መስከረም 2-መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡
በዚህችም ቀን የሰማዕት ዲዲሞስና የቅድስት መሪና መታሰቢያቸው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል።
+በዚችም ቀን በግብጽ ውስጥ ታዕዳ ከሚባል አገር ዳስያ ሰማዕት ሆነ። ይህንንም ቅዱስ የእንዴናው አገረ ገዥ አርያኖስ አሠቃየው ጽኑ ሥቃይንም ከአሠቃየው በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ ነቢይ (መጥምቀ መለኮት)፦ዮሐንስ ማለት ‹‹ፍሥሐ ወሐሴት፣ ርኅራኄ›› ማለት ነው፡፡ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ጠራጊ የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ የብሉይ ኪዳን የመጨረሻው የሐዲስ ኪዳን ደግሞ የመጀመሪያው ነቢይ ነው፡፡
ይህም እንዲህ ነው በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት ነቢዩ ዮሐንስ በገሠጸው ጊዜ ፊልጶስ ወንድሙ ስለሆነ ቅዱስ ዮሐንስም የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም ይለው ነበርና። ቅዱስ ዮሐንስም ሄሮድስን የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን ስለማግባቱና ሌላም ያደርገው ስለነበረ ክፉ ሥራ ሁሉ ይገሥጸው ነበር። ደግሞም በተግሣጽ ላይ ተግሣጽን ጨመረ ስለዚህም ዮሐንስን ተቀየመውና በግዞት ቤት አኖረው።
ሄሮድስም ዮሐንስን ይፈራው ነበር ጻድቅ ቅዱስ ሰው እንደሆነ ያውቅ ነበርና ብዙ ይጠባበቀውም ነበር። ሄሮድስ የተወለደባትን ቀን በዓል የሚያከብርባት ዕለት ነበረች መኳንንቱን አለቆቹን መሣፍንቱን ሹሞቹን በገሊላ አገር ያሉትን ታላላቅ ሰዎች ግብር አገባ።
የሄሮድያዳ ልጅም ወደ አዳራሹ ገብታ ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው ከእርሱ ጋር በማዕድ የነበሩትንም ንጉሡም ያቺን ብላቴና የምትሺውን ለምኚኝ እሰጥሻለሁ አላት። እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም ቢሆን የለመነችውን ሊሰጣት ማለላት ወጥታም እናቷን ምን ልለምነው አለቻት እናቷም የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ አለቻት ያን ጊዜም እየሮጠች ወደ ንጉሡ ገብታ የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ በወጭት አሁን እንድትሰጠኝ እሻለሁ ብላ ለመነችው ንጉሡም ስለ መሐላው አብረውት ስለ ነበሩትም ሰዎች አዘነ እምቢ ሊላት ግን አልወደደም።
ያን ጊዜም ባለወጎችን ላከ በእሥር ቤትም ሳለ የዮሐንስን ራስ ቆረጡ ራሱንም በወጭት አምጥተው ለዚያች ብላቴና ሰጡአት እርሷም ወስዳ ለእናቷ ሰጠች በዚያችም ቀን የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ከሄሮድያዳ ከእጆቿ ላይ ወደ አየር ስለ በረረች ታላቅ ድንጋፄ ሆነ። ደግሞም ሄሮድስ ሆይ የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም እያለች በመጮኽ ዘልፋዋለችና። ደቀ መዛሙርቱም በሰሙ ጊዜ መጥተው በድኑን ወስደው ቀበሩት።
የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
ምንጭ፦ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
በዚህችም ቀን የሰማዕት ዲዲሞስና የቅድስት መሪና መታሰቢያቸው መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሳቸዋል።
+በዚችም ቀን በግብጽ ውስጥ ታዕዳ ከሚባል አገር ዳስያ ሰማዕት ሆነ። ይህንንም ቅዱስ የእንዴናው አገረ ገዥ አርያኖስ አሠቃየው ጽኑ ሥቃይንም ከአሠቃየው በኋላ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ ነቢይ (መጥምቀ መለኮት)፦ዮሐንስ ማለት ‹‹ፍሥሐ ወሐሴት፣ ርኅራኄ›› ማለት ነው፡፡ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መንገድ ጠራጊ የሆነው ቅዱስ ዮሐንስ የብሉይ ኪዳን የመጨረሻው የሐዲስ ኪዳን ደግሞ የመጀመሪያው ነቢይ ነው፡፡
ይህም እንዲህ ነው በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት ነቢዩ ዮሐንስ በገሠጸው ጊዜ ፊልጶስ ወንድሙ ስለሆነ ቅዱስ ዮሐንስም የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም ይለው ነበርና። ቅዱስ ዮሐንስም ሄሮድስን የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን ስለማግባቱና ሌላም ያደርገው ስለነበረ ክፉ ሥራ ሁሉ ይገሥጸው ነበር። ደግሞም በተግሣጽ ላይ ተግሣጽን ጨመረ ስለዚህም ዮሐንስን ተቀየመውና በግዞት ቤት አኖረው።
ሄሮድስም ዮሐንስን ይፈራው ነበር ጻድቅ ቅዱስ ሰው እንደሆነ ያውቅ ነበርና ብዙ ይጠባበቀውም ነበር። ሄሮድስ የተወለደባትን ቀን በዓል የሚያከብርባት ዕለት ነበረች መኳንንቱን አለቆቹን መሣፍንቱን ሹሞቹን በገሊላ አገር ያሉትን ታላላቅ ሰዎች ግብር አገባ።
የሄሮድያዳ ልጅም ወደ አዳራሹ ገብታ ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው ከእርሱ ጋር በማዕድ የነበሩትንም ንጉሡም ያቺን ብላቴና የምትሺውን ለምኚኝ እሰጥሻለሁ አላት። እስከ መንግሥቱ እኩሌታ ድረስም ቢሆን የለመነችውን ሊሰጣት ማለላት ወጥታም እናቷን ምን ልለምነው አለቻት እናቷም የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ አለቻት ያን ጊዜም እየሮጠች ወደ ንጉሡ ገብታ የመጥምቁ ዮሐንስን ራስ በወጭት አሁን እንድትሰጠኝ እሻለሁ ብላ ለመነችው ንጉሡም ስለ መሐላው አብረውት ስለ ነበሩትም ሰዎች አዘነ እምቢ ሊላት ግን አልወደደም።
ያን ጊዜም ባለወጎችን ላከ በእሥር ቤትም ሳለ የዮሐንስን ራስ ቆረጡ ራሱንም በወጭት አምጥተው ለዚያች ብላቴና ሰጡአት እርሷም ወስዳ ለእናቷ ሰጠች በዚያችም ቀን የቅዱስ ዮሐንስ ራስ ከሄሮድያዳ ከእጆቿ ላይ ወደ አየር ስለ በረረች ታላቅ ድንጋፄ ሆነ። ደግሞም ሄሮድስ ሆይ የወንድምህን ሚስት ልታገባ አይገባህም እያለች በመጮኽ ዘልፋዋለችና። ደቀ መዛሙርቱም በሰሙ ጊዜ መጥተው በድኑን ወስደው ቀበሩት።
የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን፡፡
ምንጭ፦ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ እያልን 👉 የሰንበት ት/ቤታችን አባላት ጉዳይ በያዝነው በአዲሱ 2014 ዓ.ም
👉 የአባላትን ፎርም በአዲስ መልኩ መሙላት ስላሰበ ሁላችሁም ነባር አባላት የአገልግሎት ፎርም እስከ መስከረም 30 ድረስ እየመጣችሁ እንድትሞሉ ይሁን
👉 በዚህ ፎርም ላይ ለአገልግሎት የምትመጡበት እና የማይመቻችሁን ግዜ ማሳወቅ መሙላት ይጠበቅባቹሃል
👉 ይህን መረጃ ለሰንበት ት/ቤታችን በቅርቡ ልናሰራው ባሰብነው Database (ዳታቤዝ) ልማት አስፈላጊ ሆኖም ተገኝቷል
ይህ ማስታወቂያ ሁላችንም የሰንበት ት/ቤት አባላትን ይመለከታል የምዝገባ የመጨረሻ ቀን መስከረም 30 ነው ላልሰሙት እናሰማ
👉 የአባላትን ፎርም በአዲስ መልኩ መሙላት ስላሰበ ሁላችሁም ነባር አባላት የአገልግሎት ፎርም እስከ መስከረም 30 ድረስ እየመጣችሁ እንድትሞሉ ይሁን
👉 በዚህ ፎርም ላይ ለአገልግሎት የምትመጡበት እና የማይመቻችሁን ግዜ ማሳወቅ መሙላት ይጠበቅባቹሃል
👉 ይህን መረጃ ለሰንበት ት/ቤታችን በቅርቡ ልናሰራው ባሰብነው Database (ዳታቤዝ) ልማት አስፈላጊ ሆኖም ተገኝቷል
ይህ ማስታወቂያ ሁላችንም የሰንበት ት/ቤት አባላትን ይመለከታል የምዝገባ የመጨረሻ ቀን መስከረም 30 ነው ላልሰሙት እናሰማ
👉 በወርኃ መስከረም በዓራተኛው ቀን ከ12ቱ ሐዋርያትና ከ4ቱ ወንጌላውያን አንዱ ፍቁረ እግዚእ የተባለ አባታችን ቅዱስ ዮሐንስ ልደቱ እንደሚታሰብ አበው መምህራን ይናገራሉ።
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰ/ት/ቤት
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰ/ት/ቤት
#አቡነ_አሮን_መንክራዊ
ዳግመኛም በዚህች ቀን የዚህ ታላቅ አባት የእረፍት ቀን ነው፡፡
ኢትዮዽያዊው ጻድቅ አቡነ አሮን በ14ኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩ ኢትዮዽያዊ ሲሆኑ በገዳማዊ ሕይወታቸው በሐዋርያዊ አገልግሎታቸውና ነገሥታቱን ሳይፈሩ በመገሰጻቸው ይታወቃሉ፡፡
በተለይም ሕይወታቸው በተአምር የተሞላ ስለነበር 'አሮን መንክራዊ' (ድንቅ አባት) ተብለው ይጠራሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜም 'አሮን ዘመቄት /ዘደብረ ዳሬት/' በሚልም ይጠራሉ፡፡
የአቡነ አሮን ወላጆች ገብረ መስቀልና ዓመተ ማርያም የሚባሉ ሲሆን ከልጅነታቸው ጀምረው በቅዱስ ቃሉ የታነጹ ነበሩ፡፡ ምናኔን በደብረ ጐል ከአቡነ በጸሎተ ሚካኤል
ጀምረው ብዙ ገዳማትን መሥርተዋል፡፡ በርካታ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል::
ለወንጌል አገልግሎት በወጡበት ጸሐይን አቁመው ሕዝቡን ድንቅ አሰኝተዋል፡፡ እንኩዋን ሰዉ ይቅርና አጋንንትም ያደንቁዋቸው ነበር፡፡ ነገሥታቱንም ስለ ኃጢአታቸው በገሰጹ ጊዜ ራቁትነት እሥራት ግርፋትና ስደት ደርሶባቸዋል ከብዙ ተጋድሎ በኋላ መስከረም 5 ቀን አርፈዋል፡፡
በረከታቸው ሁላችንንም ይጠብቀን
ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
ዳግመኛም በዚህች ቀን የዚህ ታላቅ አባት የእረፍት ቀን ነው፡፡
ኢትዮዽያዊው ጻድቅ አቡነ አሮን በ14ኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩ ኢትዮዽያዊ ሲሆኑ በገዳማዊ ሕይወታቸው በሐዋርያዊ አገልግሎታቸውና ነገሥታቱን ሳይፈሩ በመገሰጻቸው ይታወቃሉ፡፡
በተለይም ሕይወታቸው በተአምር የተሞላ ስለነበር 'አሮን መንክራዊ' (ድንቅ አባት) ተብለው ይጠራሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜም 'አሮን ዘመቄት /ዘደብረ ዳሬት/' በሚልም ይጠራሉ፡፡
የአቡነ አሮን ወላጆች ገብረ መስቀልና ዓመተ ማርያም የሚባሉ ሲሆን ከልጅነታቸው ጀምረው በቅዱስ ቃሉ የታነጹ ነበሩ፡፡ ምናኔን በደብረ ጐል ከአቡነ በጸሎተ ሚካኤል
ጀምረው ብዙ ገዳማትን መሥርተዋል፡፡ በርካታ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል::
ለወንጌል አገልግሎት በወጡበት ጸሐይን አቁመው ሕዝቡን ድንቅ አሰኝተዋል፡፡ እንኩዋን ሰዉ ይቅርና አጋንንትም ያደንቁዋቸው ነበር፡፡ ነገሥታቱንም ስለ ኃጢአታቸው በገሰጹ ጊዜ ራቁትነት እሥራት ግርፋትና ስደት ደርሶባቸዋል ከብዙ ተጋድሎ በኋላ መስከረም 5 ቀን አርፈዋል፡፡
በረከታቸው ሁላችንንም ይጠብቀን
ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
መስከረም ፮ (6) ቀን።
✍️ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ለታላቁ አባት ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ዐፅማቸው ከዋልድባ አብረንታንት ወደ ደብረ ዓባይ ለፈለሰበት ቀን መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
#የአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_የሥጋ_ፍልሰት
=========================
✍️ ከዋልድባ አብረንታንት ወደ ደብረ ዓባይ፤ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ ትውልዳቸው ከካህናቱ ወገን አክሱም ነው አባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው አመተ ማርያም ይባላሉ። ለመምህር ሰጥተዋቸው ሲማሩ አድገው በኋላም ወላጆቻቸው በሞት ሲለዩአቸው ደብረ በንኰል ገዳም ገብተው ሥርዓተ ምንኩስናን ከአበው እያጠኑ ለትልቁም ለትንሹም በትሕትና እየታዘዙ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየሰበሩ በትኅርምት በጽሞና በጸሎት ይኖሩ ነበር።
✍️ ሰይጣን በውዳሴ ከንቱ ጾር ቢመጣባቸው ከማሕበረ መነኰሳቱ ተለይተው በተባሕትዎ ለመኖር ሽተው ወጥተው ሲሔዱ ተከዜ ደረሱ። ወንዙ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትምህርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉ ሳይበላሽ ተሻግረዋል። ዋልድባ ሲደርሱ ጌታ እዚህ ተቀመጥ ስላላቸው ገዳም መሥርተው ሥርዓተ ምንኩስናን እያስተማሩ ተቀመጡ። ዛሬ በዋልድባ የሚያመሰግኑበት ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያምን ከተከዜ ወዲህ ያመጡ እሳቸው ናቸው። ይህንን እየጸለዩ ሲሔዱ ክንድ ከስንዝር መሬት ለቀው ይታዩ ነበር።
✍️ አንድ ቀንም ይህንን ጸሎት ደግመው ውኃውን ቢባርኩት ኅብስተ ሕይወት ሆነላቸው ከነደቀ መዛሙርቶቻቸው ተመግበውታል። እመቤታችንም የፍቅር መግለጫ ዕጣን፣ ወርቅ፣ እንቁ ሰጥታቸዋለች። "ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ አንድ አድርጎ የደገመውን አንተ ከገባህበት መካነ ሕይወት አስገባዋለሁ" ብላ ቃልኪዳን ሰጥታቸዋለች። ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታን በስብሐተ መላእክት ተገልጦ "በስምህ የተማጸነውን በጎ የሰራውን፣ ዜና ገድልህን የጻፈውን፣ ያስጻፈውን፣ ያነበበ፣ የተማረ፣ ያስተማረ፣ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ምሬልሃለሁ። በዚህ ቦታ በዋልድባ የሚሰበሰቡ ልጆችህን ከእዳ ከፍዳ እሰውርልሃለሁ" አላቸው። እንኪያስ ቦታዋን ባርክልኝ ብለው እንደ መሶብ አንስተው አስባርከዋታል ጌታችንም "እህል አይብቀልብሽ ኃጢአት አይሻገርብሽ" ብሎ ቃል ኪዳን ገባላት ለገዳመ ዋሊ። አባታችን አቡነ ሳሙኤል በበዓታቸው ውስጥ ጸንተው ሲኖሩ ታህሣሥ 12 ቀን ያረፉ ሲሆን ዛሬ መስከረም 6 ግን ፍልሰተ አጽማቸው የተከናወነበት ዕለት ነው። ከአባታቸው ከአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን።
✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
✍️ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ለታላቁ አባት ለአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ዐፅማቸው ከዋልድባ አብረንታንት ወደ ደብረ ዓባይ ለፈለሰበት ቀን መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
#የአቡነ_ሳሙኤል_ዘዋልድባ_የሥጋ_ፍልሰት
=========================
✍️ ከዋልድባ አብረንታንት ወደ ደብረ ዓባይ፤ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ ትውልዳቸው ከካህናቱ ወገን አክሱም ነው አባታቸው እስጢፋኖስ እናታቸው አመተ ማርያም ይባላሉ። ለመምህር ሰጥተዋቸው ሲማሩ አድገው በኋላም ወላጆቻቸው በሞት ሲለዩአቸው ደብረ በንኰል ገዳም ገብተው ሥርዓተ ምንኩስናን ከአበው እያጠኑ ለትልቁም ለትንሹም በትሕትና እየታዘዙ ውሃ እየቀዱ እንጨት እየሰበሩ በትኅርምት በጽሞና በጸሎት ይኖሩ ነበር።
✍️ ሰይጣን በውዳሴ ከንቱ ጾር ቢመጣባቸው ከማሕበረ መነኰሳቱ ተለይተው በተባሕትዎ ለመኖር ሽተው ወጥተው ሲሔዱ ተከዜ ደረሱ። ወንዙ ሞልቶ የማያሻግራቸው ቢሆን ውሃውን በትምህርተ መስቀል ባርከው በአንድ እጃቸው መጽሐፍ በአንድ እጃቸው መብራት እንደያዙ ገብተው መብራቱ ሳይጠፋ መጽሐፉ ሳይበላሽ ተሻግረዋል። ዋልድባ ሲደርሱ ጌታ እዚህ ተቀመጥ ስላላቸው ገዳም መሥርተው ሥርዓተ ምንኩስናን እያስተማሩ ተቀመጡ። ዛሬ በዋልድባ የሚያመሰግኑበት ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያምን ከተከዜ ወዲህ ያመጡ እሳቸው ናቸው። ይህንን እየጸለዩ ሲሔዱ ክንድ ከስንዝር መሬት ለቀው ይታዩ ነበር።
✍️ አንድ ቀንም ይህንን ጸሎት ደግመው ውኃውን ቢባርኩት ኅብስተ ሕይወት ሆነላቸው ከነደቀ መዛሙርቶቻቸው ተመግበውታል። እመቤታችንም የፍቅር መግለጫ ዕጣን፣ ወርቅ፣ እንቁ ሰጥታቸዋለች። "ውዳሴዬን ከቅዳሴዬ አንድ አድርጎ የደገመውን አንተ ከገባህበት መካነ ሕይወት አስገባዋለሁ" ብላ ቃልኪዳን ሰጥታቸዋለች። ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታን በስብሐተ መላእክት ተገልጦ "በስምህ የተማጸነውን በጎ የሰራውን፣ ዜና ገድልህን የጻፈውን፣ ያስጻፈውን፣ ያነበበ፣ የተማረ፣ ያስተማረ፣ እስከ አሥር ትውልድ ድረስ ምሬልሃለሁ። በዚህ ቦታ በዋልድባ የሚሰበሰቡ ልጆችህን ከእዳ ከፍዳ እሰውርልሃለሁ" አላቸው። እንኪያስ ቦታዋን ባርክልኝ ብለው እንደ መሶብ አንስተው አስባርከዋታል ጌታችንም "እህል አይብቀልብሽ ኃጢአት አይሻገርብሽ" ብሎ ቃል ኪዳን ገባላት ለገዳመ ዋሊ። አባታችን አቡነ ሳሙኤል በበዓታቸው ውስጥ ጸንተው ሲኖሩ ታህሣሥ 12 ቀን ያረፉ ሲሆን ዛሬ መስከረም 6 ግን ፍልሰተ አጽማቸው የተከናወነበት ዕለት ነው። ከአባታቸው ከአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን።
✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
#መስከረም_7
መስከረም ሰባት በዚህች ቀን ....
1- አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናት #የቅድስት_ሐና ልደቷ ነው፣
2- የመጥምቁ ዮሐንስ እናት የከበረች #ቅድስት_ኤልሳቤጥ አረፈች፣
3- #የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ አረፈ፣
4- የከበረ አባት #ቅዱስ_ሳዊርያኖስ አረፈ፣
5- የከበሩ #አጋቶንና_ጴጥሮስ_ዮሀንስና_አሞን እናታቸውም ራፈቃ በሰማእትነት አረፉ።
የቅዱሳኑ በረከታቸው አማላጅነታቸው ይጠብቀን
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉን
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መስከረም እና #ከገድላት_አንደበት)
መስከረም ሰባት በዚህች ቀን ....
1- አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናት #የቅድስት_ሐና ልደቷ ነው፣
2- የመጥምቁ ዮሐንስ እናት የከበረች #ቅድስት_ኤልሳቤጥ አረፈች፣
3- #የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ዲዮስቆሮስ አረፈ፣
4- የከበረ አባት #ቅዱስ_ሳዊርያኖስ አረፈ፣
5- የከበሩ #አጋቶንና_ጴጥሮስ_ዮሀንስና_አሞን እናታቸውም ራፈቃ በሰማእትነት አረፉ።
የቅዱሳኑ በረከታቸው አማላጅነታቸው ይጠብቀን
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉን
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
👉https://t.me/finotebirhan12👈
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_መስከረም እና #ከገድላት_አንደበት)
እናመሰግናለን!
የሰንበት ት/ቤታችን Youtube Channel በእናንተ ድጋፍ እዚህ ደርሷል በቀጣይም እንበረታ ዘንድ ሰብስክራይብ አድርጋችሁ ጠብቁን አዝናኝ እና ትምህርታዊ ዝግጅቶች በቅርቡ ይለቀቃል
👇👇👇Click and Subscribe👇👇👇
https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
የሰንበት ት/ቤታችን Youtube Channel በእናንተ ድጋፍ እዚህ ደርሷል በቀጣይም እንበረታ ዘንድ ሰብስክራይብ አድርጋችሁ ጠብቁን አዝናኝ እና ትምህርታዊ ዝግጅቶች በቅርቡ ይለቀቃል
👇👇👇Click and Subscribe👇👇👇
https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
#መስከረም_9 በዚህች የመላእክት አለቃ #ቅዱስ_ሚካኤል በሮም አገር ፍሩምያ በምትባል ከተማ ላደረገው ተአምር መታሰቢያ ነው
#ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሚካኤል
በዚህች ቀን በሮም አገር ፍሩምያ በምትባል ከተማ ለሆነው ተአምር መታሰቢያ ሆነ። ይህም እንዲህ ነው የሰማይ ሠራዊት አለቃ በሆነ በከበረ መልአክ በሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚታዩ ድንቆችና ተአምራቶች ምክንያት ዮናናውያን ሰዎች ሰይጣናዊ ቅናትን እንደ ቀኑ ከመቅናታቸውም ብዛት የተነሣ በዚያ አካባቢ የሚወርደውን የወንዝ ውኃ በዚያች ቤተ ክርስቲያን ላይ ሊመልሱትና ከሚጠብቃት መጋቢዋ ጋር በውኃ ስጥመት ሊአጠፉአት ፈልገው መለሱት።
የሰማያውያን ሠራዊት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለቤተ ክርስቲያኑ መጋቢ ለናርጢኖስ ተገለጠለት ወደርሱም ቀርቦ ጽና አትፍራ አለው ይህንን ብሎ በእጁ ውስጥ ባለ በትር አለቱን መታው አለቱም ተደንጥቆ እንደ በር ሆነ የዚያ ወንዝ ውኃም በውስጡ አልፎ ሔደ።
ይህንንም ያዩ ምስጉን እግዚአብሔርን አመሰገኑት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልንም አከበሩት። ከዚያች ቀን እስከ ዛሬ የወንዙን ውኃ በዚያች በተሠነጠቀች አለት ውስጥ አልፎ ሲሔድ ያዩታል ወደ መላእክት አለቃ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ከቶ አይቀርብም።
ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
መልካም ዕለተ ሰንበት
#ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ሚካኤል
በዚህች ቀን በሮም አገር ፍሩምያ በምትባል ከተማ ለሆነው ተአምር መታሰቢያ ሆነ። ይህም እንዲህ ነው የሰማይ ሠራዊት አለቃ በሆነ በከበረ መልአክ በሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚታዩ ድንቆችና ተአምራቶች ምክንያት ዮናናውያን ሰዎች ሰይጣናዊ ቅናትን እንደ ቀኑ ከመቅናታቸውም ብዛት የተነሣ በዚያ አካባቢ የሚወርደውን የወንዝ ውኃ በዚያች ቤተ ክርስቲያን ላይ ሊመልሱትና ከሚጠብቃት መጋቢዋ ጋር በውኃ ስጥመት ሊአጠፉአት ፈልገው መለሱት።
የሰማያውያን ሠራዊት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለቤተ ክርስቲያኑ መጋቢ ለናርጢኖስ ተገለጠለት ወደርሱም ቀርቦ ጽና አትፍራ አለው ይህንን ብሎ በእጁ ውስጥ ባለ በትር አለቱን መታው አለቱም ተደንጥቆ እንደ በር ሆነ የዚያ ወንዝ ውኃም በውስጡ አልፎ ሔደ።
ይህንንም ያዩ ምስጉን እግዚአብሔርን አመሰገኑት የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልንም አከበሩት። ከዚያች ቀን እስከ ዛሬ የወንዙን ውኃ በዚያች በተሠነጠቀች አለት ውስጥ አልፎ ሲሔድ ያዩታል ወደ መላእክት አለቃ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ከቶ አይቀርብም።
ስንክሳር ዘወርኀ መስከረም
መልካም ዕለተ ሰንበት
በቅርብ ቀን
መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ በማህበራዊ ኑሮ ላይ ከምዕመናን ለተነሱላቸው ጥያቄ በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ መልስ ሰጥተዋል youtube ቻናላችን ላይ ይለቀቃል በቅርብ ቀን ሰብስክራይብ አድርገው ይጠብቁን Share
👇👇👇 Click ሰብስክራይብ አድርገው ይጠብቁን 👇👇
https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
መጋቤ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ በማህበራዊ ኑሮ ላይ ከምዕመናን ለተነሱላቸው ጥያቄ በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ መልስ ሰጥተዋል youtube ቻናላችን ላይ ይለቀቃል በቅርብ ቀን ሰብስክራይብ አድርገው ይጠብቁን Share
👇👇👇 Click ሰብስክራይብ አድርገው ይጠብቁን 👇👇
https://m.youtube.com/channel/UCXMG9oO5j1M-lRbAn0OdVdQ
#መስከረም_10
#ጼዴንያ_ማርያም እና #ተቀጸል_ጽጌ / አጼ መስቀል
#ጼዴንያ_ማርያም
በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው: ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር (በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል) ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት::
ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም ተግታ ታገለግላትም ነበር ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር::
ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር: በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች::
#ተቀጸል_ጽጌ / አጼ መስቀል
ከ1500 ዓመት በፊት አበባን ተቀዳጅ የሚል ትርጉም ያለው የ‹‹ተቀጸል ጽጌ›› ክብረ በዓል መከበር የተጀመረው በአፄ ገብረ መስቀል ዘመን ሲሆን፣ ዝማሬውን ያዘጋጀው ደግሞ ቅዱስ ያሬድ ነበር ክረምት በሚወጣበት መስከረም 25 ቀን የአበባው በዓል ሲከበር ቅዱስ ያሬድ ንጉሠ ነገሥቱን ‹‹ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ሐፀጌ›› - አፄ ገብረ መስቀል ክረምቱ አልፎልሃልና አበባን ተቀዳጅ፣ አበባን ተላበስ እያለ ያወድሰው የነበረው በዓላዊ ትውፊት እየተቀባበለ እስከ 15ኛው መ, ክ,ዘ ደርሶ ነበር፡፡
በአፄ ዳዊት ዘመን የጌታችን ግማደ መስቀሉ መስከረም 10 ቀን ከግብፃውያን እጅ በመቀበላቸው ግማዱም በንጉሡ ምክንያት በመምጣቱ ‹‹አፄ መስቀል›› እየተባለ መከበር ሲጀምር፣ የ25ኛው ቀን የአበባው
በዓልም በ15 ቀን ወደኋላ በማፈግፈግ ከርሱ ጋር ባንድነት እንዲከበር በመወሰኑ እስካሁን በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ በቀድሞ ግዜ እስከ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን (1923-1967) የ1966ቱ መስከረም 10 ድረስ በዓሉ በንጉሡ ፊት በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት፣ በኋላም በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት ይከበር ነበር፡፡
በዘመነ ደርግ ተቋርጦ የነበረው የአበባው በዓል ተቀጸል ጽጌ ከ1980ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አማካይነት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዐውደ ምሕረት በመንፈሳዊ ሥነ ሥርዓትና ለምእመኑ አበባ እየታደለ መከበር ጀምሮ እንደቀጠለ ነው፡፡ ‹‹የክረምቱ ወራት አልፎ መጸዉ ብሎም በጋው ሲተካ፣ ምድር በልምላሜ ፀጋ ተውባ አረንጓዴ ልብስ ተጎናጽፋ፣ በዕፀዋት አበባ ደምቃ፣ የመንፈስ ደስታ የምታድልበት፣ ሰማይ በከዋክብት አጊጦና አሸብርቆ የሚታይበት በመሆኑ የአበባ በዓል ስም ከግብር የተስማማለት ነው፡፡›
አምላካችን እግዚአብሔር ከዚህ ወቅት መልካሙን ነገር እንድናገኝና ከእናታችንም ረድኤት በረከቷን ምልጃ ጸሎቷን እንዲያካፍለን መልካም ፈቃዱ ይሁን።
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
#ጼዴንያ_ማርያም እና #ተቀጸል_ጽጌ / አጼ መስቀል
#ጼዴንያ_ማርያም
በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው: ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር (በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል) ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት::
ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም ተግታ ታገለግላትም ነበር ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር::
ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር: በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች::
#ተቀጸል_ጽጌ / አጼ መስቀል
ከ1500 ዓመት በፊት አበባን ተቀዳጅ የሚል ትርጉም ያለው የ‹‹ተቀጸል ጽጌ›› ክብረ በዓል መከበር የተጀመረው በአፄ ገብረ መስቀል ዘመን ሲሆን፣ ዝማሬውን ያዘጋጀው ደግሞ ቅዱስ ያሬድ ነበር ክረምት በሚወጣበት መስከረም 25 ቀን የአበባው በዓል ሲከበር ቅዱስ ያሬድ ንጉሠ ነገሥቱን ‹‹ተቀጸል ጽጌ ገብረ መስቀል ሐፀጌ›› - አፄ ገብረ መስቀል ክረምቱ አልፎልሃልና አበባን ተቀዳጅ፣ አበባን ተላበስ እያለ ያወድሰው የነበረው በዓላዊ ትውፊት እየተቀባበለ እስከ 15ኛው መ, ክ,ዘ ደርሶ ነበር፡፡
በአፄ ዳዊት ዘመን የጌታችን ግማደ መስቀሉ መስከረም 10 ቀን ከግብፃውያን እጅ በመቀበላቸው ግማዱም በንጉሡ ምክንያት በመምጣቱ ‹‹አፄ መስቀል›› እየተባለ መከበር ሲጀምር፣ የ25ኛው ቀን የአበባው
በዓልም በ15 ቀን ወደኋላ በማፈግፈግ ከርሱ ጋር ባንድነት እንዲከበር በመወሰኑ እስካሁን በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ በቀድሞ ግዜ እስከ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን (1923-1967) የ1966ቱ መስከረም 10 ድረስ በዓሉ በንጉሡ ፊት በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት፣ በኋላም በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት ይከበር ነበር፡፡
በዘመነ ደርግ ተቋርጦ የነበረው የአበባው በዓል ተቀጸል ጽጌ ከ1980ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አማካይነት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዐውደ ምሕረት በመንፈሳዊ ሥነ ሥርዓትና ለምእመኑ አበባ እየታደለ መከበር ጀምሮ እንደቀጠለ ነው፡፡ ‹‹የክረምቱ ወራት አልፎ መጸዉ ብሎም በጋው ሲተካ፣ ምድር በልምላሜ ፀጋ ተውባ አረንጓዴ ልብስ ተጎናጽፋ፣ በዕፀዋት አበባ ደምቃ፣ የመንፈስ ደስታ የምታድልበት፣ ሰማይ በከዋክብት አጊጦና አሸብርቆ የሚታይበት በመሆኑ የአበባ በዓል ስም ከግብር የተስማማለት ነው፡፡›
አምላካችን እግዚአብሔር ከዚህ ወቅት መልካሙን ነገር እንድናገኝና ከእናታችንም ረድኤት በረከቷን ምልጃ ጸሎቷን እንዲያካፍለን መልካም ፈቃዱ ይሁን።
#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
👉የ2013 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤታችን በሕጻናት እና በወጣት ክፍል ለ2ወር የክረምት መንፈሳዊ ኮርስ ሲማሩ ቆይተው እሁድ መስከረም 09/2014 ዓ.ም ተመርቀዋል፡፡
የጥበብ መገኛ የሠላም ንጉስ
ጥበብ ግለጽልን ቸሩ ክርስቶስ
መልካም አገልግሎት ግዜ
የጥበብ መገኛ የሠላም ንጉስ
ጥበብ ግለጽልን ቸሩ ክርስቶስ
መልካም አገልግሎት ግዜ