የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
2.58K subscribers
6.08K photos
67 videos
60 files
1.7K links
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
Download Telegram
ማስታወቂያ፦

የገድላት እና የድርሳናት ንባብ ከመነበቡ በፊት እና ከተነበበ በኋላ የሚዜም ሲሆን ጸሎት ላይ በቋሚነት አጥንተን የምንሞክረው ይሆናል ዜማዉን ለመያዝ ይረዳ ዘንድ ሰምታችሁ እድትመጡ እናሳስባለን ። የዚህ ዜማ ጥናት የሚጀምረው የፊታችን ረቡዕ በጥቅምት 11 ከጸሎት በኋላ ይሆናል።
​​ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም። የማርቆስ ወንጌል 13 : 33

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ውድ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት ሀገራችን በገባችበት ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት #ቅዱስ_ሲኖዶስ በሁሉም አቢያተ ክርስቲያናት #ሱባኤ እንዲያዝ የወሰነውን ውሳኔ በመቀበል #ለሶስት_ቀናት ማለትም #ዓርብ#ቅዳሜ እና #እሑድ የጸሎት እና የምህላ መርሐግብር በጎላ ቅዱስ ሚካኤል አዳራሽ ተዘጋጅቷል። በመሆኑም ሁላችንም በመገኘት ስለሃገራችን ሰላም ቀርበን እግዚአብሔርን እንለምነው።
#የመርሐግብሩ_ሰዓት
#ዓርብ--------12:00
#ቅዳሜ-------12:00
#እሑድ ------11:00
መተዳደሪያ.pdf
201.7 KB
☝️☝️☝️የሰንበት ት/ቤታችን መተዳደሪያ ደንብ።

ወድ አባሎቻችን

የፊታችን እሁድ ለሚኖረን የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ላይ የምንወያይበት የሰንበት ት/ቤታችን መተዳደሪያ ደንብ ከላይ ተያይዟል። በተለይ በቀይ ቀለም በተጻፉ ጽሑፎች ላይ ትኩረት አድርገን የምንወያይ መሆኑን ከወዲሁ ልናሳውቃችሁ እንወዳለን።

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን።
​​🕯🕯🕯የሀዘን መግለጫ🕯🕯🕯

የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነችው እህታችን #ብሌን_ደገፉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታናለች። የቀብር ሥነ ሥርዓቱም በደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም በ 9:00 ሰዓት የሚፈጸም በመሆኑ የቻልን አባላት ዩኒፎርም በመልበስ ሀዘናችንን እንድንወጣ ስንል እንጠይቃልን።

🕯🕯🕯 የእህታችንን ነፍስ ይማርልን🕯🕯🕯
እነዚህ ምስሎች የቀድሞ ጽ/ቤታችንን ወይም እስካሁን ስንገለገልበት የነበረውን ጽ/ቤት አርብ እለት መልቀቃችንን የሚያመለክቱ ሲሆን
በጽሕፈት ቤቱ የሚገኙ ንብረቶችን ለሦስት ቀናት እስከ ነገ ሰኞ በአደራ የደብሩ ልማት ቢሮ ዝውውር ተደርጎላቸው መቀመጣቸውንና
ከሰሞኑ ወደ አዲሱ መሸጋገሪያ ቢሮ እንደምንገባ ተገልጾ
እንዲሁም ቅዳሜ ጥር 1 ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ የፈረሳና ቦታውን ለግንባታ ምቹ የማድረጊያ (demolishing) ቀን መሆኑን አውቀን ሁላችንም እንድንሳተፍ ይሁን።