🔴 ስንክሳር#ጥር_14
በዚህች ቀን #ጻድቁ_አቡነ_አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው፣ የከበረችና የተመረጠች #ቅድስት_ምህራኤል በሰማእትነት አረፈች፣ በገድል የተጠመደ የከበረ #ቅዱስ_አባ_አርከሌድስ አረፈ፣ የከበረች #ቅድስት_እምራይስ በሰማእትነት አረፈች።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ጻድቁ_አቡነ_አረጋዊ (ዘሚካኤል)
ጥር አሥራ አራት በዚህች ቀን ታላቁና የከበረው አባታችን አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው።
እኚህ አባት ከ9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግስት እደና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡
የንጉሳዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል።
በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ480 ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡
ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡
አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደረሰዋል፡፡
ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር 90/91፥11-16 ላይ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡
ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡
ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ ብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት ሾመውላቸው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ ተሰውረዋል፡፡
አምላከ ቅዱሳን ለቅዱሳኑ ካደለው ፍቅራቸው ለእኛም አይንሳን:: በረከታቸውንም ያብዛልን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር_እና_ጥቅምት)
https://t.me/finotebirhan12
በዚህች ቀን #ጻድቁ_አቡነ_አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው፣ የከበረችና የተመረጠች #ቅድስት_ምህራኤል በሰማእትነት አረፈች፣ በገድል የተጠመደ የከበረ #ቅዱስ_አባ_አርከሌድስ አረፈ፣ የከበረች #ቅድስት_እምራይስ በሰማእትነት አረፈች።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ጻድቁ_አቡነ_አረጋዊ (ዘሚካኤል)
ጥር አሥራ አራት በዚህች ቀን ታላቁና የከበረው አባታችን አቡነ አረጋዊ (ዘሚካኤል) የተወለዱበት እና ወደ ደብረ ዳሞ የወጡበት ነው።
እኚህ አባት ከ9 ቅዱሳን አባቶች አንዱ ሲሆኑ አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉስ ነበሩ፡፡ እናታቸው ንግስት እደና ይባሉ ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ነው፡፡ ጥበብ መንፈሳ ሲማሩ አድገው ወደ እስክንድርያ ገዳም ገቡ፡፡ አበምኔቱ አባ ጳኩሚስ በፈቃደ እግዚአብሔር የመጡ መሆናቸውን አውቀው መዓረገ ምንኩስና ሰጥተዋቸዋል፡፡
የንጉሳዊ የቅንጦት ኑሮ ንቀው ትተው ገዳም ገብተው በምንኩስና ተወስነዋል፡፡ አባታችን በተጋድሏቸውም ከአባ እንጦንስ፣ ከአባ ጳውሊ እና ከአባ መቃርስ ቀጥሎ በአራተኛ ማዕረግ አበ መነኮሳት ሆነው ተመርጠዋል።
በገዳመ ዳውናስ 7 ዓመት ከቆዩ በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችን ኢትዮጵያን ዜና ሰምተው ለመምጣት በ480 ዓ.ም ከአባ ፍሬምናጦስ በኋላ መንገድ ጀመሩ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በክንፉ ተሸክሞ አክሱም አድርሷቸዋል፡፡
ተመልሰውም ሄደው ስለ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ መስክረዋል፡፡ ሐዋርያ ሳይላክላት በሃይማኖት በምግባር ጸንታ ትኖራለች ብለው ለሰባቱ ዘመዶቻቸው አበው መነኮሳት ነገሯቸው፡፡ ስምንቱም ጓዛቸውን ጠቅልለው በሮም ነግሶ የነበሩ ይስሐቅን (አባ ገሪማን) ጨምረው ንጉስ አልአሜዳ በነገሰ በአምስተኛ ዓመት ማለትም በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ዘጠኝ ሆነው መጥተዋል፡፡
አባ አረጋዊ እናታቸው ቅድስት እድናን ደቀ መዝሙራቸውን ማትያስን አስከትለው እግረ መንገዳቸውን እያስተማሩና ድውያንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ ደረሰዋል፡፡
ከእግረ ደብር ሆነው አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ እያሉ ሲያወጡ ሲያወርዱ በንግግሩ ሐሰት የሌለበት አምላካችን በነቢዩ ዳዊት ላይ አድሮ በመዝሙር 90/91፥11-16 ላይ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤ እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል። በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ። እንዳለው የታዘዘ ዘንዶ መጥቶ ስደሳ ክንድ በሚያህል ጅራቱ ጠምጥሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ከተራራው አናት አድርሷቸዋል፡፡
ወዲያው ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው አመስግነዋል፡፡ ቦታውም ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ በዚያ ዕለት ግማሽ ህብስት በልተው ጠገቡ፤ ከዚያ በኋላ ግን ምድራዊ ሕብስት አልተመገቡም፡፡ በሰንበተ ክርስታያን ከቅዳሴ በኋላ ሕብስተ ሰማያዊ እያመጡላቸው ይመገቡ ነበር እንጂ፡፡ ኋላም ዜና ጽድቃቸውን ሰምተው ከስድስት ሺህ ያላነሱ ደቀ መዛሙርት ተሰብስበውላቸዋል፡፡
ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁ ብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት ሾመውላቸው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ ተሰውረዋል፡፡
አምላከ ቅዱሳን ለቅዱሳኑ ካደለው ፍቅራቸው ለእኛም አይንሳን:: በረከታቸውንም ያብዛልን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር_እና_ጥቅምት)
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
🌑 ሀዘን
የመምህር ተስፋዬ ተሾመ አባት አርፈዋል ሥርዓተ ቀብራቸው ገላን ሳሎ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ከቀኑ 6ሰዓት ላይ ይፈፀማል የምንችል አባላት በመገኝት የመምህራችን ሀዘን ተካፋይ እንሁን ለመምህራችንም መጽናናቱን ይስጥልን
የመምህር ተስፋዬ ተሾመ አባት አርፈዋል ሥርዓተ ቀብራቸው ገላን ሳሎ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ከቀኑ 6ሰዓት ላይ ይፈፀማል የምንችል አባላት በመገኝት የመምህራችን ሀዘን ተካፋይ እንሁን ለመምህራችንም መጽናናቱን ይስጥልን
🔴 ስንክሳር#ጥር_15
ጥር 15 በዚህች ዕለት የከበረ ሕፃን #ቅዱስ_ቂርቆስና_ቅድስት_ኢየሉጣ በሰማዕትነት አረፉ፣ #ነብዩ_ቅዱስ_አብድዩ አረፈ፣ በሶርያ ክርስቲያን ወገኖች #የቅዱስ_ጎርጎርዮስን የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ያከብራሉ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ
በዚህችም ቀን ዳግመኛ በሶርያ አገር ያሉ የክርስቲያን ወገኖች የቅዱስ ጎርጎርዮስን የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ያከብራሉ። ይህም አባት በነፍስ በሥጋ በበጎ ሥራ ሁሉ ከወላጆቹ ጋር ፍጹም ነው። እርሱ እግዚአብሔርን መፍራትንና ትምህርቶችን ተምሮ ዐውቋልና የቋንቋም ትምህርት እጅግ የሚያውቅ የዮናናውያንንም ቋንቋ የሚያነብና የሚተረጒም ለቀና ሃይማኖትም የሚቀና ሆነ በውስጡም በጎ ሥራ በጎ ጠባይ ተፈጸመለት ኑሲስ በምትባል አገርም ላይ ሳይወድ በግድ መርጠው ኤጲስቆጶስነት ሾሙት እርሷም ደሴት ናት የእግዚአብሔርንም መንጋዎች ጠበቀ በትምህርቱና በድርሰቶቹም ልቡናቸውን ብሩህ አደረገ የብሉያትንና የሐዲሳትንም መጻሕፍት ተረጐመ።
ጳጳስ ሁኖ ስለነበረው ስለ ከሀዲው መቅዶንዮስ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን በቊስጥንጥንያ ከተማ የመቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ በሆነ ጊዜ ይህ ጎርጎርዮስ ከአባቶች ኤጲስቆጶሳት ጋር ሁኖ የሰባልዮስን ወገኖች መቅዶንዮስንና አቡሊናርዮስን ተከራከራቸው መልስ አሳጥቶም አሳፈራቸው። ስሕተታቸውንም ገለጠ። ይህም የካቲት አንድ ቀን ተጽፎአል የእነዚህንም ክህደት አስወገደ በቃሉ ሰይፍነትም የንባባቸውን የስሕተት ሐረግ ቆራርጦ አጠፋ ከተሰበሰቡትም ጋር በሰላም ተመለሰ እነርሱ በድል አድራጊነት እነዚያም ከሀድያን በኀፍረት ሁነው ተመለሱ ።
ወደ መልካም እርጅና ደርሶ እግዚአብሔርንም ደስ አሰኝቶ አገልገሎ በሰላም አረፈ እነሆ በዚህ ወር ጥር ሃያ አንድ ቀን ከገድሉ ጥቂት ጽፈናል ይኸውም በግብጻውያን ዕረፍቱ ነው።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
https://t.me/finotebirhan12
ጥር 15 በዚህች ዕለት የከበረ ሕፃን #ቅዱስ_ቂርቆስና_ቅድስት_ኢየሉጣ በሰማዕትነት አረፉ፣ #ነብዩ_ቅዱስ_አብድዩ አረፈ፣ በሶርያ ክርስቲያን ወገኖች #የቅዱስ_ጎርጎርዮስን የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ያከብራሉ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ
በዚህችም ቀን ዳግመኛ በሶርያ አገር ያሉ የክርስቲያን ወገኖች የቅዱስ ጎርጎርዮስን የዕረፍቱን መታሰቢያ በዓል ያከብራሉ። ይህም አባት በነፍስ በሥጋ በበጎ ሥራ ሁሉ ከወላጆቹ ጋር ፍጹም ነው። እርሱ እግዚአብሔርን መፍራትንና ትምህርቶችን ተምሮ ዐውቋልና የቋንቋም ትምህርት እጅግ የሚያውቅ የዮናናውያንንም ቋንቋ የሚያነብና የሚተረጒም ለቀና ሃይማኖትም የሚቀና ሆነ በውስጡም በጎ ሥራ በጎ ጠባይ ተፈጸመለት ኑሲስ በምትባል አገርም ላይ ሳይወድ በግድ መርጠው ኤጲስቆጶስነት ሾሙት እርሷም ደሴት ናት የእግዚአብሔርንም መንጋዎች ጠበቀ በትምህርቱና በድርሰቶቹም ልቡናቸውን ብሩህ አደረገ የብሉያትንና የሐዲሳትንም መጻሕፍት ተረጐመ።
ጳጳስ ሁኖ ስለነበረው ስለ ከሀዲው መቅዶንዮስ በንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን በቊስጥንጥንያ ከተማ የመቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳት የአንድነት ስብሰባ በሆነ ጊዜ ይህ ጎርጎርዮስ ከአባቶች ኤጲስቆጶሳት ጋር ሁኖ የሰባልዮስን ወገኖች መቅዶንዮስንና አቡሊናርዮስን ተከራከራቸው መልስ አሳጥቶም አሳፈራቸው። ስሕተታቸውንም ገለጠ። ይህም የካቲት አንድ ቀን ተጽፎአል የእነዚህንም ክህደት አስወገደ በቃሉ ሰይፍነትም የንባባቸውን የስሕተት ሐረግ ቆራርጦ አጠፋ ከተሰበሰቡትም ጋር በሰላም ተመለሰ እነርሱ በድል አድራጊነት እነዚያም ከሀድያን በኀፍረት ሁነው ተመለሱ ።
ወደ መልካም እርጅና ደርሶ እግዚአብሔርንም ደስ አሰኝቶ አገልገሎ በሰላም አረፈ እነሆ በዚህ ወር ጥር ሃያ አንድ ቀን ከገድሉ ጥቂት ጽፈናል ይኸውም በግብጻውያን ዕረፍቱ ነው።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
🔴 ስንክሳር#ጥር_16
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን የከበረ #ቅዱስ_ፊላታዎስ በሰማዕትነት ሞተ፣ የከበረ አባት ተጋዳይ የሆነ #ቅዱስ_ጰላድዮስ አረፈ፣ የከበረ አባት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የሶሪያ ሰው ሊቅ #ማር_ዳንኤል አረፈ፡፡
#ማር_ዳንኤል_ሶርያዊ
በዚህችም ዕለት ዓምድ ከሚባል አገር የሶሪያ ሰው ሊቅ ዳንኤል አረፈ የዚህም ቅዱስ አባቱ በወርቅና በብር ባለጸጋ የሆነ ነው። አባቱም በሞተ ጊዜ የሀገረ ዓምድ ጳጳስ አባ ዲዮናስዮስ ይህን ቅዱስ አሳደገው የቤተ ክርስቲያንንም ትምርት አስተማረው ከዚህም በኋላ ዲቁና ቅስና ሾመው የምንኲስና ልብስንም አለበሰው ሀብተ ፈውስም እስከተሰጠው ድረስ ከሰንበት እስከ ሰንበት ሳይበላ በጾም በጸሎት ጸንቶ ኖረ።
ከዚህም በኋላ የሴቶችን ፊት እንዳያይ ፈጽሞ ስዕለት አደረገ እናቱም ወሬውን በሰማች ጊዜ ወደርሱ መጣች ታየውም ዘንድ ላከችበት እርሱም የሴቶችን ፊት እንዳላይ ስዕለትን ተስያለሁ አላት። እርሷም እኔ እናትህ አይደለሁምን እንዴት እንደ ሌሎች ሴቶች ታስመስለኛለህ አለችው እምቢ በአላትም ጊዜ ክንብንቧን ገልጣ ሁለት ሴቶች አንድ ልብስ ለብሰው እያዩህ ሲጠቃቀሱብህ እግዚአብሔር ያሳየኝ ብላ ረገመችው።
ከጥቂት ቀንም በኋላ አንድ ምእመን ሰው ለሊቅ ዳንኤል ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር ወሰደለት በማታም ጊዜ ከሊቅ ዳንኤል ደጃፍ ሲደርስ ከእርሱ ጋር ያለ ወዳጁ ስለ ገንዘብ ፍቅር በላዩ ተነሥቶ ገደለው። ስለ ሟቹም የዓምድ ንጉሥ በሰማ ጊዜ አባ ዳንኤልን ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ በውሽባ ቤት ያሉ ሁለት ሴቶች የአባ ዳንኤልን መምጣት ወሬ በሰሙ ጊዜ ከችኮላቸው ብዛት የተነሣ ያዩት ዘንድ አንድ ልብስ ለብሰው ወጡ አባ ዳንኤልም እናቱ የተናገረችው ስለደረሰበት ፈገግ ብሎ ሣቀ።
ንጉሡም ስለ ሞተው ሰው አባ ዳንኤልን በመረመረው ጊዜ እኔ አልገደልሁትም ነገር ግን የገደለውን ራሱ ይናገር አለ። በዚያንም ጊዜ ሟቹ በአባ ዳንኤል ጸሎት ተነስቶ ገዳዩን ተናገረ ይህንንም ድንቅ ተአምር ንጉሡና ሕዝቡ ሁሉ አይተው በአባ ዳንኤል ፊት ሰገዱ። በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ሥራ የሚሠራ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።
ከዚህም በኋላ ለአባ ዳንኤል እጅ መንሻ ንጉሡ ብዙ ወርቅን አመጣ አባ ዳንኤልም ከርሱ መቀበልን እምቢ ባለ ጊዜ ንጉሥ ገዳምን ሠራለትና ብዙ መነኰሳት ተሰበሰቡ። ወደ መልካም ሽምግልናም በደረሰ ጊዜ ጥቂት ታመመና በሰላም አረፈ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
https://t.me/finotebirhan12
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን የከበረ #ቅዱስ_ፊላታዎስ በሰማዕትነት ሞተ፣ የከበረ አባት ተጋዳይ የሆነ #ቅዱስ_ጰላድዮስ አረፈ፣ የከበረ አባት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የሶሪያ ሰው ሊቅ #ማር_ዳንኤል አረፈ፡፡
#ማር_ዳንኤል_ሶርያዊ
በዚህችም ዕለት ዓምድ ከሚባል አገር የሶሪያ ሰው ሊቅ ዳንኤል አረፈ የዚህም ቅዱስ አባቱ በወርቅና በብር ባለጸጋ የሆነ ነው። አባቱም በሞተ ጊዜ የሀገረ ዓምድ ጳጳስ አባ ዲዮናስዮስ ይህን ቅዱስ አሳደገው የቤተ ክርስቲያንንም ትምርት አስተማረው ከዚህም በኋላ ዲቁና ቅስና ሾመው የምንኲስና ልብስንም አለበሰው ሀብተ ፈውስም እስከተሰጠው ድረስ ከሰንበት እስከ ሰንበት ሳይበላ በጾም በጸሎት ጸንቶ ኖረ።
ከዚህም በኋላ የሴቶችን ፊት እንዳያይ ፈጽሞ ስዕለት አደረገ እናቱም ወሬውን በሰማች ጊዜ ወደርሱ መጣች ታየውም ዘንድ ላከችበት እርሱም የሴቶችን ፊት እንዳላይ ስዕለትን ተስያለሁ አላት። እርሷም እኔ እናትህ አይደለሁምን እንዴት እንደ ሌሎች ሴቶች ታስመስለኛለህ አለችው እምቢ በአላትም ጊዜ ክንብንቧን ገልጣ ሁለት ሴቶች አንድ ልብስ ለብሰው እያዩህ ሲጠቃቀሱብህ እግዚአብሔር ያሳየኝ ብላ ረገመችው።
ከጥቂት ቀንም በኋላ አንድ ምእመን ሰው ለሊቅ ዳንኤል ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር ወሰደለት በማታም ጊዜ ከሊቅ ዳንኤል ደጃፍ ሲደርስ ከእርሱ ጋር ያለ ወዳጁ ስለ ገንዘብ ፍቅር በላዩ ተነሥቶ ገደለው። ስለ ሟቹም የዓምድ ንጉሥ በሰማ ጊዜ አባ ዳንኤልን ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ በውሽባ ቤት ያሉ ሁለት ሴቶች የአባ ዳንኤልን መምጣት ወሬ በሰሙ ጊዜ ከችኮላቸው ብዛት የተነሣ ያዩት ዘንድ አንድ ልብስ ለብሰው ወጡ አባ ዳንኤልም እናቱ የተናገረችው ስለደረሰበት ፈገግ ብሎ ሣቀ።
ንጉሡም ስለ ሞተው ሰው አባ ዳንኤልን በመረመረው ጊዜ እኔ አልገደልሁትም ነገር ግን የገደለውን ራሱ ይናገር አለ። በዚያንም ጊዜ ሟቹ በአባ ዳንኤል ጸሎት ተነስቶ ገዳዩን ተናገረ ይህንንም ድንቅ ተአምር ንጉሡና ሕዝቡ ሁሉ አይተው በአባ ዳንኤል ፊት ሰገዱ። በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ሥራ የሚሠራ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።
ከዚህም በኋላ ለአባ ዳንኤል እጅ መንሻ ንጉሡ ብዙ ወርቅን አመጣ አባ ዳንኤልም ከርሱ መቀበልን እምቢ ባለ ጊዜ ንጉሥ ገዳምን ሠራለትና ብዙ መነኰሳት ተሰበሰቡ። ወደ መልካም ሽምግልናም በደረሰ ጊዜ ጥቂት ታመመና በሰላም አረፈ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
#ጥር_17
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
#ቅዱስ_መክሲሞስ እና #ቅዱስ_ዱማቴዎስ
ጥር ዐሥራ ሰባት በዚህች ዕለት ለለውንድዮስ ለሮም ንጉስ ልጆቹ የሆኑ የከበሩና የተመሰገኑ መክሲሞስና ዱማቴዎስ መታሰቢያቸው ሆነ።ይህም ንጉስ ሃይማኖቱ የቀና እግዚአብሔርንም የሚፈራ በእውነትም የቀና ፍርድን የሚፈርድ ነበር ስለዚህም እሊህና ሁለት ቅዱሳን እግዚአብሔር ሰጠው እነርሱም ከታናሽነታቸው ጀምሮ በንጽህና እንደ እግዚአብሔር መላእክት ሆኑ።
ትሕትናን ፈሪሀ እግዚአብሔርን በማስተማር አሳደጋቸው የሚጾሙና የሚፀልዩ በቀንና በሌሊትም የብሉይና የሀዲስ መፃህፍቶችን የሚያነቡ ሆኑ። ከዚህም በኃላ ይህን አለም ይተውት ዘንድ የመላእከትንም ልብስ ይለብሱ ዘንድ እርሷም የከበረች የምንኩስና ልብስ ናት ከዚያም ሐሳብ መጣባቸው ሀይማኖታቸው የቀና ሶስት መቶ አስራ ስምንት አባቶች ወደ ተሰበሰቡባት ወደ ኒቅያ ሂደው ይፀልዩ ዘንድ እንዲአስናብታቸው ለአባታቸው ምክንያት አቀረቡ።
ይህንንም ከርሳቸው በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው ከብዙ አገልጋዮችና ከብዙ ሰራዊት ጋር አሰናበታቸው ከኒቅያ አገርም በደረሱ ጊዜ ከከበረ ቦታ በረከትን ተቀበሉ ሰራዊቱንም ወደ ንጉስ አባታቸው ጌታችን ንጉሥ ሆይ እኛ ከዚህ ጥቂት ቀን መቆየት እንሻለን ከሚል ጽሑፍ ጋር ጽፈው ላኩ።
ከዚህም በኃላ ለአንድ ፃድቅ መነኮስ ሐሳባቸውን ገለጡ እንዲህም አሉት ከአንተ ዘንድ የምንኩስናን ልብስ እንድንለብስ እንሻለን እርሱም እኔ ከንጉስ አባታችሁ የተነሳ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ሶሪያ ሂዱ ስሙ አጋብዮስ የሚባል ከዚያ ሀይማኖቱ የቀና ካህን ደግ መነኮስ አለ አላቸው። ይህንንም ሲላቸው ምክሩን ተቀብለው ወደ ሶሪያ ተጉዘው ወደ ቅዱስ አባ አጋብዮስ ደርሰው ኀሳባቸውን ገለጡለት እርሱም ተቀብሎ የምንኩስና ልብስን አለበሳቸው እስከሚአርፍበትም ቀን ከእርሱ ዘንድ ኖሩ።
ከዕረፍቱም አስቀድሞ ያየውን ራእይ ነገራቸው ታላቁ አባ መቃርስ ወደርሱ እንደመጣና ልጆችህ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ለኔ ልጆቼ ይሆኑኝ ዘንድ ወደ እኔ ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመጡ ከመሞቴ በፊት እዘዛቸው አለው።
ዳግመኛም እንዲህ አላቸው ልጆቹ እኔ ይህን ሰው አባ መቃርስን በስጋው አየው ዘንድ እመኝ ነበር እነሆ በመንፈስ አየሁት እናንተም ከሞትኩ በኃላ ወደርሱ ሒዱ።
ከአረፈም በኃላ አልሄዱም በዚያ በሶሪያ አገር ኖሩ እንጂ እግዚአብሔርም ሀብተ ፈውስ ሰጥቷቸው በሽተኞችን የሚፈውሱ ሆኑ ወሬያቸውም በሀገሮች ሁሉ ተሰማ በባህርና በየብስ ከሚነግዱ ነጋዴያንም የመርከብ መዛነቢያቸውን መስራት ተምረው ከድካም ዋጋቸው በየጥቂቱ የሚመገቡና የተረፈውን ለድሆችና ለችግረኞች የሚሰጡ ሆኑ።
እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ከሚሰራቸው ድንቆች ተአምራቶች የተነሳ የቅዱሳን መክሲሞስንና ዱማቴዎስን ስም መናፍስት ርኩሳን በሚሰሙ ጌዜ ከሰዎች ወጥተው ይሻሻሉ ሰዎቹም ያን ጊዜ በጌታ ኃይል ይድናሉ ጤነኞችም ይሆናሉ።
እጅግ ታላቅ የሆነ በጎዳና አጠገብ የሚኖር ከይሲ ነበር ብዙዎች ሰዎች ሰዎችንም አጥፍቷል የአገር ሰዎችም ወደ ከበሩ መክሶሞስና ዱማቴዎስ መጥተው ከዚያ ከይሲ ያድኗቸው ዘንድ ለመኗቸው አባ መክሲሞስም ክርታስ አንስቶ እንዲህ ብሎ ፃፈ የብፁእ መቃርዮስ አምላክ በሆነ መንፈስ ቅዱስንም በለበሰ በአባታችን በአጋብዮስ አምላክ በህያው እግዚአብሔር አካላዊ ቃል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ደብዳቤ ከዋሻህ ደጅ ቢደርስ አንተ ወጥተህ ሙት የሰማይ ወፎችም ይብሉህ።
አንድ ሰውም ያቺን ደብደቤ ተቀበሎ ሄደ በዚያም የዘንዶ ዋሻ ደጃፍ አኖራት በዚያንም ጊዜ ዘንዶዉ ወጥቶ ሞተ የሰማይ ወፎችም በሉት ህዝቦችም ሁሉ እጅግ አደነቁ እግዚአብሄርንም አመሰገኑት የክብር ባለቤት ጌታችንም በእሊህ ቅዱሳን በመክሲሞስና በዱማቴዎስ እጆች ብዙ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ።
በአንዲትም ዕለት ከአባታቸው መኳንንቶች አንዱ ወደ ባህር ዳርቻ ደረሰ ከመርከቦችም በአንዱ መርከብ መዛገቢያ ላይ መክሲሞስና ዱማቴዎስ የሚል ፅሁፍ በአየ ጊዜ የመርከቡን ሹም ጠየቀው እርሱም እንዲህ አለው በፀሎታቸው ከስጥመት እግዚአብሔር ያድነኝ ዘንድ የእሊህን ሁለት ወንድማማቾች የከበሩ መነኮሳት ስማቸውን በመርከቤ ላይ ፃፍኩ መኮንኑም መልካቸው ምን ይመስላል አለው እርሱም የመልካቸውን ምልክት ነገረው የንጉሱ ልጆች እንደሆኑ አውቆ ያን ነጋዴ ወደ ንጉስ አባታቸው አደረሰው።
ንጉሡም ጠየቀው ነጋዴውም የመልካቸውን አምሳል አስረዳው ንጉሡም ልጆቹ እንደሆኑ በተረዳ ጊዜ እናታቸውንና እኅታቸውን ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደነርሱ ላከ ደርሰውም በአዩአቸው ጊዜ ጩኸው አለቀሱ እናታቸውም ወደ ንጉስ አባታቸው ከእርሷ ጋር ይመጡ ዘንድ ለመነቻቸው።
እነርሱም ራሳችንን ስእለት አድርገን ለእግዚአብሔር ሰጥተናልና ቃል ኪዳናችንን ማፍረስ አይቻለንም ነገር ግን ሄጄ ለአንቺም ለአባታችንም ከመከራ ሁሉ እግዚአብሔር ያድናችሁ ዘንድ እንፀልይላችኋለን በዚህም አነጋገር አረጋጓት በመለየቷም ፈፅማ እያዘነች ተመለሰች።
ወደ ንጉሱም በደረሰች ጊዜ ከእነርሱ የሆነውን ነገረችው ንጉሱም ለሚስቱና ለባለሟሉቹ እንዲህ አለ በእግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የሕይወት ድልብ ይሆኑን ዘንድ እንተዋቸው ፀሎታቸውም ይጠቅመናል በዓለም ውስጥ ያለ ክብር ሁሉ እንደ ሕልም ኃላፊ ጠፊ ነውና እነርሱ ግን የማያልፍ መንግስትን አተረፉ።
በዚያም ወራት የሮሜ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት አረፈ ስለሚሾሙትም ሊቀ ጳጳሳት ይማከሩ ዘንድ ኤጲስቆጶሳት ጳጳሳትም ተሰበሰቡ የከበረ መክሲሞስንም አሰቡትና ሁሉም ለዚች ሹመት እርሱ በእውነት ይገባል ተባባሉ።በሽተኞችን ይፈውስ ዘንድ ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችንም ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር ታላቅ ፀጋ ሰጥቶታልና በእድሜውም ወጣት ቢሆን ክርስቶስ በውስጡ ወጣት ቢሆን ክርስቶስ በውስጡ ስለአደረ በዕውቀትና በበጎ ስራ በቤተ ክርስቲያንም ህግና ስርአት ሁሉ ፍፁም ነው።
ይህንንም በሰሙ ጊዜ አባቱና እናቱ ደስ አላቸው መኳንንቶችንም ላኩ የከበሩ መክሲሞስንና ዱማቴዎስን ወደ ሮሜ ይሰዳቸው ዘንድ ወደ ሶሪያ አገረ ገዢ ደብዳቤ አብረው ላኩ። እሊህም ቅዱሳን ሰምተው እጅግ አዘኑ አባታቸው አባ አጋብዮስም ያዘዛቸውን አሰቡ በዚያንም ጊዜ ተነሱ ልብሳቸውንም ለውጠው ወደ ኤርትራ ባህር ዳርቻ ተጓዙ ወደየትም እንደሚጓዙ አያውቁም ውኃን በሚጠሙ ጊዜም እግዚአብሔር መራራውን ውኃ ለውጦ ጣፋጭ አድርጎላቸው ይጠጣሉ ከዚህም በኃላ ከእርሱ ዘንድ ረድኤትን ኃይልን ላከላቸውና ከሶሪያ አገርም ተሸክማ ወደ አስቄጥስ ገዳም አደረሰቻቸው ወደ አባ መቃርስም ገብተው በእርሱ ዘንድ መኖርን እንደሚሹ ነረጉት።
እነርሱም በፀጋ የለመለሙ እንደሆኑ በአየ ጊዜ በገዳም መኖርን የማይችሉ መስለው በገዳም ያለውን ችግር ነገራቸውና በዚህ መኖር አትችሉም አላቸው እነርሱም አባታችን ሆይ ተወን ከዚህ መኖር ካልተቻለን እንሄዳለን ብለው መለሱለት።
ከዚህም በኃላ ሰሌን መስራትን አስተማራቸው ሰሌንም የሚቆርጡበትን ወንዝ አሳያቸው ማደሪያቸውንም እስከሚሰሩ ድረስ ረዳቸው የእጅ ስረቸውንም የሚሸጥና ምግባቸውን የሚያመጣላቸውን አንድ ህዝባዊ ሰው አምጥቶ አገናኛቸው። እንዲህም ሆነው ከቶ ከሰው ሳይገናኙ ሶስት አመት ኖሩ ነገር ግን በጭልታና በዝምታ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚገቡና ሥጋውንና ደሙን ተቀብለው ወደ ማደሪያቸው የሚመለሱ ሆኑ።
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
#ቅዱስ_መክሲሞስ እና #ቅዱስ_ዱማቴዎስ
ጥር ዐሥራ ሰባት በዚህች ዕለት ለለውንድዮስ ለሮም ንጉስ ልጆቹ የሆኑ የከበሩና የተመሰገኑ መክሲሞስና ዱማቴዎስ መታሰቢያቸው ሆነ።ይህም ንጉስ ሃይማኖቱ የቀና እግዚአብሔርንም የሚፈራ በእውነትም የቀና ፍርድን የሚፈርድ ነበር ስለዚህም እሊህና ሁለት ቅዱሳን እግዚአብሔር ሰጠው እነርሱም ከታናሽነታቸው ጀምሮ በንጽህና እንደ እግዚአብሔር መላእክት ሆኑ።
ትሕትናን ፈሪሀ እግዚአብሔርን በማስተማር አሳደጋቸው የሚጾሙና የሚፀልዩ በቀንና በሌሊትም የብሉይና የሀዲስ መፃህፍቶችን የሚያነቡ ሆኑ። ከዚህም በኃላ ይህን አለም ይተውት ዘንድ የመላእከትንም ልብስ ይለብሱ ዘንድ እርሷም የከበረች የምንኩስና ልብስ ናት ከዚያም ሐሳብ መጣባቸው ሀይማኖታቸው የቀና ሶስት መቶ አስራ ስምንት አባቶች ወደ ተሰበሰቡባት ወደ ኒቅያ ሂደው ይፀልዩ ዘንድ እንዲአስናብታቸው ለአባታቸው ምክንያት አቀረቡ።
ይህንንም ከርሳቸው በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው ከብዙ አገልጋዮችና ከብዙ ሰራዊት ጋር አሰናበታቸው ከኒቅያ አገርም በደረሱ ጊዜ ከከበረ ቦታ በረከትን ተቀበሉ ሰራዊቱንም ወደ ንጉስ አባታቸው ጌታችን ንጉሥ ሆይ እኛ ከዚህ ጥቂት ቀን መቆየት እንሻለን ከሚል ጽሑፍ ጋር ጽፈው ላኩ።
ከዚህም በኃላ ለአንድ ፃድቅ መነኮስ ሐሳባቸውን ገለጡ እንዲህም አሉት ከአንተ ዘንድ የምንኩስናን ልብስ እንድንለብስ እንሻለን እርሱም እኔ ከንጉስ አባታችሁ የተነሳ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ሶሪያ ሂዱ ስሙ አጋብዮስ የሚባል ከዚያ ሀይማኖቱ የቀና ካህን ደግ መነኮስ አለ አላቸው። ይህንንም ሲላቸው ምክሩን ተቀብለው ወደ ሶሪያ ተጉዘው ወደ ቅዱስ አባ አጋብዮስ ደርሰው ኀሳባቸውን ገለጡለት እርሱም ተቀብሎ የምንኩስና ልብስን አለበሳቸው እስከሚአርፍበትም ቀን ከእርሱ ዘንድ ኖሩ።
ከዕረፍቱም አስቀድሞ ያየውን ራእይ ነገራቸው ታላቁ አባ መቃርስ ወደርሱ እንደመጣና ልጆችህ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ለኔ ልጆቼ ይሆኑኝ ዘንድ ወደ እኔ ወደ አስቄጥስ ገዳም እንዲመጡ ከመሞቴ በፊት እዘዛቸው አለው።
ዳግመኛም እንዲህ አላቸው ልጆቹ እኔ ይህን ሰው አባ መቃርስን በስጋው አየው ዘንድ እመኝ ነበር እነሆ በመንፈስ አየሁት እናንተም ከሞትኩ በኃላ ወደርሱ ሒዱ።
ከአረፈም በኃላ አልሄዱም በዚያ በሶሪያ አገር ኖሩ እንጂ እግዚአብሔርም ሀብተ ፈውስ ሰጥቷቸው በሽተኞችን የሚፈውሱ ሆኑ ወሬያቸውም በሀገሮች ሁሉ ተሰማ በባህርና በየብስ ከሚነግዱ ነጋዴያንም የመርከብ መዛነቢያቸውን መስራት ተምረው ከድካም ዋጋቸው በየጥቂቱ የሚመገቡና የተረፈውን ለድሆችና ለችግረኞች የሚሰጡ ሆኑ።
እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ከሚሰራቸው ድንቆች ተአምራቶች የተነሳ የቅዱሳን መክሲሞስንና ዱማቴዎስን ስም መናፍስት ርኩሳን በሚሰሙ ጌዜ ከሰዎች ወጥተው ይሻሻሉ ሰዎቹም ያን ጊዜ በጌታ ኃይል ይድናሉ ጤነኞችም ይሆናሉ።
እጅግ ታላቅ የሆነ በጎዳና አጠገብ የሚኖር ከይሲ ነበር ብዙዎች ሰዎች ሰዎችንም አጥፍቷል የአገር ሰዎችም ወደ ከበሩ መክሶሞስና ዱማቴዎስ መጥተው ከዚያ ከይሲ ያድኗቸው ዘንድ ለመኗቸው አባ መክሲሞስም ክርታስ አንስቶ እንዲህ ብሎ ፃፈ የብፁእ መቃርዮስ አምላክ በሆነ መንፈስ ቅዱስንም በለበሰ በአባታችን በአጋብዮስ አምላክ በህያው እግዚአብሔር አካላዊ ቃል በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ደብዳቤ ከዋሻህ ደጅ ቢደርስ አንተ ወጥተህ ሙት የሰማይ ወፎችም ይብሉህ።
አንድ ሰውም ያቺን ደብደቤ ተቀበሎ ሄደ በዚያም የዘንዶ ዋሻ ደጃፍ አኖራት በዚያንም ጊዜ ዘንዶዉ ወጥቶ ሞተ የሰማይ ወፎችም በሉት ህዝቦችም ሁሉ እጅግ አደነቁ እግዚአብሄርንም አመሰገኑት የክብር ባለቤት ጌታችንም በእሊህ ቅዱሳን በመክሲሞስና በዱማቴዎስ እጆች ብዙ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ።
በአንዲትም ዕለት ከአባታቸው መኳንንቶች አንዱ ወደ ባህር ዳርቻ ደረሰ ከመርከቦችም በአንዱ መርከብ መዛገቢያ ላይ መክሲሞስና ዱማቴዎስ የሚል ፅሁፍ በአየ ጊዜ የመርከቡን ሹም ጠየቀው እርሱም እንዲህ አለው በፀሎታቸው ከስጥመት እግዚአብሔር ያድነኝ ዘንድ የእሊህን ሁለት ወንድማማቾች የከበሩ መነኮሳት ስማቸውን በመርከቤ ላይ ፃፍኩ መኮንኑም መልካቸው ምን ይመስላል አለው እርሱም የመልካቸውን ምልክት ነገረው የንጉሱ ልጆች እንደሆኑ አውቆ ያን ነጋዴ ወደ ንጉስ አባታቸው አደረሰው።
ንጉሡም ጠየቀው ነጋዴውም የመልካቸውን አምሳል አስረዳው ንጉሡም ልጆቹ እንደሆኑ በተረዳ ጊዜ እናታቸውንና እኅታቸውን ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደነርሱ ላከ ደርሰውም በአዩአቸው ጊዜ ጩኸው አለቀሱ እናታቸውም ወደ ንጉስ አባታቸው ከእርሷ ጋር ይመጡ ዘንድ ለመነቻቸው።
እነርሱም ራሳችንን ስእለት አድርገን ለእግዚአብሔር ሰጥተናልና ቃል ኪዳናችንን ማፍረስ አይቻለንም ነገር ግን ሄጄ ለአንቺም ለአባታችንም ከመከራ ሁሉ እግዚአብሔር ያድናችሁ ዘንድ እንፀልይላችኋለን በዚህም አነጋገር አረጋጓት በመለየቷም ፈፅማ እያዘነች ተመለሰች።
ወደ ንጉሱም በደረሰች ጊዜ ከእነርሱ የሆነውን ነገረችው ንጉሱም ለሚስቱና ለባለሟሉቹ እንዲህ አለ በእግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የሕይወት ድልብ ይሆኑን ዘንድ እንተዋቸው ፀሎታቸውም ይጠቅመናል በዓለም ውስጥ ያለ ክብር ሁሉ እንደ ሕልም ኃላፊ ጠፊ ነውና እነርሱ ግን የማያልፍ መንግስትን አተረፉ።
በዚያም ወራት የሮሜ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት አረፈ ስለሚሾሙትም ሊቀ ጳጳሳት ይማከሩ ዘንድ ኤጲስቆጶሳት ጳጳሳትም ተሰበሰቡ የከበረ መክሲሞስንም አሰቡትና ሁሉም ለዚች ሹመት እርሱ በእውነት ይገባል ተባባሉ።በሽተኞችን ይፈውስ ዘንድ ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችንም ያደርግ ዘንድ እግዚአብሔር ታላቅ ፀጋ ሰጥቶታልና በእድሜውም ወጣት ቢሆን ክርስቶስ በውስጡ ወጣት ቢሆን ክርስቶስ በውስጡ ስለአደረ በዕውቀትና በበጎ ስራ በቤተ ክርስቲያንም ህግና ስርአት ሁሉ ፍፁም ነው።
ይህንንም በሰሙ ጊዜ አባቱና እናቱ ደስ አላቸው መኳንንቶችንም ላኩ የከበሩ መክሲሞስንና ዱማቴዎስን ወደ ሮሜ ይሰዳቸው ዘንድ ወደ ሶሪያ አገረ ገዢ ደብዳቤ አብረው ላኩ። እሊህም ቅዱሳን ሰምተው እጅግ አዘኑ አባታቸው አባ አጋብዮስም ያዘዛቸውን አሰቡ በዚያንም ጊዜ ተነሱ ልብሳቸውንም ለውጠው ወደ ኤርትራ ባህር ዳርቻ ተጓዙ ወደየትም እንደሚጓዙ አያውቁም ውኃን በሚጠሙ ጊዜም እግዚአብሔር መራራውን ውኃ ለውጦ ጣፋጭ አድርጎላቸው ይጠጣሉ ከዚህም በኃላ ከእርሱ ዘንድ ረድኤትን ኃይልን ላከላቸውና ከሶሪያ አገርም ተሸክማ ወደ አስቄጥስ ገዳም አደረሰቻቸው ወደ አባ መቃርስም ገብተው በእርሱ ዘንድ መኖርን እንደሚሹ ነረጉት።
እነርሱም በፀጋ የለመለሙ እንደሆኑ በአየ ጊዜ በገዳም መኖርን የማይችሉ መስለው በገዳም ያለውን ችግር ነገራቸውና በዚህ መኖር አትችሉም አላቸው እነርሱም አባታችን ሆይ ተወን ከዚህ መኖር ካልተቻለን እንሄዳለን ብለው መለሱለት።
ከዚህም በኃላ ሰሌን መስራትን አስተማራቸው ሰሌንም የሚቆርጡበትን ወንዝ አሳያቸው ማደሪያቸውንም እስከሚሰሩ ድረስ ረዳቸው የእጅ ስረቸውንም የሚሸጥና ምግባቸውን የሚያመጣላቸውን አንድ ህዝባዊ ሰው አምጥቶ አገናኛቸው። እንዲህም ሆነው ከቶ ከሰው ሳይገናኙ ሶስት አመት ኖሩ ነገር ግን በጭልታና በዝምታ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚገቡና ሥጋውንና ደሙን ተቀብለው ወደ ማደሪያቸው የሚመለሱ ሆኑ።
ሦስት አመት ያህል ወደርሱ ስለአልመጡና ስለአልጎበኙት አባታቸው አባ መቃርስ ከስራቸው የተነሳ አደነቀ ስራቸውንም ይገልጥለት ዘንድ ወደ ጌታችን ለመነና ተነስቶ ወደ ርሳቸው ሄደ እነርሱም በመምጣቱ ደስ ተሰኙበት በዚያች ሌሊትም ከርሳቸው ጋር አደረ። ለፀሎትም በተነሱ ጊዜ የእሳት ሐብል ከአፋቸው ሲወጣና ወደ ሰማይ ሲደርስ ሰይጣናትም እንደ ዝንቦች ሲከቡት የእግዚአብሔርም መልአክ በእሳት ሰይፍ ዝንቦቹን ሲያበርራቸው የከበሩ መክሲሞስንና ዱማቴዎስን አያቸው በነጋም ጊዜ አስኬማን አለብሳቸው ፀልዩልኝ ብሏቸውም ሊሄድ ተነሳ። እንርሱም ሰገዱለትና አባታችን ሆይ አንተ በእኛ ላይ ትፀልይ ዘንድ ትባርከንም ዘንድ የሚገባ ነው አሉት።
ተጋድሎአቸውንም በፈፀሙ ጊዜ እግዚአብሔር ከዚህ አለም ድካም ሊአሳርፋቸው ወደደ መክሲሞስም በፅኑ ህመም ታመመ ስጋውም እንደ እሳት ጋለ ወደርሱም ይመጣ ዘንድ ወደ አባ መቃርስ ላከ። አባ መቃርስም በመጣ ጊዜ በደዌ ሲሰቃይ አገኘው መክሲሞስም ፀልይልኝ ባርከኝም አለው። እርሱም በላዩ አማትቦ ይህ ደዌ ከአንተ ይርቃልና አይዞህ አለው መክሲሞስም አባቴ ሆይ በዚች ደዌ ከዚህ አለም እንደምወጣ እኔ አውቃለሁ ረድኤት አገኝ ዘንድ አንተ ፀልይልኝ አለው።
ይህንንም በተናገረ ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሰ በዚያችም ጊዜ አባ መቃርስ የቅዱሳንን አንድነት ነቢያትን ሀዋርያትን መጥምቁ ዮሀንስን ንጉስ ቆስጠንጢኖስንም አያቸው። እነርሱም ነፍሱ በክብር እስከወጣች ድረስ በአባ መክሲሞስ ዙሪያ ነበሩ።
አባ መቃርስም አልቅሶ መክሲሞስ ሆይ የተመሰገንክ የከበርክ ነህ አለ። ዱማቴዎስም በውንዱሙ ላይ መራራ ልቅሶ በማልቀስ አባ መቃርስን የሚለምነው ሆነ ነፍሴን ይወስዳትና ወደ ወንድሜም ያደርሳት ዘንድ ስለ እኔ ወደ እግዚአብሔር ፀልይ አለው።
አባ መክሲሞስም ከተቀበረ በኃላ በሶስተኛው ቀን አባ ዱማቴዎስ ታመመ ስለርሱም ለአባ መቃርስ ነገሩት አባ መቃርስም ወደርሱ ሊሄድ ተነሳ በጉዞ ላይም ሳለ አስቀድሞ ወደ አባ መክሲሞስ የመጡትን የቅዱሳን አንድነት አየ የአባ ዱማቴዎስንም ነፍስ ተቀበለው በክብር ወደ ሰማይ አሳረጓት።
አባ መቃርስም ወደ በኣታቸው ሲደርስ ዱማቴዎስን አርፎ አገኘው ወስዶም ከወንድሙ ከመክሲሞስ ጋር በአንድ መቃብር በክብር ቀበረው። የመክሲሞስም እረፍት በዚህ ወር በአስራ አራት ነው ዳግመኛ የዱማቴዎስ እረፍት ጥር አስራ ሰባት በዚች ቀን ነው።
የከበረ አባ መቃርስም ያ ቦታ በስማቸው እንዲጣራ አዘዘ እንዲሁም ደብረ በርሞስ ተብሎ እስከ ዛሬ የሚጠራ ሆነ ለዘላለሙም መታሰቢያቸው ሆነ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
ተጋድሎአቸውንም በፈፀሙ ጊዜ እግዚአብሔር ከዚህ አለም ድካም ሊአሳርፋቸው ወደደ መክሲሞስም በፅኑ ህመም ታመመ ስጋውም እንደ እሳት ጋለ ወደርሱም ይመጣ ዘንድ ወደ አባ መቃርስ ላከ። አባ መቃርስም በመጣ ጊዜ በደዌ ሲሰቃይ አገኘው መክሲሞስም ፀልይልኝ ባርከኝም አለው። እርሱም በላዩ አማትቦ ይህ ደዌ ከአንተ ይርቃልና አይዞህ አለው መክሲሞስም አባቴ ሆይ በዚች ደዌ ከዚህ አለም እንደምወጣ እኔ አውቃለሁ ረድኤት አገኝ ዘንድ አንተ ፀልይልኝ አለው።
ይህንንም በተናገረ ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሰ በዚያችም ጊዜ አባ መቃርስ የቅዱሳንን አንድነት ነቢያትን ሀዋርያትን መጥምቁ ዮሀንስን ንጉስ ቆስጠንጢኖስንም አያቸው። እነርሱም ነፍሱ በክብር እስከወጣች ድረስ በአባ መክሲሞስ ዙሪያ ነበሩ።
አባ መቃርስም አልቅሶ መክሲሞስ ሆይ የተመሰገንክ የከበርክ ነህ አለ። ዱማቴዎስም በውንዱሙ ላይ መራራ ልቅሶ በማልቀስ አባ መቃርስን የሚለምነው ሆነ ነፍሴን ይወስዳትና ወደ ወንድሜም ያደርሳት ዘንድ ስለ እኔ ወደ እግዚአብሔር ፀልይ አለው።
አባ መክሲሞስም ከተቀበረ በኃላ በሶስተኛው ቀን አባ ዱማቴዎስ ታመመ ስለርሱም ለአባ መቃርስ ነገሩት አባ መቃርስም ወደርሱ ሊሄድ ተነሳ በጉዞ ላይም ሳለ አስቀድሞ ወደ አባ መክሲሞስ የመጡትን የቅዱሳን አንድነት አየ የአባ ዱማቴዎስንም ነፍስ ተቀበለው በክብር ወደ ሰማይ አሳረጓት።
አባ መቃርስም ወደ በኣታቸው ሲደርስ ዱማቴዎስን አርፎ አገኘው ወስዶም ከወንድሙ ከመክሲሞስ ጋር በአንድ መቃብር በክብር ቀበረው። የመክሲሞስም እረፍት በዚህ ወር በአስራ አራት ነው ዳግመኛ የዱማቴዎስ እረፍት ጥር አስራ ሰባት በዚች ቀን ነው።
የከበረ አባ መቃርስም ያ ቦታ በስማቸው እንዲጣራ አዘዘ እንዲሁም ደብረ በርሞስ ተብሎ እስከ ዛሬ የሚጠራ ሆነ ለዘላለሙም መታሰቢያቸው ሆነ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ መክሲሞስና ዱማቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
🔴 ስንክሳር#ጥር_18
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ #የቅዱስ_ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፣ የሀገረ ንጽቢን ኤጲስቆጶስ #አባ_ያዕቆብ አረፈ፣ #የቅዱስ_አቤላክ (ባኮስ) ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ መታሰቢያው ነው፣ የአልዓዛር እህቶች #የማርያ_እና_የማርታ መታቢያቸው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ዝርወተ_አፅሙ_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ
ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፡፡
ይኸውም ሰባ ነገሥታት ማሰቃየት በሰለቻቸው ጊዜ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደ መጭመቂያ ሆኖ ከተሠራ የስቃይ መሣሪያ ላይ አውጥተው ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት ንጉሥ ዱድያኖስ አዘዘ፡፡ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረግፉት ድረስ እንዲህ አደረጉበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስቃይ ብዛት የተነሳ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች ሥጋውንም በሙሉ በእሳት አቃጠሉት አመድም ሆነ፡፡
ከሐዲው ንጉሥ ዱዲያኖስ የተቃጠለውን የሥጋውን አመድ አፍሰው በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ወስደው ምዕመናን ራሩን አመዱን እንኳን እንዳያገኙት በነፋስ እንዲዘሩት አዘዘ፡፡ ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ማለት ነው፡፡ ወታደሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ ነስንሰው የተመለሱበት፣ የሥጋው አመድ ያረፈበት ዕፅዋት ሁሉ ጊዮርጊስ ጊዮርጊስ ያሉበት፣ ጌታችን ከመላእክት ጋር ተገልጦ አራቱን የምድር ነፋሳትንም የቅዱስ ጊዮርጊስ የሥጋውን ትቢያ እንዲሰበስብ አዞ። "የኔ ሆይ! የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ከሞት ተነሥ አትፍራ፤ እኔ አዝዤሀለሁና" ሲል ኀያሉን ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠራው። ያን ጊዜ ልዑል ንዑድ ጊዮርጊስም ከጫጉላ ቤት እንደሚወጣ ሙሽራ ምንም ሕማም ሳይኖርበት ተነሣ።
መድኃኒታችንም ባረከው። "አትፍራ፤ ይኸንን ከሀዲ ንጉሥም እስክታሳፍረው ድረስ እኔ አጸናሀለሁ። ከእንዲህስ ወዲህ አምላኩ ከእጃችን ሊያአድነው አይችሉም እንዳይሉ እነዚህን ከሐድያን ነገሥታትና የረከሱ ጣዖታቸውን ታሳፍራቸው ዘንድ ተነሣና ወደ አገር ውጣ፤ ሰላሜ ለዘለዓለም ከአንተ ጋር ይሁን" አለው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ተናግሮ ሳመው። በፍጹም ምስጋናም ወደ ሰማይ ዐረገ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጌታችን ይህንንም ቃል ኪዳን የተቀበለበት ቀን ነው፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ገድለ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፣ #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር፣ #መዝገበ_ቅዱሳን፤ #ከገድላት_አንደበት፣ #ዲያቆን_ዮርዳኖስ_አበበ)
https://t.me/finotebirhan12
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ #የቅዱስ_ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፣ የሀገረ ንጽቢን ኤጲስቆጶስ #አባ_ያዕቆብ አረፈ፣ #የቅዱስ_አቤላክ (ባኮስ) ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ መታሰቢያው ነው፣ የአልዓዛር እህቶች #የማርያ_እና_የማርታ መታቢያቸው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ዝርወተ_አፅሙ_ለቅዱስ_ጊዮርጊስ
ጥር ዐስራ ስምንት በዚች ቀን የሰማዕታት አለቃ የቅዱስ ጊዮርጊስ አፅሙ ተቃጥሎ ተደቁሶ የተበተነበት ነው፡፡
ይኸውም ሰባ ነገሥታት ማሰቃየት በሰለቻቸው ጊዜ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንደ መጭመቂያ ሆኖ ከተሠራ የስቃይ መሣሪያ ላይ አውጥተው ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት ንጉሥ ዱድያኖስ አዘዘ፡፡ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረግፉት ድረስ እንዲህ አደረጉበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስቃይ ብዛት የተነሳ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች ሥጋውንም በሙሉ በእሳት አቃጠሉት አመድም ሆነ፡፡
ከሐዲው ንጉሥ ዱዲያኖስ የተቃጠለውን የሥጋውን አመድ አፍሰው በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ወስደው ምዕመናን ራሩን አመዱን እንኳን እንዳያገኙት በነፋስ እንዲዘሩት አዘዘ፡፡ ደብረ ይድራስ ማለት ምድረ በዳ ማለት ነው፡፡ ወታደሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ ነስንሰው የተመለሱበት፣ የሥጋው አመድ ያረፈበት ዕፅዋት ሁሉ ጊዮርጊስ ጊዮርጊስ ያሉበት፣ ጌታችን ከመላእክት ጋር ተገልጦ አራቱን የምድር ነፋሳትንም የቅዱስ ጊዮርጊስ የሥጋውን ትቢያ እንዲሰበስብ አዞ። "የኔ ሆይ! የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ከሞት ተነሥ አትፍራ፤ እኔ አዝዤሀለሁና" ሲል ኀያሉን ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠራው። ያን ጊዜ ልዑል ንዑድ ጊዮርጊስም ከጫጉላ ቤት እንደሚወጣ ሙሽራ ምንም ሕማም ሳይኖርበት ተነሣ።
መድኃኒታችንም ባረከው። "አትፍራ፤ ይኸንን ከሀዲ ንጉሥም እስክታሳፍረው ድረስ እኔ አጸናሀለሁ። ከእንዲህስ ወዲህ አምላኩ ከእጃችን ሊያአድነው አይችሉም እንዳይሉ እነዚህን ከሐድያን ነገሥታትና የረከሱ ጣዖታቸውን ታሳፍራቸው ዘንድ ተነሣና ወደ አገር ውጣ፤ ሰላሜ ለዘለዓለም ከአንተ ጋር ይሁን" አለው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ተናግሮ ሳመው። በፍጹም ምስጋናም ወደ ሰማይ ዐረገ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጌታችን ይህንንም ቃል ኪዳን የተቀበለበት ቀን ነው፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ገድለ_ቅዱስ_ጊዮርጊስ፣ #ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር፣ #መዝገበ_ቅዱሳን፤ #ከገድላት_አንደበት፣ #ዲያቆን_ዮርዳኖስ_አበበ)
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
🔴 ስንክሳር#ጥር_19
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ዕለት የከበሩ #የአባ_ዝሑራ #የአባ_ባሱራ የእናታቸውም #የኔራ ሥጋቸው የተገኘበት ነው፣ የታላቁ አባት #የአቡነ_አፍቅረነ_እግዚእ እረፍታቸው ነው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ባሱራ_እና_አባ_ዝሑራ
ጥር ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ዕለት የከበሩ የአባ ዝሑራ የአባ ባሱራ የእናታቸውም የኔራ ሥጋቸው ተገኘ።
እሊህ የከበሩ ተጋዳዮችም ጣዖት በሚመለክበት ዘመን ሳብሳ ከሚባል አገር በሰማዕትነት ሞቱ ሥጋዎቻቸውም በሳብሳ አገር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚኖሩ ሆኑ ከንጹሐን ሰማዕታትም ዘመን ከዘጠኝ መቶ አርባ ሰባት ዓመት በኋላ የአፍርንጊ ሠራዊት ግብጽን ከበቧት የድምያጥንም ከተማ ወስደው በዚያ ነገሡ ከርሷ ጋርም በዙሪያዋ ያሉ ታላላቅ ከተሞችን ያዙ።
የኮሞል ንጉሥም ይህም የግብጽ ንጉሥ ነው አፍርንጊያውያንንም ይወጋቸው ዘንድ ከግብጽ ሀገር ሁሉ ብዙ ሠራዊትን ሰበሰበ ሠራዊቱም ሲጓዙ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትን አፈረሱ ከፈረሱትም ውስጥ አንዲቷ የእሊህ ቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋቸው በውስጧ ያለባት ናት። ከሠራዊቱም አንዱ የቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋ ያለበትን ሣጥን ወሰደ በውስጡ የሚደሰትበትን የዚህን ዓለም ገንዘብ እንደሚያገኝ አስቦ በከፈተው ጊዜ ከዕንቊ የከበረ የቅዱስንን ሥጋቸውን አገኘ ክብራቸውን ግን አላወቀም ከቤተ ክርስቲያኑ ግድግዳ ላይ ሥጋቸውን በትኖ ሣጥኑን ወስዶ ሸጠው።
ምሕረቱ የበዛ የሚታገሥ ልዑል እግዚአብሔርም ወደ አፍርንጊ ሠራዊት እስከሚደርስ በእርሱ ላይ ታገሠ ጦርነትም በገጠሙ ጊዜ ከሁሉ አስቀድሞ እርሱ ተገደለ ባልንጀሮቹም ምስክር እንደሆኑ ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ የእግዚአብሔርን ክብር ፈጽመው ሰበኩ እንዲህም አሉ እርሱ አስቀድሞ በሰይፍ ተመታ ራሱንም ተቆረጠ ጐኖቹንም ሠነጣጥቀውት በክፉ አሟሟት ሞተ።
የቅዱሳኑን ሥጋቸውን ያ ሰው በበተናቸው ጊዜ የአንድ ቄስ ሚስት የሆነች አንዲት ምእመን ሴት ቁማ ትመለከት ነበር ከዚህም በኋላ በጭልታ ወደርሳቸው ገብታ ደስ እያላት ወስዳ በመጐናጸፊያዋ ጠቀለለቻቸው እስላሞችንም ከመፍራቷ የተነሣ በቤተ ክርስቲያን ማዕዘን ውስጥ አኖረቻቸው በመጐናጸፊያዋም እንደ ተጠቀለሉ በጡብ ሸፈነቻቸው በዚያም ጡብ ተሸፍነው በዚያች ማዕዘን ውስጥ ሃያ ዓመት ያህል ኖሩ ከቀን ብዛትም የተነሣ ያቺ ሴት ወሬያቸውን ረሳች።
እግዚአብሔርም ለወገኖቹ ጥቅም ይገልጣቸው ዘንድ በወደደ ጊዜ በዚያች ሴት ፊት ሌሎች ሰዎች አስታወሷቸው እርሷም በዚያን ጊዜ አስታወሰቻቸው ለካህናቱና ለምእመናኑ ነግራ ቦታቸውን አሳየቻቸው። ካህናቱም ገብተው ሥጋቸውን አነሡ ያማረች ሣጥንንም ሠርተው በውስጧ በክብር አኖሩዋቸው እንደ ዛሬዪቱም ዕለት በዓልን አደረጉላቸው ሁል ጊዜ በዚች ዕለት በዓል ያደርጉላቸው ዘንድ ስማቸውን በበዓላት ግጻዌ መጽሐፍ እንዲጽፉ የአገሩ ኤጲስቆጶስ አባ ገብርኤል አዝዟልና።
ከዐፅሞቻቸውም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ከተአምራቶችም አንዲት የታወረች ልጅ ያለቻት ሴት ነበረች ተስፋ ከቆረጠችም በኋላ ከቅዱሳኑ ዐፅም በተማፀነች ጊዜ ዐይኖቿ ተገልጠውላት አየች እሊህንም ሰማዕታት በዚህ ክብር ያከበራቸውን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነችው።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር እና #ከገድላት_አንደበት)
https://t.me/finotebirhan12
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ዕለት የከበሩ #የአባ_ዝሑራ #የአባ_ባሱራ የእናታቸውም #የኔራ ሥጋቸው የተገኘበት ነው፣ የታላቁ አባት #የአቡነ_አፍቅረነ_እግዚእ እረፍታቸው ነው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ባሱራ_እና_አባ_ዝሑራ
ጥር ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ዕለት የከበሩ የአባ ዝሑራ የአባ ባሱራ የእናታቸውም የኔራ ሥጋቸው ተገኘ።
እሊህ የከበሩ ተጋዳዮችም ጣዖት በሚመለክበት ዘመን ሳብሳ ከሚባል አገር በሰማዕትነት ሞቱ ሥጋዎቻቸውም በሳብሳ አገር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚኖሩ ሆኑ ከንጹሐን ሰማዕታትም ዘመን ከዘጠኝ መቶ አርባ ሰባት ዓመት በኋላ የአፍርንጊ ሠራዊት ግብጽን ከበቧት የድምያጥንም ከተማ ወስደው በዚያ ነገሡ ከርሷ ጋርም በዙሪያዋ ያሉ ታላላቅ ከተሞችን ያዙ።
የኮሞል ንጉሥም ይህም የግብጽ ንጉሥ ነው አፍርንጊያውያንንም ይወጋቸው ዘንድ ከግብጽ ሀገር ሁሉ ብዙ ሠራዊትን ሰበሰበ ሠራዊቱም ሲጓዙ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትን አፈረሱ ከፈረሱትም ውስጥ አንዲቷ የእሊህ ቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋቸው በውስጧ ያለባት ናት። ከሠራዊቱም አንዱ የቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋ ያለበትን ሣጥን ወሰደ በውስጡ የሚደሰትበትን የዚህን ዓለም ገንዘብ እንደሚያገኝ አስቦ በከፈተው ጊዜ ከዕንቊ የከበረ የቅዱስንን ሥጋቸውን አገኘ ክብራቸውን ግን አላወቀም ከቤተ ክርስቲያኑ ግድግዳ ላይ ሥጋቸውን በትኖ ሣጥኑን ወስዶ ሸጠው።
ምሕረቱ የበዛ የሚታገሥ ልዑል እግዚአብሔርም ወደ አፍርንጊ ሠራዊት እስከሚደርስ በእርሱ ላይ ታገሠ ጦርነትም በገጠሙ ጊዜ ከሁሉ አስቀድሞ እርሱ ተገደለ ባልንጀሮቹም ምስክር እንደሆኑ ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ የእግዚአብሔርን ክብር ፈጽመው ሰበኩ እንዲህም አሉ እርሱ አስቀድሞ በሰይፍ ተመታ ራሱንም ተቆረጠ ጐኖቹንም ሠነጣጥቀውት በክፉ አሟሟት ሞተ።
የቅዱሳኑን ሥጋቸውን ያ ሰው በበተናቸው ጊዜ የአንድ ቄስ ሚስት የሆነች አንዲት ምእመን ሴት ቁማ ትመለከት ነበር ከዚህም በኋላ በጭልታ ወደርሳቸው ገብታ ደስ እያላት ወስዳ በመጐናጸፊያዋ ጠቀለለቻቸው እስላሞችንም ከመፍራቷ የተነሣ በቤተ ክርስቲያን ማዕዘን ውስጥ አኖረቻቸው በመጐናጸፊያዋም እንደ ተጠቀለሉ በጡብ ሸፈነቻቸው በዚያም ጡብ ተሸፍነው በዚያች ማዕዘን ውስጥ ሃያ ዓመት ያህል ኖሩ ከቀን ብዛትም የተነሣ ያቺ ሴት ወሬያቸውን ረሳች።
እግዚአብሔርም ለወገኖቹ ጥቅም ይገልጣቸው ዘንድ በወደደ ጊዜ በዚያች ሴት ፊት ሌሎች ሰዎች አስታወሷቸው እርሷም በዚያን ጊዜ አስታወሰቻቸው ለካህናቱና ለምእመናኑ ነግራ ቦታቸውን አሳየቻቸው። ካህናቱም ገብተው ሥጋቸውን አነሡ ያማረች ሣጥንንም ሠርተው በውስጧ በክብር አኖሩዋቸው እንደ ዛሬዪቱም ዕለት በዓልን አደረጉላቸው ሁል ጊዜ በዚች ዕለት በዓል ያደርጉላቸው ዘንድ ስማቸውን በበዓላት ግጻዌ መጽሐፍ እንዲጽፉ የአገሩ ኤጲስቆጶስ አባ ገብርኤል አዝዟልና።
ከዐፅሞቻቸውም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ከተአምራቶችም አንዲት የታወረች ልጅ ያለቻት ሴት ነበረች ተስፋ ከቆረጠችም በኋላ ከቅዱሳኑ ዐፅም በተማፀነች ጊዜ ዐይኖቿ ተገልጠውላት አየች እሊህንም ሰማዕታት በዚህ ክብር ያከበራቸውን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነችው።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር እና #ከገድላት_አንደበት)
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
🔴 ስንክሳር#ጥር_20
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ በዚህች ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የከበረ #ሐዋርያ_አብሮኮሮስ አረፈ፣ የከበረ #ቀሲስ_አክሎግ በሰማዕትነት ሞተ፣ #አባ_ዮሐንስ_ወንጌሉ_ዘወርቅ ሥጋው ወደ ሮሜ አገር የፈለሰበት እና ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ነው፣ የታላቁ ሰማዕት #የቅዱስ_መርምሕናም ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ተአምራቱ የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርምህናም
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርምሕናም ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ተአምራቱ የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡ ቅድስት ሣራና ወንድሟ መርምህናም አባታቸው የአቶር ንጉሥ ሲሆን እርሱም የተቀረጹ ጣዖታን ያመልክ ነበር፡፡ እናታቸው ግን አማኝ ክርስቲያን ነበረች፡፡ ቅዱስ መርምህናም አባቱን ለምኖና አስፈቅዶ ወደ ዱር ሄዶ አራዊትን ለማደን በወጣ ጊዜ እናቱ የሰማይና የምድር አምላክ እግዚአብሔር በላዩ በረከትን ያሳድርበት ዘንድ ከጸለየችለት በኋላ ሸኘችው፡፡ መርምህናም ከ40 ፈረሰኛ አገልጋዮቹ ጋር ወጥቶ ሄደ፡፡ ወደ አንድ ተራራም ወጥቶ በዚያ አደረ፡፡ በሌሊትም የታዘዘ መልአክ ጠራውና ‹‹መርምህናም ሆይ ተነሥተህ ወደዚህ ተራራ ጫፍ ላይ ውጣ፣ ስሙ ማቴዎስ የሚባል ቅዱስ ሰው ታገኛለህ፡፡ እርሱም የሕይወትን ነገር ይነግርሃል›› አለው፡፡ ቅዱስ መርምህናም ሲነጋ ወደ ተራራው ጫፍ ላይ ወጣና የበግ ጠጉር ለብሶ አባ ማቴዎስን ባገኘው ጊዜ እጅግ ፈራ፡፡ አባ ማቴዎስም ‹‹አይዞህ አትራ እኔም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነኝና አትፍራ›› ብለው አበረቱት፡፡ መርምህናም የእግዚአብሔርን ስም ሲጠሩ ሲሰማ ‹‹አባቴ ከአማልክቶች በቀር አምላክ አለን?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አባታችን የሃይማኖትን ነገር ሁሉንም አስተማሩት፡፡ መርምህናምም ‹‹ከራስ ጠጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ ድረስ በለምጽ የተመታች እኅት አለችኝና እርሷን የአምላክህን ስም ጠርተህ ካዳንክልኝ በእውነት በአምላክህ አምናለሁ›› አላቸው፡፡ ሁለቱም ተያይዘው ከተራራው ወርደው ወደ ንጉሡ ቤት ሄደው መርምህናም ለእናቱ ያጋጠመውን ነገር ነገራትና በለምጽ የተመታችውን እኅቱን ሣራን በሥውር ወደ አባ ማቴዎስ ዘንድ ወሰዳት፡፡ አባታችንም መሬቱን ባርከው ውኃ አፍልቀው አጠመቋትና ከለምጹዋ ፈወሷት፡፡ አርባው ጭፍራዎችም አምነው ተጠመቁ፡፡ አባታችንም ሰማዕትነትን እንደሚቀበሉ ትንቢት ነግረዋቸው ባርከው መርቀው አሰናበቷቸው፡፡
መርምህናምም ወደ አባቱ ቤት በተለመሰ ጊዜ ጣዖቱ ቤት መግባትን እምቢ አለ፡፡ ከዚህም በኋላ አርባውን ጭፍራዎችና እኅቱን ሣራን ይዞ ወደ አንዲት ተራራ ላይ ወጥቶ ተቀመጠ፡፡ የአቶሩን ንጉሥ የሆነው አባቱ ‹‹ና መንግሥቴን ውረስ›› ብሎ ለቅዱስ መርምህናም ላከበት፡፡ ነገር ግን ቅዱስ መርምህናም ‹‹የጌታዬን ፈጽሞ የማይጠፋውን መንግሥት እሻለሁ›› ብሎ ለንጉሥ አባቱ ላከበት፡፡ ንጉሡም በቅድሚያ 40ውን አገልጋዮቹን ጭፍራዎች እንዲገድሏቸው አዘዘና ራስ ራሶቻቸውን እየቆረጡ ከጉድጓድ ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ መርምህናምም ሲጸልይ ከሰማይ ‹‹መርምህናም ሆይ! ጸሎትህን ሰምቻለሁ…›› የሚል ድምፅ መጣለት፡፡ ወዲያውም በንጉሡ ወላጅ አባታቸው ትእዛዝ ቅዱስ መርምህናምና እኅቱ ቅድስት ሣራ አንገታቸውን ተሰየፉና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ሥጋቸውንም በጉድጓድ ጨምረው ሊያቃጥሏቸው ሲሉ ሥጋቸውን እግዚአብሔር ሰወረባቸው፡፡ ወዲያውም ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ፣ ፀሐይም ጨለመች፡፡ የሰየፏቸውም ፈርተው ሸሹ፡፡ ከዚህም በኋላ ሰይጣን በአባታቸው በአቶሩ ንጉሥ ላይ አድሮበት አሳበደው፡፡ እንደ እሪያም መጮህ ጀመረ፡፡ ክርስቲያን የሆነችው የቅዱስ መርምህናምና የቅደስት ሣራ እናታቸው ወደ አባ ማቴዎስ ሄዳ ንጉሡ በልጆቹ ላይ ያደረገውንና በእርሱም ላይ የተፈጸመበትን ነገር ነገረቻቸው፡፡ አባ ማቴዎስም ንጉሡን ዘይት ቀብተው ጸልየው ፈወሱት፡፡ በውስጡ አድሮበት የነበረውንም ሰይጣን በእሪያ መልክ ከንጉሡ ውስጥ አስወጡት፡፡
ንጉሡም ወደ ልቡ ሲመለስ በአባ ማቴዎስ ትምህርት በጌታችን አመነ፡፡ በሚገዛቸው አገሮች ሁሉ ያሉትን ሰዎች ይዞ ከነቤተሰቡ ተጠመቀ፡፡ ንጉሡም በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን አሠራ፡፡ ንግሥቲቱ ሚስቱም የሰማዕታቱን ልጆቿን ሥጋ በሳጥን አድርጋ በውስጧ አኖረች፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ተአምራት ተገለጡ፡፡ አባታቸው የአቶሩ ንጉሥም ለችግረኞችና ለጦም አዳሪዎች እየመጸወተ በተጋድሎ ኖረ፡፡ የቅዱስ መርምህናምና የእኅቱ የቅድስት ሣራ እረፍታቸው ታኅሣሥ 14 ቀን ነው፡፡
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የቅዱስ መርምህናም አባት ንጉሡ አቶርና የመርምህናም ማኅበርተኞች የሆኑ ቁጥራቸው 170 ሺህ የሆኑ ሰማዕታት የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይህም የአቶሩ ንጉሥ ሰማክሬም ከሞተ በኋላ መንግሥቱን መጠበቅና ማዘዝ የማይችል ታናሽ ብላቴና ልጅ በአባቱ ፋንታ ነገሠ፡፡ እናቱም ስለ እርሱ ሹሞቹን ታዛቸው ነበር፡፡ ከለዳዊ ንጉሥም ይህን ሲሰማ የአቶርን መንግሥት ለመውሰድ መጣ፡፡ የንጉሡም ወታደሮችና የቅዱስ መርምህናምን መቃብር ይጠብቁ የነበሩ ሁሉ ለመዋጋት መጡ፡፡ የከለዳውያንም ንጉሥ አሸንፎ ከተማይቱን ወረራትና ብላቴናውን ንጉሥ ከእናቱ ጋር ገደላቸው፡፡ የአቶርም ሰዎች ተገዙለትና በላያቸው ነግሦ መንግሥትን ያዘ፡፡ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ የአቶርን ሰዎች ሰብስቦ ስለ ሃይማኖታቸው ጠየቃቸው፡፡ ሕዝቡም በቅዱስ መርምህናም አምላክ አምነው በአባ ማቴዎስ ጥምቀት ክርስቲያን መሆናቸውን በነገሩት ጊዜ ለጣዖት እንዲሰግዱ አዘዛቸው፡፡ እሺ ብለው ለጣዖት የሰገዱ አሉ፡፡ የቅዱስ መርምህናምና የአባቱ አግልጋዮች ግን ንጉሡን ‹‹በሰውነታችን ላይ የፈለከውን አድርግ እንጂ ሃይማኖታችንን አንክድም›› አሉት፡፡ ነገሡም ቁጥራቸው 170 ሺህ የሆኑ ክርስቲያኖችን በሰይፍ ፈጃቸውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ እነርሱም የቅዱስ መርምህናም ማኅበርተኞች ተባሉ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥርና_ሐምሌ እና #ከገድላት_አንደበት)
https://t.me/finotebirhan12
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ በዚህች ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የከበረ #ሐዋርያ_አብሮኮሮስ አረፈ፣ የከበረ #ቀሲስ_አክሎግ በሰማዕትነት ሞተ፣ #አባ_ዮሐንስ_ወንጌሉ_ዘወርቅ ሥጋው ወደ ሮሜ አገር የፈለሰበት እና ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ነው፣ የታላቁ ሰማዕት #የቅዱስ_መርምሕናም ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ተአምራቱ የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርምህናም
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርምሕናም ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ተአምራቱ የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡ ቅድስት ሣራና ወንድሟ መርምህናም አባታቸው የአቶር ንጉሥ ሲሆን እርሱም የተቀረጹ ጣዖታን ያመልክ ነበር፡፡ እናታቸው ግን አማኝ ክርስቲያን ነበረች፡፡ ቅዱስ መርምህናም አባቱን ለምኖና አስፈቅዶ ወደ ዱር ሄዶ አራዊትን ለማደን በወጣ ጊዜ እናቱ የሰማይና የምድር አምላክ እግዚአብሔር በላዩ በረከትን ያሳድርበት ዘንድ ከጸለየችለት በኋላ ሸኘችው፡፡ መርምህናም ከ40 ፈረሰኛ አገልጋዮቹ ጋር ወጥቶ ሄደ፡፡ ወደ አንድ ተራራም ወጥቶ በዚያ አደረ፡፡ በሌሊትም የታዘዘ መልአክ ጠራውና ‹‹መርምህናም ሆይ ተነሥተህ ወደዚህ ተራራ ጫፍ ላይ ውጣ፣ ስሙ ማቴዎስ የሚባል ቅዱስ ሰው ታገኛለህ፡፡ እርሱም የሕይወትን ነገር ይነግርሃል›› አለው፡፡ ቅዱስ መርምህናም ሲነጋ ወደ ተራራው ጫፍ ላይ ወጣና የበግ ጠጉር ለብሶ አባ ማቴዎስን ባገኘው ጊዜ እጅግ ፈራ፡፡ አባ ማቴዎስም ‹‹አይዞህ አትራ እኔም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነኝና አትፍራ›› ብለው አበረቱት፡፡ መርምህናም የእግዚአብሔርን ስም ሲጠሩ ሲሰማ ‹‹አባቴ ከአማልክቶች በቀር አምላክ አለን?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አባታችን የሃይማኖትን ነገር ሁሉንም አስተማሩት፡፡ መርምህናምም ‹‹ከራስ ጠጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ ድረስ በለምጽ የተመታች እኅት አለችኝና እርሷን የአምላክህን ስም ጠርተህ ካዳንክልኝ በእውነት በአምላክህ አምናለሁ›› አላቸው፡፡ ሁለቱም ተያይዘው ከተራራው ወርደው ወደ ንጉሡ ቤት ሄደው መርምህናም ለእናቱ ያጋጠመውን ነገር ነገራትና በለምጽ የተመታችውን እኅቱን ሣራን በሥውር ወደ አባ ማቴዎስ ዘንድ ወሰዳት፡፡ አባታችንም መሬቱን ባርከው ውኃ አፍልቀው አጠመቋትና ከለምጹዋ ፈወሷት፡፡ አርባው ጭፍራዎችም አምነው ተጠመቁ፡፡ አባታችንም ሰማዕትነትን እንደሚቀበሉ ትንቢት ነግረዋቸው ባርከው መርቀው አሰናበቷቸው፡፡
መርምህናምም ወደ አባቱ ቤት በተለመሰ ጊዜ ጣዖቱ ቤት መግባትን እምቢ አለ፡፡ ከዚህም በኋላ አርባውን ጭፍራዎችና እኅቱን ሣራን ይዞ ወደ አንዲት ተራራ ላይ ወጥቶ ተቀመጠ፡፡ የአቶሩን ንጉሥ የሆነው አባቱ ‹‹ና መንግሥቴን ውረስ›› ብሎ ለቅዱስ መርምህናም ላከበት፡፡ ነገር ግን ቅዱስ መርምህናም ‹‹የጌታዬን ፈጽሞ የማይጠፋውን መንግሥት እሻለሁ›› ብሎ ለንጉሥ አባቱ ላከበት፡፡ ንጉሡም በቅድሚያ 40ውን አገልጋዮቹን ጭፍራዎች እንዲገድሏቸው አዘዘና ራስ ራሶቻቸውን እየቆረጡ ከጉድጓድ ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ መርምህናምም ሲጸልይ ከሰማይ ‹‹መርምህናም ሆይ! ጸሎትህን ሰምቻለሁ…›› የሚል ድምፅ መጣለት፡፡ ወዲያውም በንጉሡ ወላጅ አባታቸው ትእዛዝ ቅዱስ መርምህናምና እኅቱ ቅድስት ሣራ አንገታቸውን ተሰየፉና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ሥጋቸውንም በጉድጓድ ጨምረው ሊያቃጥሏቸው ሲሉ ሥጋቸውን እግዚአብሔር ሰወረባቸው፡፡ ወዲያውም ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ፣ ፀሐይም ጨለመች፡፡ የሰየፏቸውም ፈርተው ሸሹ፡፡ ከዚህም በኋላ ሰይጣን በአባታቸው በአቶሩ ንጉሥ ላይ አድሮበት አሳበደው፡፡ እንደ እሪያም መጮህ ጀመረ፡፡ ክርስቲያን የሆነችው የቅዱስ መርምህናምና የቅደስት ሣራ እናታቸው ወደ አባ ማቴዎስ ሄዳ ንጉሡ በልጆቹ ላይ ያደረገውንና በእርሱም ላይ የተፈጸመበትን ነገር ነገረቻቸው፡፡ አባ ማቴዎስም ንጉሡን ዘይት ቀብተው ጸልየው ፈወሱት፡፡ በውስጡ አድሮበት የነበረውንም ሰይጣን በእሪያ መልክ ከንጉሡ ውስጥ አስወጡት፡፡
ንጉሡም ወደ ልቡ ሲመለስ በአባ ማቴዎስ ትምህርት በጌታችን አመነ፡፡ በሚገዛቸው አገሮች ሁሉ ያሉትን ሰዎች ይዞ ከነቤተሰቡ ተጠመቀ፡፡ ንጉሡም በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን አሠራ፡፡ ንግሥቲቱ ሚስቱም የሰማዕታቱን ልጆቿን ሥጋ በሳጥን አድርጋ በውስጧ አኖረች፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ተአምራት ተገለጡ፡፡ አባታቸው የአቶሩ ንጉሥም ለችግረኞችና ለጦም አዳሪዎች እየመጸወተ በተጋድሎ ኖረ፡፡ የቅዱስ መርምህናምና የእኅቱ የቅድስት ሣራ እረፍታቸው ታኅሣሥ 14 ቀን ነው፡፡
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የቅዱስ መርምህናም አባት ንጉሡ አቶርና የመርምህናም ማኅበርተኞች የሆኑ ቁጥራቸው 170 ሺህ የሆኑ ሰማዕታት የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይህም የአቶሩ ንጉሥ ሰማክሬም ከሞተ በኋላ መንግሥቱን መጠበቅና ማዘዝ የማይችል ታናሽ ብላቴና ልጅ በአባቱ ፋንታ ነገሠ፡፡ እናቱም ስለ እርሱ ሹሞቹን ታዛቸው ነበር፡፡ ከለዳዊ ንጉሥም ይህን ሲሰማ የአቶርን መንግሥት ለመውሰድ መጣ፡፡ የንጉሡም ወታደሮችና የቅዱስ መርምህናምን መቃብር ይጠብቁ የነበሩ ሁሉ ለመዋጋት መጡ፡፡ የከለዳውያንም ንጉሥ አሸንፎ ከተማይቱን ወረራትና ብላቴናውን ንጉሥ ከእናቱ ጋር ገደላቸው፡፡ የአቶርም ሰዎች ተገዙለትና በላያቸው ነግሦ መንግሥትን ያዘ፡፡ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ የአቶርን ሰዎች ሰብስቦ ስለ ሃይማኖታቸው ጠየቃቸው፡፡ ሕዝቡም በቅዱስ መርምህናም አምላክ አምነው በአባ ማቴዎስ ጥምቀት ክርስቲያን መሆናቸውን በነገሩት ጊዜ ለጣዖት እንዲሰግዱ አዘዛቸው፡፡ እሺ ብለው ለጣዖት የሰገዱ አሉ፡፡ የቅዱስ መርምህናምና የአባቱ አግልጋዮች ግን ንጉሡን ‹‹በሰውነታችን ላይ የፈለከውን አድርግ እንጂ ሃይማኖታችንን አንክድም›› አሉት፡፡ ነገሡም ቁጥራቸው 170 ሺህ የሆኑ ክርስቲያኖችን በሰይፍ ፈጃቸውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ እነርሱም የቅዱስ መርምህናም ማኅበርተኞች ተባሉ፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥርና_ሐምሌ እና #ከገድላት_አንደበት)
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
🔴 ስንክሳር#ጥር_21
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር 21 በዚች ቀን የከበረች እመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም የእረፍቷ መታሰቢያ ነው፣ የሮሜ አገር ንጉስ የዘይኑን ልጅ የከበረች #ቅድስት_ኢላርያ አረፈች፣ የኑሲስ ኤጲስቆጶስ የባስልዮስ ወንድም የከበረ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ የካህኑ ኬልቅዩ ልጅ ታላቁ #ነቢይ_ኤርምያስ መታሰቢያው ነው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለድች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦ "ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው። እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሐዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።
በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።
ወዲያውኑ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሐዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።
ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።
እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሐዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ። የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።
ጸሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።
ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።
ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።
ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።
እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።
ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።
እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።
ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሐዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።
በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር 21 በዚች ቀን የከበረች እመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም የእረፍቷ መታሰቢያ ነው፣ የሮሜ አገር ንጉስ የዘይኑን ልጅ የከበረች #ቅድስት_ኢላርያ አረፈች፣ የኑሲስ ኤጲስቆጶስ የባስልዮስ ወንድም የከበረ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ የካህኑ ኬልቅዩ ልጅ ታላቁ #ነቢይ_ኤርምያስ መታሰቢያው ነው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም
ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለድች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው። ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦ "ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው። እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሐዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው።
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ።
በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ።
ወዲያውኑ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት።
በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሐዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ።
ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት።
እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሐዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ። የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል።
ጸሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና።
ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት።
ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው።
ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት።
እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል።
ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም።
እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ።
ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሐዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ።
በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት።
.... ከላይ የቀጠለ....
ሐዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ስጋዋንም ያሳዪት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኃላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሀሴ አስራ ስድስት በረስፋ ኖሩ።
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እመቤታችንም በጸሎቷ ከክፉ ነገር ትጠብቀን አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
https://t.me/finotebirhan12
ሐዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።
ስጋዋንም ያሳዪት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሐዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኃላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሀሴ አስራ ስድስት በረስፋ ኖሩ።
የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እመቤታችንም በጸሎቷ ከክፉ ነገር ትጠብቀን አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
🔴 ስንክሳር #ጥር_22
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ ሁለት በዚች ቀን የሊቀ መላእክት #ቅዱስ_ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፣ የከበረና የገነነ የመነኰሳት ሁሉ አባት አባት #ቅዱስ_እንጦንስ አረፈ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ዑራኤል_ሊቀ_መላዕክት
ጥር ሃያ ሁለት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፡፡
ኢዮር፣ ራማ እና ኤረር የተባሉ ሦስት የመላእክት ከተሞች አሉ፡፡ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክት ከፈጠራቸው በኋላ በነገድ 100 በአለቃ 10 አድርጎ በሦስቱ ሰማያት አስፍሯቸዋል፡፡ ኢዮርን በ4፣ ራማን በ3፣ ኤረርንም በ3 ከፍሎ ነው በዐሥሩ ከተማ ያሰፈራቸው፡፡
በዚህም መሠረት ኢዮርን ላይና ታች አድርጎ በ4 ከተማ ከፍሏታል፡፡ በእርሷ ያሉትን መላእክትን በ40 ነገድ 4 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያው ነገድ ‹‹አጋእዝት›› ይባላሉ፡፡ አለቃቸው ሣጥናኤል ነበር፤ እርሱም የመላእክትን ሁሉ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርግ ነበር፡፡ ከክብሩ ሲዋረድ ቅዱስ ሚካኤል በምትኩ ተሹሞበታል፡፡ ሁለተኛው ነገድ ‹‹ኪሩቤል›› ይባላሉ፡፡ እነርሱም መንበረ ሥላሴን ይሸከማሉ፡፡ የቀሳውስት አምሳል ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ሰብና ገጸ አንበስ ናቸው፡፡ በሦስተኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ሱራፌል ይባላሉ፡፡ የዲያቆናት አምሳል ናቸው፡፡ በትንቢተ ኢሳያስ በምዕራፍ 6 ላይ የተገለጹትና ኢሳያስን ከለምጹ እንዲፈወስ ያደረጉት ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ላህምና ገጸ ንስር ናቸው፡፡ (በነገራችን ላይ ‹‹ከሩቤል›› ወይም ‹‹ሱራፌል›› የሚባሉ የግለሰብ መጠሪያ ስሞች ስህተት ናቸው፡፡ አንደኛ እነዚህ ስሞች የብዙ መላእክት መጠሪያን የሚወክሉ ናቸው፡፡ ለአንዱ ሲሆን ‹‹ኪሩብ፣ ሱራፊ›› ይባላል፡፡ ‹ኪሩቤል› ወይም ‹ሱራፌል› ማለት ግን የብዙ ቁጥራቸው መጠሪያ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የቅዱሳን መላእክትን ስም እንዳለ በቁሙ ወስዶ ለግል መጠሪያ ስም ማዋል ተገቢ አይደለም፡፡ ‹‹ወለተ ሚካኤል፣ ክንፈ ገብርኤል….›› እየተባሉ ይሰየማሉ እንጂ ቀጥታ ‹ሚካኤል›፣ ‹ገብርኤል› እያሉ ሰዎችን መሰየም ስህተት ነው፡፡ 4ኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ኃይላት ይባላሉ፡፡ የእሳት ሰይፍ ይዘው በሥሉስ ቅዱስ ፊት የሚቆሙ ናቸው፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የዛሉና የደከሙ ክርስቲያኖችን የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡)
ዳግመኛም እግዚአብሔር በራማ ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹አርባብ›› ይባላሉ፡፡ የሥላሴ እልፍኝ አስከልካዮች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔርን መንበር በክንፎቻቸው ይሸፍናሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ሁለተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹መናብርት›› ይባላሉ፡፡ ለእግዚአብሔርን እጅግ ቅርብ የሆኑ ናቸው፡፡ የመብረቅ ጋሻቸውን የእሳት ጦራቸውን ይዘው የሥላሴ ጋሻ ጃግሬዎች ሆነው በተጠንቀቅ ይቆማሉ፡፡ የሰውን ችግር ለእግዚአብሔር ያቀርባሉ፡፡ መዝ. 88፡6፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሦስተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹ሥልጣናት›› ይባላሉ፡፡ መላውን ፍጥረት ለመጠበቅ ሥልጣን የተሰጣቸውና የምጽአት ዕለት አዋጅ ነጋሪዎች ናቸው፡፡ ዳን. 12፡1፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ነው፡፡
ዳግመኛም እግዚአብሔር በኤረር ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹መኳንንት›› ይባላሉ፡፡ የስላሴ የእሳት ባለ ቀስት ናቸው፡፡ የሰው ልጅ ልዩ ጠባቂዎች ናቸው፤ በተለይ በአደጋ ጊዜ ሎጥን እንዳዳኑት ፈጥነው ይደርሳሉ፡፡ በዕለተ ምጽዓት የሰውን ሁሉ ዐፅም ሰብስበው ለትንሣኤ ዘጉባኤ ያበቃሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ነው፡፡ ሁለተኛዎቹ ‹‹ሊቃናት›› ይላሉ፡፡ የሥላሴ የእሳት ፈረሶች ናቸው፡፡ በእሳት ፈረስ ይመላለሳሉ፡፡ እነዚህም 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሲሆኑ አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል ነው፡፡ በኤረር ከተማ የሰፈሩት ሦስተኛዎቹ ‹‹መላእክት›› ይባላሉ፡፡ ፍጥረትን ሁሉ የሚጠብቁ ናቸው፡፡ አለቃቸው ቅዱስ አናንኤል ነው፡፡ በእነዚህ የማይጠበቅ ፍጥረት የለም፡፡ ከአዝርእት ጀምሮ ሁሉን ይጠብቃሉ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ 7 መላእክትን አየሁ›› (ራዕ. 8፡2) እንዳለ ሊቃነ መላእክት በቁጥር 7 ናቸው፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ ፋኑኤል እና ቅዱስ አፍኒን ናቸው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› የሚለው ስም ‹ዑር› እና ‹ኤል› ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› ማለት ትርጉሙ ‹‹የብርሃን ጌታ፣ የአምላክ ብርሃን›› ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው፡፡ በመሆኑም መጽሐፈ ሄኖክ እንደሚገልጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል፡፡ ምሥጢረ ሰማይንና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ መጽሐፈ ሄኖክ 28፡13፡፡
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨው ይኸው ገናና መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ዕውቀት ተሠውሮበት ለነበረው ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በእመቤታችን ትእዛዝ ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡›› መጽሐፈ ዕዝራ 2፡1፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር የሕይወትና የይቅርታ ዝናም በምድራችን ላይ ያዘንብ ዘንድ እንዲሁም የእርሻችንን አዝመራ በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ለምግብነት እንዲበቃ ከፈጣሪ ዘንድ ምሕረትን የሚለምን መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በመልአኩ አማላጂነት እጅግ ብዙ ድርሰቶችን የደረሱት መልአኩ ጽዋ ሕይወትን ካጠጣቸው በኋላ ነው፡፡ በመጀመሪያም አባ ጊዮርጊስ የተወለዱት በቅዱስ ዑራኤል አብሳሪነት ነው፡፡ በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የተመሠረቱ አብዛኞቹ ቅዱሳት ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው፡፡ ድርሳኑ ላይ የማይጠቅሳቸው የሀገራችን የከበሩ ቅዱሳት ገዳማትና ቅዱሳን ነገሥታት የሉም፡፡
የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ስትሰደድ መንገድ እየመራ ወደ ግብጽ እና ወደ አገራችንን ኢትዮጵያ ያመጣቸው ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ እመቤታችንን ከተወደደ ልጇ ጋር በደመና ጭኖ መላ ኢትዮጵያን ካስጎበኛት በኋላ ቅድስት አገራችንን ለእመቤታችን የዓሥራት አገር እንድትሆን ያደረገው መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በዓመት 3 ዓበይት በዓላት አሉት፡፡ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ነው፡፡ መጋቢት 27 የጌታችንን ክቡር የሆነ ወርቀ ደሙን ለዓለም የረጨበት ነው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ነው፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን መላእክት ጸሎትና ምልጃ ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
https://t.me/finotebirhan12
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር ሃያ ሁለት በዚች ቀን የሊቀ መላእክት #ቅዱስ_ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፣ የከበረና የገነነ የመነኰሳት ሁሉ አባት አባት #ቅዱስ_እንጦንስ አረፈ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ዑራኤል_ሊቀ_መላዕክት
ጥር ሃያ ሁለት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፡፡
ኢዮር፣ ራማ እና ኤረር የተባሉ ሦስት የመላእክት ከተሞች አሉ፡፡ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክት ከፈጠራቸው በኋላ በነገድ 100 በአለቃ 10 አድርጎ በሦስቱ ሰማያት አስፍሯቸዋል፡፡ ኢዮርን በ4፣ ራማን በ3፣ ኤረርንም በ3 ከፍሎ ነው በዐሥሩ ከተማ ያሰፈራቸው፡፡
በዚህም መሠረት ኢዮርን ላይና ታች አድርጎ በ4 ከተማ ከፍሏታል፡፡ በእርሷ ያሉትን መላእክትን በ40 ነገድ 4 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያው ነገድ ‹‹አጋእዝት›› ይባላሉ፡፡ አለቃቸው ሣጥናኤል ነበር፤ እርሱም የመላእክትን ሁሉ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርግ ነበር፡፡ ከክብሩ ሲዋረድ ቅዱስ ሚካኤል በምትኩ ተሹሞበታል፡፡ ሁለተኛው ነገድ ‹‹ኪሩቤል›› ይባላሉ፡፡ እነርሱም መንበረ ሥላሴን ይሸከማሉ፡፡ የቀሳውስት አምሳል ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ሰብና ገጸ አንበስ ናቸው፡፡ በሦስተኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ሱራፌል ይባላሉ፡፡ የዲያቆናት አምሳል ናቸው፡፡ በትንቢተ ኢሳያስ በምዕራፍ 6 ላይ የተገለጹትና ኢሳያስን ከለምጹ እንዲፈወስ ያደረጉት ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ላህምና ገጸ ንስር ናቸው፡፡ (በነገራችን ላይ ‹‹ከሩቤል›› ወይም ‹‹ሱራፌል›› የሚባሉ የግለሰብ መጠሪያ ስሞች ስህተት ናቸው፡፡ አንደኛ እነዚህ ስሞች የብዙ መላእክት መጠሪያን የሚወክሉ ናቸው፡፡ ለአንዱ ሲሆን ‹‹ኪሩብ፣ ሱራፊ›› ይባላል፡፡ ‹ኪሩቤል› ወይም ‹ሱራፌል› ማለት ግን የብዙ ቁጥራቸው መጠሪያ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የቅዱሳን መላእክትን ስም እንዳለ በቁሙ ወስዶ ለግል መጠሪያ ስም ማዋል ተገቢ አይደለም፡፡ ‹‹ወለተ ሚካኤል፣ ክንፈ ገብርኤል….›› እየተባሉ ይሰየማሉ እንጂ ቀጥታ ‹ሚካኤል›፣ ‹ገብርኤል› እያሉ ሰዎችን መሰየም ስህተት ነው፡፡ 4ኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ኃይላት ይባላሉ፡፡ የእሳት ሰይፍ ይዘው በሥሉስ ቅዱስ ፊት የሚቆሙ ናቸው፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የዛሉና የደከሙ ክርስቲያኖችን የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡)
ዳግመኛም እግዚአብሔር በራማ ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹አርባብ›› ይባላሉ፡፡ የሥላሴ እልፍኝ አስከልካዮች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔርን መንበር በክንፎቻቸው ይሸፍናሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ሁለተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹መናብርት›› ይባላሉ፡፡ ለእግዚአብሔርን እጅግ ቅርብ የሆኑ ናቸው፡፡ የመብረቅ ጋሻቸውን የእሳት ጦራቸውን ይዘው የሥላሴ ጋሻ ጃግሬዎች ሆነው በተጠንቀቅ ይቆማሉ፡፡ የሰውን ችግር ለእግዚአብሔር ያቀርባሉ፡፡ መዝ. 88፡6፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሦስተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹ሥልጣናት›› ይባላሉ፡፡ መላውን ፍጥረት ለመጠበቅ ሥልጣን የተሰጣቸውና የምጽአት ዕለት አዋጅ ነጋሪዎች ናቸው፡፡ ዳን. 12፡1፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ነው፡፡
ዳግመኛም እግዚአብሔር በኤረር ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹መኳንንት›› ይባላሉ፡፡ የስላሴ የእሳት ባለ ቀስት ናቸው፡፡ የሰው ልጅ ልዩ ጠባቂዎች ናቸው፤ በተለይ በአደጋ ጊዜ ሎጥን እንዳዳኑት ፈጥነው ይደርሳሉ፡፡ በዕለተ ምጽዓት የሰውን ሁሉ ዐፅም ሰብስበው ለትንሣኤ ዘጉባኤ ያበቃሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ነው፡፡ ሁለተኛዎቹ ‹‹ሊቃናት›› ይላሉ፡፡ የሥላሴ የእሳት ፈረሶች ናቸው፡፡ በእሳት ፈረስ ይመላለሳሉ፡፡ እነዚህም 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሲሆኑ አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል ነው፡፡ በኤረር ከተማ የሰፈሩት ሦስተኛዎቹ ‹‹መላእክት›› ይባላሉ፡፡ ፍጥረትን ሁሉ የሚጠብቁ ናቸው፡፡ አለቃቸው ቅዱስ አናንኤል ነው፡፡ በእነዚህ የማይጠበቅ ፍጥረት የለም፡፡ ከአዝርእት ጀምሮ ሁሉን ይጠብቃሉ፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ 7 መላእክትን አየሁ›› (ራዕ. 8፡2) እንዳለ ሊቃነ መላእክት በቁጥር 7 ናቸው፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ ፋኑኤል እና ቅዱስ አፍኒን ናቸው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› የሚለው ስም ‹ዑር› እና ‹ኤል› ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› ማለት ትርጉሙ ‹‹የብርሃን ጌታ፣ የአምላክ ብርሃን›› ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው፡፡ በመሆኑም መጽሐፈ ሄኖክ እንደሚገልጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል፡፡ ምሥጢረ ሰማይንና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ መጽሐፈ ሄኖክ 28፡13፡፡
መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨው ይኸው ገናና መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ዕውቀት ተሠውሮበት ለነበረው ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በእመቤታችን ትእዛዝ ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡›› መጽሐፈ ዕዝራ 2፡1፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር የሕይወትና የይቅርታ ዝናም በምድራችን ላይ ያዘንብ ዘንድ እንዲሁም የእርሻችንን አዝመራ በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ለምግብነት እንዲበቃ ከፈጣሪ ዘንድ ምሕረትን የሚለምን መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በመልአኩ አማላጂነት እጅግ ብዙ ድርሰቶችን የደረሱት መልአኩ ጽዋ ሕይወትን ካጠጣቸው በኋላ ነው፡፡ በመጀመሪያም አባ ጊዮርጊስ የተወለዱት በቅዱስ ዑራኤል አብሳሪነት ነው፡፡ በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የተመሠረቱ አብዛኞቹ ቅዱሳት ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው፡፡ ድርሳኑ ላይ የማይጠቅሳቸው የሀገራችን የከበሩ ቅዱሳት ገዳማትና ቅዱሳን ነገሥታት የሉም፡፡
የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ስትሰደድ መንገድ እየመራ ወደ ግብጽ እና ወደ አገራችንን ኢትዮጵያ ያመጣቸው ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ እመቤታችንን ከተወደደ ልጇ ጋር በደመና ጭኖ መላ ኢትዮጵያን ካስጎበኛት በኋላ ቅድስት አገራችንን ለእመቤታችን የዓሥራት አገር እንድትሆን ያደረገው መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡
መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በዓመት 3 ዓበይት በዓላት አሉት፡፡ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ነው፡፡ መጋቢት 27 የጌታችንን ክቡር የሆነ ወርቀ ደሙን ለዓለም የረጨበት ነው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ነው፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን መላእክት ጸሎትና ምልጃ ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።