የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
2.62K subscribers
6.22K photos
67 videos
79 files
1.72K links
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Download Telegram
ሰንበት ትምህርት ቤታችን ባዘጋጀው የተልዕኮ ትምህርት ተምረው ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል የደብራችን አገልጋይ የሆኑት መርጌታ ብርሃነ ሕይወት ይገኙበታል ይበል የሚያሰኝ ነው እግዚአብሔር የአገልግሎት ዘመንዎትን ይባርክልን። ሌሎችም ሊበረታቱ ይገባል🙏
''ነገረ ማርያም''
     
            ክፍል ሶስት
   በመ/ር ኢዮብ በቀለ

የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር 

የፊታችን ቅዳሜ  ሐምሌ 5/2017 ዓ.ም ከምሽቱ  11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ሐምሌ አምስት በዚህች ቀን የሐዋርያት የቅዱስ ጴጥሮስ የሰማዕትነት መታሰቢያ ነው።

ቀድሞ ዓሣ አጥማጅም የነበረ በጌታችን የተመረጠ ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት መካከል የሆነ በፍጹም ሃይማኖት ለጌታው በቅንዓትና በፍቅር ያገለገለ በሐዋርያት ሁሉ ላይ አለቃ ተደርጎ የተሾመ የፈጣሪውን ማንነት በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነህ ብሎ የመሰከረ የሃይማኖት አለት የቤተ ክርስቲያንም መሠረት ነህ ተብሎ ብፅዕና የተሰጠው የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻ ቁልፍ የተሰጠው አጽናኝ የሆነ የመንፈስ ቅዱስንም ጸጋ ከተቀበለ በኃላ ተናጋሪዎች በሆኑ በዚህ ዓለም ተኩላዎች መካከል ገብቶ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በመስበክ ብዙዎች አሕዛብን መልሶ የዋሆች ምእመናን ያደረገ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ የሰማዕትነቱ መታሰቢያ ነው።
እንዲሁም
አስቀድሞ በክርስቶስ ያመኑትን የሚያሳድድ የነበረ የቀድሞ ስሙም ሳውል ይባል የነበረ ኋላ ልሳነ ዕረፍት የክርስቶስ አንደበት የቤተ ክርስቲያን መብራት የወንጌል መዶሻ የተባለው የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነቱ መታሰቢያ ነው።