ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን አስመልክቶ ያስተላለፉት እንደሚከተለው ቀርቧል።
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመት ምሕረት፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ አሜን!
+ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
+ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
+ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
+ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
+ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣
እኛ በሕይወት እንኖር ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም የላከ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓስራ ስምንት ዓመተ ምሕረት በዓለ ልደቱ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
“ወበዝንቱ ተዓውቀ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር ላዕሌነ እስመ ለወልዱ ዋሕድ ፈነዎ ውስተ ዓለም ከመ ንሕየው በእንቲኣሁ፤ ወዝንቱ ውእቱ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር፡- የእግዚአብሔር ፍቅሩ በእኛ ዘንድ ተገለጠ፤ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነው፤ (፩ዮሓ. ፬፥፱)
በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቀው እኛ ምሥራቃውያን ክርስቲያኖች በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል፣ የጌታችን የኣምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ነው፤ በዓለ ልደት የእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ለሰው ልጆች ሁሉ የታወጀበት ዕለት ነው፤ በዚህ ዕለት የሆነው የእግዚአብሔር ፍቅርና ሰላም ቃላዊ ወይም ተምኔታዊ ኣልነበረም፤ ወይም ደግሞ በርቀት በመልእክት የተላለፈ ኣልነበረም፤
ከዚህ ይልቅ ሰብእናችንን በመዋሐድ፣ በተግባር ሆኖ በመገኘት፣ እንዲሁም ለመሰጠት ዝግጁ በመሆን የተገለጠና የታየ ሰላምና ፍቅር ነው፤ እግዚአብሔር የኛን ሰላምና ፍቅር በእጅጉ የሚሻው መሆኑን ለመረዳት፣ የኛን ሰብአዊ ክዋኔ በምልአት ተዋሕዶ በመካከላችን ከመገኘት የተሻለ ሌላ ማረጋገጫ ሊኖር ኣይችልም፤ እኛ ሰዎች ለእግዚአብሔር ጠላቶቹ ተብለን በቅዱስ መጽሐፍ የተገለጽን ነን:: እግዚአብሔር ጠላቶቹን የራሱ አካል አደረጋቸው ሲባል ከመስማት የበለጠ አስደናቂ ነገር በዚህ ዓለም ምን ሊኖር ይችላል?
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
እግዚአብሔር ሰብኣዊነታችንን በምልአት ተዋሕዶ በዓለማችን እንዲገለጥ የሆነበት ዋና ምክንያት እሱ እንዳስረዳን እኛ በሕይወት እንድንኖር ነው፤ ይህንንም ያደረገው ከሁሉ በላይ የሆነ ሌላ ገፊ ኃይል ገፋፍቶት ሳይሆን ድንበር የለሽና ፍጹም ፍቅሩ አነሣሥቶት እንደሆነ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን፤ የእግዚአብሔር ፍቅር እኛ ከምናውቀው ፍቅር ሁሉ በላይ መሆኑንም በዚህ እናስተውላለን፤ ለጠላቶቹ ሕይወት ፍቅርና ሰላም ሲል እነሱን ከመሆን አልፎ እስከ ቤዛዊ መሥዋዕት የሚዘልቅ ፍቅር እጅግ በጣም ታላቅ ነው፤
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፈቃድ እኛ በሕይወት በሰላምና በፍቅር እንድንኖርለት ከሆነ የእኛ ግብረ መልስም ከዚህ የተለየ ሊሆን ኣይገባም፤ እግዚአብሔር ጠላቶቹን ለማዳን እንጂ ለማጥፋት አልመጣም፤ የእኛም ሕይወት የሚጠበቀው ኣንዱ ሌላውን በማዳን እንጂ በማጥፋት እንዳልሆነ ጌታችን በቃልም በተግባርም በኣጽንዖት ነግሮናል፤ በዚህ አስተሳሰብና እምነት እንድንኖርም አዞናል፡፡
ታድያ በቃሉ ለመኖርና ለእሱ ለመታዘዝ ቃል የገባን እኛ ክርስቲያኖች ይህን ሁሉ እርግፍ ኣድርገን በመተው እርስ በእርስ ለመጠፋፋት መሽቀዳደም ምን ይሉታል? ይህስ ለማን ይበጃል?
የአንድ ሀገር ሕዝቦች ይመካከራሉ፣ ይቻቻላሉ፣ ይታገሣሉ፣ ጊዜ ሰጥተው ያስቡና መፍትሔ ያበጃሉ እንጂ ማን በማን ላይ ይነሣል? ይህ ለማንኛችንም አይበጀንምና ወደ ኣእምሮኣችን እንመለስ የሚል ጥሪ የወቅቱ የቤተ ክርስቲያናችን መልእክት ነው፤
በመጨረሻም፤
ይህንን የተቀደሰ በዓል ስለ ሃገራችን ዘላቂ ሰላም በመጸለይና በማሰብ እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት የምግብ፣ የልብስና የመጠለያ እጥረት ያጋጠማቸው ወገኖቻችንን በመደገፍና በመርዳት ለእግዚአብሔር ክብር ብለን ለሀገር ኣንድነትና ለሕዝብ ፍጹም ሰላም መስፈን ከልብ በመነሣሣት በዓሉን እንድናከብር አባታዊ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን!!
መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን!!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመት ምሕረት፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ አሜን!
+ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
+ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣
+ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣
+ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣
+ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣
እኛ በሕይወት እንኖር ዘንድ አንድ ልጁን ወደ ዓለም የላከ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓስራ ስምንት ዓመተ ምሕረት በዓለ ልደቱ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
“ወበዝንቱ ተዓውቀ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር ላዕሌነ እስመ ለወልዱ ዋሕድ ፈነዎ ውስተ ዓለም ከመ ንሕየው በእንቲኣሁ፤ ወዝንቱ ውእቱ ፍቅሩ ለእግዚአብሔር፡- የእግዚአብሔር ፍቅሩ በእኛ ዘንድ ተገለጠ፤ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነው፤ (፩ዮሓ. ፬፥፱)
በሁሉም ዘንድ እንደሚታወቀው እኛ ምሥራቃውያን ክርስቲያኖች በዛሬው ዕለት የምናከብረው በዓል፣ የጌታችን የኣምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ነው፤ በዓለ ልደት የእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ለሰው ልጆች ሁሉ የታወጀበት ዕለት ነው፤ በዚህ ዕለት የሆነው የእግዚአብሔር ፍቅርና ሰላም ቃላዊ ወይም ተምኔታዊ ኣልነበረም፤ ወይም ደግሞ በርቀት በመልእክት የተላለፈ ኣልነበረም፤
ከዚህ ይልቅ ሰብእናችንን በመዋሐድ፣ በተግባር ሆኖ በመገኘት፣ እንዲሁም ለመሰጠት ዝግጁ በመሆን የተገለጠና የታየ ሰላምና ፍቅር ነው፤ እግዚአብሔር የኛን ሰላምና ፍቅር በእጅጉ የሚሻው መሆኑን ለመረዳት፣ የኛን ሰብአዊ ክዋኔ በምልአት ተዋሕዶ በመካከላችን ከመገኘት የተሻለ ሌላ ማረጋገጫ ሊኖር ኣይችልም፤ እኛ ሰዎች ለእግዚአብሔር ጠላቶቹ ተብለን በቅዱስ መጽሐፍ የተገለጽን ነን:: እግዚአብሔር ጠላቶቹን የራሱ አካል አደረጋቸው ሲባል ከመስማት የበለጠ አስደናቂ ነገር በዚህ ዓለም ምን ሊኖር ይችላል?
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
እግዚአብሔር ሰብኣዊነታችንን በምልአት ተዋሕዶ በዓለማችን እንዲገለጥ የሆነበት ዋና ምክንያት እሱ እንዳስረዳን እኛ በሕይወት እንድንኖር ነው፤ ይህንንም ያደረገው ከሁሉ በላይ የሆነ ሌላ ገፊ ኃይል ገፋፍቶት ሳይሆን ድንበር የለሽና ፍጹም ፍቅሩ አነሣሥቶት እንደሆነ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን፤ የእግዚአብሔር ፍቅር እኛ ከምናውቀው ፍቅር ሁሉ በላይ መሆኑንም በዚህ እናስተውላለን፤ ለጠላቶቹ ሕይወት ፍቅርና ሰላም ሲል እነሱን ከመሆን አልፎ እስከ ቤዛዊ መሥዋዕት የሚዘልቅ ፍቅር እጅግ በጣም ታላቅ ነው፤
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !
እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፈቃድ እኛ በሕይወት በሰላምና በፍቅር እንድንኖርለት ከሆነ የእኛ ግብረ መልስም ከዚህ የተለየ ሊሆን ኣይገባም፤ እግዚአብሔር ጠላቶቹን ለማዳን እንጂ ለማጥፋት አልመጣም፤ የእኛም ሕይወት የሚጠበቀው ኣንዱ ሌላውን በማዳን እንጂ በማጥፋት እንዳልሆነ ጌታችን በቃልም በተግባርም በኣጽንዖት ነግሮናል፤ በዚህ አስተሳሰብና እምነት እንድንኖርም አዞናል፡፡
ታድያ በቃሉ ለመኖርና ለእሱ ለመታዘዝ ቃል የገባን እኛ ክርስቲያኖች ይህን ሁሉ እርግፍ ኣድርገን በመተው እርስ በእርስ ለመጠፋፋት መሽቀዳደም ምን ይሉታል? ይህስ ለማን ይበጃል?
የአንድ ሀገር ሕዝቦች ይመካከራሉ፣ ይቻቻላሉ፣ ይታገሣሉ፣ ጊዜ ሰጥተው ያስቡና መፍትሔ ያበጃሉ እንጂ ማን በማን ላይ ይነሣል? ይህ ለማንኛችንም አይበጀንምና ወደ ኣእምሮኣችን እንመለስ የሚል ጥሪ የወቅቱ የቤተ ክርስቲያናችን መልእክት ነው፤
በመጨረሻም፤
ይህንን የተቀደሰ በዓል ስለ ሃገራችን ዘላቂ ሰላም በመጸለይና በማሰብ እንዲሁም በልዩ ልዩ ምክንያት የምግብ፣ የልብስና የመጠለያ እጥረት ያጋጠማቸው ወገኖቻችንን በመደገፍና በመርዳት ለእግዚአብሔር ክብር ብለን ለሀገር ኣንድነትና ለሕዝብ ፍጹም ሰላም መስፈን ከልብ በመነሣሣት በዓሉን እንድናከብር አባታዊ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን!!
መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን!!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
❤31
#ጥር ፫፤ #የአቡነ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከብርባቸው ፲፩ ገዳማትና አድባራት፡፡
(አባ ሊባኖስ በሃገራችን ላይ 80 ገዳማትን መሥተዋል)
በ79 ገዳማትና አድባራት ላይ ሲከበሩ ዐበይቶቹ የሚከተሉት ናቸው፤
#በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ ጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (ከመርካቶ) → ሽሮ ሜዳ → እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት፡፡
#ለቅምሻ_በአጭሩ፤ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም
፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ደግሞ ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡
፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው፥ ጠበሏን አፍልቀው፥ ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡
፠ በ1967 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡
፠ ባለውለታዋን ዘንግታ የቆየችው እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳምም ከ በኋላ በዕለተ እሑድ ጥር 3/2012 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ታቦተ ሕጉን አውጥታ አክብራለች፨
፪. አያት ጣፎ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን፡፡ (በድርብነት ይከበራል)
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት 2 ኮንዶሚንየም
ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ → አያት(በሲኤምሲ) አደባባይ ወደ ጣፎ በሚወስደው መንገድ
ወይም ከመገናኛ በኮተቤ ጣፎ /አባ ኪሮስ ጋር ወርደው/ በባጃጅ (በታክሲ) ያገኙታል፡፡
#በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ደብረ ወርቅ ገዳመ መጣዕ አቡነ ሊባኖስ፤ (በ523 ዓ.ም. በጻድቁ በአቡነ ሊባኖስ የተገደመና በአፄ ገብረ መስቀል የታነጸ፥ ገደል ወገብ ላይ የታነፀና የሚያስደንቅ፡፡) (የጻድቁ የከበረ አጽም የሚገኝበት፥ ሙት ያስነሳበት፥ ዕውር ያበራበት ገዳም ነው)
አድራሻ፤ ደቡብ ኤርትራ፥ አካለ ጉዛይ አውራጃ፥ ሃም ታርካ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ (በአውሮፕላን) → ኤርትራ → አካለ ጉዛይ → ሃም ታርካ፡፡
፪. አኵሱም አጠገብ የሚገኝ አባ ሊባኖስ፤ (ጻድቁ የዋሻ በዓት ሠርተው የጸለየበት፥ 7ት ዓይነት ጠበል ያፈለቀበት፤ አንዲት እናት ውኃ ነው ብላ ብትዳፈር ልጇ ሞቶባት እንደ ኤልያስ ያስነሳበት፥ የአከባቢው ካህናት ቢያድሙበት እንደ ኤልያስ በዚህ አካባቢ ላይ ለ3ት ዓመት ዝናብ እንዳይዘንብ የከለከለበት ኋላ ደግሞ በይቅርታ ቢጠይቁት ዝናብ ያዘነበበት ነው)
(ልጅ ያጡ የሚወልዱበት መታሻ ደንጊያ ያለበት፥ ከዐለት ላይ የሚፈልቅ ተአምረኛ ጠበል ያለበት)
(ገዳሙ ዋሻና ለእኅቶች ደግሞ ክብ ሕንፃ ቤ/ን አለ)
አድራሻ፤ አኵስም ሃገረ ስብከት
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ በጎንደር/በሽሬ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ) ወይም
ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/ወልድያ/መቀለ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ)
፫. ተንቤን አምበራ አቡነ ሊባኖስ (በአፄ ገብረ መስቀል የታነፀ)
አድራሻ፤ ትግራይ
ትራንስፖርት፤ ከአኵሱም → ተንቤን
፬. ላስታ ላሊበላ ቤተ አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ፥ በላስታ ከሚገኙት 11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ አንዱ የኾነና ከ11ዱ ሙሉ ለሙሉ ከተራራ ላይ ተፈልፍሎ ባለመውጣቱ በአሠራሩ ልዩ የኾነ)
አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ፥ ላሊበላ ከተማ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/በጋሸና/ → ላሊበላ
ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን) → ላሊበላ
ወይም ከጎንደር (ባህር ዳር) /በወረታ/ /ደብረ ታቦር/ /ጋሸና/ → ላሊበላ
ወይም ከመቀለ በወልድያ መስመር/ጋሸና/ → ላሊበላ
፭. ዛራ ሐሙሲት አካባቢ የሚገኘው አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ)
አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት
ትራንስፖርት፤ ከባህር ዳር /በጎንደር መስመር/ → ሐሙሲት
፮. ጎንደር ግራርጌ (ቆላ ድባ) ፈለገ ሕይወት አቡነ ሊባኖስ፤ (በአፄ ገብረ መስቀል እንደተመሠረተ የሚነገርለት፥ አጸዱ እጅግ በጣም የሚማርክ /ዕድሜ ጠገብና አርስ በእርሱ የገጠመ 4 ትላልቅ ወርካና 4 ጽድ የሚገኝበት፤ ወርካውን ፈልፍለው መነኰስ ይኖሩበት የነበረው ለምስክር ቆሞ የሚገኝበት፥ 1ዱ ጽድ በ1880 አካባቢ ወድቆ እስካሁን ዝናብና ፀሐይ እየፈራረቀበት ሳይበሰብስ የሚገኝበት)፤ ውሎ ቅዳሴ የሚቀደስበት፤ የአከባቢው ገበሬ እህሉን ወደ ጎታው ከቅዳሴ በኋላ የሚያስገባበት የበረከት ቃል ኪዳን የተሰጠው ምድር፡፡
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደንቢያ ወረዳ፥ ቆላ ድባ ከተማ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከጎንደር (አዘዞ) → ወደ ጎርጎራ መስመር (በደረስጌና በቆላ ድባ መሃል ላይ ያገኙታል) (በ25 ኪ.ሜ አስፓልቱ ዳር)
፯. በመንዝ ቀያ ሀገረ ገራዴ አባ ሊባኖስ አፅመ ቅዱሳን ዋሻ (ፈዋሽ ጠበልና አስገራሚ ዋሻ ያለበት)፡፡
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ፥ ዘመሮ ከተማ፥ በንዲ ቀበሌ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘመሮ → 9 ኪ.ሜ ያህል እንደተጓዙ በንዲ ቀበሌ (ከአዲስ አበባ 328 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ይገኛል)
፰. መንዝ ላሎ አንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ዘብር፥ ላሎ፥ አንጀትላ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘብር(247 ኪ.ሜ.) → የ2ት ሰዐት የእግር መንገድ → የአንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፡፡
፱. *** ነገር ግን የመሠረቱት፥ ለ40 ዓመታት በዓት ሠርተው የኖሩበትና፥ በስማቸው የሚጠራው ታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ ግን ባለፉት 10ር ዓመታት ውስጥ ገድላቸውን በግእዝና በአማርኛ ከማሳተም የዘለለ የሚጠበቅበትን ሥራ አልሠራም፡፡
(ያልጠቀስናቸው ካሉ በውስጥ አሳውቁን)
/ #ክብረ_በዓላት #Feasts /
/ #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches /
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
(አባ ሊባኖስ በሃገራችን ላይ 80 ገዳማትን መሥተዋል)
በ79 ገዳማትና አድባራት ላይ ሲከበሩ ዐበይቶቹ የሚከተሉት ናቸው፤
#በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_፪ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም
አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ እንጦጦ፤
ትራንስፖርት፤ ከፒያሳ ጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (ከመርካቶ) → ሽሮ ሜዳ → እንጦጦ ኪዳነ ምሕረት፡፡
#ለቅምሻ_በአጭሩ፤ #እንጦጦ_ሐመረ_ኖኅ_ኪዳነ_ምሕረት_ገዳም
፠ እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት በ485 ዓ.ም. የሸዋ አባቶች የዐብዩ መድኀኔዓለምንና የበረከት ኪዳነ ምሕረት ታቦትን ይዘው ለ3 ወራት የተሰባሰቡባት ስትሆን፤ ታቦተ ኪዳነ ምሕረትን እንጦጦ ላይ አስቀምጠውና ገዳሟን መሥርተው፤ ታቦተ መድኀኔ ዓለምን ደግሞ ይዘው ወደ ዋልድባ በመሄድ ቀድሞ ጌታችን የገደመውን ገዳም ለ2ኛ ጊዜ አስፋፍተውታል፡፡
፠ ከ16 ዓመታትት በኋላ በ500 ዓ.ም. ደግሞ አቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ ከአኵሱም ወደ ሸዋ ሲመጡ ሐመረ ኖኅን በገዳምነት ገድመው፥ ጠበሏን አፍልቀው፥ ሕሙማንን ፈውሰው ተመልሰዋል፡፡
፠ በ1967 ዓ.ም. አንድ ምዕመን ለፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት አስፈቅደው፤ ገድላቸውን ከአኵሱም አጽፈው በማምጣት ማኅሌቱ እንዲቆም፣ ገድላቸው እንዲነበብ፤ 50 ብር እየከፈሉ የጻድቁን ዝክር እንዲገለገል አስደርገዋል፡፡
፠ ባለውለታዋን ዘንግታ የቆየችው እንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳምም ከ በኋላ በዕለተ እሑድ ጥር 3/2012 ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ታቦተ ሕጉን አውጥታ አክብራለች፨
፪. አያት ጣፎ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን፡፡ (በድርብነት ይከበራል)
አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አያት 2 ኮንዶሚንየም
ትራንስፖርት፤ ከመገናኛ → አያት(በሲኤምሲ) አደባባይ ወደ ጣፎ በሚወስደው መንገድ
ወይም ከመገናኛ በኮተቤ ጣፎ /አባ ኪሮስ ጋር ወርደው/ በባጃጅ (በታክሲ) ያገኙታል፡፡
#በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከብርባቸው_፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩. ደብረ ወርቅ ገዳመ መጣዕ አቡነ ሊባኖስ፤ (በ523 ዓ.ም. በጻድቁ በአቡነ ሊባኖስ የተገደመና በአፄ ገብረ መስቀል የታነጸ፥ ገደል ወገብ ላይ የታነፀና የሚያስደንቅ፡፡) (የጻድቁ የከበረ አጽም የሚገኝበት፥ ሙት ያስነሳበት፥ ዕውር ያበራበት ገዳም ነው)
አድራሻ፤ ደቡብ ኤርትራ፥ አካለ ጉዛይ አውራጃ፥ ሃም ታርካ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ (በአውሮፕላን) → ኤርትራ → አካለ ጉዛይ → ሃም ታርካ፡፡
፪. አኵሱም አጠገብ የሚገኝ አባ ሊባኖስ፤ (ጻድቁ የዋሻ በዓት ሠርተው የጸለየበት፥ 7ት ዓይነት ጠበል ያፈለቀበት፤ አንዲት እናት ውኃ ነው ብላ ብትዳፈር ልጇ ሞቶባት እንደ ኤልያስ ያስነሳበት፥ የአከባቢው ካህናት ቢያድሙበት እንደ ኤልያስ በዚህ አካባቢ ላይ ለ3ት ዓመት ዝናብ እንዳይዘንብ የከለከለበት ኋላ ደግሞ በይቅርታ ቢጠይቁት ዝናብ ያዘነበበት ነው)
(ልጅ ያጡ የሚወልዱበት መታሻ ደንጊያ ያለበት፥ ከዐለት ላይ የሚፈልቅ ተአምረኛ ጠበል ያለበት)
(ገዳሙ ዋሻና ለእኅቶች ደግሞ ክብ ሕንፃ ቤ/ን አለ)
አድራሻ፤ አኵስም ሃገረ ስብከት
ትራንስፖርት፤ ከአዲስ አበባ መርካቶ አውቶቡስ ተራ በጎንደር/በሽሬ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ) ወይም
ከአዲስ አበባ ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/ወልድያ/መቀለ/ → አኵስም → የ10 ብር ትራንስፖርት(የ2ሰዐት የእግር መንገድ)
፫. ተንቤን አምበራ አቡነ ሊባኖስ (በአፄ ገብረ መስቀል የታነፀ)
አድራሻ፤ ትግራይ
ትራንስፖርት፤ ከአኵሱም → ተንቤን
፬. ላስታ ላሊበላ ቤተ አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ፥ በላስታ ከሚገኙት 11ዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ አንዱ የኾነና ከ11ዱ ሙሉ ለሙሉ ከተራራ ላይ ተፈልፍሎ ባለመውጣቱ በአሠራሩ ልዩ የኾነ)
አድራሻ፤ ሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት፥ ላስታ፥ ላሊበላ ከተማ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ላምበረት አውቶቡስ ተራ በደሴ/በጋሸና/ → ላሊበላ
ወይም ከአ.አ. (በአውሮፕላን) → ላሊበላ
ወይም ከጎንደር (ባህር ዳር) /በወረታ/ /ደብረ ታቦር/ /ጋሸና/ → ላሊበላ
ወይም ከመቀለ በወልድያ መስመር/ጋሸና/ → ላሊበላ
፭. ዛራ ሐሙሲት አካባቢ የሚገኘው አባ ሊባኖስ (ቅዱስ ላሊበላ ለ23ት ዓመታት ካነጻቸው አንዱ)
አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት
ትራንስፖርት፤ ከባህር ዳር /በጎንደር መስመር/ → ሐሙሲት
፮. ጎንደር ግራርጌ (ቆላ ድባ) ፈለገ ሕይወት አቡነ ሊባኖስ፤ (በአፄ ገብረ መስቀል እንደተመሠረተ የሚነገርለት፥ አጸዱ እጅግ በጣም የሚማርክ /ዕድሜ ጠገብና አርስ በእርሱ የገጠመ 4 ትላልቅ ወርካና 4 ጽድ የሚገኝበት፤ ወርካውን ፈልፍለው መነኰስ ይኖሩበት የነበረው ለምስክር ቆሞ የሚገኝበት፥ 1ዱ ጽድ በ1880 አካባቢ ወድቆ እስካሁን ዝናብና ፀሐይ እየፈራረቀበት ሳይበሰብስ የሚገኝበት)፤ ውሎ ቅዳሴ የሚቀደስበት፤ የአከባቢው ገበሬ እህሉን ወደ ጎታው ከቅዳሴ በኋላ የሚያስገባበት የበረከት ቃል ኪዳን የተሰጠው ምድር፡፡
አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ደንቢያ ወረዳ፥ ቆላ ድባ ከተማ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከጎንደር (አዘዞ) → ወደ ጎርጎራ መስመር (በደረስጌና በቆላ ድባ መሃል ላይ ያገኙታል) (በ25 ኪ.ሜ አስፓልቱ ዳር)
፯. በመንዝ ቀያ ሀገረ ገራዴ አባ ሊባኖስ አፅመ ቅዱሳን ዋሻ (ፈዋሽ ጠበልና አስገራሚ ዋሻ ያለበት)፡፡
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ፥ ዘመሮ ከተማ፥ በንዲ ቀበሌ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘመሮ → 9 ኪ.ሜ ያህል እንደተጓዙ በንዲ ቀበሌ (ከአዲስ አበባ 328 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ ይገኛል)
፰. መንዝ ላሎ አንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፤
አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት፥ መንዝ፥ ዘብር፥ ላሎ፥ አንጀትላ፡፡
ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ዘብር(247 ኪ.ሜ.) → የ2ት ሰዐት የእግር መንገድ → የአንጀትላ አቡነ ሊባኖስ ገዳም፡፡
፱. *** ነገር ግን የመሠረቱት፥ ለ40 ዓመታት በዓት ሠርተው የኖሩበትና፥ በስማቸው የሚጠራው ታላቁ ገዳም ደብረ ሊባኖስ ግን ባለፉት 10ር ዓመታት ውስጥ ገድላቸውን በግእዝና በአማርኛ ከማሳተም የዘለለ የሚጠበቅበትን ሥራ አልሠራም፡፡
(ያልጠቀስናቸው ካሉ በውስጥ አሳውቁን)
/ #ክብረ_በዓላት #Feasts /
/ #ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches /
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
❤8