የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
2.58K subscribers
6.08K photos
67 videos
60 files
1.7K links
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Download Telegram
#ደብረ_ታቦር

ነሐሴ ዐሥራ ሦስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅና ክቡር በዓል ነው።

በዚች ቀን መድኃኒታችን ሦስቱን ደቀ መዛሙርቶቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ወደ ታቦር ተራራ ላይ አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ሆነ። ስለ እነርሱም ጌታችን የሰው ልጅ በጌትነቱ ሲመጣ እስከሚያዩት ድረስ በዚህ ከቆሙት መካከል ሞትን የማይቀምሱት አሉ አለ።

ሰዎች ሁሉ እርሱ ለሙሴ ጌታውና ከሞት ያስነሣው እንደሆነ ለኤልያስም ፈጣሪው እንደሆነና ካሳረገበትም ያወረደው እርሱ እንደሆነ ያውቁ ዘንድ እነሆ ከጌታ ከኢየሱስ ጋራ እየተነጋገሩ ሙሴና ኤልያስ ወደርሱ መጡ።

ስለዚህም ጴጥሮስ ጌታችንን እንዲህ አለው አቤቱ በዚህ ትኖር ዘንድ ትወዳለህን ሦስት ሰቀላዎችንም አንድ ላንተ፣ አንድ ለሙሴ፣ አንድ ለኤልያስ እንሠራ ዘንድ።

እንኳን አደረሳችሁ
የወጣት ጉዞ የመጨረሻ ቀን ክፍያ ነሐሴ 23 ነው
ክፍያውን በጽ/ቤት እንዲሁም የሰንበት ት/ቤታችን ልማት ሱቅ ያገኛሉ
👉 ባለትዳር አባላት እፀገነት ጋር ትኬቱ ይገኛል
የዚህ አመት የፍልሰታ ጾም ትርጓሜ በዚህ አበቃ የአመት ሰው ይበለን።

#ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
የዚህ አመት የፍልሰታ ጾም ትርጓሜ በዚህ አበቃ የአመት ሰው ይበለን። #ፍኖተ_ብርሃን_ሰንበት_ት/ቤት
ሱባኤው ከተጀመረበት እስከ ተጠናቀቀበት እስከዛሬዋ እለት ድረስ ደከመኝ፣ ሰለቸኝ ሳትሉ እንደ መተርጉማኑ ሊቃውንት የዓመት ልምዳችንን ለመስማት የራቀብንን አቅርባችሁ እንድንሳተፍ ላደረጋችሁን የICT ክፍል አባላት እግዚአብሔር ድካማችሁን ያስብላችሁ። ቃለ ሕይወት ያሰማችሁ። የሊቃውነወቱን ዋጋ፣ ጸጋ ይስጣችሁ።
የሰንበት ት/ቤታችን ጉዞ እየደረሰ ነው ያልከፈልን አባላት እንክፈል ላልሰሙትም እናሰማ
የጉዞ ቀን #ነሐሴ_30
#ነሐሴ_20
በዚች ቀን መጻሕፍትን የተረጐመ #አባ_ሰላማ አረፈ፣ በከሀዲው ንጉሥ ዳኬዎስ ዘመን የነበሩ ከኤፌሶን ሀገር #ቅዱሳን_ሰባቱ_ደቂቅ አረፉ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ሰላማ_ካልዕ (መተርጉም)
ከተረጐሟቸው መጻሕፍትም፦
#ስንክሳር
#ግብረ_ሕማማት
#ላሃ_ማርያም
#ፊልክስዩስ(መጽሐፈ መነኮሳት)፣ #መጽሐፈ_ግንዘት፣ድርሳን ዘቅዱስ
#ያዕቆብ_ዘሥሩግ. . . ይጠቀሳሉ::

አቡነ ሰላማ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸውና በገዳማዊ ሕይወታቸው ይታወቁ ነበር:: በተጨማሪም በየቦታው እየዞሩ ይናዝዙ: ያጠምቁም ነበር:: በወቅቱ ልክ እንደ ስማቸው ሰላም እንዲሰፍን ይተጉ ነበር:: መሣፍንቱን: ነገሥታቱን እያስታረቁ ለቤተ ክርስቲያን በአንድነት እንዲቆሙ አድርገዋል::

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱሳን_ሰባቱ_ደቂቅ

በዚህችም ቀን በከሀዲው ንጉሥ ዳኬዎስ ዘመን የነበሩ ከኤፌሶን ሀገር ሰባቱ ደቂቅ አረፉ። እሊህም ሰባቱ ደቂቅ ከንጉሥ ዳኬዎስ ጭፍሮች ውስጥ በመዛግብቱ ላይ የሾማቸው ነበሩ። አምልኮ ጣዖትንም በአወጀ ጊዜ ጣዖትን በማምለክ ሥራ አልተሳተፉም። እሊህንም ቅዱሳን በንጉሥ ዘንድ ወነጀሏቸው ይዞም አሠራቸው።

ስማቸውም:- መክሲማኖስ፣ ታሙኪሮስ፣ መርዳዲሞስ፣ ዮሐንስ፣ ቈስጠንጢኖስ፣ አዝሚና ዲዮናስዮ ነው።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የእሊህም ቅዱሳን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን!

ምንጭ
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ነሐሴ እና #ዲያቆን_ዮርዳኖስ_አበበ)
የወጣት አባላት የጉዞ ቀን የመጨረሻ የመክፈያ ቀን ነሐሴ 23 መሆኑን አውቀን ክፍያ እንፈጽም

የክፍያ ቦታ:
1- የሰንበት ት/ቤታችን ጽ/ቤት
2- የሰንበት ት/ቤታችን ልማት ሱቅ
Forwarded from Beti@
🌿በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!🌿

#ምክረ_ሔዋን

🌸በአይነቱ ለየት ያለ ለእህቶች ብቻ የተዘጋጀ የመጀመሪያ ዙር የሁለት ቀን መርሐግብር-🌸

🌺ግቢ ጉባዔያችን ጥቁር አንበሳ ግቢ ጉባዔ በዓመት ሁለት ጊዜ እህቶችን ብቻ በሚመለከቱ ጉዳዮች ልዩ ጉባዔ ያዘጋጃል #ምክረ_ሔዋን

💐መርሃግብሩ ሙሉ በሙሉ እህቶችን ብቻ ያሳትፋል፦
👉ተጋባዥ ዘማሪት
👉ተጋባዥ መምህርት
👉ተጋባዥ እንግዶች
(ቃለ መጠይቅ)
👉ውይይት እና
👉የጣማፍ ኄራኒ አስተማሪ
የሕይወት ታሪክ እና ተዓምር

💐በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅተው ይጠብቁዎታል።
#እንዳያመልጥዎ_ቢቀሩ_ይቆጫሉ

💐ጋባዥዎ፦ልዑል እግዚአብሔር

🧭ቦታ=ጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅ/ሚካኤል
ቤ/ክ ሰ/ት/ት ቤት አዳራሽ⛪️

ቀን #ቅዳሜ_ነሐሴ_22_እና_29
ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ
የአንድ ትኬት ዋጋ :- 5 ብር ብቻ
❤️ ትኬቱን በዕለቱ ሲመጡም ማግኘት ይችላሉ
🌺ቸር ያገናኘን!🙏🌺