ፍልስፍና እና የፍልስፍና አባባሎች
4.59K subscribers
21 photos
2 links
የፍልስፍና እይታዎች
Download Telegram
🌿ስጋችሁ የነፍሳችሁ ማደርያ ነውና እንዳታቆሽሹት ፤
#ነፍሳችሁም የስጋችሁ ማእከል ናትና አታቆሽሿት !!ይህንን ምሳሌ ልብ በሉ ፦ስጋችሁን ልክ እንደ ብርጭቆ ቁጠሩ ፤ ነፍሳችሁን ደግሞ አንደ ውሃ በቆሻሻ ብርጭቆ ንፁህ ውሃ ብትጨምሩ ዞሮ ዞሮ ውሃው መበከሉ (መቆሸሹ) አይቀርም ፣ በንፁህ ብርጭቆ የቆሸሸ (የተበከለ) ውሃን ብትጨምሩ ዞሮ ዞሮ የተሟላ ንፁህነት አይገኝም። ስለዚህ በነፍሳችሁም_በስጋችሁም_ንፁህ_ሁኑ🌿
🌿ኦሾ/Osho
ሃይማኖት የፍልስፍና አስተሳሰብ ነው
🌿
ሃይማኖት በሕይወት ውስጥ አንድን አስተሳሰብ ብቻ መፍትሔ አድርጎ በእምነት መቀበል ነው። ሳይንስ ችግርን ለመፍታት ሃይማኖትን ሊጠቀም ይችላል። ሃይማኖት ችግሩን ከፈታ ይሄም ሳይንስ ነው። ካልፈታው ሌላ አስተሳሰብ መጠቀምም ሳይንስ ነው። ሃይማኖት ግን ችግርን ለመፍታት ሳይንስን አይጠቀምም። ምክንያቱም ለሃይማኖት ብዙ ችግሮችን ለመፍታት ከአንድ አስተሳሰብ ውጪ መጠቀም ሀጥያት በመሆኑ ነው ።

ሃይማኖት የፍልስፍና አስተሳሰብ ነው። ነገር ግን ፍልስፍና ውስጥ ካሉ ሌሎች አስተሳሰቦች የሚለይበት ምክንያት አስተሳሰቡ ትክክል በመሆኑ ሳይሆን ብዙ የተሳሳቱ ሰዎች ትክክል አድርገው ስለተቀበሉት ነው። ለዚህ ደግሞ ዋናው መነሻ ሌሎች ትክክል ሊሆኑ የሚችሉ የአስተሳሰብ አማራጮች ከተሳሳቱ ሰዎች ጋር በመነጣጠል ነው። ብዙ የአስተሳሰብ አማራጮችን በመዝጋት አንድ አስተሳሰብ ብቻ በእምነት መቀበል ካለማሰብ የሚመጣ ችግር ነው። ማሰብ ቢኖር ለሌሎች አስተሳሰቦች እኩል እድል ይሰጥ ነበር። አንድ አስተሳሰብ ሃይማኖት የሚሆነው ስለሌሎች አስተሳሰቦች ማሰብ አቁመህ አንዱን አስተሳሰብ ብቻ በእምነት ስትቀበለው ነው።

ምንጭ ፦ "ሰው መሆን"
እምነት ልክ እንደ ጭንብል ነው የራስህን ኦርጅናል ፊት እየደበቅክ ነው ማመን ሽግግር ነው ጥርጣሬ ምርምር ነው እና ማመን ደግሞ የምርምሩ እርካታ ነው ጥርጣሬ ጥያቄ ሲሆን ማመን መልስ ነው።
አማኝ በፍፁም አይንቀሳቀስም አንድ ጊዜ አምኗል ለዚያ ነው በቢሊዩን የሚቆጠሩ ሰዎች በቤተ ክርስትያኖች ፤ ቤተ መቅደሶች ፤ መስኪዶች ፤ ሙክራቦች ውስጥ የሚያመልኩት ዳሩ ግን አምልኳቸው ከእምነት የመነጨ ነው። አምልኳቸው ከእምነት የመነጨ በመሆኑ እኝህ በቢሊዩን የሚቆጠሩ ሰዎች ሀይማኖተኞች ሳይሆኑ ቀርተዋል። እግዚሀብሄርን አይሹም አግዚሀብሄርን አይፈልጉም እነሱ እግዚሀብሄርን ተቀብለዋል።
እየሱስን ተቀብለናል ይላሉ አቀባበላቸው ግን ደካማ ነው እየሱስን ለማግኘት አልደከሙም የሱን ኑሮ የሱን ስቃይ እሱ ባለፈበት መንገድ ሊጓዙ አይፈልጉም በህይወት ውስጥ ዋጋ የማይጠይቅ ምንም ነነር የለም ልትዋጋ ልትታገል ይገባል እናም ታገኘወለህ ።
ኦሾ/osho
ምንጭ:- ከፍስሀ ጋር መወለድ
"ለሰው ልጅ ከተነገሩት ውሸቶች መሀል እጅግ አደገኞቹ "ስልጡን ነህ" እና እንዲሁም "ሁሉም ሰብአዊ ፍጡር እኩል ነው" የሚባሉት አስተሳሰቦች ናቸው። ምክንያቱም በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ስልጣኔ አለ ብለው ኖረው ቢሞቱም ፣ የሰው ልጅ ግን ገና አልሰለጠነም።
በተጨማሪም ይህ እኩልነት የሚባለው ነገር መሰረተ
ቢስ- ተረት ነው። ሌላው ቀርቶ በማንኛውም መንገድ ፣ በማንኛውም መለኪያ ሁለት ሰዎች እንኳን እኩል ሊሆን አይችሉም።"
#ኦሾ/Osho
ራስን መሆን
ትርጉም:- ደመላሽ ጥላሁን
#ሱፊዎች #ሲመክሩ………

አንድ ቀን ነስሩዲን በመንገድ ላይ ሲሄዱ ፊቱ በሀዘን የተኮማተረ አንድ ሰው ትንሽ ከረጢት አንጠልጥሎ ይመለከታል።

በዚህ ጊዜ ነስሩዲን ወደ ሰውየው ተጠግቶ "ምን ሆነሃል"ሲል ይጠይቀዋል።
ሰውየውም"በዚህ ዓለም ላይ የደከምኩበት ነገር በሙሉ በዚች ከረጢት ብቻ ሆነና አዝኛለሁ።
ነስሩዲንም "እንዴት ያሳዝናል"በማለት የሚያፅናናው መስሎ ከረጢቱን ነጥቆት ሮጠ።

በምድር ላይ አለኝ የሚለውን ነገር በሙሉ
የተነጠቀውም ሰውዬ እሪታውን እያቀለጠ
ነስሩዲንን ተከተለው።
ጥቂት ርቀት እንደተጓዙም ነስሩዲን እየሳቀ ቆሞ ጠበቀው።
ሰውየው ከናስሩዲን አጠገብ እንደደረሰም ከረጢቱን ነጥቆ በእቅፎ ይዞ እየተደሰተ"ከረጢቴ! ከረጢቴ! የጠፋችብኝ መስሎኝ ደንግጨ ነበር" አለ።
ናስሩዲንም መሳቁን ሳያቋርጥ:-

"አየህ!የሀዘንህ ምንጭ በእጅህ የያዝከው
ነገር ትንሽ በመሆኑ አልነበረም።
ነገር ግን የሌላውን ሰው ብዙ ነገር በመመልከት ነበር በማለት ጥሎት ሄደ"።
ለዚህ ነው ሱፊዎች ሲመክሩ:-

👉"በህይወት ስጦታ በቃኝ ማለት የደስታ ሁሉ ምንጭ ነው"የሚሉን
#በአዳዲስ ህንፃዎች ውስጥ አሮጌ ችግሮቻችንን
ተሸክመን ከትላንት የተሻልን ይመስለናል...!!"ሰው መሆንን ለማወቅ የሚኬድበት ትግል፣ሁሌም ከብርድ ለመሸሽ ከለላና ጥላ፣ እንዲሁም ሽፋን እንደመፈለግ ነው ። ለዚህም ማሳያው
የአብዛኛው ሰው ቋሚ ፍላጎት ህይወትን"መለወጥ" ነው ። ሁሉም ሰው "ራሴን ለውጬ" ፣"ቤተሰቤን ለውጬ" ፣ መለወጥ አለብኝ....። " ፣"ቤተሰቤን ልለውጥ" ፣ "ሃይማኖቴን ልለውጥ" እያለ ይኖራል ። በዚህ ሁሉ ለውጥ ውስጥ
እያንዳንዱ አዲስ ለውጥ አሮጌ ህይወት እየሆነ እንደ ልብስ ከመደረብ ውጪ እውነተኛ ለውጥ ሳይሆን ይቀራል ። እውነተኛ ለውጥ የማይኖረው ሰው ስላልጣረና ስላልሞከረ ሳይሆን ለውጥ ሂደት እንጂ መድረሻ ባለመሆኑ ነው ። በአንድ ለውጥ መርጋት በሰው ተፈጥሮ ውስጥ ከማይቻሉት ሀቆች አንዱ ነው ።በመሆኑም ሰው ቢለውጥ፣ ቢለውጥ ከደረባቸው የማንነት አልባሳት አንዱን ወይም ሌላውን እንጂ " ሰው...ነቱን " ሊሆን አይችልም ። በኑሮው ግን"ሰው...ነቱን" ሳይሆን ፣ ከድርብ አልባሳት አንዱን እና ለጊዜው የተመቸውን ሲሆን ሃብቱን፣ ጉልበቱንና ወገኑን፣ ሳይሆን ሃይማኖቱንና ብሄሩን፣ አልፎ አልፎም ሃገሩን እና የመሳሰለውን እየመዘዘ፤ የተወደደም፣ የተጠላም፣ የተከበረም፣ የተደፈረም፣የተፈራም፣ የተናቀም እየመሰለው ይኖራል ።
❖አለመኖር..
❖ደራሲ ፦ ዶ/ር ዳዊት ወንድማገኝ
#እውነት እርቃኑን ነው። እናንተን ለማሳመን እውነት መኖሩ በራሱ በቂ ነው። እውነት በራሱ ተቀባይነት ከሌለው እና በክርክር ላይ የሚመሰረት ከሆነ እውነት አይደለም። በክሮክሮች ሊለወጡ ይችላል። ከእናነተ የበለጠ ማሳመኛ ሃሳብ ያለው ሰው ያጋጠማችሁ ጊዜ ሊለወጡ ይችላሉ። ትልቅ ዋጋ ያለው ነገር ክርክር ሳይሆን /ልምድ/ተሞክሮ ነው።
ተሞክሮ ክርክር አያስፈልገውም። ተሞክሮ የራሱ መሠረት ነው። ወደ ውስጥ የሚጠልቅ ነው። ውስጣችሁን ስታገኙ በውስጣችሁ በሺ የሚቆጠሩ መልካም መዓዛ ያላቸው ፅጌረዳ አበቦች የፈነዱ ይመስላል የብርሀን፣ የውበትና የደስታ እርካታን ታገኛላችሁ።
ኦሾ/Osho
#አንዳንድ_ሀሳቦች

◉ዘር ( ተዘርቶ ሚበቅለው እንደሆነ ይታወቅልኝ )
ዘር ሲበቅል ድምፅ የለውም ግን ዛፍ ሆኖ ሲወድቅ ትልቅ ድምፅ ያሰማል ብዙ ግዜ ውድቀትም ይህው ነው ጩህት አይጠፋውም ፍጥረት ግን ምን ግዜም በዝምታ ውስጥ ነው።
ይህ የዝምታ ሀይልና በዝምታ ማደግ ይባላል።
-ኮንፊሺየስ


◉ልብህ ከፈጣሪ ካልተገናኘ የቱንም ያህል ቃላት በፊቱ ብትደረድር ከንቱ ድካም ነው ። እንዲህ አይነቱ ሰውም ከቤቱ ውስጥ ቆሞ በሩን የሚያንኳኳ ሰውን ይመስላል!!
ሱፊዝም


◉በሕይወት መንገድ ላይ ስትጓዝ አዳልጦህ ብትወድቅና #ተስፋ_ብትቆርጥ ፤ የተስፋ መቁረጥህ ምክንያት የስጋህ ሳይሆን #የእምነትህ_መውደቅ መሆኑን አስተውል!
ከሱፊዝም
አንድ ቀን ሙላ ነስሩዲን አዘውትረው ቡና በሚጠጡበት ስፍራ ከአንድ ሐኪምና መምህር ጓደኞቹ ጋር ወግ ይጀምራሉ ። የወጋቸው ርእስ ደግሞ "ሞት"ነበር ።
ሀኪሙ " እኔ ከሞትኩ በኀላ በሳጥኔ ውስጥ ሆኜ ሰዎች ከደጅ የሚነጋገሩትን አንድ ጊዜ የመስማት እድል ባገኝ "ታላቅ ሐኪም ፣ቤተሰቡን አፍቃሪ ነበር" እያሉ ሲመሰክሩልኝ መስማት እሻለሁ ።" አለ ።
መምህሩም " እኔ ደግሞ ታላቅ መምህር እንደነበርኩና በትውልድ ውስጥ ታላላቅ ሰዎችን እንዳፈራሁ ፣ እንዲሁም
ትዳሬን አፍቃሪ እንደነበርኩ ሲናገሩ ብሰማ ደስ ይለኛል " አለ ።
ሙላ ነስሩዲን የሁለቱንም አድምጦ " እኔ ግን " ተመልከቱ ! ይንቀሳቀሳል እኮ ..!" በማለት ሰዎች ወደ ሳጥኑ እየጠቆሙ ሲያወሩ መስማት ምኞቴ ነው " አለ

#ተዓምራትና ጣዖታት
ከጲላጦስ
(ኀይለጊዮርጊ ማሞ)
🌘የህይወት ለውጦችን ከመቃወም ይልቅ ራስን አስተጋብሮ መራመድ ጥበብ ነው ። ሕይወት ካንተ ውጪ ሳትሆን ከእናንተ ጋር ትሁን፡፡

💫 ራስህን ስጋት አታድርግ፡፡ መልካም ሰው ማንንም አያማርርም ። ያለፍቅር ሕይወት ዋጋ የለውም ፡፡ ፍቅር የሕይወት ውሃ ነው ፣ ፍቅርን የሚያቅ ሰው የነፍስ መብራት ነው። ሁሉም ነገር እና ሁሉም ሰው ከማይታዩ ብዙ ህብረቶች ጋር የተሳሰረ ነው።

☀️ምን ዓይነት ፍቅርን መፈለግ እንዳለብህ አትጠይቅ…የምስራቃዊ ወይም ምዕራባዊ እያልክ ክፍፍል አትፍጠር፣ ያንተ ክፍፍሎች ወደ ብዙ መከፋፈል ከማምራት በቀር አንተን አይቀይሩህም፡፡ ፍቅር ስያሜ የለውም ፣ ትርጓሜ የለውም፡፡ንፁህ እና ቀላል ነው።

💫የሰዎችን ልብ አትስበር ፡፡ከአንተ ይልቅ ደካማ እንደሆኑ አርገህ ቁልቁል አትመልከት፡፡በአንደኛው የዓለም ክፍል ውስጥ ያለ ሀዘን መላውን ዓለም ሊያሰቃይ ይችላል ፣በዛው ልክ ደግሞ የአንድ ሰው ደስታ እና ፈገግታ መላውን ዓለም ፈገግ ሊያደርገው ይችላል።

☀️ አብዛኛዎቹ ግጭቶች እና ውጥረቶች በቋንቋ ምክንያት የሚከሰቱ ናቸው።ለቃላቶች በጣም ትኩረት አትስጥ ፣ በፍቅር ሀገር ውስጥ ቋንቋ የራሱ የሆነ ቦታ የለውም።
ፍቅር ውብ ዝምታ ነው ፡፡


የሱፊው ሊቅ ሸምስ ታብሪዝ (Sufi Master Shams Tabrizi )
ፖለቲከኛ የስነልቦናና የመንፈስ ታማሚ ነው። በአብዛኛው ፖለቲከኞች ጤናማ ተክለ ቁመና ይኖራቸዋል። አካላቸው እንከን አልባ ሲሆን ዋናው ሸክም የሚያርፍበት አእምሮአቸው ግን ህመምተኛ ነው። አእምሮአዊ ህመማቸው ሲበዛ ደሞ የመንፈስ ታማሚ ይሆናሉ። የህመሙ አይነት የዝቅተኝነት ( የበታችነት) ስሜት ወይም Inferiority complex የሚባለው አይነት ነው።

የስልጣን ጥማት ያለበት ማንም ሰው የበታችበት ስሜት ተጠቂ ነው። በውስጡ የሚሰማው ዋጋ ቢስነትና ከሌሎች ማነስ ብቻ ይሆናል። በተለያዩ መንገዶች ከሌሎች እናንሳለን። ይህ ማለት ግን የበታችነት ስሜት ሊሰማን የግድ ነው ማለት አይደለም። ፖለቲካኛ ግን የበታችነት ደዌ ተጠቂ ነው። ራሱን ምጡቅ ከሆኑ የሰው ልጆች ጋር ሊያነጻጽር መሞከሩ የበታችነት እንዲሰማው ያደርገዋል። ራሳችሁን ከአንስታይንና ሲግመንድ ፍሩድ ጋር የምታፎካክሩ ከሆነ ዋጋ ቢስነትና ትንሽነት ሊሰማችሁ ይችላል።
ይህ የዋጋቢስነት ስሜት በሁለት መንገዶች ይወገዳል። አንዱ ሀይማኖት ሲሆን ሌላው ደግሞ ፖለቲካ ነው።
ፖለቲካ ይህን ደዌ ይደብቀዋል እንጂ አያጠፋውም። የህመሙ ተጠቂ በዚህ የበታችነት ስሜት የሚሰቃየው ሰው ፕሬዚዳንት ሊሆን ይችላል። የመሪነትን ወንበር መያዝ በውስጣዊ ማንነታችሁ ላይ ምን ለውጥ ያመጣል?
ኦሾ/osho
ሕፃናት ዘንድ የፈጣሪ ቁጣ ; ፍርሃት ; ቅጣት ... የሚባል ነገር የለም። ለእነሱ ህይወት በራሷ ምሉዕ እና ትርጓሜም ሆነ መሻት የተሸከመች ባለመሆኗ ፈጣሪን ያለምንም ፍርሃትም ሆነ ጥያቄ ይቀርቡታል።
ታዋቂው የአሜሪካ የመፅሐፍ ቅዱስ ሰባኪ ቢሊ ግርሃም አንድ ቀን ወደ አንዲት ትንሽ የገጠር ከተማ ለስብከት አገልግሎት ይሄዳሉ ። በከተማዋ ደርሰው የአገልግሎት ሰዓታቸው እስኪደርስ ደብዳቤ ለመላክ ፖስታ ቤት ፍለጋ በጎዳና ላይ መዘዋወር ይጀምራሉ። ይሁንና የፖስታ ቤቱ አድራሻ በቀላሉ የሚገኝ አልሆነም።ዶ/ር ቢሊ ግርሃም በዚህ መካከል አንድ የስምንት ዓመት ህፃን በመንገድ ዳር ለብቻው ሲጫወት ይመለከቱትና ወደ እሱ በመሄድ "የኔ ልጅ ስምህ ማነው?" ይሉታል።

ልጁም " ጆን እባላለሁ " ይላል።

" ጆን እባክህ የፖስታ ቤቱ አድራሽ ጠፍቶኝ ተቸግሬያለው። የከተማዋ ፖስታ ቤት የት እንደሆነ ታውቃለህ?" በማለት ይጠይቁታል። ጆንም ቀኝ እጁን ከፊት ለፊቱ በተዘረጋው መንገድ ላይ እየጠቆመ ለዶ/ር ቢሊ ግርሃም የፖስታ ቤቱን አዳራሽ አሳያቸው።

ዶ/ር ቢሊ ግርሃም በዚህ ግዜ ልጁን አመስግነው "ማታ ጎስፔል ባኘቲስት ቤተክርስቲያን በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ሰዎች እንዴት መንግስት ሰማያት መግባት እንደሚችሉ መንገዱን አስተመራለሁና ከቻልክ ከወላጆችህ ጋር እንድትመጣ።" በማለት ይጋብዙታል።

ሕፃኑ ልጅ ግን በማቅማማት ፍላጎትም እንደሌለው አንገቱን በመነቅነቅ እየገለፀ "የምመጣ እንኳን አይመስለኝም " አላቸው።

በጆን ምላሽ የተገረሙት ዶ/ር ቢልግርሃም ለምን መምጣት እንዳልፈለገ ሲጠይቁት ጆን:- " የፖስታ ቤቱን መንገድ የማታውቅ ሰው እንዴት ብለህ ነው የመንግስተ ሰማይን መንገድ የምታሳየኝ ?" በማለት ማጫወቻዎቹን ይዞ ሮጠ።

#ጥበብ ከጺላጦስ
(ኅይለጊዮርጊስ ማሞ) ቅፅ 2
የስሜት ጭቆና ምንድ ነው ?
🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡
"የስሜት ጭቆና መኖር የሌለባችሁን ህይወት መኖር ማለት ነው። የስሜት ጭቆና ማለት ፈጸሞ የማትፈልጓቸውን ነገሮች ማድረግ ማለት ነው። የስሜት ጭቆና ራስን የማወደሚያ መንገድ ነው። የስሜት ጭቆና ራስን ማጥፋት ነው። በርግጥ ራስ መሠጥፉቱ በጣም የዘገየ ነው። ግንበጣም እርግጠኛ የሆነ ምረዛ ነው።
....ስሜትን መግለጽ ህይወት ሲሆን ስሜትን መጨቆን ደግሞ ራስን የማጥፋ!ት ያህል ነው።"
🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡🎡
#ነፃ ስሜቶች# ገጽ 58
#ኦሾ/Osho
#ትርጉም በዮሐንስ አዳም
🌜በሌሎች ላይ እየፈረድን እኛ ግን ያንኑ መልሠን እናደርጋለን፡፡በሀሳባቸዉ ፣ በእምነታቸው ፣በድርጊታቸዉ ወዘተ ላይ እየፈረድን መልካም እና በጎ ፣ ብርሃን እና ጨለማ በማለት እንፈርጅዋለን፡፡ አስቀድማችሁ ከራሳቸሁ ጋር አንድነት ፍጠሩ። በጨለማ እና በብርሃን ፤ በህይወት እና በሞት መካከል መስማማትን አምጡ፡፡ ያን ጊዜ ዉስጣችሁ አንድ ይሆናል። የሰዉ ልጀ ግን እንኳን አንዱን ከሌላው ጋር ቀርቶ ከራሱም በውስጡ አንድነት የሌለው እና ዘወትር ሲናወጥ እና ሲከፋፈል የሚዉል ፍጡር ነው።🌛
#ኦሾ/Osho
ፈጣሪ እኛ እንጎበኛዋለን እንጂ እሱ አይጎበኘንም

እንድ የበቁ የዜን አባት አንድ ወጣት መጥቶ " ወደ ዜን መግቢያው በር በየት ነው ? " ብሎ ጠየቃቸው ። እሳቸው ግን መልስ ከመሰጠት በአርምሞ አለፉት። ልጁ በድጋሚ ጠየቃቸው ። አባ በዛን ሰአት እንዲህ ብለው ለወጣቱ ጥያቄን በጥያቄ መለሱለት ...
" ምንጩ ይሰማኸል ? "
ወጣቱ " የምን ምንጭ ? " ...ለደቂቃዎች የምንጩን ድምፅ ለማወቅ ትኩረት ሁሉ ወደእዚያው አደረገ ። የምንጩን ድምፅ ሲፈለግ በአእምሮ ሲንጡት የነበሩ ሀሳቦች ሁሉ እንደ ጠጅ አንቡላ ቀስበቀስ ወደ ታች መዝቀጥ ጀመሩ። ከዛም ከወዲያ ማዶ ካለ ተራራ ስር ያለቸው ምንጭ ስትፈስ አዳመጣት ።
"አባ...ምንጩን ሰማሁት " አለ ወጣቱ
"የዜን መግቢያው እሱ ነው አሉት"
በህይወቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በዙሪያው ያለውን ህይወት ተረዳ ። አበቦች ፣ መስኩ ፣ ተራራዎች ፣ ወንዙ ፣ የአእዋፍ ዝማሬ ሁሉ ነገር እንደ አዲስ ነገር ተገነዘባቸው ። በህይወቱ ተሰምቶት የማያውቅ ሰሜት ተሰማው። ነፈሱ ረጋች። ብዙም ሳይቆይ ሀሳቦቹ አንሰራርተው አእምሮ በሀሳብ ተሞላ ። ነገሮች ወደ ነበሩት ተመለሱ ።
ፈጣሪ በፈጠረው ነገር ሁሉ ወስጥ ይኖራል ። የምንተነፍሰው አየር ፣ የምንጠጣው ውሀ ፣ የምንበላው ምግብ የምንኖርበት አከባቢ...በኛም ውስጥ ይኖራል ....ልብ ምታችን...ደም ዝውውር ...የተመጠኑ ሆሮሞኖች ወዘተ። ፍጥረት አንድ ትልቅ ኦኬስትራ ባንድ ትመስላለች ሳሩ ደኑ ቅጠሉ አእዋፋት አራዋት ጨረቃና ፀሀይ በአንድ ስልተ- ምት ይፈሳሉ ። የሰው ልጅ የገዛ አእምሮ ሳንካ ሆኖበት ሌላ ስልተ - ምት ይፈልጋል ። ዝና ፣ ገንዘብ ፣ ስልጣን ውስጥ እራሱን ለማግኘት ይሞክራል ። ለምሳሌ ሱናሚ በተከሰተ ጊዜ ገና ከመምጣቱ በፊት እንስሳት ሁሉ የመጣውን አደጋ ተረድተው ወደ ከፍታ ቦታ አሰቀድመው ሸሽተው ነበር። የሰው ልጅ ግን ከተፈጥሮ ስልተ-ምት ወጪ በመሆኑ 150000 የሚሆኑት ዝርያዎቹ ጠፍተዋል ። የፈጠሪና የተፈጥሮ አንድ አካል ነን...ፈጣሪ ሁሉ ነገር ውስጥ ካለ ...ሁሉም ቦታ ካለ....ልክ እንደ ወጣቱ ብርሀነ ህሊናችንን ሳንጠቀምበት ቀርተን ፤ ከስልተ - ምት ወጥተን ሳናስተውለው ቀረን እንጂ እሱ እኮ ሁሌም አለ።
ለሆዳቸው ሲሉ ሕሊናቸውን የጣሉ ትርፋቸው ምንድነው??
(እ.ብ.ይ.)

ወዳጆች ቅንነትን የሚያወድም፣ ደግነትን የሚያጠፋ፣ ፍቅርን አሽቀንጥሮ የሚጥል ልቡ በክፉ ሃሳብ የጠፋ ብቻ ነው፡፡ ብዙዎች በውስጣቸው ያለውን ቅንነት፣ በልባቸው የነበረውን ደግነት፣ በሕሊናቸው የኖረውን መልካምነት አሟጥጠው በመጨረስ ከሠውነት ጎዳና ይወጣሉ፡፡ ከትክክለኛው የሠውነት ምልክታቸው ያፈነግጣሉ፡፡ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ፣ ከደግነት ይልቅ ክፋት ዓይናቸውን ያውረዋል፡፡ ልባቸው በክፉ ሃሳብ ይጨልማል፡፡ በጨለማው ማንነታቸው ዓለሙን ይበይናሉ፡፡ በበየኑት ዓለም ውስጥ በድቅድቁ አመለካከታቸው ብቻ ነው የሚመላለሱት፡፡ ልቦናን መጣል፣ እውነትን ማርከስ፣ እምነትን ማጉደል ለነሱ ቀላል ይሆናል፡፡

ሠው ለእምነቱ፣ ለእውነቱ፣ ለሕሊናው መኖር ካልቻለ ታዲያ ለምን ሊኖር ነው?? ሠው በሆዱ፣ በቁስ ፍላጎቱ፣ በብልጭልጩ ዓለም እየታለለ እስከመቼ ይዘልቃል?? የሠውነት ውስጣዊ ዓለሙንስ የሚያረካው መቼ ነው?? የቱ ላይ ነው ሠውነቱ?? ለሆዳቸው ሲሉ አዕምሯቸውን የጣሉስ ትርፋቸው ምንድነው??

ታላቁ ቡድሃ ‹‹ምንም ዓይነት መርዝ ቀና አሳቢን አይገድለውም፡፡ ምንም ዓይነት ሕክምና ክፉ አሳቢን አያድነውም፡፡›› ይለናል፡፡

እውነት ነው! ክፉ ሃሳብን፣ ተንኮልን፣ ሌሎችን ማሳቀቅን፣ እኔ ብቻ ይድላኝ የሚል ስግብግበነትን፣ ሌሎች በየሜዳው ቢወድቁ እኔ ምን ተዳዬ የሚል ጨካኝ አመለካከትን ማከም መቻል እጅግ ከባድ ነው፡፡ በሽተኛው በሽታውንና ህመሙን ተረድቶ ለመፈወስ እስካልቆረጠ ድረስ ሊታከም የሚችል በሽታ አይሆንም፡፡

በዛው ልክ ደግሞ ቀና አስተሳሰብን የሚያወድም ምንም ዓይነት ሃይል የለም፡፡ ቀና አሳቢው ቢሞት እንኳን ቅንነቱን ሌሎች ላይ አጋብቶ ስለሚኖር በቅኖች ቅብብል ቀና አስተሳሰብ ዘላለም ይኖራል፡፡ ቀና አስተሳሰብ ባይኖር ክፉ ሃሳቦችን ለመመዘን አንችልም ነበርና፡፡

ኤሪክ ፎረም የተባለ ፀሐፊ You shall be as Gods በተባለ መፅሐፉ እንዲህ ይለናል፡-

‹‹ክፋት የሚመገብ አዕምሮ በክፋት ያድጋል፡፡ ደግነትም የሚመገብ እንዲሁ ይሆናል፡፡ የዕድገት ዋነኛ ምክንያት ግን የሠው ብቸኛ ችሎታ በሆነው ማሠብ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡›› ይለናል፡፡

እውነት ነው! ሠው ሆዱን ለሚመግበው እንደሚጠነቀቀው ሁሉ ለአዕምሮውም የሚመግበውን ሃሳቡን መፈተሸ አለበት፡፡ ያገኘውን ሁሉ አግበስብሶ የሚመገብ ከሆነ ጉዳቱ ለራሱ ነው፡፡ ቁንጣንም በሽታ ነው፤ በበቂ ሁኔታም አለመመገብ የምግብ እጥረት ነው፡፡ መጠን ግድ ይላል፡፡ መጠን እንወቅ ወዳጆች!

ለዚህም ነው ኤሪክ ፎረም፡- ‹‹የሠው ልጅ እጅግ ጨካኝም ሆነ እጅግ ደግ የሚያደርገው ዘወትር ሃሣቡን የሚመግበው ነገር እንጂ ሌላ የተለየ ምክንያት ኖሮት አይደለም፡፡›› በማለት ሠው ሃሳቡ ላይ ብዙ መስራት እንዳለበትና ሚዛን የሚደፋ ሃሳብ ተመግቦ እንዲያመርት ነው ፀሐፊው የሚመክረው፡፡

አንዳንድ ሠው ደግሞ ራሱን ለክፋት አስተሳሰብ እያጋለጠና በፍቃዱ ጨካኝ ሃሳብ በአዕምሮው እየሞላ ይሄን ያደረግኩት ሠይጣን አታሎኝ ነው እያለ ራሱን ያሞኛል፡፡ ራሱ ለፈጠረው ስህተት ከመናዘዝ ይልቅ ሠበብን ፍለጋ ይዳክራል፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሠው ለሠራው በጎ ነገር ዕውቅናን ለማግኘት ደፋ ቀና ቢልም፤ ለሠራቸው ስህተቶች ደግሞ ሃላፊነትን መውሰድ አይሻም፡፡ ሌሎች ላይ ማላከክ፣ ሠበብ መፈለግ፣ የእምዬን ወደአብዬ ማድረግ ከስህተቱ ለመታረም ያለመቻላችን ውጤት ነው፡፡

አንድ የሱፊ ተረክ አለ፡፡ በኢራን አቡል ቢስታሚ የተባሉ በእምነታቸው ፅኑ እና የታወቁ ሱፊ ነበሩ፡፡ አንድ ቀን ምሽት ከደቀመዛሙርቶቻቸው ጋር ተቀምጠው ሲያወጉ የእምነት ጉዳይ ተነሣ፡፡ ደቀመዛሙርቱ ተራ በተራ የእምነታቸውን መላላትና ብሎም መጥፋት ከነገሯቸው በኋላ ለዚህም ምክንያቱ ሠይጣን እንደሆነ አስረግጠው አስረዷቸው፡፡

በዘመኑ ተዓምራትን ማድረግ ይችሉ ነበር የሚባልላቸው አቡል ቢስታሚ የደቀመዛሙርቱን ስሞታ ካዳመጡ በኋላ ሠይጣንን ጠርተው ጠየቁት፡-

‹‹እውን የደቀመዛሙርቶቼን እምነት ሠርቀሃል?›› አሉት፡፡ ሠይጣንም መለሠ፡- ‹‹እኔ የማንንም እምነት ለመስረቅ የሚያስችል ሃይል የለኝም፡፡ ምክንያቱም የሚያምኑት አምላክ ከእኔ የላቀና እጅግም ከፍ ያለ ሃይል ያለው ነውና፡፡ ነገር ግን ብዙዎች በየጥቃቅኑ ምክንያት እምነታቸውን በየመንገዱ እየጣሉ ሲሄዱ አግኝቼ በመሠብሠብ ከእኔ ዘንድ ያስቀመጥኩትን እንደሠረቅሁ አድርገው እየዋሹ ነው፡፡›› በማለት መለሠ፡፡

አቡል ቢስታሚም ደቀመዛሙርቱን ከሠይጣን ጋር ላኳቸውና እንዲህ አሉ፡-

‹‹እምነቱን የጣለ ታግሎ ያስመልስ፡፡ ሠይጣን ያለጥፋቱ ምን ባደረገ ይቀጣ?›› በማለት ወሠኑ፡፡ እስከዛሬ ደቀመዛሙርቱ ወደቢስታሚ አልተመለሱም ይባላል፡፡

ወዳጆች ምንድነው በዓለም ያለን ትርፍ?? ካነሳነው ይልቅ የጣልነው አይበልጥም?? ምንድነው የዕድሜአችን ዓላማ?? በዕድሜአችን ውስጣችንን ካስደሰትንበት ይልቅ የተከፋንበት አይበልጥም?? የምንኖረው ለመብላት ብቻ ነውን?? የሐገርን ሃብት ለብቻ በጉልበትና በተንኮል እየመዘበሩ መኖር ጥቅሙስ፣ ሠበቡስ፣ ትርፉስ፣ ውጤቱስ ምንድነው?? የተለየ ግቡ ምንድነው?? ሕሊናን፣ ልቦናን፣ ነፍስያን፣ መንፈስን የሚያረካውና የሚያጠግበውን ፍላጎታችንን እንዴትስ ነው ልናረካው የምንችለው??

ለማንኛውም ለሆዳችን ብቻ ሳይሆን ለውስጣችንም፣ ለነፍሳችንም፣ ለህሊናችንም፣ ለልባችንም እኩል በእኩል እንኑር የዛሬው መልዕክት ነው!

ቸር ጊዜ!

__________________
(እ.ብ.ይ.)
አንድ ጊዜ ታላቁ ሸህ ኢብን ዐረቢ ወደ ደማስቆ ተራራ ይወጣና ማስተማር ይጀምራል፡፡ በመሃል "ሰዎች ሆይ! የምታመልኩት ጌታ ከእግሬ ሥር ይገኛል" አላቸው፡፡ ሰዎቹ በጣም ከመናደዳቸው የተነሳ አሰሩት፤ ሊገድሉትም ዝግጁ ሆኑ፡፡
ኢብን ዐረቢ ሥራዎቹ ጥቃት የተቀላቀሉበት ውዝግቦችን ከማስነሳታቸው የተነሳ ከሞተ በኀላ የተቀበረበት እንዳይገኝ ሃውልቱን ሁሉ አፈራርሰው ድራሹን አጠፉት፡፡
ታዲያ ኢብን ዐረቢ የሚታወቅባቸው በርካታ ንግግሮች አሉት፡፡ አንደኛው "ሲን ሺን ሲገባ ቀብሬ ይገኛል" የሚለው ዋናው ነው፡፡
ኢብን ዐረቢ ከሞተ ወደ ሶስት መቶ ዓመታት ሊሞላው ሲል ዘጠነኛው የዑስማንያ ኸሊፋ ሰሊም ሁለተኛው ደማስቆን 1516 ይማርካል፡፡ ሰሊም ከላይ የተጠቀሰውን የኢብን ዐረቢ ንግግር በወቅቱ ከነበረው ዓሊም ዘምቢሊ ዓሊ ኢፈንዲ ከነትንቢቱ ይሰማል፡፡ ሸኽ ዘምቢሊም የትንቢቱን ፍቺ ይነግሩታል- ሲን ማለት ሰሊም ወደ ሺን ማለት ሻም ሲገባ የሙሂይዲን ሐውልት ይሠራል።
ታዲያ ሰሊም ከከተማዋ የነገረ መለኮት ዓሊሞች ኢብን ዐረቢ "የምታመልኩት ጌታችሁ ከእግሬ ሥር ይገኛል" ብሎ የተናገረበትን ቦታ ጠይቆ ከተረዳ በኀላ ማስቆፈር ይጀምራል፡፡ የወርቅ ሳንቲሞች ክምር ያገኛል፡፡ ፃድቁ ኢብን ዐረቢ ምን ለማለት እንደፈለገ ይገልፃል፡፡ የወርቅ ሳንቲሞቹ ከተገኙበት ቦታ ብዙም ሳይርቅ የተቀበረበትን ቦታ ያገኘዋል፡፡ ሰሊም በተገኘው ወርቅ በቦታው ላይ መስጊድ እና የኢብን ዐረቢን ሐውልት ያሠራል፡፡
መስጊዱና ዶሪሁ አሁንም በደማስቆ ይገኛል፡፡ ሳሊሂያ ይባላል፡፡ ቃሲዩን ከሚባለው ተራራ ተዳፋቱ ላይ ነው፡፡ አሁን በአገሪቷ እየተካሄደ ባለው የእርስ በእርስ ጦርነትም ጉዳት አልደረሰበትም፡፡
አላህ ሆይ! በታላቁ ሸኽ ይሁንብህ፤ እባክህን ወዳንተ አቃርበን!
ቀደሰላህ ሲረሁ
#የትኛውም እንሰሳ የተራክቦ ስሜቱን የሚወጣው የሴቷን ሽንት አሽትቶና እርጉዝ አለመሆኗን አረጋግጦ ሲሆን ይህንንም ለማድረግ ወቅትና የሴቷን ፈቃደኝነት ተከትሎ ነው።
#የሰው ልጅ ግን ስግብግብ በመሆኑ ያለ ሴቷ ፍቃድና አስገድዶ ደፋሪ ሆኖ ከእንሰሳ በታች የዘቀጠ የስብዕና ኖሮት አለማፈሩ አስገራሚ ፍጡር ያደርገዋል ።
ኦሾ/Osho
#የምስራቃውያን_ተረት

አንድ ኃያል ንጉስ ከአስፈሪ የሞት ፅልመት ጋር ተገናኘ። ለቀናትም ከፊቱ የተደቀነው የሞት ጥላ እንቅልፍ ነሳው። "ማነህ አንተ? ምንስ ትፈልጋለህ?" ሲል ጠየቀው በድንጋጤ። ጥቁሩ የጥላ ምስልም "እኔም ሞትህ ነኝ። የመጣሁትም በትክክለኛው ስዓት እና ስፍራ እንዳገኝህ ላስታውስህ ነው።" አለው። ከንጉሡ ፊት ከመሰወሩ በፊትም "ነገ በትክክለኛው ስፍራና ስዓት እንገናኝ " ብሎት ሄደ።


በማስጠንቀቂያው የተደናገጠው ንጉሥ፤ ጠቢባን አማካሪዎቹን፣ ኮከብ ቆጣሪዎችን፣ ህልም ፈቺና ጠንቋዮችን አስጠርቶ የህልሙን ምንነት እንዲያስረዱት ጠየቀ።

ጠቢባኑ በንጉሡ እልፍኝ ተሰብስበው መከራከር ጀመሩ። ንጉሱን ከህፃንነቱ ጀምሮ የሚያውቁት አንድ አዋቂ ወደ ጆሮው ተጠግተው እንዲህ ሲሉ መከሩት፦ "የጊዜህን አታባክን የነዚህ ጠቢባን ክርክር አያልቅም። ቀኑ ያልቅና በነጋው ዕለት ይተካል። ስለዚህ ፈጣኑን ፈረስ ጫንና ከዚህ ስፍራ አምልጥ!"

ንጉሱም ፈጣኑን ፈረስ እየጋለበ ህልሙን ካየበት ቤተ መንግሥቱ ራቀ። ከከተማዋ ብዙ ርቀት ጋልቦ ቆመና "ሞት እዚህ ድረስ ሊመጣብኝ አይችልም በትክክለኛው ሥፍራና ሰዓት አልገኝለትም" አለ።

ፀሀይ ለማጥለቅ ስትቃረብ ፈረሱን አሳርፎ ምግብ ሰጠው። በፈረሱ ፈጣንነትና ከሞት መራቁ ተደስቶ ሳር ላይ ሲቀመጥ ትከሻውን አንድ ነገር ዳበሰው። ዞሮ ሲመለከት የሞት ጥላው ከኋላ ቆሞ በፈገግታ ያየው ነበር። "ምን ያስቅሃል?" ሲል የተደናገጠው ንጉሥ ጠየቀው።
ሞትም "የቀጠሮአችን ጊዜና ቦታ ይህ ነው። በቶሎ አትደርስም ብዬ ሰግቼ ነበር። ሆኖም ግን ለፈረስህ ምስጋና ይግባውና አልዘገየህም" ሲል መለሰለት።
•ንጉሱ በጣም ብርዳማ በሆነው ሌሊት ወደ ቤተመንግስቱ ሲገባ ስስ የሆነ ልብስ የለበሱ አንድ በእድሜ የገፉ የቤተመንግስቱን ጥበቃ ተመለከተ
.
ወደ እሳቸውም ተጠጋና አይበርዶትም? አላቸው
.
ሰውዬውም፦ይበርደኛል እንጂ ነገር ግን ብርድን የሚከላከል ልብስ የለኝም! አለ
.
ንጉሱ፦ወደ ህንጻው ከገባ በኋላ ከጠንካራው እና ብርድን የሚከላከል ከሱፍ የተሰራ ልብስ እንዲያመጣላቸው አንዱን አገልጋይ
ያዘዋል።
.
ጥበቃው፦በንጉሱ ቃል በጣም ተደሰቱ። ነገር ግን የንጉሱ አገልጋይ ረስቶት ሊያመጣላቸው አልቻለም።
.
ሌሊቱ ሲነጋ ግን ንጉሱ ከቤተመንግስቱ ሲወጣ ሰውዬው ሞተው ያያል።
.
አንድ ብጣሽ ወረቀትም በእጃቸው ይዘው ነበር ንጉሱን ወረቀቱም ማንበብ ጀመረ።
.
ደብዳቤውም እንዲህ ይላል
.
"ብርዳማ ሌሊቶችን መቋቋም እችል ነበር ነገር ግን ለኔ ብርድ የሚከላከል ልብስ #ቃል መግባትህ ሀይሌን ነጠቀኝ"
.
~~~~~~~ ~~~
ቃል የምትገባላቸው ሰዎች ቃልህን ከምታስበው በላይ ቦታ ሊሰጡት
ይችላሉና እናስታውስ ቃላችንን አንጠፍ።
" ......ተገቢውን ፍርድ ለመስጠት የምትሹ እናንተ ዳኞች ሆይ ...በስጋው ታማኝ ቢሆንም በመንፈስ ሌባ ለሆነ ሰው ምን ፍርድ ትሰጡታላችሁ ?......በስጋው ለሚያርድ በመንፈሱ ግን እርሱ ራሱ ለታረደውስ ምን ቅጣት ትጥሉበታላችሁ ?......እናስ በተግባር አታላይና ጨቋኝ ቢሆንም እርሱ ራሱ የተጨቆነውን የተዋረደውንስ እንደምን ትዳኙታላችሁ ?.....ገና ሳይፈረድባቸው ፀፀታቸው ከመጥፎ ድርጊታቸው በእጅጉ በልጦ የተገኘውንስ እንዴት አድርጋችሁ ነው ቅጣት የምትጥሉባቸው ?.......በአግባቡ እያገለገላችሁት የምትገኙት ያ ህግ በራሱ የሚሰጠው ፍትሀዊ ብይንስ ፀፀት አይደለምን ? እንደዚያም ሆኖ በንፁሃን ላይ ፀፀት ልታሳድሩ ወይም ከጥፋተኞች ልብ ላይ ፀፀት ነቅላችሁ ልታወጡ አይቻላችሁም ። ...." ገፅ ( 38 / 39 )

".....ወዳጆቼ ሆይ በእምነቶችና በባዶ ሐይማኖቶች ለተሞላች ሀገር እዘኑላት ....በጥባጮችን እንደ ጀግና በእልልታ ለምትቀበል ፣ አንፀባራቂ ድል አድራጊዎችን እንደ ለጋስ ለምታሞካሽ ሀገር እዘኑላት ..... መሪው ቀበሮ ፈላስፋው ቀጣፊ ጥበቡም መኮረጅና መለጣጠፍ ለሆነ ህዝብ እዘኑለት ..... አዋቂዎቿ በእድሜ መግፋት ዲዳ ለሆኑባት ፣ ብርቱ ልጆችዋ ገና ከህፃን አልጋ ላይ ላልተነሱላት ሀገር እዘኑላት ..... ግዛቷ ለተበጣጠሰባትና እያንዳንዱ ብጥስጣሽ ራሱን እንደ አንድ ሀገር ለሚቆጥርባት ሀገር እዘኑላት ..... ገፅ ( 153 )
የጠቢባን መንገድ