የተሰናበተን ልቡ የቆረጠ.....
እርቆ የሄደ ሌላ የወደደ
መማፀን ከንቱ ነው ቀኑ ከረፈደ ።
ምን ቢነጠፉለት
ልብን ቢከፍቱለት
ከቶ አይታየውም ሌላ የወደደ
ይቅርታ ምኑ ነው ሞቆ ለበረደ ።
እናም.......
ቁልቁል ለረገጡት ግዜን ተንተርሰው
ምንድን ነው መንሰፍሰፍ.....
ደግሞ ተመልሰው
ምንድን ነው ማልቀሱ....
በድለው ለሸኙት
ምንድን ነው ይቅርታ..
በናፍቆት ለቀጡት ???
እናም.....
የተሰናበተ ልቡ የቆረጠ..
እርቆ የሄደ ሌላ የወደደ
መማፀን ከንቱ ነው ቀኑ ከረፈደ ።
ፍቃዱ ግርማ /ዘ-በኩር/
t.me/fikee21
እርቆ የሄደ ሌላ የወደደ
መማፀን ከንቱ ነው ቀኑ ከረፈደ ።
ምን ቢነጠፉለት
ልብን ቢከፍቱለት
ከቶ አይታየውም ሌላ የወደደ
ይቅርታ ምኑ ነው ሞቆ ለበረደ ።
እናም.......
ቁልቁል ለረገጡት ግዜን ተንተርሰው
ምንድን ነው መንሰፍሰፍ.....
ደግሞ ተመልሰው
ምንድን ነው ማልቀሱ....
በድለው ለሸኙት
ምንድን ነው ይቅርታ..
በናፍቆት ለቀጡት ???
እናም.....
የተሰናበተ ልቡ የቆረጠ..
እርቆ የሄደ ሌላ የወደደ
መማፀን ከንቱ ነው ቀኑ ከረፈደ ።
ፍቃዱ ግርማ /ዘ-በኩር/
t.me/fikee21
❤8👏3
Forwarded from የግጥሜ አሻራ....✍ (Bitseat ❤)
እንደ ቤት...እንደልብስ...እንደ ራስ
እንደ ሀገር
ቢቻልማ ኖሮ ትላንትን መቀየር
ካገኘሁሽ ቦታ ትቼሽ አልፍ ነበር
✍ብፅእት ስዩም
እንደ ሀገር
ቢቻልማ ኖሮ ትላንትን መቀየር
ካገኘሁሽ ቦታ ትቼሽ አልፍ ነበር
✍ብፅእት ስዩም
❤15❤🔥2👍1
መንፈሳዊ ሰው የእግዚአብሔር አምሳል ነው ።
መንፈሳዊ ስው ብርቱ ነው ።
መንፈሳዊ ሰው ጠንካራ ሞራል አለው ።
መንፈሳዊ ስው ልቡ ከእግዚአብሔር ጋር ነው ።
መንፈሳዊ ሰው ከጉዳዮቹ በፊት እግዚአብሔርን ያስቀድማል ።
መንፈሳዊ ሰው በመታዘዝ እግዚአብሔርን ያስቀድማል ።
መንፈሳዊ ስው ለእግዚአብሔርም ለሰዎቾም ይታዘዛል ።
መንፍሳዊ ሰው አንዱ ችሎታው ጥልቀት ነው ።
መንፈሳዊ ሰው ልቡ በእግዚአብሔር ፊት የቀና ነው ።
'' ቃልህ ለጉሮሮዬ ጣፋጭ ነው ፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ '' መዝ 118፡103 ።
ፍቃዱ ግርማ /ዘ-በኩር/
t.me/fikee21
መንፈሳዊ ስው ብርቱ ነው ።
መንፈሳዊ ሰው ጠንካራ ሞራል አለው ።
መንፈሳዊ ስው ልቡ ከእግዚአብሔር ጋር ነው ።
መንፈሳዊ ሰው ከጉዳዮቹ በፊት እግዚአብሔርን ያስቀድማል ።
መንፈሳዊ ሰው በመታዘዝ እግዚአብሔርን ያስቀድማል ።
መንፈሳዊ ስው ለእግዚአብሔርም ለሰዎቾም ይታዘዛል ።
መንፍሳዊ ሰው አንዱ ችሎታው ጥልቀት ነው ።
መንፈሳዊ ሰው ልቡ በእግዚአብሔር ፊት የቀና ነው ።
'' ቃልህ ለጉሮሮዬ ጣፋጭ ነው ፤ ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ '' መዝ 118፡103 ።
ፍቃዱ ግርማ /ዘ-በኩር/
t.me/fikee21
❤14💯1
እሳት ወይ አበባ
ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
ወንድ ብቻውን ነው እሚያለቅስ
ከወዳጅ ዘመድ ርቆ
አንጀቱን በአንጀቱ ታጥቆ
ተሸሸጎ ተገልሎ ፥ ተሸማቆ ተሸምቆ
ከቤተ - ሰው ተደብቆ
መሽቶ የማታ ማታ ነው ፥ ሌት ነው የወንድ
ልጅ እንባው
ብቻውን ነው የሚፈታው .......
ብቻውን ነው የሚረታው .......
ችሎ ፥ ወጦ ፥ ተጨብጦ ፥ ተማምጦ
ተጣጥሮ
በሲቃ ግት ተወጥሮ
እንደ ደመና ተቋጥሮ
እውስጥ አንጀቱ ተቀብሮ ....
መሽቶ ፥ ረፍዶ ፥ ጀምበር ጠልቆ
የጨለማ ድባብ ወድቆ
በእንቅልፍ ጥላ ሲከበብ ፥ በዝምታ
ሲዋጥ አገር
ፍጡር ሁሉ ተሰለምልሞ ፥ ብቸኝነት
ብቻ ሲቀር ......
የኃላ የኃላ ማታ
ምድር አገሩ በእፎይታ
አይኑን በእንቅልፍ ሲያስፈታ
ሁሉ በእረፍት ዓለም ርቆ ፥ ብቸኝነት
ብቻ ሲቀርብ
ያኔ ነው ወንድ አይኑ የሚረጥብ
የብቻ ፥ እንባ አይኑ የሚረጥብ ።
.......................
t.me/fikee21
t.me/fikee21
t.me/fikee21
ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
ወንድ ብቻውን ነው እሚያለቅስ
ከወዳጅ ዘመድ ርቆ
አንጀቱን በአንጀቱ ታጥቆ
ተሸሸጎ ተገልሎ ፥ ተሸማቆ ተሸምቆ
ከቤተ - ሰው ተደብቆ
መሽቶ የማታ ማታ ነው ፥ ሌት ነው የወንድ
ልጅ እንባው
ብቻውን ነው የሚፈታው .......
ብቻውን ነው የሚረታው .......
ችሎ ፥ ወጦ ፥ ተጨብጦ ፥ ተማምጦ
ተጣጥሮ
በሲቃ ግት ተወጥሮ
እንደ ደመና ተቋጥሮ
እውስጥ አንጀቱ ተቀብሮ ....
መሽቶ ፥ ረፍዶ ፥ ጀምበር ጠልቆ
የጨለማ ድባብ ወድቆ
በእንቅልፍ ጥላ ሲከበብ ፥ በዝምታ
ሲዋጥ አገር
ፍጡር ሁሉ ተሰለምልሞ ፥ ብቸኝነት
ብቻ ሲቀር ......
የኃላ የኃላ ማታ
ምድር አገሩ በእፎይታ
አይኑን በእንቅልፍ ሲያስፈታ
ሁሉ በእረፍት ዓለም ርቆ ፥ ብቸኝነት
ብቻ ሲቀርብ
ያኔ ነው ወንድ አይኑ የሚረጥብ
የብቻ ፥ እንባ አይኑ የሚረጥብ ።
.......................
t.me/fikee21
t.me/fikee21
t.me/fikee21
❤12🙏1
❤6
ሰማይ ጠቀስ ጥፋት ቤቴን ስለሞላው
አምላኬ ንገረኝ.... ?
እኔ ግን አንተ ጋር ሚዛኔ ስንት ነው ?
እየዘነጋሁኝ...
ገነትን ታክል ቤት አንተን ያክል አባት
እኔኮ ድፍረቴ...
መጥቼ እቆማለሁ ደግሜ ካንተ ፊት
እባክህን አምላክ እባክህን ጌታ
ልቤን ገስፅልኝ እንዳላመነታ
እንዳላፈገፍግ ከትልቁ ክብር
አግዘኝ ልከተል የመስቀሉን ፍቅር ።
ደግፍኝ ልሻገር ልላቀቅ ከኃጢያት
ያቺን መሪር ግዛት ሶዖልን ልልፋት
እቀፈኝ በክንድህ ለደቂቃ አልውጣ
አንተው ያዘኝ ፣
አለም መቼም አታዋጣ ።
እረ አንተው ተቆጣኝ
እረ አንተው ግረፈኝ
እረ አንተው ገስፀኝ
እረ አንተው መልሰኝ
እኔማ አልሆነኝም......
የጀመርኩት መንገድ ጭራሽ እያጠፋኝ።
ሰማይ ጠቀስ ጥፋት ቤቴን ስለሞላው
አምላኬ ንገረኝ... ?
እኔ ግን አንተ ጋር ሚዛኔ ስንት ነው?
ስንት ነው ተመኑ ለነብሴ የደከምኩት
ስንቴ ነው በአንተ ስም አለምን የጣልኳት ???
ስንት ነው የሚል ቃል እኔ እማበዛብህ
ተመኔን ሚዛኔን የደጋገምኩብህ
ነብሴ ተጨናንቃ ፍፁም ሰላመመኝ
መላ ሲጠፋኝ ነው...
እኝኝ የምልብህ አትቀየምብኝ ።
እና
ሰማይ ጠቀስ ጥፋት ቤቴን ስለሞላው
ንገረኝ አምላኬ... ?
እኔ ግን አንተ ጋር ሚዛኔ ስንት ነው ።
ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር /
t.me/fikee21
t.me/fikee21
t.me/fikee21
አምላኬ ንገረኝ.... ?
እኔ ግን አንተ ጋር ሚዛኔ ስንት ነው ?
እየዘነጋሁኝ...
ገነትን ታክል ቤት አንተን ያክል አባት
እኔኮ ድፍረቴ...
መጥቼ እቆማለሁ ደግሜ ካንተ ፊት
እባክህን አምላክ እባክህን ጌታ
ልቤን ገስፅልኝ እንዳላመነታ
እንዳላፈገፍግ ከትልቁ ክብር
አግዘኝ ልከተል የመስቀሉን ፍቅር ።
ደግፍኝ ልሻገር ልላቀቅ ከኃጢያት
ያቺን መሪር ግዛት ሶዖልን ልልፋት
እቀፈኝ በክንድህ ለደቂቃ አልውጣ
አንተው ያዘኝ ፣
አለም መቼም አታዋጣ ።
እረ አንተው ተቆጣኝ
እረ አንተው ግረፈኝ
እረ አንተው ገስፀኝ
እረ አንተው መልሰኝ
እኔማ አልሆነኝም......
የጀመርኩት መንገድ ጭራሽ እያጠፋኝ።
ሰማይ ጠቀስ ጥፋት ቤቴን ስለሞላው
አምላኬ ንገረኝ... ?
እኔ ግን አንተ ጋር ሚዛኔ ስንት ነው?
ስንት ነው ተመኑ ለነብሴ የደከምኩት
ስንቴ ነው በአንተ ስም አለምን የጣልኳት ???
ስንት ነው የሚል ቃል እኔ እማበዛብህ
ተመኔን ሚዛኔን የደጋገምኩብህ
ነብሴ ተጨናንቃ ፍፁም ሰላመመኝ
መላ ሲጠፋኝ ነው...
እኝኝ የምልብህ አትቀየምብኝ ።
እና
ሰማይ ጠቀስ ጥፋት ቤቴን ስለሞላው
ንገረኝ አምላኬ... ?
እኔ ግን አንተ ጋር ሚዛኔ ስንት ነው ።
ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር /
t.me/fikee21
t.me/fikee21
t.me/fikee21
👌8❤7👏2
ለመጣ ለሄደው ልቡ ከባከነ
እግሩ መቆሚያ አጥቶ ሁሌ ከኳተነ
አእምሮ ሀሳቡ ከጠፋበት ውሉ
ማንም ሰው ሳይነካው፣
ደርሶ ካስቀየመው የገዛ አመሉ
በግርድፍ ፍርዳችን እብድ ነው ሳንለው
እንዲህ አይነቱን ሰው
በፍጥነት እንርዳው ።
ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር /
t.me/fikee21
እግሩ መቆሚያ አጥቶ ሁሌ ከኳተነ
አእምሮ ሀሳቡ ከጠፋበት ውሉ
ማንም ሰው ሳይነካው፣
ደርሶ ካስቀየመው የገዛ አመሉ
በግርድፍ ፍርዳችን እብድ ነው ሳንለው
እንዲህ አይነቱን ሰው
በፍጥነት እንርዳው ።
ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር /
t.me/fikee21
❤3👏2🤝1
❤7🙏2
አታውቀውምና ፣
ዬት እንደሚያደርስህ የሕይወትህ መስመር
ቀድመህ በማንም ለይ ጣትህን አትቀስር
እናም....
ካለሆነ ለመውደድ
አትቸኩል ለመፍረድ ።
ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር/
t.me/fikee21
t.me/fikee21
t.me/fikee21
ዬት እንደሚያደርስህ የሕይወትህ መስመር
ቀድመህ በማንም ለይ ጣትህን አትቀስር
እናም....
ካለሆነ ለመውደድ
አትቸኩል ለመፍረድ ።
ፍቃዱ ግርማ / ዘ-በኩር/
t.me/fikee21
t.me/fikee21
t.me/fikee21
❤2👏2
በነብስሽ ሰይፍ ሲያልፍ
አይሁድ ተሰብስበው..
ተወዳጁ ልጅሽ በአደባባይ ሲገረፍ
የጅራፉ ብዛት ለቁጥር የጠፋው
የጀርባው ግርፋት ልብሽን ሲያደማው
ተጠማሁ ሲል ጌታ በሚያሳዝን ልሳን
እመቤቴ ማርያም ምን ቃል ወጥቶሽ ይሆን
ምን ተናግረሽ ይሆን
እንዴት ብለሽ ይሆን
ባህር ለይ የቆሙ....
ዘለላ እግሮቹ በችንካር ሲመቱ
ማንም ሰው ሳይሰማሽ ምን አልሽ አዛኝቱ ??
ፍቃዱ ግርማ / ዘ - በኩር /
t.me/fikee21
t.me/fikee21
አይሁድ ተሰብስበው..
ተወዳጁ ልጅሽ በአደባባይ ሲገረፍ
የጅራፉ ብዛት ለቁጥር የጠፋው
የጀርባው ግርፋት ልብሽን ሲያደማው
ተጠማሁ ሲል ጌታ በሚያሳዝን ልሳን
እመቤቴ ማርያም ምን ቃል ወጥቶሽ ይሆን
ምን ተናግረሽ ይሆን
እንዴት ብለሽ ይሆን
ባህር ለይ የቆሙ....
ዘለላ እግሮቹ በችንካር ሲመቱ
ማንም ሰው ሳይሰማሽ ምን አልሽ አዛኝቱ ??
ፍቃዱ ግርማ / ዘ - በኩር /
t.me/fikee21
t.me/fikee21
❤10
❤6
❤8