የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
2.58K subscribers
6.08K photos
67 videos
60 files
1.7K links
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Download Telegram
60 የጥቁር አንበሳ ግቢ ገባኤ የሕክምና ተማሪዎች ተመረቁ።

በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ  ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርታቸውን ሲያስተምራቸው የቆዩ የጥቁር አንበሳ ግቢ ገባኤ ተማሪዎችን ዛሬ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስመርቋል።

በምትሄዱበት፣በምትሠማሩበት  የሥራ መስክ ሁሉ የዳር ተመልካቾች ሳትሆኑ በንቃትና በጥንቃቄ  ቅድስት ቤተክርስቲያንን እና ሀገራችሁን እንዲሁም ያስተማራችሁን ማኅበር ማኅበረ ቅዱሳንን በቅንነት፣ በታማኝነት እንድታገለግሉ ሲሉ በማኅበሩ የአዲስ አበባ  ማእከል የሕዝብ ግንኙነት ትብብር አገልግሎት ዋና ክፍል ኅላፊ አቶ አማረ ምትኩ  ለዕለቱ ተመራቂዎች መልእክታቸውን  አስተላልፈዋል።

በዕለቱ መምህራነ ቤተ ክርስቲያን ፣ ተመራቂ ፣የተመራቂ ቤተሰቦች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

©ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት
የሐዘን መግለጫ

የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው የእህታችን ወ/ሮ ታየች አለሙ ወንድሟ አርፎ ሥርዓተ ቀብሩ በትላንትናው እለት ተፈጽሟል። በመሆኑም መገኘት የምትችሉ አባላት መኖሪያ ቤቱ ለገዳዲ መድኀኔዓለም ቄራ ፊት ለፊት በመገኘት እንዲሁም በ0913257351 በመደወል እንድናጽናናቸው ይሁን።

አምላከ ቅዱስ ሚካኤል የወንድማችንን ነፍስ  በአጸደ ገነት ያሳርፍልን ።

        የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

  ወርሐዊ የባለትዳር አባላት ጉባኤ
———————————————

    በእለተ ኒቆዲሞስ


እሑድ መጋቢት 20/2018 ዓ.ም

  ከ5:00- 7:00

ጉባኤው በወር አንድ ቀን ብቻ የሚከናወን በመሆኑ በእለቱ  ተገኝተው ቃለ እግዚአብሔርን ይመገቡ።

            የባለትዳር ጉባኤ

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ
¯¯ ¯¯ ¯¯ ¯¯¯ ¯¯ ¯¯¯¯ ¯ ¯ ¯ ¯¯¯ ¯¯

እንደ እግዚአብሔር አምላክ መልካም ፈቃድ የአስመራጭ ኮሚቴ ምርጫ እሑድ መጋቢት 20/2018 ዓ.ም የሚከናወን በመሆኑ ከ11:30 ጀምሮ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።

አምላከ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክንን ይጠብቅልን።

     የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ሰላም እብል ለዘይቀድም ፆታሁ
እምእለ ቅውማን ገጻት ለብሉየ መዋዕል ታሕተ ክነፊሁ፤
ሚካኤል ካህን ለመልእክተ ዲያቆን በአምሳሊሁ ፤
ያትክል ዕድወ ነፍስየ እኂዞ በእዴሁ፤
ከመ ርእዮሙ ካልዓን ይፍርሑ።

ለተልዕኮ በሚፋጠን አገልጋይ አምሳል የነፍሳችንን ጠላት ሰይጣንን ፈጥኖ ያጠፋልን ዘንድ፤ ሌሎችም አይተው ይፈሩ ዘን፤ ዘመን በማይቆጠርለት በአምላክ ፊት ቆመው ከሚያመሰግኑ መላእክት ከፍ ከፍ ያለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልን ሰላም እላለሁ።

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሆይ ሐገራችን ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿንና ቅድስት ቤተክርስቲያንን በክንፈ ረድኤትህ ጠብቅልን በአልጋ ቁራኛ በደዌ ዳኛ ተይዘው የሚጨነቁትን ማርልን።

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የሐዘን መግለጫ

የሰንበት ት/ቤታችን አባል የነበረው (ነፍሱን ይማርልን) የወንድማችን ሠይፉ አማረ ወላጅ እናት አርፈዋል ሥርዓተ ቀብራቸው በዛሬው እለት መጋቢት 12/2018 ዓ.ም ክፍለ ሃገር ይፈጸማል ።  በመሆኑም መኖሪያ ቤታቸው ዘርዓይ ደረስ ት/ቤት ገባ ብሎ በመገኘት ቤተሰቦቻቸውን እንድናጽናናቸው ይሁን።

አምላከ ቅዱስ ሚካኤል የእናታችንን ነፍስ  በአጸደ ገነት ያሳርፍልን ።

        የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ለፍኖት መረዳጃ ዕድር አባላት በሙሉ
--------------------------------------------
ነገ እሑድ መጋቢት 13/2018 ዓ.ም ከቀኑ 5:00-7:00 ጠቅላላ ጉባኤ ስላለ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።