Forwarded from የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ቤት
የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ቤት
Photo
+. እግዚአብሔር መንፈስ ነው .+
የመንፈስ ቀላል ትርጕሙ «በአካላዊነት ጎልቶ ለዐይን የማይታይ» ፣ «ከመታየት በላይ» ማለት ነው። ቃሉ ወደ አካለ እግዚአብሔር ተጠግቶ ሲነገር የበለጠ ሐሳቡን ከፍ አድርጎ ይገልጣል። እግዚአብሔር የር’ቀ’ቶች ኹሉ መነሻ ስለኾነ - አእምሮአችን ከሚያሰበው ር’ቀ’ት በላይ ረቂቅ ነው። መንፈስ የሚለውም ራሱ የእኛን አስተውሎት/መረዳት ታሳቢ ተደርጎ የተነገረ እንጂ እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው ኾኖ አይደለም። እግዚአብሔር ከምንም - ስለ እሱ ከምናስበውም ከምንናገረውምም በላይ ነው!! እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው እግዚአብሔር ብቻ ነው ፤ እግዚአብሔር በእግዚአብሔርነቱ የሚገለጥለትም አካል የተገለጠውን ለመረዳት እግዚአብሔር መኾን አለበት ፤ እግዚአብሔር የሚገልጠውን እግዚአብሔርነት ማወቅ ለማንም አልተሰጠም። ለማንም አይቻልምና።
ስለ እግዚአብሔር ያለን ዕውቀት እኛ ስለ እሱ ማወቅ የቻልነው መጠን ነው ፤ ይኽም ቢኾን በራሳችን የመጣ ሳይኾን ተገልጦልን ያወቅነው ነው። ያወቅነውም እግዚአብሔርን የማወቃችን ድንበር አይደለም። ከእግዚአብሔር መልካምነት ጋር - ነፍስ በንጽሕና ወደ እሱ በመቅረብ ስትተባበር ፥ ፈቃደ ግብረ ባሕርያቱን ስትሳተፍ እየተገለጠላት የሚኼደው ዕውቀቷ የነበራትን ዕውቀት የሚበልጥ ይኾናል። የዕውቀቷ ፍጻሜም የነበሯት ዕውቀቶች ተቋጭተው ከእነሱ በበለጠ አለማወቅ በ’መ’ያ’ዝ ይኾናል!! የነፍስ ዕውቀት ስለ እግዚአብሔር ምንም አለማወቅ ውስጥ በመግባት ይፈጸማል!! ከእሱ ጋር መኖሯ በቂዋ ስለሚኾን የማወቅ ጥማቷም ይቆረጣል!!
«እግዚአብሔር መንፈስ ነው» የዚኽ ሐሳብ ተሸካሚ ቃል ነው። መንፈስ ምንድነው!? እንደ እውነታው የዚኽን ቃል ደረቅ መዝገበ ቃላዊ ፍቺን ከማስቀመጥ ውጪ ፥ ሐሳቡን በኾነው ልክ ለልብ ማስረዳት አይቻለም ፤ መንፈስ የሚለው ሐሳብ ላይ በሰው ዘንድ ያ’ለ አለመረዳት አ’ለ - «ያ አለመረዳት እግዚአብሔር በነፍሳችን ውስጥ ያለው ቦታ ነው» ለማለት «እግዚአብሔር መንፈስ ነው» ተብሏል።
❝.. ወአልቦ ዘየአምሮ ለወልድ ዘእንበለ አብ ፤ ወለአብኒ አልቦ ዘየአምሮ ዘእንበለ ወልድ - ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር አብን የሚያውቅ የለም❞ [ማቴዎስ ፲፩፥፳፯]። ማወቅ ከተነገረስ የአብ ዕውቀት/መታወቅ ወልድ ላይ ፥ የወልድ ዕውቀትም/መታወቅ አብ ላይ ታውቆ ይቀራል። «ወለዘፈቀደ ወልድ ይከሥት ሎቱ - ወልድ ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር / ወልድ ሊገልጽለት ለወደደው ይገልጥለታል» የሚለው ቀጣይ ንባብ - በአሚን አኹን ለእኛ የተገለጠው ፥ እኛነታችን ስለ እግዚአብሔር ማወቅ የቻለው የዕውቀት መጠን ነው እንጂ አብ ወልድን ፥ ወልድም አብን የሚያውቅበት ማወቅ ለእኛ ተሰጥቷል ማለት አይደለም። አብ አብነቱ ወልድ ላይ ፥ ወልድም ወልድነቱ አብ ላይ የቀረ ነው!!
አካል ከሕሊናት ኹሉ ለራቀ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ሲነገር ፥ እኒኹ ኹሉ ታሳቢ ተደርገው ነው። የእግዚአብሔር አካል ሲባል ወደ ሕሊናችን የሚመጣው ሥዕል የእኛ መሰሉ ቅርጽ ከኾነ የእግዚአብሔርን እግዚአብሔርነት መዘንጋት ነው የሚኾነው። እንደሚታወቀው መገለጦች ኹሉ የተሰጡት ለሰዎች ነው ፤ እነዚያ መገለጦች ደግሞ በሰው መረዳት ልክ የኾኑ ናቸው ፤ ለእኛ ተመጥነው የተሰጡ መገለጦችን ያለቀላቸው የእግዚአብሔር ውክያ አድርጎ መውሰድ ይኽን የምሥጢር ድንበር መዝለል ነው።
አንድ እና ኹለት የለውም እግዚአብሔር አካላዊ ነው። በኹኔታዎች [በተፈጣሪያኑ ውስጥ ያለ ፥ እነሱም ጸንተው ያሉበት] ውጥረት እና ጽምረት የሚመላለስ/ተገላጭ ኀይልም [በእሱ የሚኾን ቢኾኖም] አይደለም ፤ አማን በአማን እግዚአብሔር አካላዊ ነው። ሰው ኹነን አካላዊነትን ከእኛ አካልነት ውጪ መረዳት አይቻለንምና ፥ የእግዚአብሔር አካል በእኛ አካል አንጻር ተገልጿል። ይኽ ማለት ቀጥታ የእኛ አካል የእግዚአብሔር አካል ተመስያ ነው ማለት አይደለም። አካለ እግዚአብሔር በእኛ ሕሊና ከሚሣለው አካል የወጣ ፥ በማንም የማይመረመር የአካሎች ኹሉ ፍጻሜ የኾነ ፍጹም አካል ነው።
በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እግዚአብሔር አካል የተነገሩ ምንባባት በዚኽ አግባብ የምንረዳቸው ናቸው። እግዚአብሔር ከተጻፈው ከሚጻፈው ፥ ከታሰበው ከሚታሰበው ፥ ከተነገረው ከሚነገረው ኹሉ በላይ ነው። እንደ እግዚአብሔርነቱ ማንም ምንም ማለት አይችልም ነበር ፤ ግን ከቸርነቱ የተነሣ ለኹለቱ [መላእክት እና ሰዎች] ፍጡራን ስለ እሱ ሊሉ በሚችሉበት መጠን ፣ ሊረዱት በሚችሉበት መጠን ማንነቱን ገልጦላቸዋል። አኹን ያለን መገለጥ/መረዳት ስለ እግዚአብሔር እኛ ልናውቀው የቻልነው መጠን ነው።
-------------------------------
📜ያገምሩ ኵሎ ወአልቦ መኑሂ ዘያገምሮሙ ብርሃናት ቀዳማውያት ፤ ዘኢየአምር መኑሂ ዘከመ እፎ ውእቱ ክዋኔሁ ፤ ወኢያገምሮሙ ልቡና ፤ ወኢያስተጋብኦሙ ሕሊና ፤ ይሬእዩ ኵሎ ፥ ወኢያስተርእዩ ፤ ወአልቦ ዘይትማሰሎሙ ፤ ወይትዔረዮሙ ሕያዋን እሙንቱ እለ ኢይመውቱ ፤ ወኢይትዌለጡ ፤ ርኁቃን እምነ ኵሉ ወቅሩባን ለኵሉ ለባውያን ፤ ወማእምራን ፈድፋደ እምነ ኵሉ ፤ ኢፍጡራን ፤ ወኢይትረከቡ በሐልዮ ወበለብዎ ፤ ርኁቃን ወልዑላን እሙንቱ ፤ አምጻእያኒሆሙ ለኵሉሙ ፍጡራን እም ኀበ ኢሀልዎ ኀበ ሀልዎ፨
☞ኹሉን ይወስናሉ እንጂ የሚወስናቸው ምንም ምን የለም ፤ ኹኔታቸው እንዴት እንደኾነ ማንም የማያውቅ በቅድምና የነበሩ ብርሃናት ናቸው። ልቡና አይመረምራቸውም ፤ ሕሊና አይወስናቸውም ፤ ኹሉን ያያሉ እነርሱ ግን አይታዩም ፤ የሚመስላቸው የሚተካከላቸው የለም ፤ የማይሞቱ የማይለወጡ ሕያዋን ናቸው። ከኹሉ [መረዳህ] የራቁ ለኹሉ [በመግቦት/በሃይማኖት] የቀረቡ ናቸው ፤ ከኹሉ ይልቅ ዕውቀት የባሕርያቸው ነው። ያልተፈጠሩ ናቸው ፤ በማሰብ በመመርመር አይገኙም ፤ ከ’መ’መ’ርመር የራቁ የረቀቁ ናቸውና። ፍጥረታትን ኹሉ ካለመኖር ወደ መኖርያመጡ እነርሱ ናቸው፨
📜➬ ሃይማኖተ አበው ዘሱንትዩ ፻፱ ፥ ፫
ምሥጢሬ አይታወቅም ፤ ነገር ግን የአንተ አእምሮ ሊቀበለው የሚችለውን ምሥጢር አነግርሃለኹ።
➬ መጽሐፈ ቀሌምንጦስ
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
©️ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ
የመንፈስ ቀላል ትርጕሙ «በአካላዊነት ጎልቶ ለዐይን የማይታይ» ፣ «ከመታየት በላይ» ማለት ነው። ቃሉ ወደ አካለ እግዚአብሔር ተጠግቶ ሲነገር የበለጠ ሐሳቡን ከፍ አድርጎ ይገልጣል። እግዚአብሔር የር’ቀ’ቶች ኹሉ መነሻ ስለኾነ - አእምሮአችን ከሚያሰበው ር’ቀ’ት በላይ ረቂቅ ነው። መንፈስ የሚለውም ራሱ የእኛን አስተውሎት/መረዳት ታሳቢ ተደርጎ የተነገረ እንጂ እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው ኾኖ አይደለም። እግዚአብሔር ከምንም - ስለ እሱ ከምናስበውም ከምንናገረውምም በላይ ነው!! እግዚአብሔርን በኾነው ልክ የሚገልጠው እግዚአብሔር ብቻ ነው ፤ እግዚአብሔር በእግዚአብሔርነቱ የሚገለጥለትም አካል የተገለጠውን ለመረዳት እግዚአብሔር መኾን አለበት ፤ እግዚአብሔር የሚገልጠውን እግዚአብሔርነት ማወቅ ለማንም አልተሰጠም። ለማንም አይቻልምና።
ስለ እግዚአብሔር ያለን ዕውቀት እኛ ስለ እሱ ማወቅ የቻልነው መጠን ነው ፤ ይኽም ቢኾን በራሳችን የመጣ ሳይኾን ተገልጦልን ያወቅነው ነው። ያወቅነውም እግዚአብሔርን የማወቃችን ድንበር አይደለም። ከእግዚአብሔር መልካምነት ጋር - ነፍስ በንጽሕና ወደ እሱ በመቅረብ ስትተባበር ፥ ፈቃደ ግብረ ባሕርያቱን ስትሳተፍ እየተገለጠላት የሚኼደው ዕውቀቷ የነበራትን ዕውቀት የሚበልጥ ይኾናል። የዕውቀቷ ፍጻሜም የነበሯት ዕውቀቶች ተቋጭተው ከእነሱ በበለጠ አለማወቅ በ’መ’ያ’ዝ ይኾናል!! የነፍስ ዕውቀት ስለ እግዚአብሔር ምንም አለማወቅ ውስጥ በመግባት ይፈጸማል!! ከእሱ ጋር መኖሯ በቂዋ ስለሚኾን የማወቅ ጥማቷም ይቆረጣል!!
«እግዚአብሔር መንፈስ ነው» የዚኽ ሐሳብ ተሸካሚ ቃል ነው። መንፈስ ምንድነው!? እንደ እውነታው የዚኽን ቃል ደረቅ መዝገበ ቃላዊ ፍቺን ከማስቀመጥ ውጪ ፥ ሐሳቡን በኾነው ልክ ለልብ ማስረዳት አይቻለም ፤ መንፈስ የሚለው ሐሳብ ላይ በሰው ዘንድ ያ’ለ አለመረዳት አ’ለ - «ያ አለመረዳት እግዚአብሔር በነፍሳችን ውስጥ ያለው ቦታ ነው» ለማለት «እግዚአብሔር መንፈስ ነው» ተብሏል።
❝.. ወአልቦ ዘየአምሮ ለወልድ ዘእንበለ አብ ፤ ወለአብኒ አልቦ ዘየአምሮ ዘእንበለ ወልድ - ከአብ በቀር ወልድን የሚያውቅ የለም፥ ከወልድም በቀር አብን የሚያውቅ የለም❞ [ማቴዎስ ፲፩፥፳፯]። ማወቅ ከተነገረስ የአብ ዕውቀት/መታወቅ ወልድ ላይ ፥ የወልድ ዕውቀትም/መታወቅ አብ ላይ ታውቆ ይቀራል። «ወለዘፈቀደ ወልድ ይከሥት ሎቱ - ወልድ ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር / ወልድ ሊገልጽለት ለወደደው ይገልጥለታል» የሚለው ቀጣይ ንባብ - በአሚን አኹን ለእኛ የተገለጠው ፥ እኛነታችን ስለ እግዚአብሔር ማወቅ የቻለው የዕውቀት መጠን ነው እንጂ አብ ወልድን ፥ ወልድም አብን የሚያውቅበት ማወቅ ለእኛ ተሰጥቷል ማለት አይደለም። አብ አብነቱ ወልድ ላይ ፥ ወልድም ወልድነቱ አብ ላይ የቀረ ነው!!
አካል ከሕሊናት ኹሉ ለራቀ ለአምላካችን ለልዑል እግዚአብሔር ሲነገር ፥ እኒኹ ኹሉ ታሳቢ ተደርገው ነው። የእግዚአብሔር አካል ሲባል ወደ ሕሊናችን የሚመጣው ሥዕል የእኛ መሰሉ ቅርጽ ከኾነ የእግዚአብሔርን እግዚአብሔርነት መዘንጋት ነው የሚኾነው። እንደሚታወቀው መገለጦች ኹሉ የተሰጡት ለሰዎች ነው ፤ እነዚያ መገለጦች ደግሞ በሰው መረዳት ልክ የኾኑ ናቸው ፤ ለእኛ ተመጥነው የተሰጡ መገለጦችን ያለቀላቸው የእግዚአብሔር ውክያ አድርጎ መውሰድ ይኽን የምሥጢር ድንበር መዝለል ነው።
አንድ እና ኹለት የለውም እግዚአብሔር አካላዊ ነው። በኹኔታዎች [በተፈጣሪያኑ ውስጥ ያለ ፥ እነሱም ጸንተው ያሉበት] ውጥረት እና ጽምረት የሚመላለስ/ተገላጭ ኀይልም [በእሱ የሚኾን ቢኾኖም] አይደለም ፤ አማን በአማን እግዚአብሔር አካላዊ ነው። ሰው ኹነን አካላዊነትን ከእኛ አካልነት ውጪ መረዳት አይቻለንምና ፥ የእግዚአብሔር አካል በእኛ አካል አንጻር ተገልጿል። ይኽ ማለት ቀጥታ የእኛ አካል የእግዚአብሔር አካል ተመስያ ነው ማለት አይደለም። አካለ እግዚአብሔር በእኛ ሕሊና ከሚሣለው አካል የወጣ ፥ በማንም የማይመረመር የአካሎች ኹሉ ፍጻሜ የኾነ ፍጹም አካል ነው።
በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እግዚአብሔር አካል የተነገሩ ምንባባት በዚኽ አግባብ የምንረዳቸው ናቸው። እግዚአብሔር ከተጻፈው ከሚጻፈው ፥ ከታሰበው ከሚታሰበው ፥ ከተነገረው ከሚነገረው ኹሉ በላይ ነው። እንደ እግዚአብሔርነቱ ማንም ምንም ማለት አይችልም ነበር ፤ ግን ከቸርነቱ የተነሣ ለኹለቱ [መላእክት እና ሰዎች] ፍጡራን ስለ እሱ ሊሉ በሚችሉበት መጠን ፣ ሊረዱት በሚችሉበት መጠን ማንነቱን ገልጦላቸዋል። አኹን ያለን መገለጥ/መረዳት ስለ እግዚአብሔር እኛ ልናውቀው የቻልነው መጠን ነው።
-------------------------------
📜ያገምሩ ኵሎ ወአልቦ መኑሂ ዘያገምሮሙ ብርሃናት ቀዳማውያት ፤ ዘኢየአምር መኑሂ ዘከመ እፎ ውእቱ ክዋኔሁ ፤ ወኢያገምሮሙ ልቡና ፤ ወኢያስተጋብኦሙ ሕሊና ፤ ይሬእዩ ኵሎ ፥ ወኢያስተርእዩ ፤ ወአልቦ ዘይትማሰሎሙ ፤ ወይትዔረዮሙ ሕያዋን እሙንቱ እለ ኢይመውቱ ፤ ወኢይትዌለጡ ፤ ርኁቃን እምነ ኵሉ ወቅሩባን ለኵሉ ለባውያን ፤ ወማእምራን ፈድፋደ እምነ ኵሉ ፤ ኢፍጡራን ፤ ወኢይትረከቡ በሐልዮ ወበለብዎ ፤ ርኁቃን ወልዑላን እሙንቱ ፤ አምጻእያኒሆሙ ለኵሉሙ ፍጡራን እም ኀበ ኢሀልዎ ኀበ ሀልዎ፨
☞ኹሉን ይወስናሉ እንጂ የሚወስናቸው ምንም ምን የለም ፤ ኹኔታቸው እንዴት እንደኾነ ማንም የማያውቅ በቅድምና የነበሩ ብርሃናት ናቸው። ልቡና አይመረምራቸውም ፤ ሕሊና አይወስናቸውም ፤ ኹሉን ያያሉ እነርሱ ግን አይታዩም ፤ የሚመስላቸው የሚተካከላቸው የለም ፤ የማይሞቱ የማይለወጡ ሕያዋን ናቸው። ከኹሉ [መረዳህ] የራቁ ለኹሉ [በመግቦት/በሃይማኖት] የቀረቡ ናቸው ፤ ከኹሉ ይልቅ ዕውቀት የባሕርያቸው ነው። ያልተፈጠሩ ናቸው ፤ በማሰብ በመመርመር አይገኙም ፤ ከ’መ’መ’ርመር የራቁ የረቀቁ ናቸውና። ፍጥረታትን ኹሉ ካለመኖር ወደ መኖርያመጡ እነርሱ ናቸው፨
📜➬ ሃይማኖተ አበው ዘሱንትዩ ፻፱ ፥ ፫
ምሥጢሬ አይታወቅም ፤ ነገር ግን የአንተ አእምሮ ሊቀበለው የሚችለውን ምሥጢር አነግርሃለኹ።
➬ መጽሐፈ ቀሌምንጦስ
“ #እግዚአብሔር_መንፈስ_ነው ”
— የዮሐንስ ወንጌል ፬፥፳፬ / 4፥24
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
©️ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ
❤10😢1
Forwarded from ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
#ኢቮሊዩሺን
የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ እምነት?
ይህ “ኢቮሊዮሺን - የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ ሃይማኖት?” የሚለው ድንቅ መጽሐፍ፣ ሳይንስ መስለው የሚነገሩትንና እንደ ዶግማ የሚታዩትን የኢቮሊዩሺን ቲዎሪ እሳቤዎችን ከመሠረታቸው በመመርመርና በቂ ሳይንሳዊ ማስረጃዎችን በማቅረብ፣ እነዚህ መላ-ምቶች ሳይንስ እንዳልሆኑ ግልጽ አድርጎ አቅርቦልናል።
ይህ የመምህራችን የመምህር ያረጋል አበጋዝ ለትውልድ የሚተላለፍ ድንቅ ሥራቸው፣ በተለይ ትንሽ አስኳላ ትምህርት ለዘለቀው ማኅበረሰብ ሕሊናውን የሚያነቃበትና ራሱን የሚፈትሽበት ጠቃሚ መጽሐፍ እንደሆነ አምናለሁ። መምህራችን ከዚህ በፊት “ሳይንሰ እና ሃይማኖት” በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ያቀረቧቸውን ግሩም ሐሳቦች አጣጥመን ሳንጨርስ ይህን ጥልቅና የብዙዎቻችንን ጥያቄ የመለሱበትን ጠቃሚ መጽሐፍ በማበርከታቸው እግዚአብሔር ይስጥልን፣ በዕድሜ በጸጋ ይጠብቅልን፣ በቀጣዩስ ምን እንጠብቅ? እያልኩ ለአንባብያን መልካም ንባብ እላለሁ።
ዲ/ን ዶ/ር ዮሴፍ አጥላው - የሥነ-ኬሚካል ተመራማሪ፣ በአስትራዜኒካ ፋርማሲቲካል የመድኃኒት ምርምርና ማጎልበቻ ድርጅት
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ እምነት?
ይህ “ኢቮሊዮሺን - የተረጋገጠ ሳይንስ ወይስ ሃይማኖት?” የሚለው ድንቅ መጽሐፍ፣ ሳይንስ መስለው የሚነገሩትንና እንደ ዶግማ የሚታዩትን የኢቮሊዩሺን ቲዎሪ እሳቤዎችን ከመሠረታቸው በመመርመርና በቂ ሳይንሳዊ ማስረጃዎችን በማቅረብ፣ እነዚህ መላ-ምቶች ሳይንስ እንዳልሆኑ ግልጽ አድርጎ አቅርቦልናል።
ይህ የመምህራችን የመምህር ያረጋል አበጋዝ ለትውልድ የሚተላለፍ ድንቅ ሥራቸው፣ በተለይ ትንሽ አስኳላ ትምህርት ለዘለቀው ማኅበረሰብ ሕሊናውን የሚያነቃበትና ራሱን የሚፈትሽበት ጠቃሚ መጽሐፍ እንደሆነ አምናለሁ። መምህራችን ከዚህ በፊት “ሳይንሰ እና ሃይማኖት” በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ያቀረቧቸውን ግሩም ሐሳቦች አጣጥመን ሳንጨርስ ይህን ጥልቅና የብዙዎቻችንን ጥያቄ የመለሱበትን ጠቃሚ መጽሐፍ በማበርከታቸው እግዚአብሔር ይስጥልን፣ በዕድሜ በጸጋ ይጠብቅልን፣ በቀጣዩስ ምን እንጠብቅ? እያልኩ ለአንባብያን መልካም ንባብ እላለሁ።
ዲ/ን ዶ/ር ዮሴፍ አጥላው - የሥነ-ኬሚካል ተመራማሪ፣ በአስትራዜኒካ ፋርማሲቲካል የመድኃኒት ምርምርና ማጎልበቻ ድርጅት
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤2👍2
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Photo
◈ርቱዓዊ ልምምድ፦
◈ርቱዓዊነት በሕይወት በር እየተመላለሱ የተስፋ ፍጻሜን ለማግኘት በጸናች በቀናች ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ የተዋሕዶት ልምምድ ማድረግ ነው።
◈ወይም በዚህች ርትዕት ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ እስከ ፍጻሜ ድረስ የእውነት በሩን ሳይለቁ በግብርም በነገርም የጸና የቀና ክርስቲያን የመሆን ልምምድ ነው።
◈ወይም በሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ ሁኖ ርቱዓዊነትን በማወቅ እና በመረዳት ላይ ተመሥርቶ የመሆን ልምምድን እያስቀደሙ እስከ ህቅታ ድረስ የመዳን መንገድን ለመጨረስ ሳያቋርጡ ወደ ምድረ ርሥት መጓዝ ነው።
◈ቅዱስ ፍጹም ሐዋርያዊ ተስፋን መውረስ የሚቻለው በዚህ ሕያው መንገድ ነውና።"አመንኩ በዘነበብኩ-የተናገርሁትን አመንሁ።"መዝ.፻፲፭፥፩እን. የአፍ ሌላ የልብ ሌላ ሳይሉ ያመኑትን በሕይወት ልምምድ እየኖሩ ማሳየት የሚቻለው በርቱዓዊነት ልምምድ ውስጥ ነው።
◈የርቱዕነት መነሻው ከእግዚአብሔር ለቅዱሳን የተሰጠው፦ርቱዕ ክሡት ፍጹም የሆነው አስተሳስብ ነው።
◈በዚህ መንገድ፦ረቂቁን ከግዙፉ፣ቋሚውን ከሀላፊው፣እውነቱን ከሀሰቱ፣ጽኑዑን ከወጪ ወራጁ በመለየት የሀሳባትን ቅደም ተከተል በመረዳት ጥርት ያለ ርቱዕ ሐዋርያዊ ህሊናን መፈለግ ነው።
◈ሀሳበ እግዚአብሔር፣ሀሳበ መላእክት፣ሀሳበ ሰብእ፣ሀሳበ ደማውያን፣ሀሳበ ዕፅዋት፣ሀሳበ ፍጥረታት አለ፤
◈ከዚህ ሁሉ ሀሳብ መካከል ለድኅነተ ነፍስ ለርቱዓዊነት የሚበጀንን መለየት እና ሁሉንም በየመልኩ ተረድቶ በርቱዓዊነት መሠረት ላይ ጸንቶ በጠራ ህሊና መገለጽ ያስፈልጋል።
◈ደግሞም ከአቅማችን ድካም የተነሣ ወደ ጽሩይ ህሊና ገብቶ ልቡናን አስፍቶ አእምሮን አቅንቶ መለማመድ እና ከፍ ያለውን ጣዕመ ምሥጢር ማየት ቢያቅተን ወደ ባለቤቱ እንለምናለን፦
"ወንስአል አንቃዲወነ ላዕለ ወሶቤሃ ይሠርቅ ለነ ብርሃን እምነ መጻሕፍተ መለኮት ወእምኔሆሙ ንበርህ በአስማተ ቅድስት ሥላሴ ዘውእቱ እምነትነ-
ወደላይ አቅንተን እንለምን ያንጊዜ የመለኮተን ነገር ከማናገሩ መጻሕፍት ዕውቀት የገልጽለናል ከእነርሱም የሦስቱን ስም በመጥራት አዋቆች እንሆናለን ይሄውም ማመናችን ነው።"ሃይ.አበ.፲፥፪እን.
የኔታ ገብረ መድኅን እንየው
◈ርቱዓዊነት በሕይወት በር እየተመላለሱ የተስፋ ፍጻሜን ለማግኘት በጸናች በቀናች ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ የተዋሕዶት ልምምድ ማድረግ ነው።
◈ወይም በዚህች ርትዕት ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ እስከ ፍጻሜ ድረስ የእውነት በሩን ሳይለቁ በግብርም በነገርም የጸና የቀና ክርስቲያን የመሆን ልምምድ ነው።
◈ወይም በሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ ሁኖ ርቱዓዊነትን በማወቅ እና በመረዳት ላይ ተመሥርቶ የመሆን ልምምድን እያስቀደሙ እስከ ህቅታ ድረስ የመዳን መንገድን ለመጨረስ ሳያቋርጡ ወደ ምድረ ርሥት መጓዝ ነው።
◈ቅዱስ ፍጹም ሐዋርያዊ ተስፋን መውረስ የሚቻለው በዚህ ሕያው መንገድ ነውና።"አመንኩ በዘነበብኩ-የተናገርሁትን አመንሁ።"መዝ.፻፲፭፥፩እን. የአፍ ሌላ የልብ ሌላ ሳይሉ ያመኑትን በሕይወት ልምምድ እየኖሩ ማሳየት የሚቻለው በርቱዓዊነት ልምምድ ውስጥ ነው።
◈የርቱዕነት መነሻው ከእግዚአብሔር ለቅዱሳን የተሰጠው፦ርቱዕ ክሡት ፍጹም የሆነው አስተሳስብ ነው።
◈በዚህ መንገድ፦ረቂቁን ከግዙፉ፣ቋሚውን ከሀላፊው፣እውነቱን ከሀሰቱ፣ጽኑዑን ከወጪ ወራጁ በመለየት የሀሳባትን ቅደም ተከተል በመረዳት ጥርት ያለ ርቱዕ ሐዋርያዊ ህሊናን መፈለግ ነው።
◈ሀሳበ እግዚአብሔር፣ሀሳበ መላእክት፣ሀሳበ ሰብእ፣ሀሳበ ደማውያን፣ሀሳበ ዕፅዋት፣ሀሳበ ፍጥረታት አለ፤
◈ከዚህ ሁሉ ሀሳብ መካከል ለድኅነተ ነፍስ ለርቱዓዊነት የሚበጀንን መለየት እና ሁሉንም በየመልኩ ተረድቶ በርቱዓዊነት መሠረት ላይ ጸንቶ በጠራ ህሊና መገለጽ ያስፈልጋል።
◈ደግሞም ከአቅማችን ድካም የተነሣ ወደ ጽሩይ ህሊና ገብቶ ልቡናን አስፍቶ አእምሮን አቅንቶ መለማመድ እና ከፍ ያለውን ጣዕመ ምሥጢር ማየት ቢያቅተን ወደ ባለቤቱ እንለምናለን፦
"ወንስአል አንቃዲወነ ላዕለ ወሶቤሃ ይሠርቅ ለነ ብርሃን እምነ መጻሕፍተ መለኮት ወእምኔሆሙ ንበርህ በአስማተ ቅድስት ሥላሴ ዘውእቱ እምነትነ-
ወደላይ አቅንተን እንለምን ያንጊዜ የመለኮተን ነገር ከማናገሩ መጻሕፍት ዕውቀት የገልጽለናል ከእነርሱም የሦስቱን ስም በመጥራት አዋቆች እንሆናለን ይሄውም ማመናችን ነው።"ሃይ.አበ.፲፥፪እን.
የኔታ ገብረ መድኅን እንየው
❤4
Forwarded from ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ። (Tekle H)
💧ዜና መጽሐፍ
📚#ምናሴ
ወድቆ መነሳት
ከ ጸሐፊው የጉዳት ማስረሻ የኾነኝ ማስረሻ!በማለት የተዘጋጀልን ለእኛም ማስረሻ እንደሚኾነን ጥርጥር የለውም እንድንጠቀምበት እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን!
ስለ መጽሐፉ...👇
#ምናሴ (ማስረሻ) “አግዚአብሔር መከራዬን ኹሉ አስረሳኝ” ሲል ዮሴፍ በወንድ ልጁ ያወጣው ስም ነበረ። “ጸሎተ ምናሴ” በተሰኘው የንሰሐ ጸሎቱ በቤተ ክርስቲያን የሚታወቀው የይሁዳ ንጉሥ ምናሴ ታሪክ ደግሞ በግል ሕይወታችን ላይ፣ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ፣ አንዲሁም በሀገራችን ላይ የፈጸምናቸውን በደሎች ወለል አድርጎ የሚያሳይና በጸጸት ባሕር አስጥሞ በኀዘናችን ማስረሻ የሚኾን ታሪክ የነበረው ሰው ነው፡፡
#መምህር_ቃኘው_ወልዴ ይኽን የመጽሐፍ ቅዱስ ባለ ታሪክ የአበውን የሥነ ጽሑፍ ዘዴ ተጠቅመው የራሱን ታሪክ በአንደበቱ በማናገር በልብ ወለዳዊ ግለ ታሪክ (Fictional Autobiography) መልክ ውብ መጽሐፍ አበርክተዋል፡፡ መጽሐፈ ሃይማኖት ቀመስ ልብ ወለዳዊ የትረካ አጻጻፍን ሰሚቶሎጂያዋ ቅዠቶችና ያልተረጋገጡ አወዛጋቢ ታሪኮችን በመፍጠር ከመዋል ይልቅ አንዲህ ለአገራዊ፣ ለግላዊና ለመንፈሳዊ ቊስሎች መድኃኒት መኾን የሚችል የአጻጻፍ ስልት አንደ ኾነ የሚያሳይ ድንቅ ሥራ ነው፡፡ መጽሐፉ የአንድን ንጉሥ ድቀትና የአግዚአብሔር ምሕረት ብዛት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይና በንሰሐ የሚጠራ በምናሴ አገላለጽ “ቸርነቱን አየለመንን በልባችን ጉልበት አንድንሰግድ” የሚጣራ መጽሐፍ ነው፡፡
✍️ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
📚ፍኖተ መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
📚#ምናሴ
ወድቆ መነሳት
ከ ጸሐፊው የጉዳት ማስረሻ የኾነኝ ማስረሻ!በማለት የተዘጋጀልን ለእኛም ማስረሻ እንደሚኾነን ጥርጥር የለውም እንድንጠቀምበት እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን!
ስለ መጽሐፉ...👇
#ምናሴ (ማስረሻ) “አግዚአብሔር መከራዬን ኹሉ አስረሳኝ” ሲል ዮሴፍ በወንድ ልጁ ያወጣው ስም ነበረ። “ጸሎተ ምናሴ” በተሰኘው የንሰሐ ጸሎቱ በቤተ ክርስቲያን የሚታወቀው የይሁዳ ንጉሥ ምናሴ ታሪክ ደግሞ በግል ሕይወታችን ላይ፣ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ፣ አንዲሁም በሀገራችን ላይ የፈጸምናቸውን በደሎች ወለል አድርጎ የሚያሳይና በጸጸት ባሕር አስጥሞ በኀዘናችን ማስረሻ የሚኾን ታሪክ የነበረው ሰው ነው፡፡
#መምህር_ቃኘው_ወልዴ ይኽን የመጽሐፍ ቅዱስ ባለ ታሪክ የአበውን የሥነ ጽሑፍ ዘዴ ተጠቅመው የራሱን ታሪክ በአንደበቱ በማናገር በልብ ወለዳዊ ግለ ታሪክ (Fictional Autobiography) መልክ ውብ መጽሐፍ አበርክተዋል፡፡ መጽሐፈ ሃይማኖት ቀመስ ልብ ወለዳዊ የትረካ አጻጻፍን ሰሚቶሎጂያዋ ቅዠቶችና ያልተረጋገጡ አወዛጋቢ ታሪኮችን በመፍጠር ከመዋል ይልቅ አንዲህ ለአገራዊ፣ ለግላዊና ለመንፈሳዊ ቊስሎች መድኃኒት መኾን የሚችል የአጻጻፍ ስልት አንደ ኾነ የሚያሳይ ድንቅ ሥራ ነው፡፡ መጽሐፉ የአንድን ንጉሥ ድቀትና የአግዚአብሔር ምሕረት ብዛት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይና በንሰሐ የሚጠራ በምናሴ አገላለጽ “ቸርነቱን አየለመንን በልባችን ጉልበት አንድንሰግድ” የሚጣራ መጽሐፍ ነው፡፡
✍️ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ
📚ፍኖተ መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
facebook.com/FinoteBooks1623
❤6🙏3
💧በድጋሚ ታትሟል
# ከ መምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተገኙ እንቁ እና እጅግ ተወዳጅ መጻሕፍት መካከል አንዱነው..!
📚#ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሕይወቱ እና ትምህርቱ📚
ከሕይወቱ ቅምሻ
[....ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ራሱን ከዚህ ዓለም የበለጠ ለመሰወርና ብቻውን ዘግቶ ለመኖር በመፈለጉ ወደ ዋሻ ውስጥ ገብቶ በብሕትውናና በጽኑ ትኅርምት ለሁለት ዓመት ሲጋደል ኖረ። በዚያም በትጋሃ ሌሊት፣ ለራሱ ዕንቅልፍ በመከልከል፣ በቀዊም፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቃል በማጥናት፣ በጸሎትና በተዘክሮ ኖረ....]
(ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ)
[..ሁሉም የሌሊት ቅዠቶች ኖረዋል፡፡ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ በመምጣቱ ከጨለማው ጋር አብረው የጠፉ ህልሞች ብቻ ነበሩ፡፡ ያለ መስሎ ታይቶ እንደጠፋ ጥላ፣ ወደ አየር ተኖ እንደጠፋ ጢስ፣ ሟሙቶ እንዳለቀ አረፋ፣ እንደተበጣጠሰ የሸረሪት ድር ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሁል ጊዜ ይህንን መንፈሳዊ መዝሙር እንዘምራለን፡- “ሁሉ ከንቱ፣ የከንቱ ከንቱ ነው” የሚለውን፡፡]››
ብቅ በሉ..!
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
# ከ መምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተገኙ እንቁ እና እጅግ ተወዳጅ መጻሕፍት መካከል አንዱነው..!
📚#ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሕይወቱ እና ትምህርቱ📚
ከሕይወቱ ቅምሻ
[....ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ራሱን ከዚህ ዓለም የበለጠ ለመሰወርና ብቻውን ዘግቶ ለመኖር በመፈለጉ ወደ ዋሻ ውስጥ ገብቶ በብሕትውናና በጽኑ ትኅርምት ለሁለት ዓመት ሲጋደል ኖረ። በዚያም በትጋሃ ሌሊት፣ ለራሱ ዕንቅልፍ በመከልከል፣ በቀዊም፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቃል በማጥናት፣ በጸሎትና በተዘክሮ ኖረ....]
(ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ)
[..ሁሉም የሌሊት ቅዠቶች ኖረዋል፡፡ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ በመምጣቱ ከጨለማው ጋር አብረው የጠፉ ህልሞች ብቻ ነበሩ፡፡ ያለ መስሎ ታይቶ እንደጠፋ ጥላ፣ ወደ አየር ተኖ እንደጠፋ ጢስ፣ ሟሙቶ እንዳለቀ አረፋ፣ እንደተበጣጠሰ የሸረሪት ድር ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሁል ጊዜ ይህንን መንፈሳዊ መዝሙር እንዘምራለን፡- “ሁሉ ከንቱ፣ የከንቱ ከንቱ ነው” የሚለውን፡፡]››
ብቅ በሉ..!
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤8
Forwarded from የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ቤት
እኛን እስከ መቃብር ተከትሎ እስከ ሰማያዊው ስፍራ አስከተለን ፤ ሞትን ከባሕርያችን ነቅሎ ሕይወቱን በውስጣችን ተከለ። የመለኮት ስፍራ የትስብእትን (የክርስቶስን) ቦታ እንደወሰነ ፥ በዕርገት የኾነ የክርስቶስ ስፍራም የሰው ልጅ ዘለዓለማዊ ስፍራውን ወሰነ፨
▬▬▬▬ † ▬▬▬▬
📜ኤፌሶን ፪
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
፭ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በኾንን ጊዜ #ከክርስቶስ_ጋር_ሕይወት_ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥
፮-፯ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከኹሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን #በክርስቶስ_ኢየሱስም_በሰማያዊ_ስፍራ_ከእርሱ_ጋር_አስቀመጠን፨
ወረደ - ዐርገ - ይመጽእ!!
መልካም በዓል!!
--------------------------------------
▬▬▬▬ † ▬▬▬▬
📜ኤፌሶን ፪
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
፭ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በኾንን ጊዜ #ከክርስቶስ_ጋር_ሕይወት_ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥
፮-፯ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከኹሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን #በክርስቶስ_ኢየሱስም_በሰማያዊ_ስፍራ_ከእርሱ_ጋር_አስቀመጠን፨
ወረደ - ዐርገ - ይመጽእ!!
መልካም በዓል!!
--------------------------------------
❤7🙏2
📚#ተግሣፅ
ዘ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ።
« . . . ተግሣፅ ፡ ማለት፡ ስሕተትን ፡ ማረሚያ ፡አቋምን ፡ ማስተካከያ መናፍቃንን ፡ መቃወሚያ ፡መጭውን ፡ የሕይወት ፡ ጐዳና ፡ የሚተልም መንፈሳዊ፡መሐንዲስ ፡ ማለት ፡ ነው። ስለዚህ ፡ በዚህ ፡ የመጽሐፍ ፡ ቃለ ፡ ምዕዳን የሚመራውን ፡ ሁሉ ፡ እግዚአብሔር ለከፉ ፡ አሳልፎ አይሰጠውም ። » መዝ ፻፲፯ ፲፰ ። ኢሳ. ፳፮ ፲፮ "
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
ዘ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ።
« . . . ተግሣፅ ፡ ማለት፡ ስሕተትን ፡ ማረሚያ ፡አቋምን ፡ ማስተካከያ መናፍቃንን ፡ መቃወሚያ ፡መጭውን ፡ የሕይወት ፡ ጐዳና ፡ የሚተልም መንፈሳዊ፡መሐንዲስ ፡ ማለት ፡ ነው። ስለዚህ ፡ በዚህ ፡ የመጽሐፍ ፡ ቃለ ፡ ምዕዳን የሚመራውን ፡ ሁሉ ፡ እግዚአብሔር ለከፉ ፡ አሳልፎ አይሰጠውም ። » መዝ ፻፲፯ ፲፰ ። ኢሳ. ፳፮ ፲፮ "
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤6
በቅርብ ቀን...
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን
[የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን
[የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤7
💧አዲስ መጽሐፍ
📚#ቅዱስ_ቄርሎስ
ዘኢየሩሳሌም ትምህርቶች
[313-386]
👉ይኼ መጽሐፍ በአራተኛው ክፍለ ዘመን የኢየሩሳሌም ሊቀጳጳስ ሊቀጳጳስ በነበረው በቅዱስ ቄርሎስ የተሰጠ ትምህርት ነው። አሁን በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች ከቀደሙት አባቶች ትምህርት ጋራ ምን ያህል አንድ ዐይነት ትምህርት እናስተምራለን? የትኞቹን ትምህርቶቻችን ጠላት እንክርዳድ ዘርቶባቸዋል? ትክክለኛው የሃይማኖት ትምህርት የትኛው ነው? የሚለውን ለመመርመር የሚያግዝ መጽሐፍ ነው።
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
📚#ቅዱስ_ቄርሎስ
ዘኢየሩሳሌም ትምህርቶች
[313-386]
👉ይኼ መጽሐፍ በአራተኛው ክፍለ ዘመን የኢየሩሳሌም ሊቀጳጳስ ሊቀጳጳስ በነበረው በቅዱስ ቄርሎስ የተሰጠ ትምህርት ነው። አሁን በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች ከቀደሙት አባቶች ትምህርት ጋራ ምን ያህል አንድ ዐይነት ትምህርት እናስተምራለን? የትኞቹን ትምህርቶቻችን ጠላት እንክርዳድ ዘርቶባቸዋል? ትክክለኛው የሃይማኖት ትምህርት የትኛው ነው? የሚለውን ለመመርመር የሚያግዝ መጽሐፍ ነው።
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤6🕊4🔥1
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Photo
ጥቂት ከመምህር ደጉ ዓለም ብሂሎች፦
"ሲቀመጥ ይነፋዋል ሲቆም ይጠፋዋል""
የውሻ መልካም የለውም ነጭ ሆነ ጥቁር ያው ውሻ ነው መናፍቅም ያው መናፍቅ ነው ለውጥ የለውም፡፡"
"ሰው የሚያጣው ሰው ነው እግዚአብሔር ሰው አያጣም።"
"አዳምን ለምን ሕጻን አድርጎ አልፈጠረውም ነበር ሲባሉ ሊቁ ማን ሊያናፍጠው ነበር ያሉት።"
ለተወልዶ ተፀንሰ ብእሴ እና ብእሲ በሚለው የትምህርተ ኅቡኣት ቃል ክርክር ተነሥቶ መምህር ትክክለኛውን ይመልሳሉ አንዱ የተረታው መምህር ደጉ እርስዎ ቀለም ሲቋጥሩ እኔ በደመወዝ በልጬዎታለሁ አላቸው እሳቸውም ቀበል አድርገው ድሮም ባዶ ቦርሳ የገንዘብ ማስቀመጫ ነው አሉት፡፡"
"ቁና ሙሉ ዘርቶ ቁና ሙሉ ማፈስ ትርፍ አይደለም።"
"ቅርናታም እና ግማታም ተቃቅፈው የኔ ሽታ የኔ ሽታ ይባባላሉ።"
"ያላወቁት ናፈቀኝ ያልቀመሱት ጣፈጠኝ አይባልም፡፡"
ጥርስ የሌለው ሰው ደረቅ ባቄላ ቢቆረጥም አበላሽቶ ይተፋዋል እንጂ አይበላውም ላይበላው አበላሸው።""
ሳይመረምሩ ሳይጠረጥሩ መቀበል ሆድ መሆን ነው።"
"ደስ ትላላችሁ ነገር ግን ውሻም በቡችላነቱ ደስ ይላል።"
"ገንፎ እንደሞተ ባያውቅ ይተነፍሳል።""
ድንቡልቡል መሀይም ሰምቶ አይሰማ ነው።"
"የቅኔ መምቻ ቤት ልስጥዎት ያላቸውን ሰው ቤት አለኝ ለራስህ ቤት ሥራ ብለውታል።"
"ያልተማረ ሰው ሰማይ ቅርቡ ነው እኔም በልጅነቴ ለትምህርት ስመጣ ከሰማይ ጥግ ሄጄ ልማር ብዬ ነው ስሄድ ግን ራቀኝ፡፡"
"የዕውቀት መለኪያው በዕውቀቱ ራሱን ሲያይ ነው።"
"ተሾሞ እውነት የሌለው ሰው ተሾመ እንጂ መቼ ተማረ።"
"ከዝንጀሮ እና ከርከሮ ማን ይሻላል ቢባሉ ሁሉስ ምን ተሽለው አንዱ ከወደ ፊቱ አንዱ ከወደ ቂጡ።"
"እውነት የሌለው ሰው ከንፈሩ ይሳሳል አፉ ይላሻል፡፡"
"የሃይማኖትን ሌባ በዱላ ነው ጥቅስ የሚጠቀሰው ለሚያምን ነው።"
"የባለጌ ኃይለ ቃል እንደ ሽመል ይወቃል።"
"የደንቆሮ ሊቅነቱ ድፍረቱ።"
"የሊቅ ሞቱ በደንቆሮ መገዛቱ።"
"ካላዋቂ አዋቂ ጋር ከመጫዎት ጠጅ ካሰከረው ጋር መጫዎት ይሻላል።"
"ኦሪት ሕግ ናት ወንጌል ግን እምነት ናት።""
ምላጭ ጸጉርን ቁረጥ ቢሉት አልፎ ተርፎ ቆዳን ይቆርጣል ነገሥታትም ቅጡልኝ ቢላቸው አምላክ ነን አሉበት፡፡"
"ሚስት እና ምግብን መምረጥ በራስ ነው።"
"ውኃ ለሚወስደው በትርህን እንጂ እጅህን አትስጠው፡፡"
"በሰኔ በግንቦት ምንጩ ምንጫምንጩ እንጋባ ብለው የአባይን ልጅ አጩ።""
በአጠገብህ ትልቅ ሰው ካለ ፀሐይ እንደ መሞቅ ነው።
"ኃጢአት ሆኖ ነው እንጂ ይህችን ዓለም ታንቆ ነበር መገላገል።"
"ከ10 ቤተ ክርስቲያን አንድ ጉባኤ ቤት ይበልጣል፡፡"
"ጌታችን በዚህ ምድር ሲመላለስ ምድር እርሱን ተሸከመችው ወይስ እርሱ ነው ምድርን የተሸከማት ተብለው ሲጠየቁ ጫማህን የተሸከምኸው አንተ ነህ ወይስ እርሱ ነው ምድርን እድትሸከመው የተሸከማት እርሱ ነው፡፡"
"ብሉይ ኪዳን እና ሐዲስ ኪዳን ቡፌ የሚያነሳ ሰውን ይመስላሉ መጀመሪያ ሰሀን የማንሳት እና የወረፋ ጊዜ ነው ይሄ የብሉይ ኪዳን ዘመን ነው።ሐዲስ ኪዳን ግን የምግብ ጊዜ ነው፡፡የምትበሉትን ካላገኛችሁ ሰልፉ ባዶ ነው፡፡"
"ሙቅ እና ቀዝቃዛ ባንድ ላይ ሁኖ መኖ አይቻልም።"
"የገብርኤል አለቃ ገብርኤል ያማልዳል? ብሏቸው ሆድህንስ የሞላው ማን ነው?
"ምን አለ ሰውን መስለው ቢያልፉ ቢሏቸው ስሞት ብቻ ነው መስዬ የማልፈው፡፡"
"ወንጌል አስተምረኝ የሚለኝ ካለ ሲኦልም ቢሆን አስተምራለሁ፡፡"
"እስራኤልን ባሕር ከፍሎ ያሻገረው ሚካኤል ነው? እግዚአብሔር ነው? በጨለማ ውስጥ ስትሂድ ባትሪ ታበራለህ ብርሃን ያደረገው አንተነህ ወይስ ባትሪው ነው?"
"አዳምና ሔዋን ኃጢአት ባይሠሩ ኑሮ እንባዛ ነበርን? ቢባሉ ገና የተገለጠልንን እውነት መርምረን ሳንጨርስ ባልተገለጠው አንደክምም አሉ፡፡"
"የተማረከ አቅም የለውምና አዳምም ቅጥ የለሽ ምርኮኛ ነበርና ሰይጣን ለሁሉ አሰገደው፡፡"
"ዝንጀሮ ቅማል የሚለቅመው በማዘን ሳይሆን ለመብላት ነው፡፡"
የተገፋ ሰውነት እና ጥራጊ የወደቀበት መሬት ይመቻል ለልማት።"
"አባይ የአቡነ ዘርአ ቡሩክ ላይብረሪ ነው።""
የምላስ ሞረድ ነገርን ያሰላል።"
"የፍጡር ቀጠሮ ምን ቁም ነገር አለው ፅንስ እንኳን በ8 ወር አቋርጦ ይወለዳል።"
"ያባየን እከክ ወደ እመየ ልከክ።"
"ሰይጣን የቄራ ውሻ ማለት ነው ቢመቱት ይሄዳል ግን ተመልሶ ይመጣል።"
አይ አፈር!! አፈር አፈር ይብላ!! እኒህን ሁሉ በልቷል
ከመጻሕፍት አልፈው በስነ ፍጥረት ሁሉ የሚመራመሩ የነበሩት ሊቅ እንዲህ ብለዋል።
"ሲቀመጥ ይነፋዋል ሲቆም ይጠፋዋል""
የውሻ መልካም የለውም ነጭ ሆነ ጥቁር ያው ውሻ ነው መናፍቅም ያው መናፍቅ ነው ለውጥ የለውም፡፡"
"ሰው የሚያጣው ሰው ነው እግዚአብሔር ሰው አያጣም።"
"አዳምን ለምን ሕጻን አድርጎ አልፈጠረውም ነበር ሲባሉ ሊቁ ማን ሊያናፍጠው ነበር ያሉት።"
ለተወልዶ ተፀንሰ ብእሴ እና ብእሲ በሚለው የትምህርተ ኅቡኣት ቃል ክርክር ተነሥቶ መምህር ትክክለኛውን ይመልሳሉ አንዱ የተረታው መምህር ደጉ እርስዎ ቀለም ሲቋጥሩ እኔ በደመወዝ በልጬዎታለሁ አላቸው እሳቸውም ቀበል አድርገው ድሮም ባዶ ቦርሳ የገንዘብ ማስቀመጫ ነው አሉት፡፡"
"ቁና ሙሉ ዘርቶ ቁና ሙሉ ማፈስ ትርፍ አይደለም።"
"ቅርናታም እና ግማታም ተቃቅፈው የኔ ሽታ የኔ ሽታ ይባባላሉ።"
"ያላወቁት ናፈቀኝ ያልቀመሱት ጣፈጠኝ አይባልም፡፡"
ጥርስ የሌለው ሰው ደረቅ ባቄላ ቢቆረጥም አበላሽቶ ይተፋዋል እንጂ አይበላውም ላይበላው አበላሸው።""
ሳይመረምሩ ሳይጠረጥሩ መቀበል ሆድ መሆን ነው።"
"ደስ ትላላችሁ ነገር ግን ውሻም በቡችላነቱ ደስ ይላል።"
"ገንፎ እንደሞተ ባያውቅ ይተነፍሳል።""
ድንቡልቡል መሀይም ሰምቶ አይሰማ ነው።"
"የቅኔ መምቻ ቤት ልስጥዎት ያላቸውን ሰው ቤት አለኝ ለራስህ ቤት ሥራ ብለውታል።"
"ያልተማረ ሰው ሰማይ ቅርቡ ነው እኔም በልጅነቴ ለትምህርት ስመጣ ከሰማይ ጥግ ሄጄ ልማር ብዬ ነው ስሄድ ግን ራቀኝ፡፡"
"የዕውቀት መለኪያው በዕውቀቱ ራሱን ሲያይ ነው።"
"ተሾሞ እውነት የሌለው ሰው ተሾመ እንጂ መቼ ተማረ።"
"ከዝንጀሮ እና ከርከሮ ማን ይሻላል ቢባሉ ሁሉስ ምን ተሽለው አንዱ ከወደ ፊቱ አንዱ ከወደ ቂጡ።"
"እውነት የሌለው ሰው ከንፈሩ ይሳሳል አፉ ይላሻል፡፡"
"የሃይማኖትን ሌባ በዱላ ነው ጥቅስ የሚጠቀሰው ለሚያምን ነው።"
"የባለጌ ኃይለ ቃል እንደ ሽመል ይወቃል።"
"የደንቆሮ ሊቅነቱ ድፍረቱ።"
"የሊቅ ሞቱ በደንቆሮ መገዛቱ።"
"ካላዋቂ አዋቂ ጋር ከመጫዎት ጠጅ ካሰከረው ጋር መጫዎት ይሻላል።"
"ኦሪት ሕግ ናት ወንጌል ግን እምነት ናት።""
ምላጭ ጸጉርን ቁረጥ ቢሉት አልፎ ተርፎ ቆዳን ይቆርጣል ነገሥታትም ቅጡልኝ ቢላቸው አምላክ ነን አሉበት፡፡"
"ሚስት እና ምግብን መምረጥ በራስ ነው።"
"ውኃ ለሚወስደው በትርህን እንጂ እጅህን አትስጠው፡፡"
"በሰኔ በግንቦት ምንጩ ምንጫምንጩ እንጋባ ብለው የአባይን ልጅ አጩ።""
በአጠገብህ ትልቅ ሰው ካለ ፀሐይ እንደ መሞቅ ነው።
"ኃጢአት ሆኖ ነው እንጂ ይህችን ዓለም ታንቆ ነበር መገላገል።"
"ከ10 ቤተ ክርስቲያን አንድ ጉባኤ ቤት ይበልጣል፡፡"
"ጌታችን በዚህ ምድር ሲመላለስ ምድር እርሱን ተሸከመችው ወይስ እርሱ ነው ምድርን የተሸከማት ተብለው ሲጠየቁ ጫማህን የተሸከምኸው አንተ ነህ ወይስ እርሱ ነው ምድርን እድትሸከመው የተሸከማት እርሱ ነው፡፡"
"ብሉይ ኪዳን እና ሐዲስ ኪዳን ቡፌ የሚያነሳ ሰውን ይመስላሉ መጀመሪያ ሰሀን የማንሳት እና የወረፋ ጊዜ ነው ይሄ የብሉይ ኪዳን ዘመን ነው።ሐዲስ ኪዳን ግን የምግብ ጊዜ ነው፡፡የምትበሉትን ካላገኛችሁ ሰልፉ ባዶ ነው፡፡"
"ሙቅ እና ቀዝቃዛ ባንድ ላይ ሁኖ መኖ አይቻልም።"
"የገብርኤል አለቃ ገብርኤል ያማልዳል? ብሏቸው ሆድህንስ የሞላው ማን ነው?
"ምን አለ ሰውን መስለው ቢያልፉ ቢሏቸው ስሞት ብቻ ነው መስዬ የማልፈው፡፡"
"ወንጌል አስተምረኝ የሚለኝ ካለ ሲኦልም ቢሆን አስተምራለሁ፡፡"
"እስራኤልን ባሕር ከፍሎ ያሻገረው ሚካኤል ነው? እግዚአብሔር ነው? በጨለማ ውስጥ ስትሂድ ባትሪ ታበራለህ ብርሃን ያደረገው አንተነህ ወይስ ባትሪው ነው?"
"አዳምና ሔዋን ኃጢአት ባይሠሩ ኑሮ እንባዛ ነበርን? ቢባሉ ገና የተገለጠልንን እውነት መርምረን ሳንጨርስ ባልተገለጠው አንደክምም አሉ፡፡"
"የተማረከ አቅም የለውምና አዳምም ቅጥ የለሽ ምርኮኛ ነበርና ሰይጣን ለሁሉ አሰገደው፡፡"
"ዝንጀሮ ቅማል የሚለቅመው በማዘን ሳይሆን ለመብላት ነው፡፡"
የተገፋ ሰውነት እና ጥራጊ የወደቀበት መሬት ይመቻል ለልማት።"
"አባይ የአቡነ ዘርአ ቡሩክ ላይብረሪ ነው።""
የምላስ ሞረድ ነገርን ያሰላል።"
"የፍጡር ቀጠሮ ምን ቁም ነገር አለው ፅንስ እንኳን በ8 ወር አቋርጦ ይወለዳል።"
"ያባየን እከክ ወደ እመየ ልከክ።"
"ሰይጣን የቄራ ውሻ ማለት ነው ቢመቱት ይሄዳል ግን ተመልሶ ይመጣል።"
አይ አፈር!! አፈር አፈር ይብላ!! እኒህን ሁሉ በልቷል
ከመጻሕፍት አልፈው በስነ ፍጥረት ሁሉ የሚመራመሩ የነበሩት ሊቅ እንዲህ ብለዋል።
❤12
📚#ጸያሔ_ፍኖት
#የብሉያትና_የሐዲሳት ሊቅ የሆኑት #አባታችን_አባ_ገብረ ኪዳን ለጌታችን ቆርጠው ሊመሰክሩ መሻታቸውን አንደ አባቶቻችን ሰለዮሐንስ በመመስከር አሐዱ ብለው የጀመሩ ይመሰላል። በርግጥም ዮሐንስን የተከተሉ ከጌታ ሳይደርሱ የቀሩ የሉም፡፡ የሙሽራይቱ አጭተኛ ወይም ቤተ ከርስቲያንን ( ምእመንን ቀድሞ ያዘጋጀ ለሙሽራው ደረሳት አርሱ ነውና፡፡ ከጌታ ደቀ መዛሙርት ከመጀመሪያዎቹ ውሰጥ ከዮሐንሰ ደቀ መዛሙርትም (እነ አንድርያስ) የተመረጡ መኖራቸውም ለዚሁ ምሰክር ነው፡፡ ይህ መጽሐፍም ዮሐንሰን የሚያቀርበው በሁሉም አቅጣጫና መንገድ ወደ ጌታ ሳያደርሰ የማይቀር እውነተኛ መንገድ ጠራጊ መሆኑን ፍንትው አድርጎ በማሳየት ነው፡፡ አባታችንም ቀድመው ዮሐንስ ይዘው ስለመጡ የጌታን ነገር ሊያስከትሉ ነው ብዬ እንድገምት ማድረጉንም ልደበቅ አልችልም፡፡ እንግዲያውስ አንደ አነርሱ: አመጣጥ ከስድስት ወር ልዩነት ሳያሰበልጡ ቶሎ ይዘውልን ይምጡ አያልኩ መማጸኔን ማሳወቅ ከፋ አልመሰለኝም።
◦በዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ከመቅድሙ የተወሰደ
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
#የብሉያትና_የሐዲሳት ሊቅ የሆኑት #አባታችን_አባ_ገብረ ኪዳን ለጌታችን ቆርጠው ሊመሰክሩ መሻታቸውን አንደ አባቶቻችን ሰለዮሐንስ በመመስከር አሐዱ ብለው የጀመሩ ይመሰላል። በርግጥም ዮሐንስን የተከተሉ ከጌታ ሳይደርሱ የቀሩ የሉም፡፡ የሙሽራይቱ አጭተኛ ወይም ቤተ ከርስቲያንን ( ምእመንን ቀድሞ ያዘጋጀ ለሙሽራው ደረሳት አርሱ ነውና፡፡ ከጌታ ደቀ መዛሙርት ከመጀመሪያዎቹ ውሰጥ ከዮሐንሰ ደቀ መዛሙርትም (እነ አንድርያስ) የተመረጡ መኖራቸውም ለዚሁ ምሰክር ነው፡፡ ይህ መጽሐፍም ዮሐንሰን የሚያቀርበው በሁሉም አቅጣጫና መንገድ ወደ ጌታ ሳያደርሰ የማይቀር እውነተኛ መንገድ ጠራጊ መሆኑን ፍንትው አድርጎ በማሳየት ነው፡፡ አባታችንም ቀድመው ዮሐንስ ይዘው ስለመጡ የጌታን ነገር ሊያስከትሉ ነው ብዬ እንድገምት ማድረጉንም ልደበቅ አልችልም፡፡ እንግዲያውስ አንደ አነርሱ: አመጣጥ ከስድስት ወር ልዩነት ሳያሰበልጡ ቶሎ ይዘውልን ይምጡ አያልኩ መማጸኔን ማሳወቅ ከፋ አልመሰለኝም።
◦በዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ከመቅድሙ የተወሰደ
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤5🕊3
Forwarded from የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ቤት
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
Hiikkaa Wangeelaa Afaan Oromoo
Barsiisaa Eermiyaas Kumaatiin
Manni Barumsaa Gumii Debra Mixmaaq Barattoota afaanota adda addaan barsiisu keessa kan guyyaa Phenxeqoosxee (Pharaaqliixoos) irratti dubbifamu, wangeelli Afaan Oromoo kunoo.
ትርጓሜ ወንጌል በኦሮምኛ ቋንቋ በመ/ር ኤርምያስ ኩማ
የደብረ ምጥማቅ ጉባኤ ቤት ከሚያስተምራቸው በርካታ ልዩ ልዩ ቋንቋ ተናጋሪ ደቀመዛሙርት መካከል በዕለተ ጰራቅሊጦስ የሚነበበውን ወንጌል በኦሮምኛ ቋንቋ እነሆ
ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ጉባኤ ቤት
Barsiisaa Eermiyaas Kumaatiin
Manni Barumsaa Gumii Debra Mixmaaq Barattoota afaanota adda addaan barsiisu keessa kan guyyaa Phenxeqoosxee (Pharaaqliixoos) irratti dubbifamu, wangeelli Afaan Oromoo kunoo.
ትርጓሜ ወንጌል በኦሮምኛ ቋንቋ በመ/ር ኤርምያስ ኩማ
የደብረ ምጥማቅ ጉባኤ ቤት ከሚያስተምራቸው በርካታ ልዩ ልዩ ቋንቋ ተናጋሪ ደቀመዛሙርት መካከል በዕለተ ጰራቅሊጦስ የሚነበበውን ወንጌል በኦሮምኛ ቋንቋ እነሆ
ደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ጉባኤ ቤት
❤7🙏2
💧አዲስ መጽሐፍ
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን
[የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ]
«ታሪክ ለሕይወታችን ትርጒምን፣ ለማኅበረሰባችን ደግሞ ጽናትን የሚለግስ ሕያው መሠረት ነው፡፡ ታሪክ የአንድ ሕዝብ የወደፊት ተስፋ የሚበቅልበት ሥር ነው እንደሚባለው ሁሉ፣ ታሪኩን የዘነጋ ማኅበረሰብእ አቅጣጫውን የመሳት አደጋ ይጋረጥበታል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪክንና ማንነት በጥልቀት የሚመረምረው የዚህ መጽሐፍ ፋይዳም ከዚሁ እውነት ይመነጫል፡፡ መጽሐፉ ስለ ቤተ ክርስቲያናችንና ስለ ሀገራችን ታሪክ ለማወቅ ለሚጓጉ፣ ነገር ግን አስተማማኝ መረጃ በማግኘት ረገድ ለተቸገሩ ሁሉ ታላቅ የምሥራች ነው፡፡ ቀሲስ ዶ/ር መንግሥቱ ጎበዜ ይህንን ሥራ ለንባብ ለማብቃት ያሳዩት ምሁራዊ ትጋትና ጥረት እጅግ ሊመሰገን የሚገባው ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያናችንን የታሪክ ዐድማስ በማስፋት ረገድ ትልቅ አበርክቶ ያለው ይህ ጥናታዊ ሥራ፣ በዘርፉ ለሚደረጉ ሌሎች የጥናትና ምርምር ሥራዎች ዐዲስ መነሣሣትን የሚፈጥርና እያንዳንዱ ሰው ሊያነበው የሚገባ የዕውቀት መድብል ነው፡፡»
✍️ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
#የኢትዮጵያ_ኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ቤተክርስቲያን
[የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ]
«ታሪክ ለሕይወታችን ትርጒምን፣ ለማኅበረሰባችን ደግሞ ጽናትን የሚለግስ ሕያው መሠረት ነው፡፡ ታሪክ የአንድ ሕዝብ የወደፊት ተስፋ የሚበቅልበት ሥር ነው እንደሚባለው ሁሉ፣ ታሪኩን የዘነጋ ማኅበረሰብእ አቅጣጫውን የመሳት አደጋ ይጋረጥበታል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታሪክንና ማንነት በጥልቀት የሚመረምረው የዚህ መጽሐፍ ፋይዳም ከዚሁ እውነት ይመነጫል፡፡ መጽሐፉ ስለ ቤተ ክርስቲያናችንና ስለ ሀገራችን ታሪክ ለማወቅ ለሚጓጉ፣ ነገር ግን አስተማማኝ መረጃ በማግኘት ረገድ ለተቸገሩ ሁሉ ታላቅ የምሥራች ነው፡፡ ቀሲስ ዶ/ር መንግሥቱ ጎበዜ ይህንን ሥራ ለንባብ ለማብቃት ያሳዩት ምሁራዊ ትጋትና ጥረት እጅግ ሊመሰገን የሚገባው ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያናችንን የታሪክ ዐድማስ በማስፋት ረገድ ትልቅ አበርክቶ ያለው ይህ ጥናታዊ ሥራ፣ በዘርፉ ለሚደረጉ ሌሎች የጥናትና ምርምር ሥራዎች ዐዲስ መነሣሣትን የሚፈጥርና እያንዳንዱ ሰው ሊያነበው የሚገባ የዕውቀት መድብል ነው፡፡»
✍️ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤10
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Photo
◈አባቶች እነማን ናቸው?
(፩)
◈ለምንስ እናከብራቸዋለን?◈በጸናች በቀናች ሃይማኖት ጸንተው የኖሩ፦የቀድሞዎቹ ነቢያት፣ ቀጥሎም ሐዋርያት በኋላም በእነርሱ እግር የተተኩ ሊቃውንት ሁሉ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ናቸው።
◈ቤተ ክርስቲያን ትምህርቷን እና ሕይወቷን ከትውልድ ወደ ትውልድ የምታስተላልፍበት ሕያው መንገዷ በየዘመኑ የሚነሱ በሕይዎታቸውም በትምህርታቸውም የወንጌልን ሕይወት የኖሩ እና ሌሎችም ይቀበሉት ዘንድ ባስተማሩ መምህራን አበው ርቱዕነት ነው
◈የቤተ ክርስቲያን ርቱዕ ትምህርት እና ሕይወት በእውነተኛ ሃይማኖት ጸንተው በኖሩ እና የመጻሕፍትን ምሥጢር በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተረዱ ርቱዓን መምህራን በኩል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚስተላለፍ እውነት ነው እንጂ በቅዱሳት መጻሕፍት ንባብ ብቻ የሚረዳ አይደለምና።
◈በኦርቶዶክሳዊት ሕይወት ጸንተው የቅድስና ኑሮን እየኖሩ ርቱዕ አስተምህሮን ሳይበርዙ ሳይከልሱ ያስተማሩ፣እንደየዘመኑ ሁኔታ ያብራሩ እና የተረጎሙ አበው እጅግ ብዙዎች ናቸው፡፡ ◈እነዚሁም ርቱዓን አበው የሚባሉት፦በዕውቀት፣በአሚን፣በሕይወት፣በጥብዓት፣በጥበብ፣በትጋት፣በጸሎት ጸንተው፣በኅብረት፣ኦርቶዶክሳዊነትን የገለጡ ናቸው።
◈በኦርቶዶክሳዊት ሕይወት አምሳለ ክርስቶስ ሁነው የተመላለሱ አበው፦ከመምህራን፣ከመጻሕፍት፣ከልምድ፣ከመከራ፣ከተግባር ፣ከእድሜ ፣ከሕይወት መንፈሳዊት፣መላ ዘመናቸውን ሳያቋርጡ ዕውቀትን ሲቀስሙ የኖሩ ናቸው።
◈የእኛው ትውልድ፦በዕውቀታቸው፣በሕወታቸው፣በጥብዓታቸው፣በንጽሕናቸውበደቀመዛሙርቶቻቸው፣በእይታቸው፣ትናንትን ለዛሬ በማትረፋቸው፣ሕያዋን አስተማሪዎቻችን ናቸውና እናከብራቸዋለን።
◈በአንድ ወቅት(በ2013ዓ.ም.)ከዚህ ዓለም በሥጋ የተለዩን ሕያዋን አባቶች
◈መልአከ ምሕረት የኔታ ጥበቡ(ዘዛራ ሚካኤል)
◈ሊቀ ማዕምራ የኔታ ደጉ ዓለም ካሣ(ዘዳሞትፍኖተ ሰላም)
◈የኔታ ዓለሙ (ዘደሴ መድኃኔዓለም)
◈የኔታ መሠረት(ዘባሕርዳር)
◈የኔታ አክሊሉ (ዘሸዋ)
◈የኔታ ሊባኖስ (ዘደብረ ማርቆስ)ተጠቃሾች ናቸው።
➻በንጉሡ ዘመን በተከታታይ ትልልቅ ሰዎች ሲያልፉ ምህላ ያስይዙ ነበር ይባላል።
➻"እግዚአብሔር ሰው አያጣም ሰው የሚያጣው ሰው ነው"
ሊቀ ማዕምራን ደጉ ዓለም ካሣ።
(፩)
◈ለምንስ እናከብራቸዋለን?◈በጸናች በቀናች ሃይማኖት ጸንተው የኖሩ፦የቀድሞዎቹ ነቢያት፣ ቀጥሎም ሐዋርያት በኋላም በእነርሱ እግር የተተኩ ሊቃውንት ሁሉ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ናቸው።
◈ቤተ ክርስቲያን ትምህርቷን እና ሕይወቷን ከትውልድ ወደ ትውልድ የምታስተላልፍበት ሕያው መንገዷ በየዘመኑ የሚነሱ በሕይዎታቸውም በትምህርታቸውም የወንጌልን ሕይወት የኖሩ እና ሌሎችም ይቀበሉት ዘንድ ባስተማሩ መምህራን አበው ርቱዕነት ነው
◈የቤተ ክርስቲያን ርቱዕ ትምህርት እና ሕይወት በእውነተኛ ሃይማኖት ጸንተው በኖሩ እና የመጻሕፍትን ምሥጢር በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተረዱ ርቱዓን መምህራን በኩል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚስተላለፍ እውነት ነው እንጂ በቅዱሳት መጻሕፍት ንባብ ብቻ የሚረዳ አይደለምና።
◈በኦርቶዶክሳዊት ሕይወት ጸንተው የቅድስና ኑሮን እየኖሩ ርቱዕ አስተምህሮን ሳይበርዙ ሳይከልሱ ያስተማሩ፣እንደየዘመኑ ሁኔታ ያብራሩ እና የተረጎሙ አበው እጅግ ብዙዎች ናቸው፡፡ ◈እነዚሁም ርቱዓን አበው የሚባሉት፦በዕውቀት፣በአሚን፣በሕይወት፣በጥብዓት፣በጥበብ፣በትጋት፣በጸሎት ጸንተው፣በኅብረት፣ኦርቶዶክሳዊነትን የገለጡ ናቸው።
◈በኦርቶዶክሳዊት ሕይወት አምሳለ ክርስቶስ ሁነው የተመላለሱ አበው፦ከመምህራን፣ከመጻሕፍት፣ከልምድ፣ከመከራ፣ከተግባር ፣ከእድሜ ፣ከሕይወት መንፈሳዊት፣መላ ዘመናቸውን ሳያቋርጡ ዕውቀትን ሲቀስሙ የኖሩ ናቸው።
◈የእኛው ትውልድ፦በዕውቀታቸው፣በሕወታቸው፣በጥብዓታቸው፣በንጽሕናቸውበደቀመዛሙርቶቻቸው፣በእይታቸው፣ትናንትን ለዛሬ በማትረፋቸው፣ሕያዋን አስተማሪዎቻችን ናቸውና እናከብራቸዋለን።
◈በአንድ ወቅት(በ2013ዓ.ም.)ከዚህ ዓለም በሥጋ የተለዩን ሕያዋን አባቶች
◈መልአከ ምሕረት የኔታ ጥበቡ(ዘዛራ ሚካኤል)
◈ሊቀ ማዕምራ የኔታ ደጉ ዓለም ካሣ(ዘዳሞትፍኖተ ሰላም)
◈የኔታ ዓለሙ (ዘደሴ መድኃኔዓለም)
◈የኔታ መሠረት(ዘባሕርዳር)
◈የኔታ አክሊሉ (ዘሸዋ)
◈የኔታ ሊባኖስ (ዘደብረ ማርቆስ)ተጠቃሾች ናቸው።
➻በንጉሡ ዘመን በተከታታይ ትልልቅ ሰዎች ሲያልፉ ምህላ ያስይዙ ነበር ይባላል።
➻"እግዚአብሔር ሰው አያጣም ሰው የሚያጣው ሰው ነው"
ሊቀ ማዕምራን ደጉ ዓለም ካሣ።
❤5
📚#ሃይማኖተ_አበው📚
[ከቀድሞ አባቶች ሲወርድ የመጣው ንባቡና ትርጓሜው በአንድምታ]
➾ይህም፡መጽሐፍ፡በአራት፡ዐበይት፡ክፍላት፡ይከፈላል፡በአራቱ፡ክፍላተ ወንጌል፡አምሳል፡፡ከመጀመሪያው እስከ፡ኤጲፋንዮስ፡ያለው፡አንድ፡ክፍል፡፡ከኤጲፋንዮስ፡እስከ፡እመልዕክተ ሲኖዲቆን፡ሁለት፡ከእመልዕክተሲኖዲቆን፡እስከ፡ግዘት፡ሦስት፡፡ግዘትና፡ስምዓት፡እስከ፡መጨረሻው፡አራት ፡ተደርጎ በከፋፈል፡ክቡር፡ጌታው ሊቀሊ ቃውንት፡መንክር፡መኰንን፡ያዘጋጁበትን ረቂቁን፡እንደገና፡በመጻፍና በማዘጋጀት፡ሙሉ፡ንባቡ ከትርጓሜ ው፡ይዘቱን፡እንደጠበቀ፡የአብነት መምህራን፡ጉባኤ፡አስፍተው፡እንዲያስምሩበት፡ደቀ፡መዛሙርት ተምረ ው፡እንዲተኩበት፡ሕዝበ፡ክርስቲያን፡በሙሉ፡ሃይማኖታቸውን አውቀው ተረድተው፡በተዋሕዶ፡ሃይማኖታ ቸው ጸንተው፡ከክሕደት፡ከኑፋቄ እንዲጠበቁበት፡መናፍቃንን ተከራክረው እንዲረቱበት፡ቤተ፡ክርስቲያና ቸውን በሕግና፡በሥርዓት፡ጸንተው፡እንዲያገለግሉበት፡ፈጣሪያቸው፡እግዚአብሔርን፡እንዲያመሰግኑበት፡በማሰብ፡ለመጀመሪያ፡ጊዜ፡በጉባኤ፡ቤቱ፡ስም፡ታትሟል፡፡በማለት በ[ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ]የቀረበልንን ምግበ ነፍስ ለመመገብ አንዘግይ !!!
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
ፍኖተ መጻሕፍት
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
[ከቀድሞ አባቶች ሲወርድ የመጣው ንባቡና ትርጓሜው በአንድምታ]
➾ይህም፡መጽሐፍ፡በአራት፡ዐበይት፡ክፍላት፡ይከፈላል፡በአራቱ፡ክፍላተ ወንጌል፡አምሳል፡፡ከመጀመሪያው እስከ፡ኤጲፋንዮስ፡ያለው፡አንድ፡ክፍል፡፡ከኤጲፋንዮስ፡እስከ፡እመልዕክተ ሲኖዲቆን፡ሁለት፡ከእመልዕክተሲኖዲቆን፡እስከ፡ግዘት፡ሦስት፡፡ግዘትና፡ስምዓት፡እስከ፡መጨረሻው፡አራት ፡ተደርጎ በከፋፈል፡ክቡር፡ጌታው ሊቀሊ ቃውንት፡መንክር፡መኰንን፡ያዘጋጁበትን ረቂቁን፡እንደገና፡በመጻፍና በማዘጋጀት፡ሙሉ፡ንባቡ ከትርጓሜ ው፡ይዘቱን፡እንደጠበቀ፡የአብነት መምህራን፡ጉባኤ፡አስፍተው፡እንዲያስምሩበት፡ደቀ፡መዛሙርት ተምረ ው፡እንዲተኩበት፡ሕዝበ፡ክርስቲያን፡በሙሉ፡ሃይማኖታቸውን አውቀው ተረድተው፡በተዋሕዶ፡ሃይማኖታ ቸው ጸንተው፡ከክሕደት፡ከኑፋቄ እንዲጠበቁበት፡መናፍቃንን ተከራክረው እንዲረቱበት፡ቤተ፡ክርስቲያና ቸውን በሕግና፡በሥርዓት፡ጸንተው፡እንዲያገለግሉበት፡ፈጣሪያቸው፡እግዚአብሔርን፡እንዲያመሰግኑበት፡በማሰብ፡ለመጀመሪያ፡ጊዜ፡በጉባኤ፡ቤቱ፡ስም፡ታትሟል፡፡በማለት በ[ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ]የቀረበልንን ምግበ ነፍስ ለመመገብ አንዘግይ !!!
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
ፍኖተ መጻሕፍት
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
❤3