የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
2.62K subscribers
6.21K photos
67 videos
79 files
1.72K links
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Download Telegram
ለመስቀል ዘማርያን በሙሉ
እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ነገ ለምናከብረው የመስቀል ደመራ በዓል ለዝማሬ አገልግሎት ስንመጣ

* ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጭ የሆኑ አላስፈላጊ ጌጣጌጦችን( ትውዝፍት ፣ምንዝር ጌጥ ) እንዳትጠቀሙ ከወዲሁ ልናሳስብ እንወዳለን።  ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን  አክብረን ማስከበር ያለብን እኛው ራሳችን በመሆኑ ስለዚህ የተከለከሉ ጌጣጌጦች         

1.የከንፈር ቀለም (ሊፕ እስቲክ)    
2.ቅንድብመቀንደብ                         
3.የጥፍር ቀለም ና የጥፍር ተከላ እንዲሁም 4.አላስፈላጊ ሜካፕ .....
5.ወንዶች አግባብነት የሌለው ጸጉር ቁርጥ በማስወገድ እንዲሁም ሌሎችም ተገቢ ያልሆኑ ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ያሉ ተግባራትን አትጠቀሙ።      
    
         * መገኛሰዓት:- የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አጥኚዎች ከቀኑ 6:00 ጎላ ጊቢ እንድትገኙ ይሁን።
                                  

   መልካም የመስቀል ደመራ በዓል እንዲሆንልን እንመኛለን።
እጸ መስቀል

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ሊያወጣ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ በቀራንዮ አደባባይ በመካነ ጎልጎታ በፈቃዱ ተሰቀለ። ሞተ ጥልንም በመስቀሉ ገደለ። ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታችን ስቅለት በኋላ የድኅነት ምልክት ሆነ::

ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምር በማድረጉ የተመቀኙ  አይሁድ መስቀሉን ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ የቆሻሻ መጣያ አደረጉት።

ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡

ከዚህ በኋላ ልጇ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ.ም ተጠመቀ፡፡ ንግስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች የጌታችንን መስቀል መፈለግ ብትጀምርም ያለበት ስፍራ የሚነግራት ሰው ልታገኝ አልቻለችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ፍላጎት ባይኖራቸውም  አንድ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊ ሰው አስጨንቃ ስለያዘችው መስቀሉ የሚገኝበትን ስፍራ ጠቆማት ነገር ግን ለዘመናት ቆሻሻ ሲጣልበት የነበረ ስፍራ በመሆኑ ተራራ ሰርቷል በቦታው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አልተቻለም፡፡

ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር ረዳትነት ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ወዳለበት ተራራ ላይ በማረፍ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡

መስከረም አስራ ስድስት ቀን ቁፋሮው ተጀምሮ መጋቢት አስር ቀን ሦስት መስቀሎች  ተገኙ፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል  የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው ሙት ላይ ቢያስቀምጡ ጌታችን  በዕለተ አርብ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው አስነሳው ሌሎቹ ሁለቱ መስቀሎች ግን ሙትን ማስነሳት  ባለመቻላቸው የጌታችንን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል።  ንግስት እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት

የመስቀሉ በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን።

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
‹‹… መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል ቤዛነ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ አይሁድ ክህዱ ንሕነሰ አመነ ወእለ አመነ በኃይለ መስቀሉ ድኅነ፤ … መስቀል ኀይላችን፣ ጽንዓችን፣ ቤዛችን፣ የነፍሳችን መዳኛ ነው፡፡ አይሁድ ይክዱታል፤ እኛ ግን እናምንበታለን፡፡ ያመነውም እኛ በመስቀሉ ኀይል እንድናለን፤ ድነናልም››

እንኳን ለበዓለ መስቀል በሰላም አደረሳችሁ