This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕሉ ሲያሸበሽብ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፤ ጣርማ በር ወረዳ፤ ጋሹ አምባ ቀበሌ፤ አርማንያ ቅዱስ መርቆሬዎስ፡፡
t.me/finotehiwott
t.me/finotehiwott
❤50
#ኅዳር_26_ #አቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ፤
#_ከደብረ_ዳሞ_ቀጥሎ_በሃገራችን_ሁለተኛውን_መካነ_አእምሮ(#University)#የመሠረተ፤
#_በሃገራችን_ወርቃማ_ዘመን_ተብሎ_የሚታወቀውን_ዘመን_ፋና_ወግቶ_የጀመረ_
#_መጻሕፍትን በእጁ በመጻፍ ለትውልድ የታሪክ አሻራን ያሳረፈ
#_የሐይቅ_እስጢፋኖስ_ገዳምን_ዳግመኛ_ያቀናና_ያስፋፋ፥
#በደብረ ዳሞ አስኬማ ዘመላእክትን የተማረ
#እንደ እስጢፋኖስ ጸጋን ጽድቅንና ሞገስን የተመላ፥ በሥራው ፍጹም የኾነ፥
#የመጀመሪያውን_የዐቃቤ_ሰዐት_ማዕርግ_ያገኘ፡፡
#_ለቡነ_በጸሎተ_ሚካኤል ፥ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ ፥ #አቡነ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫና_ #ለሌሎችም_በርከካታ_ቅዱሳን_ወላዴ_አእላፍ_ቅዱሳን_የኾነ፡፡
* በበጌምድር ዳኅና(አሁን ስማዳ) ገብርኤል በተባለ ቦታ ከአባታቸው ዘክርስቶስና ከእናታቸው እግዚእ ክብራ ነሐሴ 26 ሰኞ ተጸንሰው፤ ግንቦት 26/1205 ዓ.ም. ረቡዕ በቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ዘመነ መንግሥት ተወለዱ፡፡ ወንድሞቻቸው ገብረ ጽዮንና ስቡሕ አምላክ ይባላሉ፡፡
*እስከ 30 ዓመታቸው ድረስ በእናት አባታቸው ቤት እያገለገሉና ትምህርት እየቀሰሙ ቆዩ፤ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾላቸው ወደ 5ኛው የደብረ ዳሞ አበምኔት ዳግማዊ አቡነ ዮሐኒ ዘንድ እንዲሄዱ በራዕይ ነገራቸው፤ በመንገድም ሲሄዱም የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን አግኝተው ይምጻአ ምሕረት የሚባል ዲያቆንን አስከትለው ወደ ደብረ ዳሞ እንዲሄዱ መልአኩ ባዘዛቸው መሠረት ወደ ገዳሙ አቀኑ፡፡
*በደብረ ዳሞ ቆይታቸውም እህልን በመፍጨትና ለገዳሙ ንግድን (ሩቅ መንገድንና አስጨናቂ ኹኔታዎችን በማለፍ ) ይነግዱ ነበር፡፡ እንዲሁም ቅዱሳት መጻሕፍትን በመጻፍ (በመገልበጥም) ትጉህ ጸሓፊ ናቸው፤ ይህ ይታወቅ ዘንድ በቅርብ የደብረ ዳሞ ዕቃ ቤት እስከተቃጠለበት ድረስ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በእጃቸው የጻፉት ወንጌል ይገኝ ነበር፡፡
*37ዓመት ሲኾናቸው ከአባ ዮሐኒ ሥርዐተ አስኬማ ዘመላእክትን ከተቀበሉ በኋላ መልአኩ ወደ ሐይቅ እንዲሄዱ በገለጻላቸው መሠረት በ1237 ዓ.ም. ወደ ሐይቅ በመምጣት በሐይቁ ዳር በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤ.ክ. ለ6ወራት አገለገሉ፤ በዚሁ ደብር የሚገኘው ‹‹#ሔር_አምላክ_›› የተባለ ካህንም የጻድቁን ታሪካቸውን ጠይቆ ከተረዳ በኋላ ወደ ደሴቱ አስገባቸው፤ የአካባቢው ሕዝብም አገልግሎታቸውንና መንፈሳዊ ተጋድሏቸውን አይተው ንጉሡ ይትባረክ ዘንድ በመሄድ የገዳሙ አበምኔት እንዲያደርገው ጠየቁት እርሱም ሾመው፡፡ ጻድቁም ይህን ገዳም በዮዲት ጉዲት ከጠፋ ከ300 ዓመታት በኋላ ዳግም አቅንቶታል፡፡
*እርሳቸውም ደሴቲቷም ስለወደዷት ከገዳሟ ላለመውጣት፤ የባሕሩን ወደብም ላለመርገጥ ብፅዓት ገብተው 20 ዓመታት ያህል እንደኖሩ፤ አፄ ይኵኖ አምላክ እንደነገሠ ጻድቁ ወደ ንጉሡ እንዲመጡ ላከበቸው፤ እርሳቸው ግን ከሐየቁ እንደማይወጡ ብፅዓት እንዳለባቸው፤ ንጉሡ ወደ እርሳቸው እንዲመጣ ላኩበት፤ ንጉሡም በበቅሎ እስከ ጉልበቱ ድረስ ወደ ባሕሩ ገብቶ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ኂሩተ አምላክና ኀረየነ ክርስቶስ ከሚባሉ ደቀመዛሙርቶቹ ጋር በታንኳ (በጀልባ) መጥተው ተጨዋወቱ፤ ንጉሡም ምን ላደርግልህ ትወዳለህ ሲላቸው፤
* ገዳሟ የወንዶች ገዳም እንድትኾን ነው አሉት፤ ንጉሡም በቦታው ያሉትን ሴቶች ይህ ቦታ የወንዶች ገዳም ብቻ እንዲኾን ስለወሰንኩ የፈቀዳችሁ ከእኔ ጋር በከተማዬ መኖር አሊያ በፈቀዳችሁትና በመረጣችሁት ቦታ መኖር ትችላላችሁ የምትፈልጉትንም ኹሉ እሰጣችኋለሁ በማለት ሥርዐት አበጁለት፡፡ ደሴቲቱን ለቀው እየሄዱ ካሉት ሴቶች መካከልም አንዲቷ ምጧ ደርሶ ነበረና በደሴቱ ጫፍ ወለደች ቦታውም ‹‹#ምጥ_ገበታ_›› ተባለ፡፡ ዛሬ ክብረ በዓል የሚከበረው በዚሁ ምጥ ገበታ በተባለው ቦታ ነው፡፡ (ከምጥ ገበታ በስተምዕራብ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ፤ በስተሰሜን ምዕራብ መካነ አእምሮ (University)፤ በስተሰሜን የሴቶች ገዳም ይገኛል)
* በንግግራቸው ሳሉም እባብና አለቅት በንጉሡን በቅሎ እግር ላይ ተጠመጠሙ፤ ጻድቁም መርዛማነት ያላቸው እንስሳት በዚህ ገዳም ሰውን እንዳይጎዱ አወገዟቸው፤ የደወልም ድምፅ ተሰማ ንጉሡም አሁን ስንት ሰዐት ነው የደወል ድምፁስ ምንድን ነው ብሎ ጻድቁን ጠየቀ፤ ጻድቁም ፱ኝ ሰዐት በመኾኑ ደወሉ ከገዳሙ የተደወለ መኾኑን ነገሩት ንጉሡም ለጻድቁ #የዐቃቤ_ሰዐት_ ማዕርግን ሰጣቸው (በአሁኔ ሰዐት ዐቃቤ ሰዐት የጠቅላይ ሚንስትሩ ዋና አማካሪ ከሚለው ጋር የተካከለ ነው)፡፡ (ምንም እንኳን እርሳቸው በሹመቱ ለመጠቀም ባይፈልጉም)፤ ከተከታያቸው ከአባ ዘኢየሱስ አንስቶ እስከ 16ኛው መጀመሪያ አጋማሽ ድረስ በሐይቅ መምህራን እጅ ቆይቷል፤ ኋላ የንጉሦች መናገሻ ከሸዋ ወደ ጎንደር ሲዛወር በቦታ ርቀት ምክንያት ይህ ሹመት በገጽ የሚሰጥ ሹመት ሁኗል፡፡)
✤ንጉሡ ይኵኖ አምላክ ለገዳሟ የሚከተለውን ሥርዐት ሠርተው መደ መናገሻቸው፤ ጻድቁም ወደ ደሴታቸው ተመለሱ ፤
መኳንንት፣ መሳፍንትና ነገሥታት የሰጡትን የገዳሙን ርስት ጉልት ማንም እንዳይነካ፤
ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይገቡ (የአባቶች መነኰሳትና የባሕታውያን ብቻ መኖሪያ እንዲኾንና እኅቶች እንዳይቀላቀሉ በማሰብ)
መነኰስ ያልኾነ ማንም በሐይቅ ገዳም ቤትን እንዳይሠራ፡፡
፠ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በሃገራችን አንጋፋና ቀደምት በኾነው ደብረ ዳሞ መካነ አእምሮ (University) የተማሩ እንደመኾናቸው፤ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሲመለሱም በሃገራችን በትምህርት መካነ አእምሮነቱ ዋናና ግንባር ቀደምቱን፤ በርካታ ሊቃውንትን ቅዱሳንን ያፈለቀውን የሐይቅ እስጢፋኖስ መካነ አእምሮ መሠረቱ፤ በዚህም የኢትዮጵያን ወርቃማ ዘመን መሥራች ነው፤ ልጆቻቸውም ይህን ወርቃማ ዘመን አስቀጥለውታል፡፡ በቆብ የወለዷቸው ቅዱሳን ሊቃውንት ብዙ ቢኾኑም ለአብነት ያህል ዐበይቶቹ፤
✤ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘደብረ ጎል (ምድረ ዐማራን፣ ሸዋንና ደቡብን፤ ምድረ ትግራይን ያስተማሩ፤ የአቡነ ተክለሃይማኖት የመጀመሪያ መምህር የኾኑ)
✤ አቡነ ተክለሃይማኖት (ሐዲስ ሐዋርያ ተብሎ የተሰየመ፤ በሐይቅ ከመመንኰሳቸው በፊት 7 ዓመታት፣ ከመነኰሱ በኋላ 3 ዓመታት ተቀምጠዋል)
✤ አባ ሕዝቅያስ (ከምድረ ወግዳ ይዞ እስከ ጎጃም ያስተማሩ)
✤ አባ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት (በጸበላቸው የእንጨት ቅርፊትን እንደ ደንጊያ መቁጠሪያ የሚያደርጉ፣ በድንጋይ ሠረገላ የሚጓጓዙ)
✤ እጨጌ አባ አሮን ዘደብረ ዳሪት (ከምድረ ዋድላ አንስቶ እስከ ዳውንት፤ ከበጌምድር እስከ ደምቢያ የሰበከ)
✤ አባ ገብረ ናዝራዊ ዘበለሳ (ምድረ ትግሬን ያስተማረ)
✤ አባ ኂሩተ አምላክ ዘዳጋ (እንደ መምህሩ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በእስጢፋኖስ ስም በጣና ላይ የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳምን የመሠረተ፤ ምድረ ሳርክን ይዞ እስከ ጋዝጌ፤ መላዋን የአላፋና ጣቁሳ እና የአገው ምድርን ያስተማረ)
✤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ዘደብረ ባሕርይ) (የኢትዮጵያ መብራት)፤ አብዛኛዋን የኢትዮጵያ ምድር ያስተማረና ቤተ ክርስቲያንን ከ40 በላይ በሚደርሱ ድርሳናቱ ያስጌጠ፡፡
✤ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ፡፡
✤✤ እንዲሁም ንጉሡ ይኵኖ አምላክ (ከንግሥናው በፊት በልጅነቱ ያደገውና የተማረው ከጻድቁ ዘንድ ነው፡፡)
#_ከደብረ_ዳሞ_ቀጥሎ_በሃገራችን_ሁለተኛውን_መካነ_አእምሮ(#University)#የመሠረተ፤
#_በሃገራችን_ወርቃማ_ዘመን_ተብሎ_የሚታወቀውን_ዘመን_ፋና_ወግቶ_የጀመረ_
#_መጻሕፍትን በእጁ በመጻፍ ለትውልድ የታሪክ አሻራን ያሳረፈ
#_የሐይቅ_እስጢፋኖስ_ገዳምን_ዳግመኛ_ያቀናና_ያስፋፋ፥
#በደብረ ዳሞ አስኬማ ዘመላእክትን የተማረ
#እንደ እስጢፋኖስ ጸጋን ጽድቅንና ሞገስን የተመላ፥ በሥራው ፍጹም የኾነ፥
#የመጀመሪያውን_የዐቃቤ_ሰዐት_ማዕርግ_ያገኘ፡፡
#_ለቡነ_በጸሎተ_ሚካኤል ፥ #አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ ፥ #አቡነ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫና_ #ለሌሎችም_በርከካታ_ቅዱሳን_ወላዴ_አእላፍ_ቅዱሳን_የኾነ፡፡
* በበጌምድር ዳኅና(አሁን ስማዳ) ገብርኤል በተባለ ቦታ ከአባታቸው ዘክርስቶስና ከእናታቸው እግዚእ ክብራ ነሐሴ 26 ሰኞ ተጸንሰው፤ ግንቦት 26/1205 ዓ.ም. ረቡዕ በቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ዘመነ መንግሥት ተወለዱ፡፡ ወንድሞቻቸው ገብረ ጽዮንና ስቡሕ አምላክ ይባላሉ፡፡
*እስከ 30 ዓመታቸው ድረስ በእናት አባታቸው ቤት እያገለገሉና ትምህርት እየቀሰሙ ቆዩ፤ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾላቸው ወደ 5ኛው የደብረ ዳሞ አበምኔት ዳግማዊ አቡነ ዮሐኒ ዘንድ እንዲሄዱ በራዕይ ነገራቸው፤ በመንገድም ሲሄዱም የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንን አግኝተው ይምጻአ ምሕረት የሚባል ዲያቆንን አስከትለው ወደ ደብረ ዳሞ እንዲሄዱ መልአኩ ባዘዛቸው መሠረት ወደ ገዳሙ አቀኑ፡፡
*በደብረ ዳሞ ቆይታቸውም እህልን በመፍጨትና ለገዳሙ ንግድን (ሩቅ መንገድንና አስጨናቂ ኹኔታዎችን በማለፍ ) ይነግዱ ነበር፡፡ እንዲሁም ቅዱሳት መጻሕፍትን በመጻፍ (በመገልበጥም) ትጉህ ጸሓፊ ናቸው፤ ይህ ይታወቅ ዘንድ በቅርብ የደብረ ዳሞ ዕቃ ቤት እስከተቃጠለበት ድረስ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በእጃቸው የጻፉት ወንጌል ይገኝ ነበር፡፡
*37ዓመት ሲኾናቸው ከአባ ዮሐኒ ሥርዐተ አስኬማ ዘመላእክትን ከተቀበሉ በኋላ መልአኩ ወደ ሐይቅ እንዲሄዱ በገለጻላቸው መሠረት በ1237 ዓ.ም. ወደ ሐይቅ በመምጣት በሐይቁ ዳር በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤ.ክ. ለ6ወራት አገለገሉ፤ በዚሁ ደብር የሚገኘው ‹‹#ሔር_አምላክ_›› የተባለ ካህንም የጻድቁን ታሪካቸውን ጠይቆ ከተረዳ በኋላ ወደ ደሴቱ አስገባቸው፤ የአካባቢው ሕዝብም አገልግሎታቸውንና መንፈሳዊ ተጋድሏቸውን አይተው ንጉሡ ይትባረክ ዘንድ በመሄድ የገዳሙ አበምኔት እንዲያደርገው ጠየቁት እርሱም ሾመው፡፡ ጻድቁም ይህን ገዳም በዮዲት ጉዲት ከጠፋ ከ300 ዓመታት በኋላ ዳግም አቅንቶታል፡፡
*እርሳቸውም ደሴቲቷም ስለወደዷት ከገዳሟ ላለመውጣት፤ የባሕሩን ወደብም ላለመርገጥ ብፅዓት ገብተው 20 ዓመታት ያህል እንደኖሩ፤ አፄ ይኵኖ አምላክ እንደነገሠ ጻድቁ ወደ ንጉሡ እንዲመጡ ላከበቸው፤ እርሳቸው ግን ከሐየቁ እንደማይወጡ ብፅዓት እንዳለባቸው፤ ንጉሡ ወደ እርሳቸው እንዲመጣ ላኩበት፤ ንጉሡም በበቅሎ እስከ ጉልበቱ ድረስ ወደ ባሕሩ ገብቶ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ኂሩተ አምላክና ኀረየነ ክርስቶስ ከሚባሉ ደቀመዛሙርቶቹ ጋር በታንኳ (በጀልባ) መጥተው ተጨዋወቱ፤ ንጉሡም ምን ላደርግልህ ትወዳለህ ሲላቸው፤
* ገዳሟ የወንዶች ገዳም እንድትኾን ነው አሉት፤ ንጉሡም በቦታው ያሉትን ሴቶች ይህ ቦታ የወንዶች ገዳም ብቻ እንዲኾን ስለወሰንኩ የፈቀዳችሁ ከእኔ ጋር በከተማዬ መኖር አሊያ በፈቀዳችሁትና በመረጣችሁት ቦታ መኖር ትችላላችሁ የምትፈልጉትንም ኹሉ እሰጣችኋለሁ በማለት ሥርዐት አበጁለት፡፡ ደሴቲቱን ለቀው እየሄዱ ካሉት ሴቶች መካከልም አንዲቷ ምጧ ደርሶ ነበረና በደሴቱ ጫፍ ወለደች ቦታውም ‹‹#ምጥ_ገበታ_›› ተባለ፡፡ ዛሬ ክብረ በዓል የሚከበረው በዚሁ ምጥ ገበታ በተባለው ቦታ ነው፡፡ (ከምጥ ገበታ በስተምዕራብ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ፤ በስተሰሜን ምዕራብ መካነ አእምሮ (University)፤ በስተሰሜን የሴቶች ገዳም ይገኛል)
* በንግግራቸው ሳሉም እባብና አለቅት በንጉሡን በቅሎ እግር ላይ ተጠመጠሙ፤ ጻድቁም መርዛማነት ያላቸው እንስሳት በዚህ ገዳም ሰውን እንዳይጎዱ አወገዟቸው፤ የደወልም ድምፅ ተሰማ ንጉሡም አሁን ስንት ሰዐት ነው የደወል ድምፁስ ምንድን ነው ብሎ ጻድቁን ጠየቀ፤ ጻድቁም ፱ኝ ሰዐት በመኾኑ ደወሉ ከገዳሙ የተደወለ መኾኑን ነገሩት ንጉሡም ለጻድቁ #የዐቃቤ_ሰዐት_ ማዕርግን ሰጣቸው (በአሁኔ ሰዐት ዐቃቤ ሰዐት የጠቅላይ ሚንስትሩ ዋና አማካሪ ከሚለው ጋር የተካከለ ነው)፡፡ (ምንም እንኳን እርሳቸው በሹመቱ ለመጠቀም ባይፈልጉም)፤ ከተከታያቸው ከአባ ዘኢየሱስ አንስቶ እስከ 16ኛው መጀመሪያ አጋማሽ ድረስ በሐይቅ መምህራን እጅ ቆይቷል፤ ኋላ የንጉሦች መናገሻ ከሸዋ ወደ ጎንደር ሲዛወር በቦታ ርቀት ምክንያት ይህ ሹመት በገጽ የሚሰጥ ሹመት ሁኗል፡፡)
✤ንጉሡ ይኵኖ አምላክ ለገዳሟ የሚከተለውን ሥርዐት ሠርተው መደ መናገሻቸው፤ ጻድቁም ወደ ደሴታቸው ተመለሱ ፤
መኳንንት፣ መሳፍንትና ነገሥታት የሰጡትን የገዳሙን ርስት ጉልት ማንም እንዳይነካ፤
ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይገቡ (የአባቶች መነኰሳትና የባሕታውያን ብቻ መኖሪያ እንዲኾንና እኅቶች እንዳይቀላቀሉ በማሰብ)
መነኰስ ያልኾነ ማንም በሐይቅ ገዳም ቤትን እንዳይሠራ፡፡
፠ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በሃገራችን አንጋፋና ቀደምት በኾነው ደብረ ዳሞ መካነ አእምሮ (University) የተማሩ እንደመኾናቸው፤ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ሲመለሱም በሃገራችን በትምህርት መካነ አእምሮነቱ ዋናና ግንባር ቀደምቱን፤ በርካታ ሊቃውንትን ቅዱሳንን ያፈለቀውን የሐይቅ እስጢፋኖስ መካነ አእምሮ መሠረቱ፤ በዚህም የኢትዮጵያን ወርቃማ ዘመን መሥራች ነው፤ ልጆቻቸውም ይህን ወርቃማ ዘመን አስቀጥለውታል፡፡ በቆብ የወለዷቸው ቅዱሳን ሊቃውንት ብዙ ቢኾኑም ለአብነት ያህል ዐበይቶቹ፤
✤ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል ዘደብረ ጎል (ምድረ ዐማራን፣ ሸዋንና ደቡብን፤ ምድረ ትግራይን ያስተማሩ፤ የአቡነ ተክለሃይማኖት የመጀመሪያ መምህር የኾኑ)
✤ አቡነ ተክለሃይማኖት (ሐዲስ ሐዋርያ ተብሎ የተሰየመ፤ በሐይቅ ከመመንኰሳቸው በፊት 7 ዓመታት፣ ከመነኰሱ በኋላ 3 ዓመታት ተቀምጠዋል)
✤ አባ ሕዝቅያስ (ከምድረ ወግዳ ይዞ እስከ ጎጃም ያስተማሩ)
✤ አባ ገብረ እንድርያስ ዘደብረ ቆዘት (በጸበላቸው የእንጨት ቅርፊትን እንደ ደንጊያ መቁጠሪያ የሚያደርጉ፣ በድንጋይ ሠረገላ የሚጓጓዙ)
✤ እጨጌ አባ አሮን ዘደብረ ዳሪት (ከምድረ ዋድላ አንስቶ እስከ ዳውንት፤ ከበጌምድር እስከ ደምቢያ የሰበከ)
✤ አባ ገብረ ናዝራዊ ዘበለሳ (ምድረ ትግሬን ያስተማረ)
✤ አባ ኂሩተ አምላክ ዘዳጋ (እንደ መምህሩ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ በእስጢፋኖስ ስም በጣና ላይ የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳምን የመሠረተ፤ ምድረ ሳርክን ይዞ እስከ ጋዝጌ፤ መላዋን የአላፋና ጣቁሳ እና የአገው ምድርን ያስተማረ)
✤ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ዘደብረ ባሕርይ) (የኢትዮጵያ መብራት)፤ አብዛኛዋን የኢትዮጵያ ምድር ያስተማረና ቤተ ክርስቲያንን ከ40 በላይ በሚደርሱ ድርሳናቱ ያስጌጠ፡፡
✤ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ፡፡
✤✤ እንዲሁም ንጉሡ ይኵኖ አምላክ (ከንግሥናው በፊት በልጅነቱ ያደገውና የተማረው ከጻድቁ ዘንድ ነው፡፡)
❤5
፠ ጻድቁ በአጠቃላይ 44 ዓመታትን ማለትም፤
* 20 ዓመት በይትባረክ ዘመነ መንግሥት
* 15 ዓመት በይኵኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት
* 9 ዓመት በአግብዓ ጽዮን ዘመነ መንግሥት የኖሩ ሲኾን፤ ለ44 ዓመታት በገዳም ቆይታቸው ለዓይናቸው እንቅልፍን አላስመኙትም፥ ለሰውነታቸውም(ለጎናቸውም) ምኝታን አላስለመዱትም፡፡
‹‹እንዘ የኀሊ ዘበሰማያት ዐስቦ፤
መጠነ ዓመታት ሃምሳ ኢሰከበ በገቦ፡፡›› እንዲል፡፡
ጻድቁ በሐይቅ ውስጥ ገብተው ሲጸልዩም የብርሃን ምሰሶ ይወርድላቸው ነበር፡፡
** የማረፊያው እለት በደረሰ ጊዜ ደቀመዛሙርቱና ሰዎች ተሰባሰቡ፤ በደብረ ነጐድጓድ ያደገውን ተክለ ኢየሱስን መምህር አድርጎ ሾመላቸው እነርሱንም ባርኳቸው፤ ኅዳር 26 በ1286ዓ.ም. በእለተ እሑድ ጧት ፀሐይ ስትወጣ ዐረፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም እንደሚገባ አድርገው በፍየል ሌጦ አድርገው ገንዘው በክብር ቀበሩት፡፡
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
* 20 ዓመት በይትባረክ ዘመነ መንግሥት
* 15 ዓመት በይኵኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት
* 9 ዓመት በአግብዓ ጽዮን ዘመነ መንግሥት የኖሩ ሲኾን፤ ለ44 ዓመታት በገዳም ቆይታቸው ለዓይናቸው እንቅልፍን አላስመኙትም፥ ለሰውነታቸውም(ለጎናቸውም) ምኝታን አላስለመዱትም፡፡
‹‹እንዘ የኀሊ ዘበሰማያት ዐስቦ፤
መጠነ ዓመታት ሃምሳ ኢሰከበ በገቦ፡፡›› እንዲል፡፡
ጻድቁ በሐይቅ ውስጥ ገብተው ሲጸልዩም የብርሃን ምሰሶ ይወርድላቸው ነበር፡፡
** የማረፊያው እለት በደረሰ ጊዜ ደቀመዛሙርቱና ሰዎች ተሰባሰቡ፤ በደብረ ነጐድጓድ ያደገውን ተክለ ኢየሱስን መምህር አድርጎ ሾመላቸው እነርሱንም ባርኳቸው፤ ኅዳር 26 በ1286ዓ.ም. በእለተ እሑድ ጧት ፀሐይ ስትወጣ ዐረፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም እንደሚገባ አድርገው በፍየል ሌጦ አድርገው ገንዘው በክብር ቀበሩት፡፡
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
❤4
#ኅዳር_26
#_ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተማርያም፡፡
፠ አቡነ_ሀብተማርያም በሽዋ (የራውዕይ /ቡልጋ/) ከአባታቸው ፍሬ ቡሩክ ከእናታቸው ቅድስት ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡
፠ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መናኝ ነበረች፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡
፠ ጻድቁ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ ይህንንም በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል፤ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡
፠ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ መንነዋል፤ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኰሱ በኋላም ብዙ ትርፋትንና ተጋድሎን ሠሩ፡፡ ለአብነትም፤
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ፤
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ፤
*በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ፤
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ነው፤
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ፤
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ፥ ክቡር ደሙን ይጠጣሉ፤
*በልባቸው ውስጥ በፍጹም ቂምን፥ መከፋትን አላሳደሩም፡፡
* ረአዬ ኅቡዓት በመባል ይታወቃሉ፡፡
* በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርኩት ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡
* ‹‹#ጽድቅና_ትሩፋት_እንደ_ሀብተ_ማርያም፠››
፠ ጌታችን ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔዱ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው፤
* ‹‹ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ፤ ስለ ምናኔህ፣ ስለ ተባረከ ምንኵስናህ፣ ስለ ንጹሕ ድንግልናህ፣ ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ፣ ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ፣ ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ፡፡››
* በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን፤ 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ፡፡ በስምህ የሚለምኑ፤ በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ ‹አማንየ በርእስየ› ብዬሃለሁ›› አላቸው፡፡
* ቅዱሳን መላእክትም ‹‹ሀብተ ማርያም ወንድማችን›› ሲሉ አቀፏቸው፡፡ ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው፡፡ ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች፡፡ በዝማሬም ወሰዷት፡፡
✤ ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤
1ኛ. #_መብረቅ፣
2ኛ. #_ቸነፈር፣
3ኛ. #_ረሃብ፣
4ኛ. #_ወረርሽኝ፣
5ኛ. #_የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
፠ በተሰጣቸው ቃል ኪዳንም ከላይ ያሉትን 5ት መቅሰፍቶች የሚያርቁ በመሆናቸው፤ ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን በደብረ ሊባኖስ ገዳም እነዚህ 5ቱ መቅሰፍቶች እንዳይቀርቡ የሀብተማርያም ካህናት ከኅዳር 1-7(10) ማዕጠንት ያጥናሉ፤ ደብረ ሊባኖስ ገዳምም ለደብረ ይሰበይ አቡነ ሀብተማርያም ገዳም 1ድ በሬ ስጦታን ያበረክታሉ፡፡
፠ በዛሬው ዕለት በኅዳር 26 ባረፈ ጊዜ፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው፤ በዝማሬ ፥ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በጻድቁ መቃብር ቀበሩት፡፡
(ከወርቅ ንፁህ ፥ ከብርም የጠራ ፥ ከሁሉ የሚበልጥ ፥ የተመረጠ ፥ ሀብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡)
#_በዛሬዋ ዕለት #በናግራን ያሉ ክርስቲያኖች በ6ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት የኾኑበት ዕለትም ነው፡፡
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
#_ኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_ሀብተማርያም፡፡
፠ አቡነ_ሀብተማርያም በሽዋ (የራውዕይ /ቡልጋ/) ከአባታቸው ፍሬ ቡሩክ ከእናታቸው ቅድስት ዮስቴና ነው የተወለዱት፡፡
፠ ወላጆቹ በተለይም እናቱ ከማግባቷ በፊት መናኝ ነበረች፡፡ ጻድቁን እንደምትወልድ በበቃ ባሕታዊ ተነግሯት ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡
፠ ጻድቁ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ ይህንንም በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል፤ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡
፠ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ መንነዋል፤ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኰሱ በኋላም ብዙ ትርፋትንና ተጋድሎን ሠሩ፡፡ ለአብነትም፤
*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ፤
*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ፤
*በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ፤
*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ነው፤
*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ፤
*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ፥ ክቡር ደሙን ይጠጣሉ፤
*በልባቸው ውስጥ በፍጹም ቂምን፥ መከፋትን አላሳደሩም፡፡
* ረአዬ ኅቡዓት በመባል ይታወቃሉ፡፡
* በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርኩት ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡
* ‹‹#ጽድቅና_ትሩፋት_እንደ_ሀብተ_ማርያም፠››
፠ ጌታችን ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔዱ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው፤
* ‹‹ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ፤ ስለ ምናኔህ፣ ስለ ተባረከ ምንኵስናህ፣ ስለ ንጹሕ ድንግልናህ፣ ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ፣ ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ፣ ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ፡፡››
* በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን፤ 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ፡፡ በስምህ የሚለምኑ፤ በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ ‹አማንየ በርእስየ› ብዬሃለሁ›› አላቸው፡፡
* ቅዱሳን መላእክትም ‹‹ሀብተ ማርያም ወንድማችን›› ሲሉ አቀፏቸው፡፡ ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው፡፡ ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች፡፡ በዝማሬም ወሰዷት፡፡
✤ ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤
1ኛ. #_መብረቅ፣
2ኛ. #_ቸነፈር፣
3ኛ. #_ረሃብ፣
4ኛ. #_ወረርሽኝ፣
5ኛ. #_የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡
፠ በተሰጣቸው ቃል ኪዳንም ከላይ ያሉትን 5ት መቅሰፍቶች የሚያርቁ በመሆናቸው፤ ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን በደብረ ሊባኖስ ገዳም እነዚህ 5ቱ መቅሰፍቶች እንዳይቀርቡ የሀብተማርያም ካህናት ከኅዳር 1-7(10) ማዕጠንት ያጥናሉ፤ ደብረ ሊባኖስ ገዳምም ለደብረ ይሰበይ አቡነ ሀብተማርያም ገዳም 1ድ በሬ ስጦታን ያበረክታሉ፡፡
፠ በዛሬው ዕለት በኅዳር 26 ባረፈ ጊዜ፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው፤ በዝማሬ ፥ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በጻድቁ መቃብር ቀበሩት፡፡
(ከወርቅ ንፁህ ፥ ከብርም የጠራ ፥ ከሁሉ የሚበልጥ ፥ የተመረጠ ፥ ሀብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡)
#_በዛሬዋ ዕለት #በናግራን ያሉ ክርስቲያኖች በ6ኛው ክፍለ ዘመን ሰማዕታት የኾኑበት ዕለትም ነው፡፡
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
❤17