ጨ – መ – ላ – ል – ቁ !
ሲ
. . . ያ
. . . . . . በ
. . . . . . . . . ሽ
. . . . . . . . . . . . ቁ !!!
እዚያና እዚህ ሆኖ የህልማችን ጫፉ
ስንፋተግ አለን ቀኖች ሲቀጠፉ
እስኪ እንጠጋጋ ወፎቹ እንዳይረግፉ።
/ አብዲ ሰዒድ /
😊
@getem
@getem
ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅን
——————
መሸ ደግሞ አምባ ልውጣ!
አምባ ወጥቼ እኩለ-ሌት ፤ ስለት ገብቼ በስሟ
ከርሞ ሰይጣን በሷ አስቶኝ፤ ልገላገል ከህመሟ
ጠበሏ አፋፍ በጨረቃ፤ ደጋግሜ፤ ማህሌት ቆሜ
ሆዴ ቃትቶ ባር ባር ብሎ፤እርቃኔን ከሷ ታድሜ
ደጀ ሰላሟን በአራት እግር፤ ተንበርክኬ ተሳልሜ
በስጋዬ እሚነደውን፤ በጸሎት ላቤ አጣጥሜ
እፎይ ብዬ አመስግኜ፤ ውዳሴዋን ደጋግሜ…
ገና ከደጅዋ እልፍ ሳልል፤ ደሞ ይምጣ የቁም ህልሜ?
ሌት በጥምቀቷ የነጣው፤ ነጋ፤ ደፈረሰ ደሜ።
ለሷ እንጂ ለኔ አልያዘልኝ፤ አዬ የስለት አታምጣ!
በውጣ ውረድ በጠበል፤ ባሣር ወዜ ቢገረጣ
ልክፍቷ እንደሁ አልለቀቀኝ፤ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ!
@getem
@getem
@lula_al_greeko
——————
መሸ ደግሞ አምባ ልውጣ!
አምባ ወጥቼ እኩለ-ሌት ፤ ስለት ገብቼ በስሟ
ከርሞ ሰይጣን በሷ አስቶኝ፤ ልገላገል ከህመሟ
ጠበሏ አፋፍ በጨረቃ፤ ደጋግሜ፤ ማህሌት ቆሜ
ሆዴ ቃትቶ ባር ባር ብሎ፤እርቃኔን ከሷ ታድሜ
ደጀ ሰላሟን በአራት እግር፤ ተንበርክኬ ተሳልሜ
በስጋዬ እሚነደውን፤ በጸሎት ላቤ አጣጥሜ
እፎይ ብዬ አመስግኜ፤ ውዳሴዋን ደጋግሜ…
ገና ከደጅዋ እልፍ ሳልል፤ ደሞ ይምጣ የቁም ህልሜ?
ሌት በጥምቀቷ የነጣው፤ ነጋ፤ ደፈረሰ ደሜ።
ለሷ እንጂ ለኔ አልያዘልኝ፤ አዬ የስለት አታምጣ!
በውጣ ውረድ በጠበል፤ ባሣር ወዜ ቢገረጣ
ልክፍቷ እንደሁ አልለቀቀኝ፤ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ!
@getem
@getem
@lula_al_greeko
#እኔና_ቤቴ
.
በእንባ ለማራጨት ፥ ቀልድ መቼ ጠፋ?
ከእሬት የመረረ ፥ ከእናት ሞት የከፋ።
.
እንቀልድ ካልንማ ፥ ብዙ አለ ቁምነገር
በሳቅ አንከትክቶ ፥ ጥሎ 'ሚያንፈራፍር።
.
ጠላው በጋን ሞልቷል፥ ምንጭ ውሃም አላጣን
ይሁን ብለን አለን ፥፥ ቅ..ራ..ሪ እየጠጣን ።፡
--------------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@lula_al_greeko
.
በእንባ ለማራጨት ፥ ቀልድ መቼ ጠፋ?
ከእሬት የመረረ ፥ ከእናት ሞት የከፋ።
.
እንቀልድ ካልንማ ፥ ብዙ አለ ቁምነገር
በሳቅ አንከትክቶ ፥ ጥሎ 'ሚያንፈራፍር።
.
ጠላው በጋን ሞልቷል፥ ምንጭ ውሃም አላጣን
ይሁን ብለን አለን ፥፥ ቅ..ራ..ሪ እየጠጣን ።፡
--------------------------//--------------------------
( በርናባስ ከበደ )
@getem
@getem
@lula_al_greeko
#ሊያባብ_ነው_መሰለኝ
:
ሳይሰምርልኝ ቀርቶ ሳያፈራም ቢቀር
ከዐመታት በፊት ዘር ዘርቼ ነበር።
:
ለዚያውም ምርጥ ዘር ....
...ከእውነት ፍሬ ማህፀን በእውነት ተረግዞ
...ደርሶ የተወለደ ብዙ ተወዝውዞ።
:
ምንም እንኳ ያኔ እውነት ቢያጅበውም
ከዘራሁት ዘር ግን ፍሬ አላገኘውም።
:
በዚም የተነሳ ስላጣሁት ፍሬ
ውስጤ ደምቶ ነበር እየው እስከዛሬ።
:
ዛሬ ግን ቀን ቆጥሮ ለድካሜ ዋጋ
እውነት ጀንበሪቷን ወደኔ ሊያነጋ
ተስፋ አትቁረጥ ብሎ ቡቃያን አሳየኝ
ያኔ የዘራውት ዘር ሊያብብ ነው መሰለኝ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
አስተያየቶን @Henokbirhanu
@getem
@getem
:
ሳይሰምርልኝ ቀርቶ ሳያፈራም ቢቀር
ከዐመታት በፊት ዘር ዘርቼ ነበር።
:
ለዚያውም ምርጥ ዘር ....
...ከእውነት ፍሬ ማህፀን በእውነት ተረግዞ
...ደርሶ የተወለደ ብዙ ተወዝውዞ።
:
ምንም እንኳ ያኔ እውነት ቢያጅበውም
ከዘራሁት ዘር ግን ፍሬ አላገኘውም።
:
በዚም የተነሳ ስላጣሁት ፍሬ
ውስጤ ደምቶ ነበር እየው እስከዛሬ።
:
ዛሬ ግን ቀን ቆጥሮ ለድካሜ ዋጋ
እውነት ጀንበሪቷን ወደኔ ሊያነጋ
ተስፋ አትቁረጥ ብሎ ቡቃያን አሳየኝ
ያኔ የዘራውት ዘር ሊያብብ ነው መሰለኝ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
አስተያየቶን @Henokbirhanu
@getem
@getem
//ባክህ ቶሎ ይምጣ// (፪)
(ስምረት አበበ)
ልጅ የአባቱን መምጣት ስለምን ይጠላል
ደም ያስተሳሰረው ገመድ መች ይላላል
ከነሀጢያቴ ወዶ ልጁ ካደረገኝ
ምንም ሳልሰራለት ጽድቁን ከሸለመኝ
ሸክላ ሰሪው እርሱ እኔን ሸክላ ወዶ
ሀጢያቴን ካነፃ በመስቀል ጠርቆ
እኔ ማን ሆንኩና እርሱን የማርመው
ሲሳሳት አላውቅም ሁሌም ትክክል ነው
በሱ ጽድቅ ሙሉነት አልጠራጠርም
የኔን ጨምር ብዬ የሱን አላጎድፍም
ጊዜው ቢረዝም ቢያጥር መምጫው የወዳጄ
ሁሌም ናፍቃለው እስካየው በደጄ!
[ማራናታ]
(ለእዮብ እና ማርያማዊት ግጥም የተሰጠ ምላሽ 😍😍)
@getem
@getem
@poemmedia
(ስምረት አበበ)
ልጅ የአባቱን መምጣት ስለምን ይጠላል
ደም ያስተሳሰረው ገመድ መች ይላላል
ከነሀጢያቴ ወዶ ልጁ ካደረገኝ
ምንም ሳልሰራለት ጽድቁን ከሸለመኝ
ሸክላ ሰሪው እርሱ እኔን ሸክላ ወዶ
ሀጢያቴን ካነፃ በመስቀል ጠርቆ
እኔ ማን ሆንኩና እርሱን የማርመው
ሲሳሳት አላውቅም ሁሌም ትክክል ነው
በሱ ጽድቅ ሙሉነት አልጠራጠርም
የኔን ጨምር ብዬ የሱን አላጎድፍም
ጊዜው ቢረዝም ቢያጥር መምጫው የወዳጄ
ሁሌም ናፍቃለው እስካየው በደጄ!
[ማራናታ]
(ለእዮብ እና ማርያማዊት ግጥም የተሰጠ ምላሽ 😍😍)
@getem
@getem
@poemmedia
''አንቺነትሽ''
ያማረ ገላሽ ውብ ፊትሽ
አይደለም ያሸነፈኝ
ያንበረከከኝ ።
ይልቁንም እቴ
በምርጫ የሰራሺው ስብዕናሽ
አመለካከከትሽ እና ምግባርሽ
ትህትናሽ: ቀናነትሽ እና ቁም ነገርሽ
በምከንያት በጥበብ; በጥልቅ መረዳት
የገነባሺው ማንነት ።
ሺ እጥፍ በልጦ ከደማቁ ውበት
ስንቱን ድንቅ ካሰኘ ደም ግባት
አንቺነትሽ ረታኝ
አሸነፈኝ ።
እቴ
የሴትነት ትርጉሙ አንቺ ነሽ
ከዳሌ እና ጡትሽ
ከከንፈር እና ጥርስሸ
ከአይንሽ እና ቅንድቦችሽ
ካማረው ገላሽ
ከውቡ ፊትሽ
.
.
.
.
በልጠሽ የተገኘሸ
ተፃፈ በቴድሮስ ገ.አብዝጊ በላይ
@getem
@getem
ያማረ ገላሽ ውብ ፊትሽ
አይደለም ያሸነፈኝ
ያንበረከከኝ ።
ይልቁንም እቴ
በምርጫ የሰራሺው ስብዕናሽ
አመለካከከትሽ እና ምግባርሽ
ትህትናሽ: ቀናነትሽ እና ቁም ነገርሽ
በምከንያት በጥበብ; በጥልቅ መረዳት
የገነባሺው ማንነት ።
ሺ እጥፍ በልጦ ከደማቁ ውበት
ስንቱን ድንቅ ካሰኘ ደም ግባት
አንቺነትሽ ረታኝ
አሸነፈኝ ።
እቴ
የሴትነት ትርጉሙ አንቺ ነሽ
ከዳሌ እና ጡትሽ
ከከንፈር እና ጥርስሸ
ከአይንሽ እና ቅንድቦችሽ
ካማረው ገላሽ
ከውቡ ፊትሽ
.
.
.
.
በልጠሽ የተገኘሸ
ተፃፈ በቴድሮስ ገ.አብዝጊ በላይ
@getem
@getem
የተዘበራረቀን ማዘባረቅ(ልዑል ሀይሌ)
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
ሳልምሽ ሌቱ መሸ
ሳስብሽ ቀኑ ነጋ
ስራብሽ ውሃ አጥቼ
ስጠማሽ ጉርሻ ጠፋ
.
ጆሮዬ ተለጉሞ
ቃል ማውጣት እያቃተው
አፌ መስማቱን ረሳ
ፍቅርሽ አቅሌን እያሳተው
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
ጫማ ቁጥርሽን ከኮቴሽ
ለማንበብ እየተጣጣርኩ
ከርቀት በምታልፊበት
ሀሳብ ህልምሽን እየሳልኩ
የምራብሽ ጥጋበኛ
የምፆምሽ ፆም ገዳፊ
ምናል ደህንነቴን ባትጠይቂኝ
ምናል ብኖርበት ብታርፊ
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ ግን
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
እራቴን በጠራራ ፀሐይ በልቼ
ቀን ላልምሽ ማንቀላፋ
በድቅድቅ ጨለማ ምሳ በልቼ
አንቺን ላገኝ
ከጨረቃ ከዋክብቱ የምጋፋ
.
እኔ እንዲህ ነኝ
.
ነይ
አዘባርቂው ንግግሬን
ነይ
ውሎዬን አበላሺው
.
የተዘባረቀን ማዘባረቅ
ማስተካከል እንደሆነ እንዳትረሺው
.
ነይ!
(እንዴት ነህ ካልሺኝ ግን
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
17-09-10
@getem
@getem
@lula_al_greeko
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
ሳልምሽ ሌቱ መሸ
ሳስብሽ ቀኑ ነጋ
ስራብሽ ውሃ አጥቼ
ስጠማሽ ጉርሻ ጠፋ
.
ጆሮዬ ተለጉሞ
ቃል ማውጣት እያቃተው
አፌ መስማቱን ረሳ
ፍቅርሽ አቅሌን እያሳተው
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
ጫማ ቁጥርሽን ከኮቴሽ
ለማንበብ እየተጣጣርኩ
ከርቀት በምታልፊበት
ሀሳብ ህልምሽን እየሳልኩ
የምራብሽ ጥጋበኛ
የምፆምሽ ፆም ገዳፊ
ምናል ደህንነቴን ባትጠይቂኝ
ምናል ብኖርበት ብታርፊ
.
(እንዴት ነህ ካልሺኝ ግን
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
.
እራቴን በጠራራ ፀሐይ በልቼ
ቀን ላልምሽ ማንቀላፋ
በድቅድቅ ጨለማ ምሳ በልቼ
አንቺን ላገኝ
ከጨረቃ ከዋክብቱ የምጋፋ
.
እኔ እንዲህ ነኝ
.
ነይ
አዘባርቂው ንግግሬን
ነይ
ውሎዬን አበላሺው
.
የተዘባረቀን ማዘባረቅ
ማስተካከል እንደሆነ እንዳትረሺው
.
ነይ!
(እንዴት ነህ ካልሺኝ ግን
ይመስገነው እንዲህ ነኝ)
17-09-10
@getem
@getem
@lula_al_greeko
🔥1
//ምስኪኗ//
ማሬ ነሽ እያለ
ልብ እያማለለ
ማሬ ነሽ ሲያበዛ
በፍቅሩ ደንዝዛ
በምላሱ ፈዝዛ
በሰው አገር ሆና
በሃሳብ መንምና
አገሩ ቁጭ ብሎ
ለሷ ያዘነ መስሎ
መቼ! ትመጫለሽ?
ምን! ትፈልጊያለሽ?
ብሩን ልያዝልሽ
መሬትም ልግዛልሽ
እያለ ሲሞላት
ሃቅ እየመሰላት
ስትልክ ስትሰጠው
እሷ በሰው አገር
በጣም ስትቸገር
ያልፍልኛል ብላ
ሃሳብ በሱ ጥላ
ያላትን ሳትሳሳ
ልካለት ጨርሳ
ጨራርሳ ስትወጣ
ወደአገር ስትመጣ
ያመነችው ወጣት
እሷን የጠበቃት
ለለፋችው ልፋት
ምንም ሳይገዛላት
እቃም ባይገዛላት
ገንዘቧን ባይሰጣት
ታማኝ በሆነላት!
እሱ ሌላ ይዞ
በሱሱ ደንዝዞ
ማሬ መሬት ቀርቶ
እሱ የልቡን ሰርቶ
አሷን አንከራቶ
ባዶ አስቅርቶ።
ምስኪኗ እህታችን!
ይህን ሁሉ ለፍታ
ወደ አገሯ ገብታ
ድካሟን ሳትረሳ
ያለውን አበሳ
ወጣች ተመልሳ
@getem
@getem
@fuadmeansheart
ማሬ ነሽ እያለ
ልብ እያማለለ
ማሬ ነሽ ሲያበዛ
በፍቅሩ ደንዝዛ
በምላሱ ፈዝዛ
በሰው አገር ሆና
በሃሳብ መንምና
አገሩ ቁጭ ብሎ
ለሷ ያዘነ መስሎ
መቼ! ትመጫለሽ?
ምን! ትፈልጊያለሽ?
ብሩን ልያዝልሽ
መሬትም ልግዛልሽ
እያለ ሲሞላት
ሃቅ እየመሰላት
ስትልክ ስትሰጠው
እሷ በሰው አገር
በጣም ስትቸገር
ያልፍልኛል ብላ
ሃሳብ በሱ ጥላ
ያላትን ሳትሳሳ
ልካለት ጨርሳ
ጨራርሳ ስትወጣ
ወደአገር ስትመጣ
ያመነችው ወጣት
እሷን የጠበቃት
ለለፋችው ልፋት
ምንም ሳይገዛላት
እቃም ባይገዛላት
ገንዘቧን ባይሰጣት
ታማኝ በሆነላት!
እሱ ሌላ ይዞ
በሱሱ ደንዝዞ
ማሬ መሬት ቀርቶ
እሱ የልቡን ሰርቶ
አሷን አንከራቶ
ባዶ አስቅርቶ።
ምስኪኗ እህታችን!
ይህን ሁሉ ለፍታ
ወደ አገሯ ገብታ
ድካሟን ሳትረሳ
ያለውን አበሳ
ወጣች ተመልሳ
@getem
@getem
@fuadmeansheart
👍1
Birhanu Henok:
#ይታየኛል
:
:
ሴት ከሆን ማናግር ስልክ ተደውሎ
አናትሽ ላይ ወቶ የሆነ ዛር ዘሎ
ምትደውለው ማናት?
የት ነውስ ምታውቃት?
ደርሶ ቁጥርክን ለምንስ ሰጠሀት?
አምጣው ስልኩን በቃ!! እንደውም ላዋራት!!
ሁሌ ባልሺኝ ቁጥር አላማርርሽም
አሁንስ ሰለቸሺኝ መቼም አልልሽም።
:
:
ሁለታችን ሆነን ስናቀና መንገድ
በፊት ከማታውቂያት ወይ ወዳጅ ወይ ዘመድ
ድንገት ስንገናኝ ከሁሉ አስቀድመሽ
እኔ ባለቤቱ አንቺ ግን ምኑ ነሽ?
ባልሺም ጊዜ ከቶ አልነደድኩብሽም
ለሰው ይምሰል እንጂ ለኔ ግን በፍፁም ጨቅጫቃ አይደለሽም።
:
:
ስልኬን ስትነካኪ ካየሽ የሴት ፎቶ
ቁጣሽ ግሎ ንሮ ወዲያው ደምሽ ፈልቶ
ባይንሽ ቂጥ እያየሽ የጥያቄ ውርጅብኝ
ገና አንዱን ሳልመልስ ስላዘነብሺብኝ
ጭራሽ አይከፋኝም
አዎንታዊነቱ እኔን አይጠፋኝም።
:
:
እቤታችን ሆነን ተቃቅፈን በደስታ
እየተሳሳቅን ፊልም ያየንም ለታ
አንዲቷን ተዋናይት እንደው ሳላስበው
ያልኩሽ እንደሆነ በጣም ነው ምታምረው
ከባጡም ከቆጡም ሰበቦች ደርድረሽ
እየገላመጥሺኝ ቻናሉን ቀይረሽ
ሌላ ሌላ ነገር ስትከፍቺብኝም
ጨቅጫቃነት መስሎ እኔን አይሰማኝም።
:
:
አንዳች ጉዳይ ገጥሞኝ
ከደጅ ውዬ ማታ እቤቴ ስመጣ
እየቀየጥሺብኝ ሰላምታና ቁጣ
ከማን ጋር የት ገብተክ ከማን ጋር የት ወጣ
ከማን ጋራ ምን በልተ ምንስ ደግሞ ጠጣ
ብለሺኛል ብዬ አልበሳጭ እኔ
የልብሽ ነው እንጂ የአፍሽ ለምኔ።
:
:
የሚገርመው ነገር ...
ዘንድሮ ሰው ሁሉ የት ገባ የት ወጣ ጭቅጭቅ መስሎታል
"ቅናት" ካሉት ቅኔ ሰሙን ብቻ አንግቦ ወርቁን ዘንግቶታል።
:
:
እውነት እውነት ውዴ ...
ገብቶኛል ድብቁ
ጌጥ ሆኖኛል ወርቁ።
:
:
እንዲ አረግሺኝ ብዬ እንዲያም አልሺኝ ብዬ
አላፈገፍግም ፍቅራችንን ጥዬ።
:
:
እንደውም የኔ ውድ
በየቀኑ ቅኚ በየቀኑ በዪኝ እጅግ ደስ ይለኛል
ከቅናትሽ ጀርባ ፍቅርሽ ይታየኛል
"ቅናት" ሚሉት ቅኔ ወርቁ በርቶልኛል።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ
@henokbirhanu
@getem
@getem
@getem
#ይታየኛል
:
:
ሴት ከሆን ማናግር ስልክ ተደውሎ
አናትሽ ላይ ወቶ የሆነ ዛር ዘሎ
ምትደውለው ማናት?
የት ነውስ ምታውቃት?
ደርሶ ቁጥርክን ለምንስ ሰጠሀት?
አምጣው ስልኩን በቃ!! እንደውም ላዋራት!!
ሁሌ ባልሺኝ ቁጥር አላማርርሽም
አሁንስ ሰለቸሺኝ መቼም አልልሽም።
:
:
ሁለታችን ሆነን ስናቀና መንገድ
በፊት ከማታውቂያት ወይ ወዳጅ ወይ ዘመድ
ድንገት ስንገናኝ ከሁሉ አስቀድመሽ
እኔ ባለቤቱ አንቺ ግን ምኑ ነሽ?
ባልሺም ጊዜ ከቶ አልነደድኩብሽም
ለሰው ይምሰል እንጂ ለኔ ግን በፍፁም ጨቅጫቃ አይደለሽም።
:
:
ስልኬን ስትነካኪ ካየሽ የሴት ፎቶ
ቁጣሽ ግሎ ንሮ ወዲያው ደምሽ ፈልቶ
ባይንሽ ቂጥ እያየሽ የጥያቄ ውርጅብኝ
ገና አንዱን ሳልመልስ ስላዘነብሺብኝ
ጭራሽ አይከፋኝም
አዎንታዊነቱ እኔን አይጠፋኝም።
:
:
እቤታችን ሆነን ተቃቅፈን በደስታ
እየተሳሳቅን ፊልም ያየንም ለታ
አንዲቷን ተዋናይት እንደው ሳላስበው
ያልኩሽ እንደሆነ በጣም ነው ምታምረው
ከባጡም ከቆጡም ሰበቦች ደርድረሽ
እየገላመጥሺኝ ቻናሉን ቀይረሽ
ሌላ ሌላ ነገር ስትከፍቺብኝም
ጨቅጫቃነት መስሎ እኔን አይሰማኝም።
:
:
አንዳች ጉዳይ ገጥሞኝ
ከደጅ ውዬ ማታ እቤቴ ስመጣ
እየቀየጥሺብኝ ሰላምታና ቁጣ
ከማን ጋር የት ገብተክ ከማን ጋር የት ወጣ
ከማን ጋራ ምን በልተ ምንስ ደግሞ ጠጣ
ብለሺኛል ብዬ አልበሳጭ እኔ
የልብሽ ነው እንጂ የአፍሽ ለምኔ።
:
:
የሚገርመው ነገር ...
ዘንድሮ ሰው ሁሉ የት ገባ የት ወጣ ጭቅጭቅ መስሎታል
"ቅናት" ካሉት ቅኔ ሰሙን ብቻ አንግቦ ወርቁን ዘንግቶታል።
:
:
እውነት እውነት ውዴ ...
ገብቶኛል ድብቁ
ጌጥ ሆኖኛል ወርቁ።
:
:
እንዲ አረግሺኝ ብዬ እንዲያም አልሺኝ ብዬ
አላፈገፍግም ፍቅራችንን ጥዬ።
:
:
እንደውም የኔ ውድ
በየቀኑ ቅኚ በየቀኑ በዪኝ እጅግ ደስ ይለኛል
ከቅናትሽ ጀርባ ፍቅርሽ ይታየኛል
"ቅናት" ሚሉት ቅኔ ወርቁ በርቶልኛል።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
ለአስተያየቶ
@henokbirhanu
@getem
@getem
@getem
👍1