Genius Tutorial Service
142 subscribers
191 photos
5 videos
51 links
Empowering Genius Mind
Download Telegram
የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
................................................

ህዳር 22/2015 (ትምህርት ሚኒስቴር) መውጫ ፈተና በሁሉም መደበኛና መደበኛ ባልሆኑ መርሀግብሮች የሚመረቁ ተማሪዎችን እንደሚመለከትና ፈተናውን በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ገልጸዋል።

የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ከመደበኛ ተማሪዎች ባሻገር የማታና የርቀት ተመራቂ ተማሪዎችን እንደሚመለከት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በመውጫ ፈተና ዙሪያ ለመንግስትና ለግል ዩኒቨርስቲዎች የተዘጋጀ የምክክር መድረክ ሲከፍቱ እንዳሉት መውጫ ፈተና በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ለሚማሩ የቀን ፣የማታና የርቀት መርሀ ግብር ተመራቂዎች ይሰጣል።

ከዚህ ዓመት ጀምሮ በመንግስትና የግል ዩኒቨርስቲዎች ተግባራዊ የሚደረገውን የመውጫ ፈተና በኦንላይን ለመስጠት መታቀዱንም ዶክተር ሳሙኤል ጠቁመዋል።

በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የመሠረተ ልማት አቅሞቻቸውን ከወዲሁ በማረጋገጥ ለፈተናው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።

የከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር ) በዚሁ ጊዜ ሲናገሩ የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ ባሻገር የተማሪዎችንና የተቋማቱን ብቃት ለማሳደግ እንደሚያስችል ጠቁመዋል።

በምክክር መድረኩ ሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተገኝተዋል።

በምክክር መድረኩም በመውጫ ፈተና ዙሪያ እየተደረገ ያለው ቅድመ ዝግጅት ፣ የመሠረተ ልማትና የ2015 ምሩቃን መረጃዎች ቀርበው ውይይት ተደርጓል።
Our Office is Located Megenagna Mulugeta Zeleke BLDG 5th floor 505/03
👍4
Our Office is Located Megenagna Mulugeta Zeleke BLDG 5th floor 505/03
👍5
Our Office is Located Megenagna Mulugeta Zeleke BLDG 5th floor 505/03
👍4
Our Office is Located Megenagna Mulugeta Zeleke BLDG 5th floor 505/03
👍4
Forwarded from HILLSIDE SCHOOL ETHIOPIA (HSSAdmin)
Culture Day As celebrated by Senior Class
👍4
Forwarded from Ministry of education ®
ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከታህሳስ 18 እስከ 21/2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የሁሉም ክልል ተማሪዎች በሁለተኛው ዙር ለፈተናው እንዲቀመጡ የተለየ ሲሆኑ እነርሱም፦

• የመጀመሪያ ዙር ፈተናን በወሊድ ወይም በእርግዝና ምክንያት መፈተን ያልቻሉ፣

• በህግ ጥላ ስር ወይም በማረሚያ ቤት ሆነው በነበረው መፈተኛ ሁኔታ ለመፈተን ያልቻሉ፣

• የሀገር መከላከያ ሠራዊት ወይም የፌዴራል ፖሊስ ወይም የክልል ልዩ ኃይል አባል ሆነው በወቅቱ በግዳጅ ላይ በመሆናቸው ያልተፈተኑ፣

• በህመም ወይም ተቀባይነት ባገኘና ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ፈተና ያልወሰዱ፣

• ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በደረሰው የድልድይ መደርመስ አደጋ ምክንያት ያልተፈተኑ፣

• በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ችግር ምክንያት አንድ ፈተና እንዲፈተኑ የተወሰነላቸው፣

• ተቀባይነት ባገኙ ችግሮች ምክንያት ፈተና እንዲወስዱ የተወሰነላቸው።

የትምህርት ሚኒስቴር ትክክለኛ የተረጋገጡ ዜናዎችን ለ ጓደኛዎ ያጋሩ ‼️

https://t.me/Temhert_Minister
https://t.me/Temhert_Minister
👍4
Our Office is Located Megenagna Mulugeta Zeleke BLDG 5th floor 505/03
👍4
Our Office is Located Megenagna Mulugeta Zeleke BLDG 5th floor 505/03
👍3
መምህራን ቴክኖሎጂን በአግባቡ በመጠቀም የተሻለች አገር የሚፈጥር ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ማነጽ እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ
....................................................................................

ታህሳስ 13/2015ዓም (ትምህርት ሚኒስቴር) ከአንድ ሺ ለሚበልጡ የ2ኛ ደረጃ መምህራን በቴክኖሎጁ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል።

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ በስልጠናው ወቅት እንደገለጹት የጊዜውን ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ አገሩን የሚገነባ ትውልድ መፍጠር ከመምህራን የሚጠበቅ ተግባር ነው።

በመሆኑም መምህራን የቴክኖሎጂ አቅማቸውን በማሳደግ በስርዓተ ትምህርቱ ላይ የተቀመጡ ዓላማዎችን ተማሪዎች በቀላሉና በተሻለ እንዲረዱ ማስቻል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ከፍተኛ የድጋፍና ክትትል ባለሙያ አቶ አለሙ ተስፋዬ በበኩላቸው የስልጠናው ዓላማ መምህራን ቴክኖሎጁን አማራጭ የትምህርት መረጃ መሳሪያ በማድረግ የመማር ማስተማር ስራውን ለማጠናከር ነው ብለዋል።

ስልጠናው መምህራን የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን በማሳደግ አዳዲስ ዕውቀቶችን እንዳያብሩና በአንድ ጊዜ ብዙ ተማሪዎችን ለመድረስ እንደሚያስችላቸውም አቶ አለሙ ተናግረዋል።

ከሁሉም ክልሎች ለተመለመሉ የ2ኛ ደረጃ መምህራን በ11 የስልጠና ማዕከላት በተሰጠው በዚህ ስልጠና ከአንድ ሺ አንድ መቶ የሚበልጡ ተሳታፊዎች መገኘታቸውንም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ 3ሺ 12 የትምህርት ቤት አመራሮች አቅም ለማጎልበት ልዩ የአንድ ዓመት የስራ ላይ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማትና አስተዳደር ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ ገልጸዋል።
👍3