ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
675 subscribers
1.76K photos
16 videos
460 links
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27
የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel

©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
Download Telegram
"አቤቱ ጌታዬ ንጉሤ ሆይ ራሴን ጥፋት አስመልክተኝ እንጂ በወንድሜ ላይ እንድፈርድ አታድርገኝ ፡፡"

  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ከአርሲ የኦርቶዶክሳውያን ጭፍጨፋ ለተረፈው ህጻን ህክምና የሚውል የ70ሺ ብር ድጋፍ በማድረግ አጽናንተው ተመልሰዋል።
***

የወላይታ ሀገረስብከት ከአርሲ የኦርቶዶክሳውያን ጭፍጨፋ በታምር ተርፎ በወላይታ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል በህክምና ላይ ለሚገኘው የአራት ዓመት ህጻን የመጀመርያ ዙር የህክምና ወጪ ማስፈጸሚያ የሚውል የ70ሺ ብር የገንዘብ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን

በብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የተመራው የወላይታ ሀገረስብከቱ ልዑክ ህጻኑ ወደ ተኛበት ክርስቲያን ሆስፒታል በመጓዝ ቤተሰቡን በማጽናናት እና ከእዚህ በኃላ እነርሱ ላይ የሚደርሰው ማንኛውም አይነት ችግር ሀገረስብከቱ እንደሚወጣው ጭምር በማሳሰብ ተመልሰዋል።

ይህኝን ታላቅ የበረከት አባት አመስግኑልኝ !
13🥰2👏2
🍂🌿

ወንድምህን አትናቀው

ወዳጄ ሆይ! ክርስቲያን ነህን? እንኪያስ በፍጹም ወንድምህን አትናቀው። እህትህን አትናቃት። ምንም ይሁን ምን ሰው አትናቅ። ይህ የምትንቀው ወንድም በተለይ ክርስቲያን ከሆነ ክርስቶስን እየሰደብከዉ እንደሆን አስተውል።

"እንዴት?"  ያልከኝ እንደሆንም ይህ የምትንቀው ወንድምህ የከደርስቶስ ሕዋስ (ብልት) ኾኗል። የክርስቶስ ሕዋስ ከኾነ ደግሞ እሱን ናቅኸው ማለት ክርቶስን ናቅኸው ማለት ነው።

ወንድምህን የምትንቅ ከሆነም በጲላጦስ አደባባይ ጌታን ከገረፉት፣ እራቁቱን ከሰቀሉት፣ ሐሞትንና ከርቤን ቀላቅለው ከሰጡት፣ በፊቱ ላይም ከተፉበት ሰዎች በምንም አትተናነስም። ስለዘህ ወንድምህን ከመናቅ ተጠንቀቅ።

📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

🍂🌿
👍31
የጌታችን የመድኃኒታችን የመድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት መታሰቢያ በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ይከበራል።


ሐሙስ ጥቅምት 27 አይቀርም።
🥰54👍2
"አንተ በክርስቶስ ከተጠመድክ እርሱ በግል ጉዳዩችህ ይጠመዳል ።"

ቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊም
3
ማስታወቂያ 📢

መንፈሳዊ የ9ኛ ክፍል(ሳልሳይ) ትምህርት መጀመሩን ሰምተዋል?

ከዚህ በፊት በየትኛውም ደብር መንፈሳዊ ኮርስ እስከ 8ኛ ክፍል( ካዕላይ) የተማራቹ 9ኛ ክፍል(ሣልሳይ) በመግባት ትምህርታቹን መከታተል ትችላላችሁ።መንፈሳዊ ትምህርቱን መከታተላችሁን ማስረጃ ማቅረብ ግዴታ ነው።

🕰 ትምህርቱ የሚሰጥበት ሰዓት አርብ ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ከሰዓት 11:30- 1:00 ሰዓት ድረስ።

📍 ትምህርቱ የሚሰጥበት ቦታ በአሰላ ደብረ መ/መ/ዓ/ካቴድራል በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ

👍51
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት pinned «ማስታወቂያ 📢 መንፈሳዊ የ9ኛ ክፍል(ሳልሳይ) ትምህርት መጀመሩን ሰምተዋል? ከዚህ በፊት በየትኛውም ደብር መንፈሳዊ ኮርስ እስከ 8ኛ ክፍል( ካዕላይ) የተማራቹ 9ኛ ክፍል(ሣልሳይ) በመግባት ትምህርታቹን መከታተል ትችላላችሁ።መንፈሳዊ ትምህርቱን መከታተላችሁን ማስረጃ ማቅረብ ግዴታ ነው። 🕰 ትምህርቱ የሚሰጥበት ሰዓት አርብ ፣ ቅዳሜ እና እሁድ ከሰዓት 11:30…»
"በሥራና በእውነት እንጂ በቃልና በአንደበት እንዋደድ።"
  
  1ኛ ዮሐ 3÷18




መንፈሳዊ ትምህርት መማር የምትፈልጉ:-

በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በፍኖተ ወንጌል ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ በመገኘት መመዝገብ ትችላላችሁ።
እንኳን ለ2018ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ!

"አንተ ግን በተማርበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር!" ፪ኛ ጢሞ ፫፥፲፬


እነሆ ዘንድሮም እንደአምናው በሰ/ት/ቤቱ የሚሰጠው ተከታታይ መንፈሳዊ ትምርት ለመስጠት ዝግጅታችንን ጨርሰን ተማሪዎችን በመመዝገብ ላይ እንገኛል።
በሁለቱም ቋንቋዎች በአፋን ኦሮሞና በአማርኛ ከ1-9ኛ ክፍል ነባርና አዲስ ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅታችንን ጨርሰናል ይምጡና ይመዝገቡ ይማሩ!

የመመዝገቢያ ቦታ

👉ዘወትር ቀን ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ በአውደ ምህረት፣ በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽና ቤተ መጽሐፍት

👉ሁሌም በስራ ሰዓት በሰ/ት/ቤቱ ነዋየ ቅዱሳት መሸጫ

👉 በፈለጉት ሰዓት ባሉበት ሆነው በሚከተለው ሊንክ በመግባት በonline መመዝገብ ይችላሉ( https://forms.gle/9RDHjM9H9Ymy924R6 )

ለበለጠ መረጃ

👉0968903347
👉0998646565
👉0938117125
1
‘’አልጋ መግዛት ለምትፈልጉ ኑ አልጋ ላሳያችሁ! ይህ አልጋ የተራ ሰው ወይም የወታደር አልጋ አይደለም፡፡ የንጉሥ አልጋ ነው፡፡ ንጉሥም ቢባል ተራ ንጉሥ ሳይሆን በዓለም ሁሉ የሚዘመርለት ታላቅ ንጉሥ አልጋ ነው፡፡ የንጉሥ ዳዊትን አልጋ ላሳያችሁ፡፡ ይህ አልጋ ከወርቅ ወይም ከአልማዝ ወይም ከከበሩ ድንጋዮች የተሠራ አይደለም፡፡ ይህ አልጋ ከዕንባ የተሠራ አልጋ ነው፡፡ እርሱ ‘ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ ፤ በዕንባዬም መኝታዬን አርሳለሁ’ ብሏልና’’

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
8
"
እነሆ በፊትህ የተከፈተች ደጅ ሰጥቼሀለሁ ሊዘጋት የሚችል የለም"ራዕ 3:7

"በእርግጥም እግዚአብሔር ለአንድ ሰው በርን በከፈተለት ጊዜ ሊዘጋበት የሚችል ማንም የለም።በመሆኑም እግዚአብሔር እንዲከፍትልህ ብትሻ የሚያስፈልግህ ነገር ቢኖር መጸለይ ነው። ስለዚህ ፕሮጀክትህን ሁሉ ዕቅድህንም ሁሉ ልትጀምር በፈለግህ ጊዜ ይህንን ጸሎት አድርስ።"

አቡነ ሺኖዳ


ኑ አብረን እናንግስ
መድኃኔዓለም (በዓለ ስቅለት) ጥቅምት ፳፯ ለመድኃኔ ዓለም ዓመታዊ ክብረ በዓል እንኳን አደረሰን፤ አደረሳችሁ!!!
8🥰4🙏1