በአምባ አራዶም 50 ሺህ፣ በሽሬና በተንቤን 15 ሺህ ሰው ሙቶ 200 ሺህ ሰው ቆስሏል፡፡
በሚያዝያ 24/1928 ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ለተባበሩት መንግሥታት አቤቱታ ሊያቀርቡ ወደ ጄኔቫ ሄዱ፤ በሃገሪቱ ንጉሠ ነገሥቱ አለመኖሩን ጣሊያኖ ሲያውቁ በ3 ቀናት በመገስገስ በሚያዝያ 27 አዲስ አበባን ተቈጣጠሩ፡፡ በእነዚህ 3ት ቀናት ውስጥም ሽብር ዘረፈና ግድያ በአዲስ አበባ እጅጉን በርቶቶ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ የቁርጥ ልጆች የሆኑት አርበኞችም፤ ጎራዴ መዝዘው ነፍጥ ይዘው በተለያዩ ቦታዎች እምቢ ለሃገሬ በማለት ሸፈቱ፤ በጎጃም ዱር ቤቴ ያሉት ለጣሊያን ፋታ አልሰጥ አሉት፡፡ ራስ አበበ አረጋይ ግንቦት 6/1928ዓ.ም. ጅሩ ገብተው የአርበኝነት ተግባራቸውን ሲጀምሩ ሌሎች ጀግኖች አርበኞችም እርስ በእርሳቸውም ተባበሩ፡፡ ለአብነትም ዋና ዋናዎቹ ከፊት መሪዎቹና አስተባባሪዎቹ ፊታውራሪ ዘውዱ አባ ኮራን፣ ዳዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ፣ ደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው፣ ፊታውራሪ በለው ቸርነት፣ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ፣ ግራዝማች ዘውዱ አስፋው፣ ባሻ ወልደ ጻድቅ ሲሆኑ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በጎጃም ታላቁቅ የጅግንነት ጀብዱ ከፈጸመው ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ጋር ሕብረት ፈጠሩ፡፡ ይህ ሕብረትም ለጣሊያን ፋታ ሲያሳጣው፤ በሌሎች ቦታ ላሉ ኢትዮጵያውያኝ ፈር ቀዳጅ በመሆኑ ሁሉም ይተባባርና እምቢ ለሃገሬ ይል ጀመር፡፡
ለምሳሌም፤ ሰኔ 1928ዓ.ም. የሆለታ የጦር አካዳሚ ምሩቃን(ዶ.ር ያለም ወርቅ በየነን ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጦ)ና በውጭ ሃገር የተሰማሪ ሲቪሎች በመተባበር የመሠረቱት ‹‹‹ጥቁር አንበሳ›› አንዱ ነው፡፡ ‹‹ጥቁር አንበሳ›› ራስ እምሩን መሪው በማድረግ ብዙ ጀብዱዎችን ፈጽሟል፤ ጣሊያን ደቡብ ኢትዮጵያን ለመያዝ ካቶሊካዊውን ደጃዝማች ሀብተ ማርያምን በመጠቀም ቦንጋ አውሮፕላኖቿን ስታሳርፍ የጥቁር አንበሳ ማኅበርም በቦንጋ አውሮፕላን ማረፊያ የሰራው ጀብዱ ግን ከሁሉም የላቀና የማይረሳ ነው፡፡
ስለ ታላቁ አርበኛ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ እንዲሁም ለጃዝማች ኃይሉ እንዲህ ተብሎ ተገጥሞላቸዋል፤
እውነተኛው ጀግና ኃይለ ማርያም፤
ስሙ እንዳይረሳ ጻፈልን በደም፡፡
እንዲህ ያለው ጀግና እንዲህ ያለ ወንድ፤
ጌጥ ይሆናቸዋል ለታሪኮች ዐምድ፡፡ የተባለለት
የደጃዝማች ኃይሉ እጁ ውድ ናት፤
የቀመሱ ሁሉ ሲያመሰግኗት፡፡
ሌላው ፋሽስትን በተባበረና ስልታዊ በሆነ መልኩ በሐምሌ 21/1928ዓ.ም. በአዲስ አበባ መቀመጫና መቆሚያ ያሳጡት የሸዋ አርበኞች ሲሆኑ አሰላለፋቸውም፤
በሰሜን አዲስ አበባ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች አበራ ካሣና ወንድወሰን ካሣ የሚመሩት ሲሆን በውስጡ ሰማዕት የሆኑትን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን ያካተተ ነው፡፡
በሰሜን ምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በራስ አበበ አረጋይ የሚመራ፡፡
በምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው (አባ ተጫን)ና ነጋድራስ ቦጋለ የሚመራ፡፡
በደቡብ አዲስ አበባ፤ በደጃዘማች ባልቻ አባ ነፍሶ የሚመራ ሠራዊት ተጀምሯል፡፡ነገር ግን ወቅቱ ክረምት በመሆኑና ወንዞች በመሙላታቸው አርበኞች ተቀናጅተው እንዳይዋጉና ሕዝቡንም እንዳይቀሰቅሱ ትልቅ እክል ሁኖባቸው ነበር፡፡ በዚህም ሙሉ አዲስ አበባ ላይ አደጋ ጥሎ ጣሊያንን የማስለቀቁ ተግባር የታለመለትን ያክል ባየሳካም በጠቂት አቅጣጫዎች ጀግኖች አርበኞች ተዋግተዋል፡፡ የተወሰኑትም ወደ ፍቼ ሸሽተዋል፤ ታላቁ አባት ብፁዕ ጴጥሮስም የታያዙት በዚሁ ወቅት ነበር፡፡ ጀግኖቹም ጣሊያንን እምቢ ለሃገገሬ በማለት እስከ የካቲት 12/1929ዓ.ም. የጉያ ረመጥ ሁነውበታል፡፡
ከ1927-1934 ዓ.ም. ለ7ት ዓመታት ጣሊያን በሀጋረችን ላይ ያደረሰችው ጥፋት፤
*በኢትዮጵያ ሰሜንና ደቡብ በየቀለቡና በማደሪያው ከዘመተው የሞቱ፤
*ጠላት አዲስ አበባ በገባ ጊዜ ዓረቦችና ዓርመኖች ግሪኮች ተዘርፈናል በማለታቸው ምክንያት የሞቱ፤
**የካቲት ሚካኤል (የካቲት 12) ዕለት በአካፋ በዱላ በእሳት ያለቁ የሞቱ፤
*በአርበኝነት በየጊዜው በጠላት እጅ የሞቱ፤
*በደኅንነት አገር ቤት ላይ ሳሉ ሳያስቡት በጠላት እጅ የሞቱ፤
*ወደ ስደት ሲሄዱ በችግር ምክንያት በየመንገዱ የሞቱ፤
*በፌርማቶሪ አመልካችነት በየቀኑ የሞቱ፤
*ጠላት ከኢትዮጵያ ሊወጣ ሲል በተደረገው ጦርነት የሞቱ፤
*ከጠላት ወገን ሆነው (ባንዳዎች) ሆነው ከተዋጉ ባንዳ የሞቱ፡፡
*ሞሶሎኒ ባነሳው ጦርነት በየቀኑ በሚደረገው የግፍ ሥራ ያላግባብ የሞቱ (በሆለታ ተማሪ ቤት የነበሩ ወጣቶች፣
#የካቲት_12/1929ዓ.ም. (#የሰማዕታት_ቀን)
ግራዚያኒ በናፖሊ መስፍን አልጋ ወራሹ ኡምቤርቶ ወራሽ በማግኘቱ ምክንያት ዐርብ የካቲት 12/1929ዓ.ም. በአዲስ አበባ የሚገኙ ድሃዎችንና ነዳያንን እንዲሰበሰቡ አደረገ፡፡ በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ቀትር ላይም ንግግር ማድረግ ሲጀምር በወቅቱ የተገኙትና የጣሊያን ፋሽስትነት ያንገፈገፋቸው አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ሰባት ቦንብ በግራዚያኑ ላይ ወረወሩ፤ በጥቃቱም ግራዚያኑ 365 ቦታዎች ላይ ቆሰለ /በይበልጥ እግሩ ቆሰለ/፣ 3ት ኢጣሊያናውያን ሞቱ፣ 50 ቆሰሉ፣ በተለይም የጦር አዛዡ አውራሊያ ሊአታ ከን ዓይኑ ጠፋ፡፡ በዚህም አንድም ኢትዮጵያዊ እንዳያመልጥህ ግደል በመታዘዙ በፋሽስት ኢጣሊያ በመትረየስ፣ .... በአካፋ ጭምር ሊረዳ የመጣውን ድሃና ነዳይን ጨምሮ 30 ሺህ የአዲስ አበባ ነዋሪ በሰዕትነት አረፈ፡፡ ይህ ግድያ ወደ ታላላቆቹ ገዳማትና አድባራትም በመዛመት በደብረ ሊባኖስ ያሉ 2200፤በዝቋላ ገዳምም 120 መነኰሳትና ምዕመናን ተረሸኑ፡፡ አስከሬናቸውንም ክብር ባለመስጠት በአካፋ በማንሳት አሰቃዩት፡፡ እንዲሁም 350 የሚጠጉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ወደ ሮምና ሞቃድሾ እስር ቤት ተላኩ፤ ከ2500 በላይ ደግሞ በእስር ቤት ታጉረው እንዲማቅቁ ተደረጉ፡፡ በእስረኞችና በምርኮኞች ላይም አሰቃቂ ድርጊቶችን ፈጽማለች፡፡
ፋሽስት ኢጣሊያ በ5ቱ ዓመት ወረራዋ ጀግኖች አርበኞችን ስላልቻለቻቸው ንጹሐን ዜጋዎችን በመግደል፤ እንዲሁም የተደበቁበትን ገድልና ዱር አላገኝ ስትል ገዳማትንና አድባራትን አቃጥላለች፡፡ እንደ ተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት 460 770 (በጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጽሐፋቸው ደግሞ 746 800 ሰዎችን በግፍ ገድላለች፤ 300ሺህ ሰዎች ደግሞ በስደት ሲንከራተቱ በረሃብ አልቀዋል፤ 2000 አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥላላች፣ በርካታ ንዋያተ ቅድሳትንም ዘርፋ ለካቶሊኳ ቫቲካን ሰጥታለች፡፡ ለአብነትም ካቃጠለቻቸው ገዳማትና አድባራት መካከል፤
*ይደመቆ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን /ሰሜን ሸዋ/
*አፈር ባይኔ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
*አክርሚት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
*ጎበጥ አገር ገብርኤል ቤ.ክ ሰሜን ሸዋ እም ምሕረት/
*አንኮበር ቅድስት ማርያም ቤ.ክ.
*ደረፎ ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. /ሰሜን ሸዋ ደረፎ/
*ጎንቻ መድኃኔ ዓለም ገዳም /ምሥራቅ ጎጃም/
*አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. ይገኙበታል፡፡ (ምንም እንኳን አልፎ አልፎ እንደ ማኅበረ ሥላሴ ያሉ ገዳማት አባቶች በጸሎታቸው አውሮፕላናቸውን እንዲከሰከሱ ቢያደርጉባቸውም)
ኢጣሊያ ላደረሰችው ጥፋት 326 ቢሊዮን ሊሬ ቢወሰንባትም የሰጠችው ግን 105 ቢሊዮን ሊሬ ብቻ ነው፡፡ (እንደ ጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ ዘገባ ደግሞ 175 ሚሊዮን ስተርሊንግ ተወስኖባት የከፈለችው 25 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው)፡፡ በከፈለችው ገንዘብም የቆቃ ግድብ ብቻ ተሠርቶበታል፡፡
በሚያዝያ 24/1928 ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ለተባበሩት መንግሥታት አቤቱታ ሊያቀርቡ ወደ ጄኔቫ ሄዱ፤ በሃገሪቱ ንጉሠ ነገሥቱ አለመኖሩን ጣሊያኖ ሲያውቁ በ3 ቀናት በመገስገስ በሚያዝያ 27 አዲስ አበባን ተቈጣጠሩ፡፡ በእነዚህ 3ት ቀናት ውስጥም ሽብር ዘረፈና ግድያ በአዲስ አበባ እጅጉን በርቶቶ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ የቁርጥ ልጆች የሆኑት አርበኞችም፤ ጎራዴ መዝዘው ነፍጥ ይዘው በተለያዩ ቦታዎች እምቢ ለሃገሬ በማለት ሸፈቱ፤ በጎጃም ዱር ቤቴ ያሉት ለጣሊያን ፋታ አልሰጥ አሉት፡፡ ራስ አበበ አረጋይ ግንቦት 6/1928ዓ.ም. ጅሩ ገብተው የአርበኝነት ተግባራቸውን ሲጀምሩ ሌሎች ጀግኖች አርበኞችም እርስ በእርሳቸውም ተባበሩ፡፡ ለአብነትም ዋና ዋናዎቹ ከፊት መሪዎቹና አስተባባሪዎቹ ፊታውራሪ ዘውዱ አባ ኮራን፣ ዳዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ፣ ደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው፣ ፊታውራሪ በለው ቸርነት፣ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ፣ ግራዝማች ዘውዱ አስፋው፣ ባሻ ወልደ ጻድቅ ሲሆኑ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በጎጃም ታላቁቅ የጅግንነት ጀብዱ ከፈጸመው ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ጋር ሕብረት ፈጠሩ፡፡ ይህ ሕብረትም ለጣሊያን ፋታ ሲያሳጣው፤ በሌሎች ቦታ ላሉ ኢትዮጵያውያኝ ፈር ቀዳጅ በመሆኑ ሁሉም ይተባባርና እምቢ ለሃገሬ ይል ጀመር፡፡
ለምሳሌም፤ ሰኔ 1928ዓ.ም. የሆለታ የጦር አካዳሚ ምሩቃን(ዶ.ር ያለም ወርቅ በየነን ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጦ)ና በውጭ ሃገር የተሰማሪ ሲቪሎች በመተባበር የመሠረቱት ‹‹‹ጥቁር አንበሳ›› አንዱ ነው፡፡ ‹‹ጥቁር አንበሳ›› ራስ እምሩን መሪው በማድረግ ብዙ ጀብዱዎችን ፈጽሟል፤ ጣሊያን ደቡብ ኢትዮጵያን ለመያዝ ካቶሊካዊውን ደጃዝማች ሀብተ ማርያምን በመጠቀም ቦንጋ አውሮፕላኖቿን ስታሳርፍ የጥቁር አንበሳ ማኅበርም በቦንጋ አውሮፕላን ማረፊያ የሰራው ጀብዱ ግን ከሁሉም የላቀና የማይረሳ ነው፡፡
ስለ ታላቁ አርበኛ ልጅ ኃይለ ማርያም ማሞ እንዲሁም ለጃዝማች ኃይሉ እንዲህ ተብሎ ተገጥሞላቸዋል፤
እውነተኛው ጀግና ኃይለ ማርያም፤
ስሙ እንዳይረሳ ጻፈልን በደም፡፡
እንዲህ ያለው ጀግና እንዲህ ያለ ወንድ፤
ጌጥ ይሆናቸዋል ለታሪኮች ዐምድ፡፡ የተባለለት
የደጃዝማች ኃይሉ እጁ ውድ ናት፤
የቀመሱ ሁሉ ሲያመሰግኗት፡፡
ሌላው ፋሽስትን በተባበረና ስልታዊ በሆነ መልኩ በሐምሌ 21/1928ዓ.ም. በአዲስ አበባ መቀመጫና መቆሚያ ያሳጡት የሸዋ አርበኞች ሲሆኑ አሰላለፋቸውም፤
በሰሜን አዲስ አበባ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች አበራ ካሣና ወንድወሰን ካሣ የሚመሩት ሲሆን በውስጡ ሰማዕት የሆኑትን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን ያካተተ ነው፡፡
በሰሜን ምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በራስ አበበ አረጋይ የሚመራ፡፡
በምሥራቅ አዲስ አበባ፤ በደጃዝማች ፍቅረ ማርያም ናደው (አባ ተጫን)ና ነጋድራስ ቦጋለ የሚመራ፡፡
በደቡብ አዲስ አበባ፤ በደጃዘማች ባልቻ አባ ነፍሶ የሚመራ ሠራዊት ተጀምሯል፡፡ነገር ግን ወቅቱ ክረምት በመሆኑና ወንዞች በመሙላታቸው አርበኞች ተቀናጅተው እንዳይዋጉና ሕዝቡንም እንዳይቀሰቅሱ ትልቅ እክል ሁኖባቸው ነበር፡፡ በዚህም ሙሉ አዲስ አበባ ላይ አደጋ ጥሎ ጣሊያንን የማስለቀቁ ተግባር የታለመለትን ያክል ባየሳካም በጠቂት አቅጣጫዎች ጀግኖች አርበኞች ተዋግተዋል፡፡ የተወሰኑትም ወደ ፍቼ ሸሽተዋል፤ ታላቁ አባት ብፁዕ ጴጥሮስም የታያዙት በዚሁ ወቅት ነበር፡፡ ጀግኖቹም ጣሊያንን እምቢ ለሃገገሬ በማለት እስከ የካቲት 12/1929ዓ.ም. የጉያ ረመጥ ሁነውበታል፡፡
ከ1927-1934 ዓ.ም. ለ7ት ዓመታት ጣሊያን በሀጋረችን ላይ ያደረሰችው ጥፋት፤
*በኢትዮጵያ ሰሜንና ደቡብ በየቀለቡና በማደሪያው ከዘመተው የሞቱ፤
*ጠላት አዲስ አበባ በገባ ጊዜ ዓረቦችና ዓርመኖች ግሪኮች ተዘርፈናል በማለታቸው ምክንያት የሞቱ፤
**የካቲት ሚካኤል (የካቲት 12) ዕለት በአካፋ በዱላ በእሳት ያለቁ የሞቱ፤
*በአርበኝነት በየጊዜው በጠላት እጅ የሞቱ፤
*በደኅንነት አገር ቤት ላይ ሳሉ ሳያስቡት በጠላት እጅ የሞቱ፤
*ወደ ስደት ሲሄዱ በችግር ምክንያት በየመንገዱ የሞቱ፤
*በፌርማቶሪ አመልካችነት በየቀኑ የሞቱ፤
*ጠላት ከኢትዮጵያ ሊወጣ ሲል በተደረገው ጦርነት የሞቱ፤
*ከጠላት ወገን ሆነው (ባንዳዎች) ሆነው ከተዋጉ ባንዳ የሞቱ፡፡
*ሞሶሎኒ ባነሳው ጦርነት በየቀኑ በሚደረገው የግፍ ሥራ ያላግባብ የሞቱ (በሆለታ ተማሪ ቤት የነበሩ ወጣቶች፣
#የካቲት_12/1929ዓ.ም. (#የሰማዕታት_ቀን)
ግራዚያኒ በናፖሊ መስፍን አልጋ ወራሹ ኡምቤርቶ ወራሽ በማግኘቱ ምክንያት ዐርብ የካቲት 12/1929ዓ.ም. በአዲስ አበባ የሚገኙ ድሃዎችንና ነዳያንን እንዲሰበሰቡ አደረገ፡፡ በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ቀትር ላይም ንግግር ማድረግ ሲጀምር በወቅቱ የተገኙትና የጣሊያን ፋሽስትነት ያንገፈገፋቸው አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ሰባት ቦንብ በግራዚያኑ ላይ ወረወሩ፤ በጥቃቱም ግራዚያኑ 365 ቦታዎች ላይ ቆሰለ /በይበልጥ እግሩ ቆሰለ/፣ 3ት ኢጣሊያናውያን ሞቱ፣ 50 ቆሰሉ፣ በተለይም የጦር አዛዡ አውራሊያ ሊአታ ከን ዓይኑ ጠፋ፡፡ በዚህም አንድም ኢትዮጵያዊ እንዳያመልጥህ ግደል በመታዘዙ በፋሽስት ኢጣሊያ በመትረየስ፣ .... በአካፋ ጭምር ሊረዳ የመጣውን ድሃና ነዳይን ጨምሮ 30 ሺህ የአዲስ አበባ ነዋሪ በሰዕትነት አረፈ፡፡ ይህ ግድያ ወደ ታላላቆቹ ገዳማትና አድባራትም በመዛመት በደብረ ሊባኖስ ያሉ 2200፤በዝቋላ ገዳምም 120 መነኰሳትና ምዕመናን ተረሸኑ፡፡ አስከሬናቸውንም ክብር ባለመስጠት በአካፋ በማንሳት አሰቃዩት፡፡ እንዲሁም 350 የሚጠጉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ወደ ሮምና ሞቃድሾ እስር ቤት ተላኩ፤ ከ2500 በላይ ደግሞ በእስር ቤት ታጉረው እንዲማቅቁ ተደረጉ፡፡ በእስረኞችና በምርኮኞች ላይም አሰቃቂ ድርጊቶችን ፈጽማለች፡፡
ፋሽስት ኢጣሊያ በ5ቱ ዓመት ወረራዋ ጀግኖች አርበኞችን ስላልቻለቻቸው ንጹሐን ዜጋዎችን በመግደል፤ እንዲሁም የተደበቁበትን ገድልና ዱር አላገኝ ስትል ገዳማትንና አድባራትን አቃጥላለች፡፡ እንደ ተባበሩት መንግሥታት ሪፖርት 460 770 (በጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጽሐፋቸው ደግሞ 746 800 ሰዎችን በግፍ ገድላለች፤ 300ሺህ ሰዎች ደግሞ በስደት ሲንከራተቱ በረሃብ አልቀዋል፤ 2000 አብያተ ክርስቲያናትን አቃጥላላች፣ በርካታ ንዋያተ ቅድሳትንም ዘርፋ ለካቶሊኳ ቫቲካን ሰጥታለች፡፡ ለአብነትም ካቃጠለቻቸው ገዳማትና አድባራት መካከል፤
*ይደመቆ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን /ሰሜን ሸዋ/
*አፈር ባይኔ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
*አክርሚት ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ /ሰሜን ሸዋ/
*ጎበጥ አገር ገብርኤል ቤ.ክ ሰሜን ሸዋ እም ምሕረት/
*አንኮበር ቅድስት ማርያም ቤ.ክ.
*ደረፎ ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. /ሰሜን ሸዋ ደረፎ/
*ጎንቻ መድኃኔ ዓለም ገዳም /ምሥራቅ ጎጃም/
*አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. ይገኙበታል፡፡ (ምንም እንኳን አልፎ አልፎ እንደ ማኅበረ ሥላሴ ያሉ ገዳማት አባቶች በጸሎታቸው አውሮፕላናቸውን እንዲከሰከሱ ቢያደርጉባቸውም)
ኢጣሊያ ላደረሰችው ጥፋት 326 ቢሊዮን ሊሬ ቢወሰንባትም የሰጠችው ግን 105 ቢሊዮን ሊሬ ብቻ ነው፡፡ (እንደ ጥላሁን ብርሃነ ሥላሴ ዘገባ ደግሞ 175 ሚሊዮን ስተርሊንግ ተወስኖባት የከፈለችው 25 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው)፡፡ በከፈለችው ገንዘብም የቆቃ ግድብ ብቻ ተሠርቶበታል፡፡
👍8🙏2❤1
ዐጤ ኃይለ ሥላሴም ወደ ሃገራቸው ከተመለሱ በኋላ በ6 ኪሎ ለሰማዕታቱ ሐውልት ቆመ መጀመሪያ የተሠራው አነስተኛ በመሆኑ ኋላ አሁን ያለው ትልቅ ተደርጎ ተሠርቷል፡፡ ቀኑ እንዳይረሳም ቤተ ሳይዳ ተብሎ ይጠራ የነበረው የካቲት 12 ሆስፒታል ተባለ፡፡ ከ8 ዓመት በኋላም የሰማዕታቱንም ዐፅም ሰብሰብሰበውና አፍልሰው በ4ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በክብር እንዲያርፍና መቃብር ቤት እንዲሠራለት ተደረገ፡፡ በሐውልቱ ላይ ያለው ጽሑፍና ግጥም እንዲህ ይነበባል፤
#‹‹ዝንቱ ውእቱ ምዕራፈ አዕጽምቲሆሙ ለብዙኃን ኢትዮጵያውያን እለ ተቀትሉ በግፍዕ በእደዊሆሙ ለሕዝበ ኢጣሊያ ፋሽስታውያን አመ ፲ወ፪ ለየካቲት በ፲ወ፱፻፳ወ፱ ዓ.ም.፤ ወተቀትሎቶሙኒ ኮኑ በውግረተ አእባን ወበአብትር፥ በመክርይ ወበመስኤ፥ በመሕፄ ወበዕፀው፥ በመብረቀ ሐፂን ወበፀዓዕ፥ ወበውዕየተ እሳት ውስተ ቤቶሙ፡፡ ወበራብዕ ዓመት እምዘኮነ ዝንቱ ነገረ ግፍዕ ተመይጠ እግዚእነ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እም ሀገረ ብሪታንያ በግርማ መዊዕ፤ ወአቲዎ ብሔሮሙ ሠረዎሙ ለጸላእትነ ወአቀመ ትእምርተ ግዕዛንነ፡፡ ወእምድኅረዝ አዘዞሙ ለኅሩያኒሁ ከመ ያስተጋብኡ አዕጽምቲሆሙ ለእሉ እለ ተቀትሉ በግፍዕ ወያንብርዎሙ ውስተ ዝንቱ መካን ቅዱስ ዘሕኑፅ ለዝክረ ነገር ወለዝክረ ስሙ፤ ወኮነ በዓለ ፍልሰቶሙ ወተጋብኦቶሙ ለእሙንቱ አዕጽምተ ምውታን በ፲ወ፬ ዓመተ በዓለ ንግሡ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትየጵያ አመ ፳ወ፫ ለጥቅምት በዕለተ ኀሙስ በ፲ወ፱፻፴ወ፯ዓ.ም.፡፡››
#ራስን ካንገት ላይ ቈራርጦ እየጣለ፤
በችንካር ቸንክሮ ሰው እየገደለ፤
ሰውን ከነቤቱ አብሮ እያቃጠለ፤
ማነው እንደ ፋሽስት በሰው ግፍ የዋለ?፡፡
ሥጋችንን ገድለው ሳይቀብሩ እየጣሉ፤
ስማችንን ገድለው ሊቀብሩት ከጀሉ፡፡
በዚህ ያልነበሩ ሐሰት እንዳይሉ፤
እሊህ አስከሬኖች ይመሰክራሉ፡፡
ይህን ታላቅ ስቃይ መከራና ግፍ፤
ሲያስታውስ ይኖራል የታሪክ መጽሐፍ፡፡
አትርሱት አንርሳው ያስታውሰው ዘራችን፤
ኢጣሊያ መሆኗን መርዛም ጠላታችን፡፡
እናንት አእጽምቶች ዕድለኞች ናችሁ፤
በኃይለ ሥላሴ ትንሣኤ አገኛችሁ፡፡
#‹‹ዝንቱ ውእቱ ምዕራፈ አዕጽምቲሆሙ ለብዙኃን ኢትዮጵያውያን እለ ተቀትሉ በግፍዕ በእደዊሆሙ ለሕዝበ ኢጣሊያ ፋሽስታውያን አመ ፲ወ፪ ለየካቲት በ፲ወ፱፻፳ወ፱ ዓ.ም.፤ ወተቀትሎቶሙኒ ኮኑ በውግረተ አእባን ወበአብትር፥ በመክርይ ወበመስኤ፥ በመሕፄ ወበዕፀው፥ በመብረቀ ሐፂን ወበፀዓዕ፥ ወበውዕየተ እሳት ውስተ ቤቶሙ፡፡ ወበራብዕ ዓመት እምዘኮነ ዝንቱ ነገረ ግፍዕ ተመይጠ እግዚእነ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እም ሀገረ ብሪታንያ በግርማ መዊዕ፤ ወአቲዎ ብሔሮሙ ሠረዎሙ ለጸላእትነ ወአቀመ ትእምርተ ግዕዛንነ፡፡ ወእምድኅረዝ አዘዞሙ ለኅሩያኒሁ ከመ ያስተጋብኡ አዕጽምቲሆሙ ለእሉ እለ ተቀትሉ በግፍዕ ወያንብርዎሙ ውስተ ዝንቱ መካን ቅዱስ ዘሕኑፅ ለዝክረ ነገር ወለዝክረ ስሙ፤ ወኮነ በዓለ ፍልሰቶሙ ወተጋብኦቶሙ ለእሙንቱ አዕጽምተ ምውታን በ፲ወ፬ ዓመተ በዓለ ንግሡ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትየጵያ አመ ፳ወ፫ ለጥቅምት በዕለተ ኀሙስ በ፲ወ፱፻፴ወ፯ዓ.ም.፡፡››
#ራስን ካንገት ላይ ቈራርጦ እየጣለ፤
በችንካር ቸንክሮ ሰው እየገደለ፤
ሰውን ከነቤቱ አብሮ እያቃጠለ፤
ማነው እንደ ፋሽስት በሰው ግፍ የዋለ?፡፡
ሥጋችንን ገድለው ሳይቀብሩ እየጣሉ፤
ስማችንን ገድለው ሊቀብሩት ከጀሉ፡፡
በዚህ ያልነበሩ ሐሰት እንዳይሉ፤
እሊህ አስከሬኖች ይመሰክራሉ፡፡
ይህን ታላቅ ስቃይ መከራና ግፍ፤
ሲያስታውስ ይኖራል የታሪክ መጽሐፍ፡፡
አትርሱት አንርሳው ያስታውሰው ዘራችን፤
ኢጣሊያ መሆኗን መርዛም ጠላታችን፡፡
እናንት አእጽምቶች ዕድለኞች ናችሁ፤
በኃይለ ሥላሴ ትንሣኤ አገኛችሁ፡፡
👍8
#ጀግናውና_የቅኔው_አዝመራ_አለቃ_መርሻ_ወልደ_ማርያም
ከዚህ በታች የቀረበውን ግጥማዊ ቅኔ ብዙዎቻችን እናውቀዋለን፡፡ ሊገድሏቸው የመጡትን ጣልያኖች አብዛኛውን ፈጅተው በሐምሌ 12/1928ዓ.ም. በሰማዕትነት ያረፉት የ70 አዛውንቱ ጀግናና የቅኔው አዝመራ አለቃ መርሻ ወልደ ማርያም ከመሞታቸው ከ8 ቀን ቀድመው እንዲህ ብለው ተቀኙ፡፡
ተምሮ ተምሮ ካልሰበሰቡት፤
እንዴት ያሳዝናል ሲባክን ዕውቀት፡፡
ሂጅ ተመለሽ ግቢ አገርሽ ቅኔ፤
ወንዶች ከዋሉበት መዋሌ ነው እኔ፡፡
ለጀግንነታቸውም መታሰቢያ የሚቀጥለው ግጥማዌ ቅኔ ቀረበላቸው፤
አለቃ መርሻ አይፈራም እጁ፤
ጠላት ሲጋበዝ እንደ ወዳጁ፤
ገሥግሠው ሄደው እንደ ጐመጁ፤
በሽጉጥ ጠርሙስ ፩ድ ፩ዱን ፈጁ፡፡
መርሻ ቢያጠጣው የሽጉጥ ጠላን፤
ወዲያው ወደቀ ግብዙ ጣሊያን፡፡
/ቢያነቧቸው ስለ የካቲት 12ና ስለ 5ቱ ዓመት የመከራ ዘመን በርካታ ቁም ነገርን ያስጨብትዎታል፤/
#አምስቱ የመከራ ዘመናት፣ ቅጽ 1፤ 44 የተመዘበሩ. የተቃጠሉና የጠፉ አብያተ ክርስቲያናት ታሪክ፣ እርቅይሁን በላይ፣ 2007
#“The Massacre of Debre Libanos, Ethiopia 1937” (“የደብረ ሊባኖስ እልቂት)፣ ኢያን ካምፕቤል፣ # "ሕይወቴ(ግለ ታሪክ)" ተመስገን ገብሬ፤
#የሸንቁጥ ልጆች፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ
#"Yekatit" 12 Revisited: new light on the strike against Graziani Author(s): Ian Campbell Source: Journal of Ethiopian Studies, Vol. 40, No. 1/2, Festschrift Dedicated in Honour of Prof. Richard Pankhurst & Mrs. Rita Pankhurst (June-December 2007), pp. 135-154
/ታሪኩን ከመጻሕፍት አገላብጦና ምሁራንን ጠይቆ ላቀረበልን አምላከ ኢትዮጵያ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በእድሜ በጤና ይጠብቅልን፡፡/
ከዚህ በታች የቀረበውን ግጥማዊ ቅኔ ብዙዎቻችን እናውቀዋለን፡፡ ሊገድሏቸው የመጡትን ጣልያኖች አብዛኛውን ፈጅተው በሐምሌ 12/1928ዓ.ም. በሰማዕትነት ያረፉት የ70 አዛውንቱ ጀግናና የቅኔው አዝመራ አለቃ መርሻ ወልደ ማርያም ከመሞታቸው ከ8 ቀን ቀድመው እንዲህ ብለው ተቀኙ፡፡
ተምሮ ተምሮ ካልሰበሰቡት፤
እንዴት ያሳዝናል ሲባክን ዕውቀት፡፡
ሂጅ ተመለሽ ግቢ አገርሽ ቅኔ፤
ወንዶች ከዋሉበት መዋሌ ነው እኔ፡፡
ለጀግንነታቸውም መታሰቢያ የሚቀጥለው ግጥማዌ ቅኔ ቀረበላቸው፤
አለቃ መርሻ አይፈራም እጁ፤
ጠላት ሲጋበዝ እንደ ወዳጁ፤
ገሥግሠው ሄደው እንደ ጐመጁ፤
በሽጉጥ ጠርሙስ ፩ድ ፩ዱን ፈጁ፡፡
መርሻ ቢያጠጣው የሽጉጥ ጠላን፤
ወዲያው ወደቀ ግብዙ ጣሊያን፡፡
/ቢያነቧቸው ስለ የካቲት 12ና ስለ 5ቱ ዓመት የመከራ ዘመን በርካታ ቁም ነገርን ያስጨብትዎታል፤/
#አምስቱ የመከራ ዘመናት፣ ቅጽ 1፤ 44 የተመዘበሩ. የተቃጠሉና የጠፉ አብያተ ክርስቲያናት ታሪክ፣ እርቅይሁን በላይ፣ 2007
#“The Massacre of Debre Libanos, Ethiopia 1937” (“የደብረ ሊባኖስ እልቂት)፣ ኢያን ካምፕቤል፣ # "ሕይወቴ(ግለ ታሪክ)" ተመስገን ገብሬ፤
#የሸንቁጥ ልጆች፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ
#"Yekatit" 12 Revisited: new light on the strike against Graziani Author(s): Ian Campbell Source: Journal of Ethiopian Studies, Vol. 40, No. 1/2, Festschrift Dedicated in Honour of Prof. Richard Pankhurst & Mrs. Rita Pankhurst (June-December 2007), pp. 135-154
/ታሪኩን ከመጻሕፍት አገላብጦና ምሁራንን ጠይቆ ላቀረበልን አምላከ ኢትዮጵያ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በእድሜ በጤና ይጠብቅልን፡፡/
👍8❤2
የእርዳታ ጥሪ
የደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ ፈለገ ዮርዳኖስ ሰ/ት/ቤት አባል የሆነች እኅታችን በልብ ሕመም ከሁለት ጊዜ በላይ ቀዶ ጥገና አድርጋለች የተደረገላት ህክምና በቂ ባለመሆኑ ሌላ ቀዶ ጥገና ለመደረግ ተወስኗል ለዚህ ህክምና የተጠየቀችው ገንዘብ በቂ ስላልሆነ ይህ ትኬት ተዘጋጅቷል ትኬቱ 100 ብር ነው ሁላችን በመግዛት የልጅቷን ሕይወት እናትርፍ።
ትኬቱን በሰ/ት/ ቤታችን በበጎ አድራጎት ክፍል ያገኙታል
ሄኖክ 0900021866
ሰሎሞን 0933062383 በመደወል ትኬቱን ይውሰዱ።
#Share
የደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ ፈለገ ዮርዳኖስ ሰ/ት/ቤት አባል የሆነች እኅታችን በልብ ሕመም ከሁለት ጊዜ በላይ ቀዶ ጥገና አድርጋለች የተደረገላት ህክምና በቂ ባለመሆኑ ሌላ ቀዶ ጥገና ለመደረግ ተወስኗል ለዚህ ህክምና የተጠየቀችው ገንዘብ በቂ ስላልሆነ ይህ ትኬት ተዘጋጅቷል ትኬቱ 100 ብር ነው ሁላችን በመግዛት የልጅቷን ሕይወት እናትርፍ።
ትኬቱን በሰ/ት/ ቤታችን በበጎ አድራጎት ክፍል ያገኙታል
ሄኖክ 0900021866
ሰሎሞን 0933062383 በመደወል ትኬቱን ይውሰዱ።
#Share
👍28❤12🙏9🤝2
እንኳን ለእመቤታችን ኪዳነ ምሕረት ዓመታዊ ክብረ በዓል (ቃል ኪዳን ለተቀበለችበት) በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡
ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ፤
ፈለገ እሳት ወደይን እምአስጠመ ኵሎ፡፡
(ድንግል ሆይ ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የሲኦል እሳት ባሰጠመን ነበር፡፡)
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሲዖልን ካየች በኋላ ስለኃጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች የካቲት አሥራ ስድስት ቀንም በጎልጎታ ቦታ ቆማ ወደ ልጇ እንዲህ ብላ ለመነች፡፡
ጸሎትና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ አገልጋይህ የምለምንህን ይህ ነው፡፡ መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ፣ አብያተ ክርስቲያኔን ለሚሠሩ፣ ወይም ለታረዙ ለሚያለብሱ፣ ለተራቡ ለሚያጠግቡ፣ የተጠማውንም የሚያጠጡ(በስሜ ለድሆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጡ) ፣ የታመመውንም የሚጎበኝ፣ ያዘነውንም የሚያረጋጉ፣ የተከዘውንም ደስ የሚያሰኙ ወይም ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ በዓይን ያልታየውን በጆሮ ያልተሰማውን በጎ ዋጋ ስጣቸው፡፡ በአማላጅነቴም የሚተማመኑትን ሁሉ ከሲዖል ነፃ አድርጋቸው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረሃብና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽን ቃልኪዳን እንዳይታበይ በራሴ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣት፡፡
#ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘየካቲት_16፤ #በዓለ_ኪዳነ_ምሕረት፡፡
በሃገራችን በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚቆመው፤ የ3ት ዐበይት አድባራት አብነት ነው፡፡ እነዚህም፤
1ኛ) የላይ ቤት፤ የደብረ መድኀኒት ዐቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት
2ኛ) የታች ቤት አብነት፤ የደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ
3ኛ) የደፈጫ ኪዳነ ምሕረት አብነት ናቸው፡፡
እኛም ከላይ ከተጠቀሱት ውስጥ የዐቢየ እግዚእንና የበዓታን ይትበሃል አንድ ላይ በቅደም ተከተል አድረገን አዘጋጅተንላችኋል፤ የደፈጫ ከላይ ከተጠቀሱት ከ2ቱ በጥቂት ቀለም ብቻ የሚለይ በመኾኑ አላካተትነውም፡፡ ስለዚህ እንደ የደብራችሁ ይተበሃል የላይ ቤት ከኾነ ‹‹ዘዐቢየ እግዚእ›› የሚለውን፤ የታች ቤት ከኾነ ‹‹ዘበዓታ) የሚለውን እንድትጠቀሙ እናሳስባልን፡፡
መልካም ማኅሌት፡፡
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ፤
ፈለገ እሳት ወደይን እምአስጠመ ኵሎ፡፡
(ድንግል ሆይ ቃል ኪዳንሽ ባይኖር ኖሮ የሲኦል እሳት ባሰጠመን ነበር፡፡)
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሲዖልን ካየች በኋላ ስለኃጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች የካቲት አሥራ ስድስት ቀንም በጎልጎታ ቦታ ቆማ ወደ ልጇ እንዲህ ብላ ለመነች፡፡
ጸሎትና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ አገልጋይህ የምለምንህን ይህ ነው፡፡ መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ፣ አብያተ ክርስቲያኔን ለሚሠሩ፣ ወይም ለታረዙ ለሚያለብሱ፣ ለተራቡ ለሚያጠግቡ፣ የተጠማውንም የሚያጠጡ(በስሜ ለድሆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጡ) ፣ የታመመውንም የሚጎበኝ፣ ያዘነውንም የሚያረጋጉ፣ የተከዘውንም ደስ የሚያሰኙ ወይም ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ በዓይን ያልታየውን በጆሮ ያልተሰማውን በጎ ዋጋ ስጣቸው፡፡ በአማላጅነቴም የሚተማመኑትን ሁሉ ከሲዖል ነፃ አድርጋቸው ከአንተ ጋር የደረሰብኝን ረሃብና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንዳልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽን ቃልኪዳን እንዳይታበይ በራሴ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ማልኩልሽ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣት፡፡
#ሥርዐተ_ማኅሌት_ዘየካቲት_16፤ #በዓለ_ኪዳነ_ምሕረት፡፡
በሃገራችን በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚቆመው፤ የ3ት ዐበይት አድባራት አብነት ነው፡፡ እነዚህም፤
1ኛ) የላይ ቤት፤ የደብረ መድኀኒት ዐቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት
2ኛ) የታች ቤት አብነት፤ የደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ
3ኛ) የደፈጫ ኪዳነ ምሕረት አብነት ናቸው፡፡
እኛም ከላይ ከተጠቀሱት ውስጥ የዐቢየ እግዚእንና የበዓታን ይትበሃል አንድ ላይ በቅደም ተከተል አድረገን አዘጋጅተንላችኋል፤ የደፈጫ ከላይ ከተጠቀሱት ከ2ቱ በጥቂት ቀለም ብቻ የሚለይ በመኾኑ አላካተትነውም፡፡ ስለዚህ እንደ የደብራችሁ ይተበሃል የላይ ቤት ከኾነ ‹‹ዘዐቢየ እግዚእ›› የሚለውን፤ የታች ቤት ከኾነ ‹‹ዘበዓታ) የሚለውን እንድትጠቀሙ እናሳስባልን፡፡
መልካም ማኅሌት፡፡
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/
• Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
• Telegram 👉 t.me/finotehiwott
• Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot
• YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
👍8❤5