Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
15.3K subscribers
14.7K photos
78 videos
156 files
1.71K links
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።
Download Telegram
#ግንቦት_24_በዓተ_ግብጽ_፤ እመቤታችን እመ አምላክ ድንግል ማርያም ከልጇና ከአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ጋር ለ3 ዓመት ከ6 ወር ከተሰደዱ በኋላ ወደ ግብጽ ሃገር ገብታ በሰላም ያረፈችበት ቀን ነው፡፡
ዖፍኒ ረከበት ላቲ ቤተ፤ ወፍም ቤቷን ሰራች፡፡ መዝ. ፹፫፥፫
*በአዲስ አበባ ታቦተ ሕጉ የሚነግሥባቸው ቦታዎች፤
፠እንጦጦ መንበረ ንግሥት ቅድስት ቊስቋም ማርያም፡፡ (365ት ቀናት ሙሉ ዝክር በማኅበረ መድኀኔ ዓለም አዳራሽ የሚዘከርባት ቤ/ክ)
፠ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን፡፡ (የቤ/ክርስቲያኑ ዐጸድ እጅጉን ልብን የሚገዛና የሚማርክ)
24
የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ግብፅ ሀገር የገባበት በዓል ላይ 8 አዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ሾመዋል።

አዳዲሶቹ ኤጲስ ቆጶሳት በተለያዩ አህጉረ ስብከት እና በታላላቅ ገዳማት ኃላፊነት የተሾሙ ናቸው። ኤጲስ ቆጶሳቱ በቅርቡ ያረፉትን ብፁዓን ጳጳሳትን ሜትሮፖሊታን ጳኩሚስ፣ ኤጲስ ቆጶስ አግቢዮስን እና ኤጲስ ቆጶስ ሚካኤልን ክፍተትና ሌሎች ክፍተቶችን ለመሙላት የተደረገ መሆኑን ቅዱስነታቸው ተናግረዋል። በፓትርያርክ አቡነ ታዋድሮስ አንብሮተ ዕድ የተሾሙ መነኮሳት

1. አባ ገብርኤል አል-ማህራቂ  በኤጲስ ቆጶስ ጳኩሚስ ስም በአል-ቃላሊ ተራራ ኤልቃላሊ የእስክንድርያ የቅዱስ መቃርስ ገዳም ሊቀ ጳጳስ እና አበምኔት
2. አባ አንድራዎስ አል-ሶሪያኒ - ብፁዕ አቡነ ካራስ  ተብለው የማትሮው ሀገረ ስብከት እና የአምስቱ ምዕራባዊ ከተሞች ጳጳስ
3. አባ ቴዎፋን አቫ ሚና - ብፁዕ አቡነ ሚና ተብለው የቦርግ አል አረብ ሀገረ ስብከት ጳጳስ
4. አባ ዳንኤል አል-ጊዮርጊስ - ብፁዕ አቡነ ቦክተር ተብለው የዲርምዋስ እና ዴልጋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ
5. አባ ዲስኮረስ አል-አንቱኒ - ብፁዕ አቡነ ዲስኮረስ ተብለው የደቡባዊ ጀርመን እና በክሮፍልባች የቅዱስ አንቶኒ ገዳም አበምኔትና ጳጳስ
6. አባ ኦሎጊዩስ አል-ባራሞሲ - ብፁዕ አቡነ ኦሎጊዩስ ተብለው በአይን ሻምስ፣ ማታሪያ እና ሄልሚት ኤል-ዘይቱን ላሉት አብያተ ክርስቲያናት ጳጳስ
7. አባ ያኮቦስ አንባ ቢሾይ - ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ ተብለው በሃዳቅ አል-ቁባ፣ አል-ዋይሊ፣ አባሲያ እና ማንሺየት አል-ሳድር ላሉት አብያተ ክርስቲያናት  ጳጳስ።
8. አባ ኢግናቲየስ አል-ሶሪያኒ - ብፁዕ አቡነ ኢግናቲየስ ተብለው የቄና ሀገረ ስብከት ጳጳስ እና የሜትሮፖሊታን ሻሮቢም ረዳት ጳጳስ ሆነው ተሹመዋል።

/ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል።/

• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott

• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot 
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
9
ዜና ዕረፍት

የፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ት ቤት ቀደምትና አንጋፋ አባል የሆነው አሰግደው ጌትዬ
ዛሬ ግንቦት ፳፭ ቀን ፳፻፲፯ዓ.ም ሌሊት ፰ ሰዓት ላይ ከዚህ ዓለም ድካም በሞተ ሥጋ ተለይቷል። ወንድማችን ለረጅም ዓመታት እናት ቤተክርስቲያናቸውን በሰንበት ት/ት ቤት በኩል በተለያዩ የአገልግሎት ደረጃዎች ያገለገለ እና በማገልገል ላይ የነበረ ታላቅ ወንድማችን ነበረ ። ለቤተሰቦቹና ለወዳጅ ዘመድ መፅናናትን እንመኛለን ።

ቀብሩ ዛሬ ግንቦት 25 ከ7:00 - 8:00
በቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤ/ክር ይፈጸማል
😢8910