⬆️
የሰ/ት/ቤታችን የእንኳን አደረሰን መልዕክት
የሰ/ት/ቤታችን የእንኳን አደረሰን መልዕክት
💠 ነፍስ የሌለው ሥጋ የሞተ እንደሆነ እንዲሁ ፀሎትን የማደታደርግ ነፍስ ሕይወት የላትም፡፡
/ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
/ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
እንኳን ለቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሰን።
#ጥር_1
💠የቅዱስ እስጢፋኖስ የልደቱም የዕረፍቱም ቀን ነው።
#የስሙ_ትርጉም
💠 ወደብ፣ ጸጥታ ማለት ነው።
#ለምን_ሊቀ_ዲያቆናት_ተባለ?
💠 በሐዋርያት እጅ ከተሾሙት 7 ዲያቆናት ውስጥ የሁሉም አለቃ ስለሆነ።
#ለምን_ቀዳሚ_ሰማዕት_ተባለ ?
💠 ከጌታችን ዕርገት በኋላ ስለ ጌታችን መውረድ መወለድ መስክሮ ስለሞተ።
#ሰማዕትነት_እንዴት_ተቀበለ ?
💠 ሐዋ ም 6 ቁ 8 ጀምሮ እንዲህ ይላል
እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር። የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም። በዚያን ጊዜ በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ። ሕዝቡንና ሽማግሌዎችንም ጻፎችንም አናደዱ፥ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና። ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤ ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ። በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት።
ይልና ወረድ ብሎ ም 7 ቁ 51 ላይ እንዲህ ይላል
እናንተ አንገተ ደንዳኖች ልባችሁና ጆሮአችሁም ያልተገረዘ፥ እናንተ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስን ትቃወማላችሁ፤ አባቶቻችሁ እንደ ተቃወሙት እናንተ ደግሞ። ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም። ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና። እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ። በታላቅ ድምፅም እየጮኹ ጆሮአቸውን ደፈኑ፥ በአንድ ልብ ሆነውም ወደ እርሱ ሮጡ፥ ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ። እስጢፋኖስም ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር። ተንበርክኮም ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር።
በረከቱ ይደርብን!!
#ጥር_1
💠የቅዱስ እስጢፋኖስ የልደቱም የዕረፍቱም ቀን ነው።
#የስሙ_ትርጉም
💠 ወደብ፣ ጸጥታ ማለት ነው።
#ለምን_ሊቀ_ዲያቆናት_ተባለ?
💠 በሐዋርያት እጅ ከተሾሙት 7 ዲያቆናት ውስጥ የሁሉም አለቃ ስለሆነ።
#ለምን_ቀዳሚ_ሰማዕት_ተባለ ?
💠 ከጌታችን ዕርገት በኋላ ስለ ጌታችን መውረድ መወለድ መስክሮ ስለሞተ።
#ሰማዕትነት_እንዴት_ተቀበለ ?
💠 ሐዋ ም 6 ቁ 8 ጀምሮ እንዲህ ይላል
እስጢፋኖስም ጸጋንና ኃይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅንና ታላቅ ምልክትን ያደርግ ነበር። የነፃ ወጪዎች ከተባለችው ምኵራብም ከቀሬናና ከእስክንድርያም ሰዎች ከኪልቅያና ከእስያም ከነበሩት አንዳንዶቹ ተነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ነበር፤ ይናገርበት የነበረውንም ጥበብና መንፈስ ይቃወሙ ዘንድ አልቻሉም። በዚያን ጊዜ በሙሴ ላይ በእግዚአብሔርም ላይ የስድብን ነገር ሲናገር ሰምተነዋል የሚሉ ሰዎችን አስነሡ። ሕዝቡንና ሽማግሌዎችንም ጻፎችንም አናደዱ፥ ቀርበውም ያዙት ወደ ሸንጎም አመጡትና። ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራ በሕግም ላይ የስድብን ነገር ለመናገር አይተውም፤ ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ ያፈርሰዋል ሙሴም ያስተላለፈልንን ሥርዓት ይለውጣል ሲል ሰምተነዋልና የሚሉ የሐሰት ምስክሮችን አቆሙ። በሸንጎም የተቀመጡት ሁሉ ትኵር ብለው ሲመለከቱት እንደ መልአክ ፊት ሆኖ ፊቱን አዩት።
ይልና ወረድ ብሎ ም 7 ቁ 51 ላይ እንዲህ ይላል
እናንተ አንገተ ደንዳኖች ልባችሁና ጆሮአችሁም ያልተገረዘ፥ እናንተ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስን ትቃወማላችሁ፤ አባቶቻችሁ እንደ ተቃወሙት እናንተ ደግሞ። ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም። ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና። እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ። በታላቅ ድምፅም እየጮኹ ጆሮአቸውን ደፈኑ፥ በአንድ ልብ ሆነውም ወደ እርሱ ሮጡ፥ ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ። እስጢፋኖስም ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር። ተንበርክኮም ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር።
በረከቱ ይደርብን!!
⬆️
የተክለሃይማኖት አደባባይ ለጥምቀት በኖኅ መርከብ አምሳያ ተውቧል።
የተክለሃይማኖት አደባባይ ለጥምቀት በኖኅ መርከብ አምሳያ ተውቧል።
የሰ/ት/ቤታችን ልማት ክፍል ለጥምቀት በዓል የተለያዩ ቲሸርቶችን፣ ባጆችን፣ ኮፍያዎችን፣ ለስላሳ መጠጦችን፣ ችፕስ፣ ውሃ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቦላችኋል።
ልማት ክፍላችን ያሰራው ቲሸርት ይህን ይመስላል። ከነገ ጀምሮ ለሽያጭ ይቀርባል።
የሰ/ት/ቤታችን ልማት ክፍል ለጥምቀት በዓል የተለያዩ ቲሸርቶችን፣ ባጆችን፣ ኮፍያዎችን፣ ለስላሳ መጠጦችን፣ ችፕስ፣ ውሃ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቦላችኋል።