#መስከረም_20
#ቅዱስ_አትናቴዎስ_ካልዕ
መስከረም ሃያ በዚች ቀን ለሊቃነ ጳጳሳት ሃያ ስምንተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባት አትናቴዎስ አረፈ።
ይህም አባት አስቀድሞ የእስክንድርያ አገር ቤተክርስቲያን መጋቢ ነበር ከእርሱም በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ በአረፈ ጊዜ ይህን አባት ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ሁሉም ኤጲስቆጶሳት መኳንንቱና ሊቃውንቱ ሕዝቡም በአንድ ምክር ተስማሙ በእግዚአብሔር ሕግ በመጽናት ያደረገው መልካም ተጋድሎውና ቅድስናው ስለርሱ ስለተነገረ መንፈስ ቅዱስም እንደ አደረበት ስለ ተረዱ ያለ ፈቃዱም ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።
ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በምክሩ፣ በትምህርቱ፣ በጸሎቱ ከዲያብሎስ ተኵላዎች በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው እሊህም ሃይማኖትን የሚለውጡ መናፍቃን ናቸው።
በሊቀ ጵጵስናውም ፯ት ዓመት ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መስከረም)
#ቅዱስ_አትናቴዎስ_ካልዕ
መስከረም ሃያ በዚች ቀን ለሊቃነ ጳጳሳት ሃያ ስምንተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባት አትናቴዎስ አረፈ።
ይህም አባት አስቀድሞ የእስክንድርያ አገር ቤተክርስቲያን መጋቢ ነበር ከእርሱም በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጴጥሮስ በአረፈ ጊዜ ይህን አባት ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ሁሉም ኤጲስቆጶሳት መኳንንቱና ሊቃውንቱ ሕዝቡም በአንድ ምክር ተስማሙ በእግዚአብሔር ሕግ በመጽናት ያደረገው መልካም ተጋድሎውና ቅድስናው ስለርሱ ስለተነገረ መንፈስ ቅዱስም እንደ አደረበት ስለ ተረዱ ያለ ፈቃዱም ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።
ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና የክርስቶስን መንጋዎች በምክሩ፣ በትምህርቱ፣ በጸሎቱ ከዲያብሎስ ተኵላዎች በመልካም አጠባበቅ ጠበቃቸው እሊህም ሃይማኖትን የሚለውጡ መናፍቃን ናቸው።
በሊቀ ጵጵስናውም ፯ት ዓመት ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን ።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መስከረም)
#መስከረም_21
መስከረም 21 በዚህች ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት ነው
#ዕፀ_መስቀል (#ግሸን_ማርያም)
በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤
ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡
ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡
መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ፲፬፻፵፮ (1446) ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡
ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም ፳፩ ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣ ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም ጤፉት በተባለችው መጽሐፍ ተጠቅሷል፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
#ስንክሳር_ዘወርኅ_መስከረም
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/finotebirhan12
https://t.me/finotebirhan12
መስከረም 21 በዚህች ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት ነው
#ዕፀ_መስቀል (#ግሸን_ማርያም)
በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤
ዐፄ ዳዊት መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡ ዐፄ ዳዊትም ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር "የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡
ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡ መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡
መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ፲፬፻፵፮ (1446) ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡
ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም ፳፩ ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡ ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣ ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም ጤፉት በተባለችው መጽሐፍ ተጠቅሷል፡፡
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
#ስንክሳር_ዘወርኅ_መስከረም
ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/finotebirhan12
https://t.me/finotebirhan12
Telegram
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ
እንኳን ለዚህ ክብር አበቃዎት ለማለት እንወዳለን በሰንበት ት/ቤታችን በማስተማር በመምከር እንዲሁም በኃላፊነት የሚያገለግሉን አሁንም እያገለገሉን ያሉትን ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ መልካም የአገልግሎት ግዜ ከልብ እንመኛለን
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
እንኳን ለዚህ ክብር አበቃዎት ለማለት እንወዳለን በሰንበት ት/ቤታችን በማስተማር በመምከር እንዲሁም በኃላፊነት የሚያገለግሉን አሁንም እያገለገሉን ያሉትን ቀሲስ ዮሴፍ ይኩኖ አምላክ መልካም የአገልግሎት ግዜ ከልብ እንመኛለን
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
#መስከረም_23
"ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከዓውሎ ነፋስ ይልቅ በተፋጠነ ሩጫ ነው እኮን።
ጊዮርጊስ ሆይ! የዘወትር ጸሎታችንንና የቃላችንንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምሕረት ፈጥነህ ወደ እኛ ቅረብ።"
👉(መልክአ ጊዮርጊስ)
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
መልካም ዕለተ ሰንበት
"ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! አንተን በመታመን ለጠራህ ሁሉ ፈጥነህ ስትደርስለት ከዓውሎ ነፋስ ይልቅ በተፋጠነ ሩጫ ነው እኮን።
ጊዮርጊስ ሆይ! የዘወትር ጸሎታችንንና የቃላችንንም የልመና ጩኸት ትቀበል ዘንድ ለይቅርታና ለምሕረት ፈጥነህ ወደ እኛ ቅረብ።"
👉(መልክአ ጊዮርጊስ)
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
መልካም ዕለተ ሰንበት
እናመሰግናለን 🙏
👉 አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን.. በቀጣይ የተለያዩ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት ላይ ነን ሰብስክራይብ ያላደረጋችሁ አድርጋችሁ ጠብቁን ከታች ያለው link በመጫን
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
👉 አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን.. በቀጣይ የተለያዩ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት ላይ ነን ሰብስክራይብ ያላደረጋችሁ አድርጋችሁ ጠብቁን ከታች ያለው link በመጫን
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
#እንኳን_ለዘመነ_ጽጌ_በሠላም_አደረሳችሁ
👉 እነሆ ክረምቱ አለፈ ከሰኔ 25 እስከ መስከረም 25 ክረምት ይባላል።
👉 ከመስከረም 26 እስከ ሕዳር 5 #ዘመነ_ጽጌ ይባላል የእናታችን የእመቤታችን ስደቷን እያሰብን እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ወራት ነው።
👉 ቅዳሜ ማታ ለእሁድ ከአባቶቻችን ጋር በማኅሌቱ እንሳተፍ።
የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
👉 እነሆ ክረምቱ አለፈ ከሰኔ 25 እስከ መስከረም 25 ክረምት ይባላል።
👉 ከመስከረም 26 እስከ ሕዳር 5 #ዘመነ_ጽጌ ይባላል የእናታችን የእመቤታችን ስደቷን እያሰብን እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ወራት ነው።
👉 ቅዳሜ ማታ ለእሁድ ከአባቶቻችን ጋር በማኅሌቱ እንሳተፍ።
የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
የሰንበት ት/ቤታችን ወረብ / ዝማሬዎችን በዚህ Link ያገኛሉ ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/finotewereb
https://t.me/finotewereb
https://t.me/finotewereb
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/finotewereb
https://t.me/finotewereb
https://t.me/finotewereb
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️
#መስከረም_29 በዚህችም ቀን #ከቅድስት_አርሴማ በሰማዕትነት አረፈች
ከቅድስት አርሴማና ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ።
ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ።
እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።
ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።
ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።
የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።
ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።
አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።
ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።
(#ስንክሳር_ዘወርኅ_መስከረም እና #ከገድላት_አንደበት)
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
ከቅድስት አርሴማና ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ።
ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ።
እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።
ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።
ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።
የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።
ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።
አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።
ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።
(#ስንክሳር_ዘወርኅ_መስከረም እና #ከገድላት_አንደበት)
Youtube Channel: https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
ማኅሌተ ጽጌ መስከረም 30
፩ ነግሥ ( ለኵልያቲክሙ)
ሰላም፡ ለኵልያቲክሙ፡ እለ፡ ዕሩያን፡ በአካል፤
ዓለመክሙ፡ ሥላሴ፡ አመ፡ ሐወፀ፣ ለሣህል፤
እምኔክሙ፡ አሐዱ፡ እግዚአብሔር፡ ቃል፤
ተፈጸመ፡ ተስፋ፡ አበው፡ በማርያም፡ ድንግል፤
ወበቀራንዮ፡ ተተክለ፡ መድኃኒት፡ መስቀል ፡፡
ዚቅ
ወኃይዝተ፡ ወንጌል፡ የዓውዳ፡ ለቤተክርስቲያን፤
እም፡ አርባዕቱ፡ አፍላጋት፤ እንተ፡ ትሰቀይ፡ ትእምርተ፡ ለለጽባሑ፤
እማቴዎስ፡ ልደቶ፡ ወእማርቆስ፡ መንክራቶ፤
እም፡ ሉቃስ፡ ዜናዊ፡ ተሰምዮ፡ ወእም፡ ዮሐንስ፡ በግዓ፤
ወዘንተ፡ ሰሚዓ፡ ትገብር፡ በዓለ፡ በፍግዓ።
፪ ጽጌ አስተርአየ
ጽጌ፡ አስተርአየ ፡ ሠሪጾ፡ እምዐጽሙ፤
ለዘአምኃኪ፡ ጽጌ፡ ለገብርኤል፡ ምስለ፡ ሰላሙ፤
ወበእንተዝ ፡ ማርያም ፡ ሶበ ፡ ሐወዘኒ ፡ ጣዕሙ፤
ለተአምርኪ ፡ አኀሊ፡ እሙ፤
ማኅሌተ፡ ጽጌ፡ ዘይሰመይ፡ ስሙ፡፡
ወረብ
መዓዛ፡ ጣዕሙ፡ ለተአምርኪ፡ ሶበ፡ ሶበ፡ ሐወዘኒ፤
ወበእንተዝ፡ ማርያም፡ አሐሊ፡ ለተአምርኪ፡፡
ዚቅ
ሃሌ፡ ሉያ፡ ሃሌ፡ ሃሌ፡ ሉያ፤
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤
መርዓቱኒ፡ ትቤ፡ ወልድ፡ እኁየ ፡ ይምዕዝ ፡ ከርቤ፤
ናሁ ፡ አስተርአየ ፡ ጽጌ፤
ዕንባቆም ፡ ነቢይ ፡ ግብረ፡ ምግባሩ፡ ለወልድ፡ አንከርኩ፡ ይቤ፤
ናሁ ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤
ንጉሠ ፡ ሰላም፡ ክርስቶስ፤
ዓቢይ፡ ልዕልናከ፡ ወመንክር፡ ስብሐቲከ፡ ለዕረፍት፡ ሰንበተ ፡ ሠራዕከ፡፡
፫ እንዘ ተሐቅፊዮ
እንዘ ፡ ተሐቅፊዮ ፡ ለሕጻንኪ ፡ ጽጌ፡ ፀዓዳ ፡ ወቀይሕ፤
አመ ፡ ቤተ ፡ መቅደስ ፡ ቦእኪ ፡ በዕለተ ፡ ተአምር ፡ ወንጽሕ፤
ንዒ ፡ ርግብየ ፡ ትናዝዝኒ ፡ እምላህ፤
ወንዒ ፡ ሠናይትየ ፡ ምስለ ፡ ገብርኤል ፡ ፍሡሕ፤
ወሚካኤል ፡ ከማኪ ፡ ርኅሩኅ ፡፡
ወረብ
እንዘ፡ ተሐቅፊዮ፡ ለሕጻንኪ፡ ጽጌ፡ ፀዓዳ፡ ወቀይሕ፤
አመ፡ ቤተ፡ መቅደስ፡ ቦእኪ፡ በዕለተ፡ ተአምር፡ ወንጽሕ፤
ዚቅ
ንዒ፡ ርግብየ፡ ወንዒ፡ ሠናይትየ፤ እንተ፡ ሐዋርያት፡ ይሴብሑኪ፤
መላእክት፡ ይትለአኩኪ፤ ፃዒ፡ እምሊባኖስ፡ ሥነ፡ ሕይወት፡፡
፬ ሰዊተ ሥርናዩ
ሰዊተ፡ ሥርናዩ፡ ለታዴዎስ፡ ወለበርተሎሜዎስ፡ ወይኑ፤
እንተ፡ ጸገይኪ፡ አስካለ፡ በዕለተ፡ ተከለኪ፡ ዕደ፡ የማኑ፤
ማርያም፡ ለጴጥሮስ፡ ጽላሎቱ፡ ወለጳውሎስ፡ ሰበኑ፤
ብኪ፡ ምውታን፡ ሕያዋነ፡ ኮኑ፤
ወሐዋርያት፡ መላእክተ፡ በሰማይ፡ ኮነኑ፡፡
ወረብ
ማርያም፡ ለጴጥሮስ፡ ጽላሎቱ፡ ጽላሎቱ፡ ወለጳውሎስ፡ ሰበኑ፤
ወሐዋርያት፡ መላእክተ፡ መላእክተ፡ በሰማይ፡ ኮነኑ፡፡
ዚቅ
ኦ፡ መድኃኒት፡ ለነገሥት፤ ማኅበረ፡ ቅዱሳን፡ የዓውዱኪ፤
ነቢያት፡ የአኵቱኪ፡ ወሐዋርያት፡ ይዌድሱኪ፤
እስመ፡ ኪያኪ፡ ኃርየ፡ ለታዕካሁ፡ ከመ፡ ትኩኒዮ፡ ማኅደረ ፤
መላእክት፡ ይኬልሉኪ፡ ጻድቃን፡ ይባርኩኪ፡ አበው፡ ይገንዩ፡ ለኪ፤
እስመ፡ ኪያኪ፡ ኃርየ፡ ለታዕካሁ፡ ከመ፡ ትኩኒዮ፡ ማኅደረ፡፡
፭ ክበበ ጌራ ወርቅ
ክበበ፡ ጌራ ወርቅ፡ ጽሩይ ፡ እምዕንቈ ባሕርይ ፡ ዘየኃቱ፣
ዘተጽሕፈ ፡ ብኪ ፡ ትእምርተ ፡ ስሙ ፡ ወተዝካረ ፡ ሞቱ፣
አክሊለ ጽጌ ፡ ማርያም ፡ ለጊዮርጊስ ፡ ቀጸላ መንግሥቱ፣
አንቲ ፡ ኵሎ ፡ ታሰግዲ ፡ ሎቱ፣
ወለኪኒ ፡ ይሰግድ ፡ ውእቱ፡፡
ወረብ
ክበበ፡ ጌራ፡ ወርቅ፡ ጽሩይ፡ ዘየኃቱ፡ እምዕንቈ፡ ባሕርይ፤
ማርያም፡ አክሊለ፡ ጽጌ፡ ለጊዮርጊስ፡ ቀጸላ፡ መንግሥቱ፤
ዚቅ
ውድስት፡ አንቲ፡ በአፈ፡ ነቢያት፤ ወስብሕት፡ በሐዋርያት፤
አክሊለ፡ በረከቱ፡ ለጊዮርጊስ፤
ወትምክህተ፡ ቤቱ፡ ለእሥራኤል፡፡
፮ በስመ እግዚአብሔር (ሰቆቃወ ድንግል)
በስመ፡ እግዚአብሔር፡ ሥሉስ፡ ሕጸተ፡ ግጻዌ፡ ዘአልቦ፤
ሰቆቃወ፡ ድንግል፡ እጽሕፍ፡ በቀለመ፡ አንብዕ፡ ወአንጠብጥቦ፤
ወይሌ፡ ወላህ፡ ለይበል፡ ዘአንበቦ፤
ከማሃ፡ ኀዘን፡ ወተሰዶ፡ ሶበ፡ በኵለሄ፡ ረከቦ፤
ርእዮ፡ ለይብኪ፡ ዓይነ፡ ልብ፡ ዘቦ።
ወረብ
ከማሃ፡ ኀዘን(፪)፡ ወተሰዶ፡ ኀዘን፤
ርእዮ፡ ለይብኪ፡ ዓይነ፡ ልብ፡ ዘቦ፡ ዓይነ፡ ልብ።
ዚቅ
እወ፡ አማን፡ እምውሉደ፡ ሰብእ፡ አልቦ፤
ምንዳቤ፡ ወግፍዕ፡ ዘከማኪ፡ በውስተ፡ ኵሉ፡ ዘረከቦ።
++++++++++++++
መዝሙር
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ እንዘ፡ ትብል፡ ነዓ፡ ወልድ፡ እኁየ፡ ንፃእ፡ ኃቅለ፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ ንርአይ፡ ለእመ፡ ጸገየ፡ ወይን፡ ወፈረየ፡ ሮማን፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ አሠርገወ፡ ሰማየ፡ በከዋክብት፡ ወምድርኒ፡ በስነ፡ ጽጌያት፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ እስመ፡ ውእቱ፡ ወልድ፡ ዋሕድ፡ እግዚአ፡ ለሰንበት፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፡ ወትብሎ፤ ወልድ፡ እኁየ፡ ቃልከ፡ አዳም፡፡
አመላለስ
ትዌድሶ፡ መርዓት፡ ወትብሎ፤
ወልድ፡ እኁየ፡ ቃልከ፡ አዳም።
ሰላም
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤ መርዓቱኒ፡ ትቤ፡ ወልድ፡ እኁየ ፡ ይምዕዝ ፡ ከርቤ፤
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤ ዕንባቆም፡ ነቢይ፡ ግብረ፡ ምግባሩ፡ ለወልድ፡ አንከርኩ፡ ይቤ፤
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤ ንጉሠ፡ ሰላም፡ ክርስቶስ፤
ዓቢይ፡ ልዕልናከ፡ ወመንክር፡ ስብሐቲከ፡ ለዕረፍት፡ ሰንበተ ፡ ሠራዕከ፡፡
+++
፩ ነግሥ ( ለኵልያቲክሙ)
ሰላም፡ ለኵልያቲክሙ፡ እለ፡ ዕሩያን፡ በአካል፤
ዓለመክሙ፡ ሥላሴ፡ አመ፡ ሐወፀ፣ ለሣህል፤
እምኔክሙ፡ አሐዱ፡ እግዚአብሔር፡ ቃል፤
ተፈጸመ፡ ተስፋ፡ አበው፡ በማርያም፡ ድንግል፤
ወበቀራንዮ፡ ተተክለ፡ መድኃኒት፡ መስቀል ፡፡
ዚቅ
ወኃይዝተ፡ ወንጌል፡ የዓውዳ፡ ለቤተክርስቲያን፤
እም፡ አርባዕቱ፡ አፍላጋት፤ እንተ፡ ትሰቀይ፡ ትእምርተ፡ ለለጽባሑ፤
እማቴዎስ፡ ልደቶ፡ ወእማርቆስ፡ መንክራቶ፤
እም፡ ሉቃስ፡ ዜናዊ፡ ተሰምዮ፡ ወእም፡ ዮሐንስ፡ በግዓ፤
ወዘንተ፡ ሰሚዓ፡ ትገብር፡ በዓለ፡ በፍግዓ።
፪ ጽጌ አስተርአየ
ጽጌ፡ አስተርአየ ፡ ሠሪጾ፡ እምዐጽሙ፤
ለዘአምኃኪ፡ ጽጌ፡ ለገብርኤል፡ ምስለ፡ ሰላሙ፤
ወበእንተዝ ፡ ማርያም ፡ ሶበ ፡ ሐወዘኒ ፡ ጣዕሙ፤
ለተአምርኪ ፡ አኀሊ፡ እሙ፤
ማኅሌተ፡ ጽጌ፡ ዘይሰመይ፡ ስሙ፡፡
ወረብ
መዓዛ፡ ጣዕሙ፡ ለተአምርኪ፡ ሶበ፡ ሶበ፡ ሐወዘኒ፤
ወበእንተዝ፡ ማርያም፡ አሐሊ፡ ለተአምርኪ፡፡
ዚቅ
ሃሌ፡ ሉያ፡ ሃሌ፡ ሃሌ፡ ሉያ፤
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤
መርዓቱኒ፡ ትቤ፡ ወልድ፡ እኁየ ፡ ይምዕዝ ፡ ከርቤ፤
ናሁ ፡ አስተርአየ ፡ ጽጌ፤
ዕንባቆም ፡ ነቢይ ፡ ግብረ፡ ምግባሩ፡ ለወልድ፡ አንከርኩ፡ ይቤ፤
ናሁ ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤
ንጉሠ ፡ ሰላም፡ ክርስቶስ፤
ዓቢይ፡ ልዕልናከ፡ ወመንክር፡ ስብሐቲከ፡ ለዕረፍት፡ ሰንበተ ፡ ሠራዕከ፡፡
፫ እንዘ ተሐቅፊዮ
እንዘ ፡ ተሐቅፊዮ ፡ ለሕጻንኪ ፡ ጽጌ፡ ፀዓዳ ፡ ወቀይሕ፤
አመ ፡ ቤተ ፡ መቅደስ ፡ ቦእኪ ፡ በዕለተ ፡ ተአምር ፡ ወንጽሕ፤
ንዒ ፡ ርግብየ ፡ ትናዝዝኒ ፡ እምላህ፤
ወንዒ ፡ ሠናይትየ ፡ ምስለ ፡ ገብርኤል ፡ ፍሡሕ፤
ወሚካኤል ፡ ከማኪ ፡ ርኅሩኅ ፡፡
ወረብ
እንዘ፡ ተሐቅፊዮ፡ ለሕጻንኪ፡ ጽጌ፡ ፀዓዳ፡ ወቀይሕ፤
አመ፡ ቤተ፡ መቅደስ፡ ቦእኪ፡ በዕለተ፡ ተአምር፡ ወንጽሕ፤
ዚቅ
ንዒ፡ ርግብየ፡ ወንዒ፡ ሠናይትየ፤ እንተ፡ ሐዋርያት፡ ይሴብሑኪ፤
መላእክት፡ ይትለአኩኪ፤ ፃዒ፡ እምሊባኖስ፡ ሥነ፡ ሕይወት፡፡
፬ ሰዊተ ሥርናዩ
ሰዊተ፡ ሥርናዩ፡ ለታዴዎስ፡ ወለበርተሎሜዎስ፡ ወይኑ፤
እንተ፡ ጸገይኪ፡ አስካለ፡ በዕለተ፡ ተከለኪ፡ ዕደ፡ የማኑ፤
ማርያም፡ ለጴጥሮስ፡ ጽላሎቱ፡ ወለጳውሎስ፡ ሰበኑ፤
ብኪ፡ ምውታን፡ ሕያዋነ፡ ኮኑ፤
ወሐዋርያት፡ መላእክተ፡ በሰማይ፡ ኮነኑ፡፡
ወረብ
ማርያም፡ ለጴጥሮስ፡ ጽላሎቱ፡ ጽላሎቱ፡ ወለጳውሎስ፡ ሰበኑ፤
ወሐዋርያት፡ መላእክተ፡ መላእክተ፡ በሰማይ፡ ኮነኑ፡፡
ዚቅ
ኦ፡ መድኃኒት፡ ለነገሥት፤ ማኅበረ፡ ቅዱሳን፡ የዓውዱኪ፤
ነቢያት፡ የአኵቱኪ፡ ወሐዋርያት፡ ይዌድሱኪ፤
እስመ፡ ኪያኪ፡ ኃርየ፡ ለታዕካሁ፡ ከመ፡ ትኩኒዮ፡ ማኅደረ ፤
መላእክት፡ ይኬልሉኪ፡ ጻድቃን፡ ይባርኩኪ፡ አበው፡ ይገንዩ፡ ለኪ፤
እስመ፡ ኪያኪ፡ ኃርየ፡ ለታዕካሁ፡ ከመ፡ ትኩኒዮ፡ ማኅደረ፡፡
፭ ክበበ ጌራ ወርቅ
ክበበ፡ ጌራ ወርቅ፡ ጽሩይ ፡ እምዕንቈ ባሕርይ ፡ ዘየኃቱ፣
ዘተጽሕፈ ፡ ብኪ ፡ ትእምርተ ፡ ስሙ ፡ ወተዝካረ ፡ ሞቱ፣
አክሊለ ጽጌ ፡ ማርያም ፡ ለጊዮርጊስ ፡ ቀጸላ መንግሥቱ፣
አንቲ ፡ ኵሎ ፡ ታሰግዲ ፡ ሎቱ፣
ወለኪኒ ፡ ይሰግድ ፡ ውእቱ፡፡
ወረብ
ክበበ፡ ጌራ፡ ወርቅ፡ ጽሩይ፡ ዘየኃቱ፡ እምዕንቈ፡ ባሕርይ፤
ማርያም፡ አክሊለ፡ ጽጌ፡ ለጊዮርጊስ፡ ቀጸላ፡ መንግሥቱ፤
ዚቅ
ውድስት፡ አንቲ፡ በአፈ፡ ነቢያት፤ ወስብሕት፡ በሐዋርያት፤
አክሊለ፡ በረከቱ፡ ለጊዮርጊስ፤
ወትምክህተ፡ ቤቱ፡ ለእሥራኤል፡፡
፮ በስመ እግዚአብሔር (ሰቆቃወ ድንግል)
በስመ፡ እግዚአብሔር፡ ሥሉስ፡ ሕጸተ፡ ግጻዌ፡ ዘአልቦ፤
ሰቆቃወ፡ ድንግል፡ እጽሕፍ፡ በቀለመ፡ አንብዕ፡ ወአንጠብጥቦ፤
ወይሌ፡ ወላህ፡ ለይበል፡ ዘአንበቦ፤
ከማሃ፡ ኀዘን፡ ወተሰዶ፡ ሶበ፡ በኵለሄ፡ ረከቦ፤
ርእዮ፡ ለይብኪ፡ ዓይነ፡ ልብ፡ ዘቦ።
ወረብ
ከማሃ፡ ኀዘን(፪)፡ ወተሰዶ፡ ኀዘን፤
ርእዮ፡ ለይብኪ፡ ዓይነ፡ ልብ፡ ዘቦ፡ ዓይነ፡ ልብ።
ዚቅ
እወ፡ አማን፡ እምውሉደ፡ ሰብእ፡ አልቦ፤
ምንዳቤ፡ ወግፍዕ፡ ዘከማኪ፡ በውስተ፡ ኵሉ፡ ዘረከቦ።
++++++++++++++
መዝሙር
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ እንዘ፡ ትብል፡ ነዓ፡ ወልድ፡ እኁየ፡ ንፃእ፡ ኃቅለ፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ ንርአይ፡ ለእመ፡ ጸገየ፡ ወይን፡ ወፈረየ፡ ሮማን፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ አሠርገወ፡ ሰማየ፡ በከዋክብት፡ ወምድርኒ፡ በስነ፡ ጽጌያት፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፤ እስመ፡ ውእቱ፡ ወልድ፡ ዋሕድ፡ እግዚአ፡ ለሰንበት፤
ትዌድሶ፡ መርዓት፡ ወትብሎ፤ ወልድ፡ እኁየ፡ ቃልከ፡ አዳም፡፡
አመላለስ
ትዌድሶ፡ መርዓት፡ ወትብሎ፤
ወልድ፡ እኁየ፡ ቃልከ፡ አዳም።
ሰላም
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤ መርዓቱኒ፡ ትቤ፡ ወልድ፡ እኁየ ፡ ይምዕዝ ፡ ከርቤ፤
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤ ዕንባቆም፡ ነቢይ፡ ግብረ፡ ምግባሩ፡ ለወልድ፡ አንከርኩ፡ ይቤ፤
ናሁ፡ አስተርአየ፡ ጽጌ፤ ንጉሠ፡ ሰላም፡ ክርስቶስ፤
ዓቢይ፡ ልዕልናከ፡ ወመንክር፡ ስብሐቲከ፡ ለዕረፍት፡ ሰንበተ ፡ ሠራዕከ፡፡
+++
#ጥቅምት_1 በዚህች ቀን የማርታና የአልዓዛር እህት #የቅድስት_ማርያም_እንተ_ዕፍረት የእረፍቷ መታሰቢያ ነው።
#ቅድስት_ማርያም_እንተ_ዕፍረት
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የማርታና የአልዓዛር እህት ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት የእረፍቷ መታሰቢያ ነው።
በዘመነ ሐዋርያት በተመሳሳይ 'እንተ ዕፍረት' (ባለ ሽቱ) ተብለው የሚጠሩ 2 እናቶች ነበሩ:: ሁለቱም ስማቸው ማርያም ስለ ነበር ለመለየት እንዲያመች አንደኛዋን 'ማርያም ኃጥዕት (ከኃጢአት የተመለሰች) ሁለተኛዋን ደግሞ 'ማርያም እኅተ አልዓዛር በቢታንያ የነበረችው ብለው አበው ይጠሯቸዋል።
በሉቃስ ወንጌል ላይ የምትገኘው ከኃጢአት ሕይወት የተመለሰችው ስትሆን በዮሐ. 12:1 ላይ ያለችው የአልዓዛር እህት (ድንግሊቱ) ናት። ዛሬም የምናስባት ይህቺውን እናታችን ነው።
ቅድስት ማርያም መድኃኒታችን ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ በሚያስተመርበት ዘመን በቢታንያ አካባቢ ትኖር የነበረች ድንግል ወጣት ናት። ወላጆች ባልነበረበት ቤት ውስጥ ታላቆቿ አልዓዛርና ማርታ አሳድገዋታል።
በቤተሰብ ደረጃ እንግዳን ይቀበሉ ነበርና ጌታችን ወደዳቸው። አልዓዛርን ከ72ቱ አርድእት: ማርያምና ማርታን ደግሞ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ቆጥሯቸዋል። ወንድማቸው አልዓዛር በታመመ ጊዜ ወደ ጌታ ልከው ነበር።
ያለ ጊዜው የማይሠራ ጌታ ባይመጣ አልዓዛር ሞተ። በ4ኛው ቀን አምላክ ሲመጣ ቅድስት ማርያም በጌታ ፊት ሰግዳ "እግዚእየ ሶበሰ ኀሎከ ዝየ እምኢሞተ እኁየ" "አንተ በዚህ በኖርክስ ወንድሜ ባልሞተ ነበር" ብላ አለቀሰች። (ዮሐ.11)
ጌታም ስታለቅስ ባያት ጊዜ አምላክነቱ አራርቶት አለቀሰ። ወዲያውም በስልጣነ ቃሉ አዞ አልዓዛርን አስነሳው። ከፋሲካ (ጌታ ከመሰቀሉ 6 ቀናት) በፊትም ቅዱሳኑ ለጌታ ግብር አገቡ። እርሱም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ታደመላቸው። (ዮሐ.12፥1)
በዚያም አልዓዛር ከጌታ ጐን ሲቀመጥ ቅድስት ማርያም ከጌታ ሥር ተንበርክካ ናርዶስ የሚሉትን የ300 ዲናር ሽቱ በጌታ ላይ አፈሰሰች። መዓዛ መለኮቱና ሽቱው ሲገናኝ "መልዐ መዓዛሁ" እንዲል የሚመስጥ ሽታ ቤቱን ሞላው።
በወቅቱ ይሁዳ ቢቃወምም ጌታ ምላሹን ሰጥቶታል። ቅድስት ማርያምንም "ማርያምሰ ኃርየት መክፈልተ ሠናየ ዘኢየኃይድዋ" ብሎ አመስግኗታል። ያስመሰገናት ቁጭ ብላ በተመስጦ መማሯ ብቻ እንዳልሆነ አባ ሕርያቆስ መስከሯል።
ሲመክረንም "አርምሞንና ትዕግስትን እንደ ማርያም ገንዘብ እናድርግ" ብሎናል። (ቅዳሴ ማርያም) ቅድስት ማርያም በጌታችን ክርስቶስ በኅማሙ ጊዜ ሲቀብሩት ነበረች። ትንሳኤውንም ዐይታለች።
ከጌታ እርገት በኋላም መንፈስ ቅዱስን ተከትላ ለወንጌል አገልግሎት ተግታለች። ቅድስት እናታችን ማርያም እንተ ዕፍረት ዛሬ እንዳረፈች እናዘክራለን።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥቅምት)
#ቅድስት_ማርያም_እንተ_ዕፍረት
ዳግመኛም በዚህች ዕለት የማርታና የአልዓዛር እህት ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት የእረፍቷ መታሰቢያ ነው።
በዘመነ ሐዋርያት በተመሳሳይ 'እንተ ዕፍረት' (ባለ ሽቱ) ተብለው የሚጠሩ 2 እናቶች ነበሩ:: ሁለቱም ስማቸው ማርያም ስለ ነበር ለመለየት እንዲያመች አንደኛዋን 'ማርያም ኃጥዕት (ከኃጢአት የተመለሰች) ሁለተኛዋን ደግሞ 'ማርያም እኅተ አልዓዛር በቢታንያ የነበረችው ብለው አበው ይጠሯቸዋል።
በሉቃስ ወንጌል ላይ የምትገኘው ከኃጢአት ሕይወት የተመለሰችው ስትሆን በዮሐ. 12:1 ላይ ያለችው የአልዓዛር እህት (ድንግሊቱ) ናት። ዛሬም የምናስባት ይህቺውን እናታችን ነው።
ቅድስት ማርያም መድኃኒታችን ክርስቶስ ወደዚህ ዓለም መጥቶ በሚያስተመርበት ዘመን በቢታንያ አካባቢ ትኖር የነበረች ድንግል ወጣት ናት። ወላጆች ባልነበረበት ቤት ውስጥ ታላቆቿ አልዓዛርና ማርታ አሳድገዋታል።
በቤተሰብ ደረጃ እንግዳን ይቀበሉ ነበርና ጌታችን ወደዳቸው። አልዓዛርን ከ72ቱ አርድእት: ማርያምና ማርታን ደግሞ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ቆጥሯቸዋል። ወንድማቸው አልዓዛር በታመመ ጊዜ ወደ ጌታ ልከው ነበር።
ያለ ጊዜው የማይሠራ ጌታ ባይመጣ አልዓዛር ሞተ። በ4ኛው ቀን አምላክ ሲመጣ ቅድስት ማርያም በጌታ ፊት ሰግዳ "እግዚእየ ሶበሰ ኀሎከ ዝየ እምኢሞተ እኁየ" "አንተ በዚህ በኖርክስ ወንድሜ ባልሞተ ነበር" ብላ አለቀሰች። (ዮሐ.11)
ጌታም ስታለቅስ ባያት ጊዜ አምላክነቱ አራርቶት አለቀሰ። ወዲያውም በስልጣነ ቃሉ አዞ አልዓዛርን አስነሳው። ከፋሲካ (ጌታ ከመሰቀሉ 6 ቀናት) በፊትም ቅዱሳኑ ለጌታ ግብር አገቡ። እርሱም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ታደመላቸው። (ዮሐ.12፥1)
በዚያም አልዓዛር ከጌታ ጐን ሲቀመጥ ቅድስት ማርያም ከጌታ ሥር ተንበርክካ ናርዶስ የሚሉትን የ300 ዲናር ሽቱ በጌታ ላይ አፈሰሰች። መዓዛ መለኮቱና ሽቱው ሲገናኝ "መልዐ መዓዛሁ" እንዲል የሚመስጥ ሽታ ቤቱን ሞላው።
በወቅቱ ይሁዳ ቢቃወምም ጌታ ምላሹን ሰጥቶታል። ቅድስት ማርያምንም "ማርያምሰ ኃርየት መክፈልተ ሠናየ ዘኢየኃይድዋ" ብሎ አመስግኗታል። ያስመሰገናት ቁጭ ብላ በተመስጦ መማሯ ብቻ እንዳልሆነ አባ ሕርያቆስ መስከሯል።
ሲመክረንም "አርምሞንና ትዕግስትን እንደ ማርያም ገንዘብ እናድርግ" ብሎናል። (ቅዳሴ ማርያም) ቅድስት ማርያም በጌታችን ክርስቶስ በኅማሙ ጊዜ ሲቀብሩት ነበረች። ትንሳኤውንም ዐይታለች።
ከጌታ እርገት በኋላም መንፈስ ቅዱስን ተከትላ ለወንጌል አገልግሎት ተግታለች። ቅድስት እናታችን ማርያም እንተ ዕፍረት ዛሬ እንዳረፈች እናዘክራለን።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥቅምት)
ጉባኤ ጽዮን የሰንበት ት/ቤታችን ወርሃዊ ጉባኤ ተካሄደ
ጥቅምት 16, 2014 ዓ.ም
ጥቅምት 16, 2014 ዓ.ም