Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
15.3K subscribers
14.7K photos
78 videos
156 files
1.71K links
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።
Download Telegram
የአምና ማስታወሻ...
 💒  ቸሩ መድኃኔዓለም ዕድሜን ለንስሐ ጨምሮ ለዚህ ቀን ካደረሰን
              የእናታችን ቅድስት ኪዳነምሕረት 29 ዓመት ዝክር በታላቅ ድምቀት ፤ በዚህም ዓመት የደብራችን አስተዳዳሪ ፣ የሰንበት ትምህርት ቤታችን የበላይ ጠባቂ አባት መጋቤ ምሥጢር ቀጸላ ፈንቴ እንዲሁም ዘማርያን በተገኙበት ለማክበር ሽር ጉድ እያልን ነው
📆 በዕለቱ እኔ ሌላ ቀጠሮ አልይዝም
      🙎🏽‍♀️🙎🏽‍♂️  አንቺም እህቴ ፤ አንተም ወንድሜ
           📍📖 ቀጠሮህን በፍኖተ
                      "  የአብሮነት ቀን
"
22👍1
"ገዳማውያንን መግደል የሚያስገኘው ትርፍ የለም" 
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ

"ገዳማውያንን መግደል የሚያስገኘው ትርፍ የለም" ሲሉ  ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገለጹ።

ብፁዕነታቸውን ይሄንን ያሉት በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም መነኮሳት ላይ በደረሰው የግፍ ግድያ አስመልክተው በፌስቡክ ገጻቸው ባሠፈሩት የኀዘን መግለጫ  ነው።
 
ድርጊቱ በቤተ ክርስቲያንና በክርስትና ላይ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት ከማሳያቱ በላይ ራሳቸውን ከዓለም ለይተው በበዓታቸው ተወስነው ያሉ መነኮሳትን በግፍ መግደል ትርፍ የሌለውና ልብ የሚሰብር አሳዛኝ ድንጊትም ነው ብለዋል።

ሙሉ መልእክታቸው እንደሚከተለው ነው።

"በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ።” ዮሐ ፲፮፥፴፫

በትናንትናው ዕለት በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስቅዱስ ገዳም በገዳማውያን አባቶች ላይ በታጣቂ ኃይሎች የደረሰው ግፍ የተሞላበት ግድያ ዓለም በክርስትና እና በክርስቲያኖች ላይ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት የሚያሳይ ነው።

በበዓታቸው ተወስነው ራሳቸውን ከዓለም ለይተው በጸሎት እና በጾም የሚደክሙ ገዳማውያንን መግደል የሚያስገኘው ትርፍ የሌለ ከመሆኑም በላይ የፍትሕን መዛባት የሚያሳይ፤ አሳዛኝና ልብ የሚሰብር ነው።

የሰማዕታቱ በረከት አይለየን !
አባ ሄኖክ
የደቡብና የምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት
ሊቀ ጳጳስ
😢318
🌿           💒 ሰኔ 16 💒
         ዝክረ ቅድስት ኪዳነ ምህረት

፦ በደመቀ መልኩ የሰበካ ጉባኤ አባላት ካህናት አባቶች ፣ ነባር አባላት በተገኙበት እንዲህ ባማረ መልኩ ተከብሮ ዋለ ።

❝  ሁሉን ታደርግ ዘንድ ቻይ እንደ ሆንህ ፥
       አሳብህም ይከለከል ዘንድ ከቶ 
         እንደማይቻል አወቅሁ። ❞

              [ ኢዮ . ፵፪ ፥ ፪   ]