የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
2.62K subscribers
6.23K photos
67 videos
79 files
1.72K links
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Download Telegram
በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም

ታኅሣሥ ሦስት በዚህች ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት ሲሆናት ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ነው ። እርሷ ለእግዚአብሔር የስእለት ልጅ ነበረችና።

እናቷ ቅድስት ሐና ልጅ የሌላት ስለሆነች በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ከሴቶች ተለይታ ርቃ ትኖር ነበር ሽማግሌ ከሆነ ከኢያቄም ከባሏ ጋርም እጅግ የምታዝን ሆነች ። እግዚአብሔርም ኀዘናቸውን ሰማ ቅድስት ሐናም እንዲህ ብላ ለእግዚአብሔር ተሳለች የሰጠኸኝን ፍሬ ለእግዚአብሔር አገልጋይ አደርጋለሁ ።

ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምንም በወለደቻት ጊዜ ሦስት ዓመት በቤቷ ውስጥ አሳደገቻት ከዚህም በኋላ ከደናግል ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ወሰደቻት በቤተ መቅደስም ምግቧን ከመላእክት እጅ እየተቀበለች ዐሥራ ሁለት ዓመት ኖረች ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም መጥቶ ከእርሷ ሥጋን እስከ ነሣ ድረስ።

ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት ያሳትፈን። በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን ሀገራችን ኢትዮጵያንና ቅድስት ቤተክርስቲያንን ይጠብቅልን ። አሜን


ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+ ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያረዝሙ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለሽም በቅድስናና በንጽሕና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ።
+ ድንግል ሆይ ምድራዊ ሕብስትን የተመገብሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ሕብስትን እንጂ።
+ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን እንጂ።    (ቅዳሴ ማርያም)

ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት ያሳትፈን። በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን ሀገራችን ኢትዮጵያንና ቅድስት ቤተክርስቲያንን ይጠብቅልን ። አሜን


ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
እንኳን ለሐዋርያዊ እንድርያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።

የቅዳሜ መደበኛ ትምህርት ታህሳስ 05/2017 ዓ.ም ከ11:30 ጀምሮ በጠበል ቤት አዳራሽ ኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትምህርት ይሰጣል እኛም በሰዓቱ በመገኘት ትምህርቱን እንድንማር ተጋብዘናል።

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
💫🌺💫🌺💫🌺💫🌺🌺💫🌺💫🌺💫🌺🌺

" ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ " {መዝ 117 ÷ 26}
    
#የ2016_ዓ_ም_የተማሪዎች_የምርቃት_መርሐግብር

💫🌺💫🌺💫🌺💫🌺🌺💫🌺💫🌺💫🌺🌺

በአዲስ አበባ  ሀገረ ስብከት የአ/አ/ሰ/ት/ቤቶች አንድነት
#ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም #በ4ኛ#በ6ኛ እና #በ10ኛ ክፍል ያስተማራቸውን ተማሪዎች ዕውቅና የመስጠት መርሐ ግብር።

🗓እሑድ  ታህሳስ 6/2017 ዓ.ም
     ከቀኑ 6:30 ጀምሮ
         💒በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም እና መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ ካቴድራል

💫🌺💫🌺💫🌺💫🌺🌺💫🌺💫🌺💫🌺🌺

       
#በመርሐግብሩ_ላይ 👇
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤ ብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፤ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመሪያው ኃላፊዎች ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እና የክፍለ ከተማ ቤተክህነት  የየክፍሉ ኃላፊዎች ፤ የደብራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፤ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አባቶች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፤ የየሰንበት  ት/ቤቱ የሥራ አመራር  አባላቶች ፤ የተመራቂ ተማሪ ወላጆች እንዲሁም ምዕመናን/ት ይገኛሉ።

 
#ኑ_ተማሪዎቻችን_በጋራ_እንመርቅ!!!
         
#የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት

እንኳን ለሐዋርያዊ እንድርያስ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ።
©የሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት  የምዘና ፈተና የወሰዱ #የ4ኛ#የ6ኛ እና #የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት የእውቅና እና የቡራኬ መርሐ ግብር ተከናወነ።

              ታኅሣሥ 06/04/2016 ዓ.ም


በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለ4ኛ ጊዜ በ2016 ዓ.ም በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የምዘና ፈተና የወሰዱ ቁጥራቸው 6209  የሚሆኑ የ4ኛ ፣ የ6ኛ እና የ10ኛ ክፍል  ተማሪዎችን ዛሬ ታኅሣሥ 06 2017 ዓ.ም በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔ ዓለም ወመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወአቡነ አረጋዊ ካቴድራል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያሪክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፤ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሐላፊዎች ፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮች ፣ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች  በተገኙበት የእውቅና እና የቡራኬ መርሐ ግብሩ ተከናውኗል።

መርሐ ግብሩ በቅዱስ ፓትርያርኩ ጸሎት የተጀመረ ሲሆን ከጸሎቱ በማስቀጠል ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ "ሰንበት ተማሪዎች ዋነኛ የቤተ ክርስቲያን ተተኪ መሆናቸው ታውቆ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛል፤ ሰንበት ተማሪው ከበዓል አድማቂነት ወጥቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት የሚያውቅና የሚጠብቅ እንዲሆን እንረባረባለን በተጨማሪም በከተማው የሚገኙ ወጣቶች ሁሉ በሰንበት ት/ቤቶች እስኪታቀፉ እንሠራለን።" በማለት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ " ልጅህን በሚሔድበት መንገድ ምራው በሸመገለ ጊዜ ከሱ ፈቀቅ አይልም" የሚል አምላካዊ ቃልን መነሻ በማድረግ አባታዊ ምክር አስተላልፈዋል። ሀገረ ስብከቱም ለአንድነቱ ከዚህ የበለጠ እገዛ እንደሚያደርግ ብጹዕ አባታችን ቃል ገብተዋል።

በቅዱስነታቸው መልካም ፈቃድ የዕለቱን ቃለ እግዚአብሔር ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ

"ይህንን እዘዝና አስተምር በቃልም በተግባርም በእምነትም ለሚያምኑ ምሳሌ ሁን እንጂ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው።(1ኛ ጢሞ 4÷12) መነሻ በማድረግ " ማንም ታናሽነታቹሁን አይናቀው የቤተ ክርስቲያን ተተኪ ናችሁ ብለው ቃለ ወንጌል ሰጥተዋል።

በመቀጠልም ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ " ሥርዓተ ትምህርቱ ነገ ሀገርና ቤተ ክርስቲያን ተስፋ የምትጥልባቸውን ሕጻናትና ወጣቶች በኹለት በኩል የተሳሉ ሰይፍ እንዲሆኑ የሚሠራ ወጥነት ያለው ነው። ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ሊተገብሩት ይገባል ብለዋል። የታተሙትንና ስርጭት ላይ የሚገኙትን ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍትንም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ገዝተው ይጠቀሙ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ "በዚህ ዕድሜያቹ የቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት በማወቃቹ ለቤተ ክርስቲያን ዘብ መቆም የምትችሉ የቤተ ክርስቲያን የጀርባ አጥንት ናችሁ በሃይማኖት ጽኑ" በማለት አባታዊ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል።

በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች የሜዳልያ ሽልማት ፤ ምዘናውን ላስፈተኑ 121 ሰንበት ትምህርት ቤቶች ፤ በትምህርት አሰጣጥ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የክፍለ ከተማ አንድነት ትምህርት ክፍሎች  እንዲሁም ለመርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት ከቅዱስነታቸው እጅ ቡራኬ ተቀብለዋል።

  © የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ቅዱስ አባ ኪሮስ

በዚችም ዕለት በምዕራባዊ በረሀ የሚኖር ታላቅና ክቡር አባት የሆነው የአባ ኪሮስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ።

ይህም ቅዱስ የታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ወንድሙ ነበር በከተማ ውስጥ የሚሠራውን ዐመፅ በአየ ጊዜ ገንዘቡን ሁሉ ትቶ ከሀገሩ ወጣ። ጌታቸንም መርቶ ወደዚች ምዕራባዊት በረሀ አደረሰው በውስጧም ብዙ ዘመናት ብቻውን ኖረ ከሰው ማንም አላየውም በዚህ ሁሉ ዘመን የዱር አራዊትም ቢሆኑ ።

በአስቄጥስም ገዳም ስሙ አባ ባውማ የሚባል አንድ ቄስ ነበረ እርሱም የንጉሥ ዘይኑን ልጅ ቅድስት ኢላርያን ሥጋዋን የገነዘ ነው ። እርሱም እንዲህ አለ በቤተ ክርስቲያን ወስጥ እያለሁ አባ ባውማ ሆይ ተነሥ ወደ በረሀው ውስጥ ገብተህ ወደ ፀሐይ መግቢያ ሒድ ከቅዱሳን ሁሉ አብዝቶ ፈቃዴን የፈጸመውን የአንድ ገዳማዊ ሥጋ ትገንዝ ዘንድ የሚለኝን ቃል ከሰማይ ሰማሁ።

ያን ጊዜም ደስ ብሎኝ ተነሣሁ በበረሀውም ውስጥ ሦስት ቀን ተጉዤ ከአንድ ገዳማዊ በዓት ደርሼ ደጁን አንኳኳሁ አንድ ሽማግሌ ገዳማዊም ከፈተልኝና እርስ በርሳችን ሰላምታ ተለዋወጥን በዚች በረሀ ሌላ ገዳማዊ አለን ብዬ ጠየቅሁት አዎን አለኝ ። ሁለተኛም ስምህ ማነው አባቴ ሆይ በዚችስ በረሀ ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ኖርክ አልሁት ስሜ ስምዖን ነው በዚች በረሀ የኖርኩትም ሰባ ዓመታት ነው አለኝ።

ከእርሱ ዘንድም ወጥቼ ሦስት ቀን ተጓዝኩ ሁለተኛም ስሙ ባሞን የሚባል ገዳማዊ አገኘሁ ሰላምታም ሰጠሁትና በዚች በረሀ ሌላ ገዳማዊ አለን አልሁት አዎን አለ አለኝ ። አራት ቀንም ተጓዝኩ ወደ አባ ኪሮስ በዓት ደረስኩ ቅዱስ አባት ሆይ ባርከኝ እያልኩ ደጁን አንኳኳሁ አባ ባውማ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው ብሎ ከውስጥ ተናገረኝ ። እግዚአብሔር ያከበረህ ሰው በሰላም በፍቅር ወደእኔ ግባ አለኝ ያን ጊዜ ገብቼ ከእርሱ ተባረክሁ በፊቱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ክብር አየሁ የራሱ ጠጉርና ጽሕሙ እንደ በረድ የነጣ ነበር ።

ከዚህም በኋላ ተቀመጥሁ በብብቻውም አቀፈኝ እንዲህም አለኝ እነሆ ይችን ሰዓት እየጠበቅኋት በዚች በዓት ሃምሳ ሰባት ዓመት ኖርኩ ይህንንም ሲል ጥቂት ታመመና ተኛ እየደነገጠ ያቺን ሌሊት አደረ ሲነጋም በበዓቱ ውስጥ ታላቅ ብርሃን በራ ብርሃናዊ ሰውም ገባ በእጁም የብርሃን መስቀል አለ በአባ ኪሮስ አጠገብም ተቀምጦ ሳመዉ ባረከውም አጽናናው ሰላምን ፍቅርን አንድነትን አደረገለት ከእርሱም ተሠወረ እኔም ፈራሁ እንዲህ የሚበራ ይህን ክብር የተጐናጸፈ ይህ ማነው አልሁት ።

እርሱም ልጄ ሆይ ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ልማዱ ስለ ሆነ ሁልጊዜ ይመጣል ያጽናናኛልም አለኝ ። በቀዳሚት ሰንበት ዕለትም ዘጠኝ ሰዓት በሆነ ጊዜ እስከ ሰማይ የሚደርስ ታላቅ ጩኸትን ሰማሁ ከጩኸታቸውም ኃይል የተነሣ ምድር ተናወጸች። እኔም ይህ የምሰማው ጩኸት ምንድነው ብዬ ጠየቅሁት እርሱም ልጄ ሆይ ይህ በሲኦል የሚኖሩ የኃጥአን ጩኸት ነው ስለ ቅድስት ትንሣኤው የእሑድ ፀሐይ እስክትጠልቅ ድረስ እግዚአብሔር ያሳርፋቸዋልና ስለዚህም እግዚአብሔርን ያመሰግኑታል አለኝ ።

ሐምሌ ሰባት ቀን ቅዱስ አባ ኪሮስ ጩኾ አለቀሰ ዛሬ በግብጽ አገር ታላቅ ምሰሶ ወደቀ ይኸውም የገዳማውያን አለቃ ቅዱስ አባ ሲኖዳ ነው አለ ።

ከዚህም በኋላ ከደዌው ጽናት የተነሣ እሑድ ሌሊት እጅግ ደነገጠ በበዓቱም ውስጥ እነሆ ታላቅ ብርሃን በራ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ገብቶ በአባ ኪሮስ ራስ አጠገብ ተቀመጠ ። አባ ኪሮስም መድኃኒታችንን ጌታዬ ሆይ ይህን ሰው ባርከው አለው መድኃኒታችንም የመረጥሁህ አባ ባውማ ሆይ ጽና አትፍራም ሰላሜ በረከቴም ከአንተ ጋራ ይኑር ። አሁንም ታማኝ አገልጋዬ የሆነ የዚህን የቅዱስ ኪሮስን ያየኸውንና የሰማኸውን ወደፊትም ዳግመኛ የምታየውንና የምትሰማውን ገድሉን ጻፍ አለኝ ።

ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን አባ ኪሮስን እንዲህ አለው እነሆ አንተ ትሞታለህና አትዘን ሞትህ ሞት አይደለም የዘላለም ሕይወት ነው እንጂ ። የገድልህን መጽሐፍ የሚጽፈውን ወይም የሚያነበውን የሚሰማውንም ሁሉ በምድርም መታሰቢያህን የሚያደርገውን ሁሉ በደብረ ጽዮን በሚደረገው የሽህ ዓመት በዓል ምሳ ከእኔ ጋር ይቀመጥ ዘንድ አደርገዋለሁ ከቅዱሳኖቼም ጋራ እቆጥረዋለሁ ። የኃጢአቱንም መጽሐፍ ቀድጄ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፋለሁ ። ለመሥዋዕት የሚገባውንም ዕጣኑንና ወይኑን መብራቱንም መባ አድርጎ ለሚሰጥም በስምህም ለድኆችና ለችግረኞች ምጽዋትን ለሚያደርግ ዓይን ያላየውን ጆሮም ያልሰማውን በሰው ልቡናም ያልታሰበውን በጎ ዋጋ እኔ እጥፍ ድርብ አድርጌ እሰጠዋለሁ ። በበኵር ቤተ ክርስቲያንም ሥጋዬንና ደሜን አቀብላቸዋለሁ በዚህም ዓለም ቤታቸውን እባርካለሁ ። ልጆቻቸውን አሳድጋለሁ ከበጎ ነገር ሁሉ ምንም ምን አያጡም ።

መድኃኒታችንም አባ ኪሮስን እነሆ ዘማሪው ዳዊት መጥቷልና ይዘምርልህ ዘንድ የምትሻውን ንገር አለው። ዳዊትም ቅዱስ አባ ኪሮስን በየትኛው አውታር እንድዘምርልህ ትሻለህ ደግሞስ በየትኛው ዜማ በየትኛው ስልት በመጀመሪያው ነውን ወይስ በሁለተኛው ወይስ በሦስተኛው አለው። ቅዱስ አባ ኪሮስም በዐሥሩም አውታር በየስልታቸውና በየዜማቸው ልሰማ እሻለሁ አለ። ያን ጊዜ ዳዊት መሰንቆውን አዘጋጅቶ የጻድቅ ሞቱ በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው አለ ዳግመኛም ጐለመስሁ አረጀሁም የሚወድቅ ጻድቅን አላየሁም አለ ። ዳዊትም ድምፁን አሣምሮ ዘመረ መሰንቆውንም በስልት መታት ። ያን ጊዜም የቅዱስ አባ ኪሮስ ነፍሱ ወጣች መድኃኒታችንም ተቀብሎ ሳማት ለመላእክት አለቃ ለሚካኤልም ሰጣት ።

እኔ አባ ባውማም የቅዱስ አባ ኪሮስን ሥጋውን ቀበርኩ ከበዓቱም በወጣሁ ጊዜ በረሀው በሰማይ ሠራዊት ተመልቶ አየሁ መድኃኒታችንም የቅዱስ አባ ኪሮስ ሥጋው ባለበት በዓት ላይ መስቀሉን አኑሮ ዘጋት ። ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን ለኔ ሰላምታ ሰጥቶኝ መላእክትና የመላእክት አለቆች በፊቱ እያመሰገኑና እየዘመሩ በታላቅ ክብር ዐረገ ። የቅዱስ አባ ኪሮስን ነፍስ ከመድኃኒታችን ጋራ እንደዚህ አሳረጓት ። እርሷም በተሰጣት ክብር ደስ እያላት ዐረገች ።

እኔም አባ ባውማ በዚያ ቦታ ብቻዬን ቀረሁ ተመልሼም ወደ አባ አሞን በዓት ደረስሁ ። ከዚያም የሦስት ቀን መንገድ ተጉዤ ወደ አባ ስምዖን በዓት ደረስሁ ። ከዚያም ሦስት ቀን ተጉዤ ወደ ቦታዬ ወደ አስቄጥስ ገዳም ደረስ። ለመነኰሳቱም ሁሉ ያየሁትንና የሰማሁትን ሁሉ የቅዱስ አባ ኪሮስን ገድሉን ስለ አባ ሲኖዳም ዕረፍት ትንቢት እንደ ተናገረ ነገርኋቸው።

መነኰሳቱም ሰምተው እጅግ አደነቁ የተመሰገነ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ። እኔ አባ ባውማም የቅዱስ አባ ኪሮስን ገድሉን ጽፌ ለሚያነበውና ለሚሰማው ሁሉ መጽናኛ ይሆን ዘንድ ወደ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉና ወደ ገዳማትም ላክሁ።

  በአባታችን በአባ ኪሮስ ጸሎት ይማረን።

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com