#ከእለታት አንድ ቀን አንድ የፐርሺያ ንጉሥ ሁለት ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ ፈረደባቸው፡፡
በመጨረሻም፤ “የሞት ፍርዱ ከመፈፀሙ በፊት የፈለጋችሁትን ተናገሩ” ሲል እድል ይሰጣቸዋል፡፡
አንደኛው፤ “ምንም የምናገረው የለኝም” አለ ሁለተኛው፤
ንጉሡ ምን ያህል ፈረሳቸውን እንደሚወዱት ስለሚያውቅ፤“ንጉሥ ሆይ፤ የአንድ ዓመት ጊዜ ከሰጡኝ ፈረስዎ ወደ ሰማይ እየከነፈ እንዲሄድ ላስተምረው እችላለሁ” አላቸው፡፡ንጉሡ በሰማይ ላይ የሚከንፍ ፈረስ እየጋለቡ ሲሄዱ ታያቸው፡፡ ካሁኑ ነሸጣቸውና ይቁነጠነጡ ጀመር፡፡“ይሁን አንድ ዓመት ሰጥተንሃል፡፡ ፈረሱን አምጥተው እንዲያስረክቡህ አደርጋለሁ” አሉ፡፡
የመጀመሪያው እሥረኛ በምንም አይነት ፈረስ እንደማይበር ስለሚያውቅ ፈረስ አስተማሪውን እሥረኛ ጓደኛውን እንዲህ ሲል ጠየቀው፤“ወዳጄ፤ ፈረስ በሰማይ እንደማይበር አሳምረህ ታውቃለህ፡፡ እንዲህ ያለ የዕብድ ሀሳብ ከየት አምጥተህ ነው ቃል የገባኸው፡፡ የመሞቻችንን ጊዜ ከማራዘም በስተቀር ምን ይፈይድልሃል?”
ፈረስ አስተማሪውም፤“አይምሰልህ ወዳጄ፤ ነፃነቴን የማገኝባቸውን አራት ዕድሎች ራሴ መስጠቴ ነው”አለ
አንደኛው እሥረኛም፤
“አራቱ ዕድሎች ምን ምን ናቸው?” ሲል በመጓጓት ጠየቀው፡፡
ፈረስ አስተማሪው፤ እንዲህ ሲል ዘረዘረለት፡-
1ኛ ወይ በዚህ ዓመት ውስጥ ንጉሡ ሊሞቱ ይችላሉ
2ኛ እኔም ልሞት እችላለሁ
3ኛ ወይ ደሞ ፈረሱም ሊሞት ይችላል
4ኛ ደሞስ ማን ያውቃል እኔ ፈረሱ በሰማይ እንዲበር ላስተምረው እችል ይሆናል አለው ይባላል።
* * *
እና ምን ልልህ ፈልጌ መሰለህ በችግሮች ተሸንፈህ ቀድመህ እጅ አትስጥ ጣር ሞክር ልፋ ታገል በነገሮች ተስፋ አድርግ እንጂ ተስፋ አትጣ።ህይወት አንድ ሺህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ አንድ ሺህ ጊዜ ተስፋ የምታደርግባት የግብግብ መድረክ ናት።
"ተስፋ በሌለበት እንኳ ተስፍ አድርግ ያለው ጸሐፊው በምክንያት ነው።አይህ ወዳጄ ከመሰንበት መላ አይጠፋምና።
በመጨረሻም፤ “የሞት ፍርዱ ከመፈፀሙ በፊት የፈለጋችሁትን ተናገሩ” ሲል እድል ይሰጣቸዋል፡፡
አንደኛው፤ “ምንም የምናገረው የለኝም” አለ ሁለተኛው፤
ንጉሡ ምን ያህል ፈረሳቸውን እንደሚወዱት ስለሚያውቅ፤“ንጉሥ ሆይ፤ የአንድ ዓመት ጊዜ ከሰጡኝ ፈረስዎ ወደ ሰማይ እየከነፈ እንዲሄድ ላስተምረው እችላለሁ” አላቸው፡፡ንጉሡ በሰማይ ላይ የሚከንፍ ፈረስ እየጋለቡ ሲሄዱ ታያቸው፡፡ ካሁኑ ነሸጣቸውና ይቁነጠነጡ ጀመር፡፡“ይሁን አንድ ዓመት ሰጥተንሃል፡፡ ፈረሱን አምጥተው እንዲያስረክቡህ አደርጋለሁ” አሉ፡፡
የመጀመሪያው እሥረኛ በምንም አይነት ፈረስ እንደማይበር ስለሚያውቅ ፈረስ አስተማሪውን እሥረኛ ጓደኛውን እንዲህ ሲል ጠየቀው፤“ወዳጄ፤ ፈረስ በሰማይ እንደማይበር አሳምረህ ታውቃለህ፡፡ እንዲህ ያለ የዕብድ ሀሳብ ከየት አምጥተህ ነው ቃል የገባኸው፡፡ የመሞቻችንን ጊዜ ከማራዘም በስተቀር ምን ይፈይድልሃል?”
ፈረስ አስተማሪውም፤“አይምሰልህ ወዳጄ፤ ነፃነቴን የማገኝባቸውን አራት ዕድሎች ራሴ መስጠቴ ነው”አለ
አንደኛው እሥረኛም፤
“አራቱ ዕድሎች ምን ምን ናቸው?” ሲል በመጓጓት ጠየቀው፡፡
ፈረስ አስተማሪው፤ እንዲህ ሲል ዘረዘረለት፡-
1ኛ ወይ በዚህ ዓመት ውስጥ ንጉሡ ሊሞቱ ይችላሉ
2ኛ እኔም ልሞት እችላለሁ
3ኛ ወይ ደሞ ፈረሱም ሊሞት ይችላል
4ኛ ደሞስ ማን ያውቃል እኔ ፈረሱ በሰማይ እንዲበር ላስተምረው እችል ይሆናል አለው ይባላል።
* * *
እና ምን ልልህ ፈልጌ መሰለህ በችግሮች ተሸንፈህ ቀድመህ እጅ አትስጥ ጣር ሞክር ልፋ ታገል በነገሮች ተስፋ አድርግ እንጂ ተስፋ አትጣ።ህይወት አንድ ሺህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ አንድ ሺህ ጊዜ ተስፋ የምታደርግባት የግብግብ መድረክ ናት።
"ተስፋ በሌለበት እንኳ ተስፍ አድርግ ያለው ጸሐፊው በምክንያት ነው።አይህ ወዳጄ ከመሰንበት መላ አይጠፋምና።
አንድን ሰው የግል ንብረት አድርጎ እንደማሰብ መርዘኛ ነገር የለም ሰውን የግል የማድረግ መሻት የውሸት ፍቅር ነው ከእንዲህ አይነቱ ስሜት ቢያንስ ጥላቻ ይሻላል በጥላቻ ውስጥ ውሸት የለም ከዚያ በላይም ጥላቻ አንድ ቀን ፍቅር ሆኖ ሊቀየር ይችላል
የሰውን ልጅ ግን የግል የማድረግ ፍላጎት ፈጽሞ ወደ ፍቅር ሊቀየር አይችልም ፍቅር ማለት በምትወደው ሰው ነፍስ ውስጥ ራስህን መግደል ነው ፍቅር ማለት ሞት ነው
ኦሾ/Osho
የሰውን ልጅ ግን የግል የማድረግ ፍላጎት ፈጽሞ ወደ ፍቅር ሊቀየር አይችልም ፍቅር ማለት በምትወደው ሰው ነፍስ ውስጥ ራስህን መግደል ነው ፍቅር ማለት ሞት ነው
ኦሾ/Osho
"...የሰው ልጅ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ መጠኑና ስፋቱ ቢለያይም ፣ ራሱ በሠራው አሊያም ሌሎች ባጠሩለት እስር ቤት ይኖራል፡፡ እንደ ራሱ አሳብና አመለካከት ግን ትልቅ እስር ቤት የሚኾንበት አንዳች ነገር የለም፡፡
ለካስ እስር ቤት ቦታ ሳይኾን አስተሳሰብ ነው፡፡ በዚህች ምድር እጅግ ብዙ ሰው በአእምሮው እስር ቤት ውስጥ በአሉታዊ አስተሳሰብ ታስሮ፣ በከንቱና እንቶ ፈንቶ ፍርሀት ተይዞ ማንም እንዳይረዳው ኾኖ የእስር ቤት ቊልፉን ራሱ ደብቆ ይኖራል፡፡"
በዚህ አጋጣሚ
"ሜሎሪና" መጽሐፍን ተጋበዙልኝ
ለካስ እስር ቤት ቦታ ሳይኾን አስተሳሰብ ነው፡፡ በዚህች ምድር እጅግ ብዙ ሰው በአእምሮው እስር ቤት ውስጥ በአሉታዊ አስተሳሰብ ታስሮ፣ በከንቱና እንቶ ፈንቶ ፍርሀት ተይዞ ማንም እንዳይረዳው ኾኖ የእስር ቤት ቊልፉን ራሱ ደብቆ ይኖራል፡፡"
በዚህ አጋጣሚ
"ሜሎሪና" መጽሐፍን ተጋበዙልኝ
#ለዕለተ ቅዳሜያችን
ብዙ ጊዜ ትወድቃላችሁ። ይህ ለክፉ አይሰጥም። እንደገና ተነስታችሁ ቁሙና ዳግም ያለመውደቅን ተማሩ። የበለጠ ንቁ። ስህተት መስራታችሁ አይቀርም ፣ ግን አንድ ስሄተት ደግማችሁ አትስሩ። ይህን የምላችሁ ሰው ጥበብን የሚያገኘው በዚህ መልኩ ነው።
አጭር ሆናችሁ አትቅሩ። የምትችሉት ርቀት ላይ ለመድረስ ሞክሩ። ሊያኮራ የሚችለውን ብቃት ይዞ ያልተፈጠረ ማንም ሰው የለም። አንድን አዲስና ውብ ነገር የመውለድ፣ህላዊን የበለጠ የማበልፀግ ብቃትን ሳይዝ የተፈጠረ ሰው የለም።
#ኦሾ/Osho
#ራስን የመኾን ድፍረት
#ትርጉም፦ዘላለም ንጉሴ
ብዙ ጊዜ ትወድቃላችሁ። ይህ ለክፉ አይሰጥም። እንደገና ተነስታችሁ ቁሙና ዳግም ያለመውደቅን ተማሩ። የበለጠ ንቁ። ስህተት መስራታችሁ አይቀርም ፣ ግን አንድ ስሄተት ደግማችሁ አትስሩ። ይህን የምላችሁ ሰው ጥበብን የሚያገኘው በዚህ መልኩ ነው።
አጭር ሆናችሁ አትቅሩ። የምትችሉት ርቀት ላይ ለመድረስ ሞክሩ። ሊያኮራ የሚችለውን ብቃት ይዞ ያልተፈጠረ ማንም ሰው የለም። አንድን አዲስና ውብ ነገር የመውለድ፣ህላዊን የበለጠ የማበልፀግ ብቃትን ሳይዝ የተፈጠረ ሰው የለም።
#ኦሾ/Osho
#ራስን የመኾን ድፍረት
#ትርጉም፦ዘላለም ንጉሴ
ሀገር ከራስ ለራስ የሚገነባ እምነት ነው።
*
"የስኬታማ ሰውነት ትልቅ መለኪያ የሚያካብተው ሀብት ወይም የሚኖረው ዝናና እውቀት አይደለም ትልቅ ሚዛን በሌሎች ላይ ልዩነት መፍጠር መቻል ነው።"
ኢትዮጵያዊ ዘር....
ከሀሳብ የሚወለድ የዘር ብይን ያስፈልጋል። ልማድና ጥንተ-ተረት አያሳድግም። የዛሬን ፈተና አይመልስም። በየአጥቢያ የምናየውን ጎሰኝነት አያቆምም። ኢትዮጵያዊ ዘር የተሰኝ የባህል ዝርያ ማዳበር አለብን። ቨከምርጥ ሀሳብ የሚፈልቅ የባህል ዝርያ የመስራት ራዕይ ያስፈልገናል።
****//*********
የዘር ካርድ
ቡርሐን አዲስ/መሀመድ አሊ/
*
"የስኬታማ ሰውነት ትልቅ መለኪያ የሚያካብተው ሀብት ወይም የሚኖረው ዝናና እውቀት አይደለም ትልቅ ሚዛን በሌሎች ላይ ልዩነት መፍጠር መቻል ነው።"
ኢትዮጵያዊ ዘር....
ከሀሳብ የሚወለድ የዘር ብይን ያስፈልጋል። ልማድና ጥንተ-ተረት አያሳድግም። የዛሬን ፈተና አይመልስም። በየአጥቢያ የምናየውን ጎሰኝነት አያቆምም። ኢትዮጵያዊ ዘር የተሰኝ የባህል ዝርያ ማዳበር አለብን። ቨከምርጥ ሀሳብ የሚፈልቅ የባህል ዝርያ የመስራት ራዕይ ያስፈልገናል።
****//*********
የዘር ካርድ
ቡርሐን አዲስ/መሀመድ አሊ/
የኒቼ እና የኦሾ ቅራኔ ምን ነበር...?
፨፨፨
በፍልስፍናው ዓለም በሃይማኖት እይታ ላይ ጥሩ ነገር ያላበረከቱ ወይም ክፉኛ ሃይማኖትን እና አምላክን ተዳፍረው አልፈዋል ከሚባሉት ፈላስፋዎች መሃል
#ፍሬድሪክ ኒቼ እና #ራጅናሽ ኦሾ ግንባር ቀደሞቹ ናቸው ።
ፍሬድሪክ ኒቼ ምን ነበር ያለው...?
" አምላክ ሞቷል(God is dead) ዛሬ እናንተ አምላክ የምትሉት በሰዎች አስተሳሰብ ውስጥ ተፈጥሮ አድጎና ጎልምሶ እንዲሁም አርጅቶ ያለፈ አስተሳሰብ ነው። "
በነገራችን ላይ ፍሬድሪክ ኒቼ የሱ ቀዳሚ የነበረው ፈላስፋ #አርተር ሾፐንሀወር አድናቂ ነበር እንዲሁም በፍልስፍና እይታዎቹ ላይም የሱ ተጽእኖ አለበት ይባላል...አርተር ሾፐን ሀወርም በፈጣሪ ህልውና የማያምን እንዲሁም ለስነ መለኮት መምህራን ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት የነበረው ፈላስፋ ነበር ።
ኒቼ ይህንን ሃሳብ ማለትም "God is Dead" የሚለውን እይታውን "Joyful wisdom" በሚለው መጽሐፉ ላይ ለሕትመት ባበቃ ሰአት ከብዙ የሃይማኖት ተከታዮች ተቃውሞ ደርሶበት ነበር...ይህንን ንግግሩንም አንስቶ ራጅናሽ ኦሾ እኔም በጊዜው ብኖር እቃወመው ነበር ይለናል።
ይህንን እይታም ያስቀምጣል...
<< ፍሬድሪክ ኒቼ አምላክ ሞቷል ሲል ብዙ እምነቶች ተቃውሞ አንስተውበት ነበር። እኔም እቃወመዋለሁ ምክንያቱም እኔ ደግሞ የምለው እንኳን ሊሞት መጀመርያም #አልነበረም ነውና >> ይለናል ይህንን ንግግሩን ብርሃነ ኅሊና የሚለው መጽሐፍ ላይ እናገኘዋለን ።
ባብዛኛው ሰዎች ራጅናሽ ኦሾን የሳይኮሎጂስቱን ሲግመን ፍሩድ እና ፍሬድሪክ ኒቼን ፍልስፍናዎች ያስተጋባ ብለው የሃሰት ካባ ሊያለብሱት ቢሞክሩም እሱ ግን ከነሱም የተለየ አስተሳሰብ እንደነበረ ካሳየባቸው ንግግሮቹ አንዱ ይህ ነበር ።
#አሁን ታድያ ማን ይፍረድ እንደ ኒቼ የፈጣሪን ህልውና የተገዳደረ ፈላስፋ የለም የሚባለው ሚዛን ይደፋ ይሆን የኦሾን አይን ያወጣ #ክህደት በሉት #እውነት አፍጥጠን ስናይ...?
መልሱን ለህሊናችሁ...!!
፨ የዚህ ጽሑፍ አላማ የፈጣሪን መኖር መካድ ሳይሆን በሁለቱ ፈላስፎች መሃከል በሀለዎተ ፈጣሪ ዙርያ ያለውን እይታ ማሳወቅ ነው። በሌላ እንዳይተረጎም...
ግብዓት ምንጮች ፦ "ጥበብ ከጲላጦስ" እንዲሁም "ብርኀነ ኅሊና" መጽሐፍት
Via:- ራስን ፍለጋ
፨፨፨
በፍልስፍናው ዓለም በሃይማኖት እይታ ላይ ጥሩ ነገር ያላበረከቱ ወይም ክፉኛ ሃይማኖትን እና አምላክን ተዳፍረው አልፈዋል ከሚባሉት ፈላስፋዎች መሃል
#ፍሬድሪክ ኒቼ እና #ራጅናሽ ኦሾ ግንባር ቀደሞቹ ናቸው ።
ፍሬድሪክ ኒቼ ምን ነበር ያለው...?
" አምላክ ሞቷል(God is dead) ዛሬ እናንተ አምላክ የምትሉት በሰዎች አስተሳሰብ ውስጥ ተፈጥሮ አድጎና ጎልምሶ እንዲሁም አርጅቶ ያለፈ አስተሳሰብ ነው። "
በነገራችን ላይ ፍሬድሪክ ኒቼ የሱ ቀዳሚ የነበረው ፈላስፋ #አርተር ሾፐንሀወር አድናቂ ነበር እንዲሁም በፍልስፍና እይታዎቹ ላይም የሱ ተጽእኖ አለበት ይባላል...አርተር ሾፐን ሀወርም በፈጣሪ ህልውና የማያምን እንዲሁም ለስነ መለኮት መምህራን ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት የነበረው ፈላስፋ ነበር ።
ኒቼ ይህንን ሃሳብ ማለትም "God is Dead" የሚለውን እይታውን "Joyful wisdom" በሚለው መጽሐፉ ላይ ለሕትመት ባበቃ ሰአት ከብዙ የሃይማኖት ተከታዮች ተቃውሞ ደርሶበት ነበር...ይህንን ንግግሩንም አንስቶ ራጅናሽ ኦሾ እኔም በጊዜው ብኖር እቃወመው ነበር ይለናል።
ይህንን እይታም ያስቀምጣል...
<< ፍሬድሪክ ኒቼ አምላክ ሞቷል ሲል ብዙ እምነቶች ተቃውሞ አንስተውበት ነበር። እኔም እቃወመዋለሁ ምክንያቱም እኔ ደግሞ የምለው እንኳን ሊሞት መጀመርያም #አልነበረም ነውና >> ይለናል ይህንን ንግግሩን ብርሃነ ኅሊና የሚለው መጽሐፍ ላይ እናገኘዋለን ።
ባብዛኛው ሰዎች ራጅናሽ ኦሾን የሳይኮሎጂስቱን ሲግመን ፍሩድ እና ፍሬድሪክ ኒቼን ፍልስፍናዎች ያስተጋባ ብለው የሃሰት ካባ ሊያለብሱት ቢሞክሩም እሱ ግን ከነሱም የተለየ አስተሳሰብ እንደነበረ ካሳየባቸው ንግግሮቹ አንዱ ይህ ነበር ።
#አሁን ታድያ ማን ይፍረድ እንደ ኒቼ የፈጣሪን ህልውና የተገዳደረ ፈላስፋ የለም የሚባለው ሚዛን ይደፋ ይሆን የኦሾን አይን ያወጣ #ክህደት በሉት #እውነት አፍጥጠን ስናይ...?
መልሱን ለህሊናችሁ...!!
፨ የዚህ ጽሑፍ አላማ የፈጣሪን መኖር መካድ ሳይሆን በሁለቱ ፈላስፎች መሃከል በሀለዎተ ፈጣሪ ዙርያ ያለውን እይታ ማሳወቅ ነው። በሌላ እንዳይተረጎም...
ግብዓት ምንጮች ፦ "ጥበብ ከጲላጦስ" እንዲሁም "ብርኀነ ኅሊና" መጽሐፍት
Via:- ራስን ፍለጋ
"እንደ #ንስር
የሆነ ቀን በናሽናል ጂኦግራፊ ንስር መርዛማውን ኮብራ እባብ ሲያድን ተመልክቼ ግራ ተጋባሁ፡፡ እባቡ ግዙፍ እና አደገኛ ሆኖ ሳለ እንዴት በንስሩ ሊሸነፍ ቻለ? አልኩኝ፡፡
መልሱ ግልጽ ነው፡፡ ንስሩ መጫወቻ ሜዳውን ያውቃል!!
ምናልባት ንስሩ እና እባቡ መሬት ላይ ቢገናኙ ኖሮ እባቡ አሸናፊ ንስሩ ደግሞ ተሸናፊ ይሆኑ ነበር፡፡
ንስሩ እባቡን ከላይ ወደታች ተመለከተ፡፡ እባቡን ሲገጥመውም ከመሬት ወደላይ ወሰደው፡፡ የንስሩ መርህ መጫወቻ ሜዳን መለየት ነው!!
እባብ መሬት መጫወቻ ሜዳው(አለሙ) ነው፡፡ መሬት ላይ እባብ ሃይለኛና አሸናፊ ነው፡፡ የንስሩ መጫወቻ ሜዳ (አለም) ደግሞ ከፍታ ነው፡፡ የከፍታን አለም ከማንም በላይ ያውቀዋል፡፡ በሜዳው ድል ማድረግንም ይችልበታል!!
ንስር ይህን ጠንቅቆ ያውቃልና እባቡን ከራሱ አለም አንፃር ተመለከተው፡፡ ቀጥሎም ተጋጣሚውን ከአለሙ (መሬት) ነጥሎ ወደራሱ አለም ወሰደው፡፡ በገዛ ሜዳውም ድልን ተቀናጀ!!
ወዳጄ ሆይ በየትኛውም መስክ ድልን ከፈለክ እንደ ንስር ሁን!!
መጫወቻ ሜዳህን ለይ፡፡ አለምህን በትክክል እውቅ፡፡ ካንተ አለም አንፃር መመልከትን ተለማመድ!!
ከምንም በላይ በምንም ምክንያት በተጋጣሚክ መጫወቻ ሜዳ ላይ አትፋለም፡፡ ያለህን አቅም ሁሉ ተጠቅመህ ተጋጣሚህን ወደ ራስህ መጫወቻ ሜዳ ውስደው!!!!!!!!!
የሆነ ቀን በናሽናል ጂኦግራፊ ንስር መርዛማውን ኮብራ እባብ ሲያድን ተመልክቼ ግራ ተጋባሁ፡፡ እባቡ ግዙፍ እና አደገኛ ሆኖ ሳለ እንዴት በንስሩ ሊሸነፍ ቻለ? አልኩኝ፡፡
መልሱ ግልጽ ነው፡፡ ንስሩ መጫወቻ ሜዳውን ያውቃል!!
ምናልባት ንስሩ እና እባቡ መሬት ላይ ቢገናኙ ኖሮ እባቡ አሸናፊ ንስሩ ደግሞ ተሸናፊ ይሆኑ ነበር፡፡
ንስሩ እባቡን ከላይ ወደታች ተመለከተ፡፡ እባቡን ሲገጥመውም ከመሬት ወደላይ ወሰደው፡፡ የንስሩ መርህ መጫወቻ ሜዳን መለየት ነው!!
እባብ መሬት መጫወቻ ሜዳው(አለሙ) ነው፡፡ መሬት ላይ እባብ ሃይለኛና አሸናፊ ነው፡፡ የንስሩ መጫወቻ ሜዳ (አለም) ደግሞ ከፍታ ነው፡፡ የከፍታን አለም ከማንም በላይ ያውቀዋል፡፡ በሜዳው ድል ማድረግንም ይችልበታል!!
ንስር ይህን ጠንቅቆ ያውቃልና እባቡን ከራሱ አለም አንፃር ተመለከተው፡፡ ቀጥሎም ተጋጣሚውን ከአለሙ (መሬት) ነጥሎ ወደራሱ አለም ወሰደው፡፡ በገዛ ሜዳውም ድልን ተቀናጀ!!
ወዳጄ ሆይ በየትኛውም መስክ ድልን ከፈለክ እንደ ንስር ሁን!!
መጫወቻ ሜዳህን ለይ፡፡ አለምህን በትክክል እውቅ፡፡ ካንተ አለም አንፃር መመልከትን ተለማመድ!!
ከምንም በላይ በምንም ምክንያት በተጋጣሚክ መጫወቻ ሜዳ ላይ አትፋለም፡፡ ያለህን አቅም ሁሉ ተጠቅመህ ተጋጣሚህን ወደ ራስህ መጫወቻ ሜዳ ውስደው!!!!!!!!!
በመጀመሪያ እራስ ወዳድነት ተፈጥሮችሁ መሆኑን ተቀበሉ። ተፈጥሮችሁ መሆኑን ከተቀበላችሁ ደግሞ ይህ እራስ ወዳድነታችሁ ውስጣችሁ የሆነ እያገለገለ ያለው ነገር አለ ማለት ነው። ያለዚያማ በዚያ አይኖርም ነበር ።
እራስ ወዳድ ስለሆናችሁ ነው መኖር ያበዛችሁት እንዲሁም የገዛ እራሳችሁን እምትከባከቡት። ያ ባይሆን ኖሮ ፣ እራስ ወዳድነት ተፈጥሮ ተፈጥሮዓዊ ባይሆንማ ኖሮ የሰው ልጅ ከዘመናት በፊት ነበር ይጠፋ የነበረው።
በሚኒሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ተርበው እኛ እንበላለን ፣ በአለማችን ላይ ብዙዎች ተጠምተው እኛ እንጠጣለን፣ እራስ ወዳድነት ይሄ ነው። ታዲያ ሌሎች እራስ ወዳድ አትሁኑ እያሉ በመጀመሪያ እራስ ወዳድነት ተፈጥሮችሁ መሆኑን ተቀበሉ። ተፈጥሮችሁ መሆኑን ከተቀበላችሁ ደግሞ ይህ እራስ ወዳድነታችሁ ውስጣችሁ የሆነ እያገለገለ ያለው ነገር አለ ማለት ነው። ያለዚያማ በዚያ አይኖርም ነበር ።
እራስ ወዳድ ስለሆናችሁ ነው መኖር ያበዛችሁት እንዲሁም የገዛ እራሳችሁን እምትከባከቡት። ያ ባይሆን ኖሮ ፣ እራስ ወዳድነት ተፈጥሮ ተፈጥሮዓዊ ባይሆንማ ኖሮ የሰው ልጅ ከዘመናት በፊት ነበር ይጠፋ የነበረው።
በሚኒሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ተርበው እኛ እንበላለን ፣ በአለማችን ላይ ብዙዎች ተጠምተው እኛ እንጠጣለን፣ እራስ ወዳድነት ይሄ ነው። ታዲያ ሌሎች እራስ ወዳድ አትሁኑ እያሉ ሲያስተምሯችሁ ከተፈጥሮአችሁ ውጭ ሁኑ እያሏችሁ መሆኑን አትዘንጉ።
እኔ ግን ተፈጥሮአችሁን እንድትሆኑ አስተምሯችኋለሁ። ማንም ተፈጥሮ አችሁን እንድትሆኑ አይነግራችሁም። ምክንያቱም ደግሞ እነሱም እራስ ወዳዶች ስለሆኑ ነው።
ከሞት በኋላ የዘላለም ህይወት ፣ የተትረፈረፈ ህይወት ስለሚበዛላችሁ ይህች 70 እና 80 አመት የምትሆን ምድራዊ ህይወችታሁን ለውጡ እያሉ ይሰብኳች ኋል። ይሄ ግን ያወድማችኋል እንጅ አያበለጽጋችሁም ።
ኦሾ/Osho
እራስ ወዳድ ስለሆናችሁ ነው መኖር ያበዛችሁት እንዲሁም የገዛ እራሳችሁን እምትከባከቡት። ያ ባይሆን ኖሮ ፣ እራስ ወዳድነት ተፈጥሮ ተፈጥሮዓዊ ባይሆንማ ኖሮ የሰው ልጅ ከዘመናት በፊት ነበር ይጠፋ የነበረው።
በሚኒሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ተርበው እኛ እንበላለን ፣ በአለማችን ላይ ብዙዎች ተጠምተው እኛ እንጠጣለን፣ እራስ ወዳድነት ይሄ ነው። ታዲያ ሌሎች እራስ ወዳድ አትሁኑ እያሉ በመጀመሪያ እራስ ወዳድነት ተፈጥሮችሁ መሆኑን ተቀበሉ። ተፈጥሮችሁ መሆኑን ከተቀበላችሁ ደግሞ ይህ እራስ ወዳድነታችሁ ውስጣችሁ የሆነ እያገለገለ ያለው ነገር አለ ማለት ነው። ያለዚያማ በዚያ አይኖርም ነበር ።
እራስ ወዳድ ስለሆናችሁ ነው መኖር ያበዛችሁት እንዲሁም የገዛ እራሳችሁን እምትከባከቡት። ያ ባይሆን ኖሮ ፣ እራስ ወዳድነት ተፈጥሮ ተፈጥሮዓዊ ባይሆንማ ኖሮ የሰው ልጅ ከዘመናት በፊት ነበር ይጠፋ የነበረው።
በሚኒሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ተርበው እኛ እንበላለን ፣ በአለማችን ላይ ብዙዎች ተጠምተው እኛ እንጠጣለን፣ እራስ ወዳድነት ይሄ ነው። ታዲያ ሌሎች እራስ ወዳድ አትሁኑ እያሉ ሲያስተምሯችሁ ከተፈጥሮአችሁ ውጭ ሁኑ እያሏችሁ መሆኑን አትዘንጉ።
እኔ ግን ተፈጥሮአችሁን እንድትሆኑ አስተምሯችኋለሁ። ማንም ተፈጥሮ አችሁን እንድትሆኑ አይነግራችሁም። ምክንያቱም ደግሞ እነሱም እራስ ወዳዶች ስለሆኑ ነው።
ከሞት በኋላ የዘላለም ህይወት ፣ የተትረፈረፈ ህይወት ስለሚበዛላችሁ ይህች 70 እና 80 አመት የምትሆን ምድራዊ ህይወችታሁን ለውጡ እያሉ ይሰብኳች ኋል። ይሄ ግን ያወድማችኋል እንጅ አያበለጽጋችሁም ።
ኦሾ/Osho
"ህይወት፣ በምድር ላይ ከተቀደደ መንገድ ይልቅ ወዳሰኘህ አቅጣጫ የምትበርበትን ሰማይ ትመስላለች። የምድር ላይ ሀያላን በቀደዱልህ መንገድ ላይ በካርታቸው እየተመራህ መሄድ መንገድ ተጓዥ አያሰኝም፤ ኑሮህም ኑሮ አይሆንም። ገና ወዳልተዳሰሰው ድንግል ሰማይ ለመንጎድ የምታስችልህን ክንፍ አነቃቃ። የራስህ የሆነም ካርታ ከአሻራዎችህ ላይ ቅዳ።"
ኦሾ /Osho
"ራስን መሆን..
ኦሾ /Osho
"ራስን መሆን..
አለም ከገደል ማሚቶ የተሻለ አይደለም!!
ፍቅር በራችሁን አንኳኩቶ ያውቃል? በጭራሽ! ምክንያቱም ገና ፍቅር መስጠት አልቻላችሁም። ማስታወስ ያለባችሁ የሰጠነው ሁሉ ወደ እኛው ተመልሶ እንደሚመጣ ነው። ይህም ከህይወት ህጎች አንዱ ነው።
መላው ዓለም ከገደል ማሚቶ የተሻለ አይደለም። ጥላቻ እንሰጣለን፣ ጥላቻም ወደኛው ተመልሶ ይመጣል። ሌሎችን እንሳደባለን ከዛም ስድብ ወደኛ ተመልሶ ይመጣል። እሾህ ስንሰጥ እሾህ ወደኛው ተመልሶ ይመጣል፡፡ የምንሰጠው ሁሉ በተለያዩ መንገዶች ወደኛ ተመልሶ ይመጣል። ፍቅርን ካካፈልንም እንደዚሁ በተለያዪ መንገዶች ተመልሶ ወደኛው ይመጣል። ስፍር ቁጥር በሌላቸው መንገዶች ፍቅር ወደ እኛ ተመልሶ ካልመጣ ፍቅር እንዳልሰጠን ማወቅ አለብን፡፡
ፍቅር እምትሰጠው እንጂ እምትቀበለው አይደለም።
ኦሾ/osho
ፍቅር በራችሁን አንኳኩቶ ያውቃል? በጭራሽ! ምክንያቱም ገና ፍቅር መስጠት አልቻላችሁም። ማስታወስ ያለባችሁ የሰጠነው ሁሉ ወደ እኛው ተመልሶ እንደሚመጣ ነው። ይህም ከህይወት ህጎች አንዱ ነው።
መላው ዓለም ከገደል ማሚቶ የተሻለ አይደለም። ጥላቻ እንሰጣለን፣ ጥላቻም ወደኛው ተመልሶ ይመጣል። ሌሎችን እንሳደባለን ከዛም ስድብ ወደኛ ተመልሶ ይመጣል። እሾህ ስንሰጥ እሾህ ወደኛው ተመልሶ ይመጣል፡፡ የምንሰጠው ሁሉ በተለያዩ መንገዶች ወደኛ ተመልሶ ይመጣል። ፍቅርን ካካፈልንም እንደዚሁ በተለያዪ መንገዶች ተመልሶ ወደኛው ይመጣል። ስፍር ቁጥር በሌላቸው መንገዶች ፍቅር ወደ እኛ ተመልሶ ካልመጣ ፍቅር እንዳልሰጠን ማወቅ አለብን፡፡
ፍቅር እምትሰጠው እንጂ እምትቀበለው አይደለም።
ኦሾ/osho
በእዚህ ዓለም የህይወታችን መስመር የሚወሰነው ዘውትር ስለህይወት በምናንፀባርቀው አመለካከት ነው፤ ይህ አመለካከታችን ድርጊታችንን ይወልዳል ፤ ከአመለካከታችን የሚወለደው ድርጊት ደግሞ ወይ ያጠፋናል አላያም ያድነናል። በአጠቃላይ የወደፊት እጣፈንታችን ቅርጽ የሚበጀው ለህይወት በየቀኑ በምንሰጠው ትርጓሜ ነው። ስለዚህ የአንድ ሰው ወደ ነፍስ ወይም እውነተኛ ማንነቱ የሚያደርገውን የጉዞ አቅጣጫው የሚወስነው ለህይወት ባለው አመለካከት ይሆናል ማለት ነው። ነገር ግን የሰው ልጅ ይህ አመለካከቱ የእጣፈንታውን ተፈጥሮ እንደሚወሰን አውቆ ቢሆን ኖሮ እስከ ዛሬ ሲራመድ የነበረበትን የተበላሸ/ህይወትን በአስቀያሚነት እና በፋይዳቢስነት የሚስለውን/መንገድ እርግፍ አድርጎ በተወ ነበር።
ኦሾ/Osho
ኦሾ/Osho
🎎
"ዓለም በሙሉ በብርሃን ልትጥለቀለቅ ትችላለች፣ ውስጥህ ግን አሁንም በጨለማ እየኖረ ነው። ከውልደትህ በኃላ የተጨመረልህ ነገር ሁሉ እውነተኛ ማንነትህ ያለመሆኑን ቀስ በቀስ የሚያሳይህ ጭላንጭል ብርሃን በውስጥህ ሳይኖር በብርሃን የተሞላ ዓለም ምን ይጠቅምሀል?"
' ' '
OSHO ኦሾ
#ነፃነት/
ራስን የመሆን ድፍረት
"ዓለም በሙሉ በብርሃን ልትጥለቀለቅ ትችላለች፣ ውስጥህ ግን አሁንም በጨለማ እየኖረ ነው። ከውልደትህ በኃላ የተጨመረልህ ነገር ሁሉ እውነተኛ ማንነትህ ያለመሆኑን ቀስ በቀስ የሚያሳይህ ጭላንጭል ብርሃን በውስጥህ ሳይኖር በብርሃን የተሞላ ዓለም ምን ይጠቅምሀል?"
' ' '
OSHO ኦሾ
#ነፃነት/
ራስን የመሆን ድፍረት
#ምን ይዞ እንደሚመጣ ለማይታወቀው መጪው ጊዜ መፈንጠዝና በምኞት ፈረስ መጋለብ ካላቆማችሁና፣ ትናንትናንና ነገን ትታችሁ ዛሬን መኖር ካልጀመራችሁ ነፃ አትወጡም። ነፃነት አሁን እዚህ ናት።
ያለህበት ጊዜ ብቻ ናት እውነት ህልውና ያላት። መጪው ጊዜ ምኞትህ፣ ያለፈውም ጊዜ ትዝታህ ነው። ህልውና የላቸውም።
የአሁኑን ጊዜ በንቃት ማሳለፍ ንቃተ ሂሊናህና ካለፈውና ከመጪው ጊዜ ሰብስበህ በአሁኑ ጊዜ ላይ ማትኮር ማለት የነፃነትን ጣዕም ማወቅ ነው።
ኦሾ/Osho
ያለህበት ጊዜ ብቻ ናት እውነት ህልውና ያላት። መጪው ጊዜ ምኞትህ፣ ያለፈውም ጊዜ ትዝታህ ነው። ህልውና የላቸውም።
የአሁኑን ጊዜ በንቃት ማሳለፍ ንቃተ ሂሊናህና ካለፈውና ከመጪው ጊዜ ሰብስበህ በአሁኑ ጊዜ ላይ ማትኮር ማለት የነፃነትን ጣዕም ማወቅ ነው።
ኦሾ/Osho
እራስን መሆን ማለት እራሳችንን ከማንም ከምንም ጋር አለማመሳሰል ማለት ነው። እራስን መሆን ቀላል ነገር አይደለም፤ ነገር ግን ሌሎችን እንደመምሰል አይከብድም። ሁላችንም ልዩ እንድንሆን ባይፈልግ ኖር አምላክ ተመሳሳይ አድርጎ በፈጠረን ነበር። ነገር ግን እኛን የሚመስል ፈጽሞ አይደገምም።
ብዙ ጊዜ ሰዎች ራሳቸውን በሌሎች የማንነት ሚዛን እየመዘኑ ነው የበታችነት ስሜት የሚያድርባቸው፡፡
Osho/ኦሾ
ብዙ ጊዜ ሰዎች ራሳቸውን በሌሎች የማንነት ሚዛን እየመዘኑ ነው የበታችነት ስሜት የሚያድርባቸው፡፡
Osho/ኦሾ
አራት ዓይነት እብደት...
.
1💗
ብቸኝነት ብርዱ ገላህን ቀዝቅዞ
ከሰው መሀል አንተን ለብቻህ ሰቅዞ
መጠየቅ ስትጀምር ...
ለምን!...እንዴት?...ስትል?
ጥያቄህ በራሱ እብደት ነው የሚባል
ኡፍፍፍ...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
.
2💗
መጠየቅ ሰልችቶህ ከሕዝቦች ስትርቅ
በራስህ ዓለም ላይ ህሊናህ ሲራቀቅ
አፍህ ዝም ባለ
እብድ መባል አለ።
ኤጭ!...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
.
3💗
የሕዝብ ሁሉ ሀሳብ የእብደት ሲመስልህ
ያንተ አሳብ የእውነት....
እውነት እንደሆነ ውስጥህን ሲሰማህ
እብዱ ትባላለህ።
ኤዲያ!...
አውቆ የሚተኛ ሕዝብ መሀል ነቅተን፣
አቦ ተሰቃየን!
.
4💗
ዓለሙም እብድ ነው!
ግና ያለም እብደት ካንተ የሚለየው
አንተ የምታብደው ለዓለም ስትል ነው
ዓለሙ ያበደው አንተን ሊያሳብድ ነው።
ወገን ተሰቃየን!
አውቆ በተኛ አቋመ ቢስ መሐል...
ለብቻችን ነቅተን
አወይ ተሰቃየን!!
.....
ኤፍሬም ሥዩም ( ኑ ግድግዳ እናፍርስ!)
.
1💗
ብቸኝነት ብርዱ ገላህን ቀዝቅዞ
ከሰው መሀል አንተን ለብቻህ ሰቅዞ
መጠየቅ ስትጀምር ...
ለምን!...እንዴት?...ስትል?
ጥያቄህ በራሱ እብደት ነው የሚባል
ኡፍፍፍ...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
.
2💗
መጠየቅ ሰልችቶህ ከሕዝቦች ስትርቅ
በራስህ ዓለም ላይ ህሊናህ ሲራቀቅ
አፍህ ዝም ባለ
እብድ መባል አለ።
ኤጭ!...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
.
3💗
የሕዝብ ሁሉ ሀሳብ የእብደት ሲመስልህ
ያንተ አሳብ የእውነት....
እውነት እንደሆነ ውስጥህን ሲሰማህ
እብዱ ትባላለህ።
ኤዲያ!...
አውቆ የሚተኛ ሕዝብ መሀል ነቅተን፣
አቦ ተሰቃየን!
.
4💗
ዓለሙም እብድ ነው!
ግና ያለም እብደት ካንተ የሚለየው
አንተ የምታብደው ለዓለም ስትል ነው
ዓለሙ ያበደው አንተን ሊያሳብድ ነው።
ወገን ተሰቃየን!
አውቆ በተኛ አቋመ ቢስ መሐል...
ለብቻችን ነቅተን
አወይ ተሰቃየን!!
.....
ኤፍሬም ሥዩም ( ኑ ግድግዳ እናፍርስ!)
አራት መቶ ዓመታት የቀደመን ታላቁ ፈላስፋ ዘርያቆብ
የሀሳብ ባይተዋሮች ነን እኛ፡፡ ከክፍለ ዘመናት በፊት ቀድሞን የኖረው ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ ይበልጠናል፡፡ ይህ ታላቅ አሳቢ አይዛክ ኒውተን ወይም ኢማኑኤል ካንትና ሄግል ሳይወለዱ በፊት የተወለደ ተራማጅ ፈላስፋ ነው፡፡ ሀሳቦቹ ዛሬ በታላላቅ የአዉሮፓና አሜሪካ የፍልስፍና ትምህርት ቤቶች ይጠናሉ፡፡በአፍሪካ ጭምር የመጀመሪያው ዘመናዊ ፍልስፍናን ያስተማረ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ከ400 ዓመታት በፊት የኖረ ሲሆን አስደናቂ ፍልስፍናዎችም ነበሩት፡፡ በኃይማኖት ትምህርት ብዙ የገፋ ነበር፡፡ሆኖም አካባቢው ላይ ያስተዋላቸው ችግሮች መለስ ብሎ እውቀቱን እንዲያሰላስል መነሻ ሆነው፡፡ የተለያዩ ኃይማኖቶች የተለያዩ አምላኮችና፣ ምግባሮች ያስተምራሉ፡፡ ሁሉም የኔ ልክ ነው ብለውም ይነሳሉ፡፡ ያ እንዴት ይሆናል? እውነት አንድ ሆና ሳለ የተለያዩ አማኞች የተለያዩ መንገዶችን እየተከተሉ እውነቱ የኔ ነው ብለው ማሰባቸው ልክ ሊሆን አይችልም፡፡ ይህን መሰረት ይዞ ተነሳ ዘርያቆብ እናም እምነቶችን ለመዳኘት ምክኒያት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት አስረገጠ፡፡ በዚያ እምነትን መንካት እሳትን ከመንካት በላይ አስፈሪ በነበረበት ዘመን ደፍሮ ፍልስፍናዊ አተያይ ያስተዋወቀ ጀግና ኢትዮጵያዊ ነበር፡፡ምክኒያትን ማዕከል አድርጎ ራሱን ብሎም ዓለምን ለማየት የሞከረ ‹ዘመናዊ› ፈላስፋ ነው፡፡ ስለሱ ማወቅ የቻልነው በቅርቡ ነው፡፡እንደኢትዮጵያዊ አሳቢ ግን ከሱ በኋላ የተነሳ እሱን የሚፎካከር ፈላስፋ አልተነሳም፡፡ከአራት መቶ ዓመታት በፊት የኖረ ኢትዮጵያዊ ነው፤ ረኔ ዴካርት፣
ፍራንሲስ ቤከን፣ ዊሊያም ሸክስፒር፣ ቶማስ ሆብስ፣ ጆን ሎክና ሌሎች ታዋቂ የአዉሮፓ ፈላስፎችና ጠበብት በተነሱበት ዘመን የኖረ ወርቅማ ልቅና የነበረው አፍሪካዊ ሊቅ ነው፡፡በተለይ ኃይማኖትን ደፍሮ በምክኒያት ለመረዳት ያደረገው ጥረት ብዙ ፈተና አስከትሎበታል፡፡
ያም ሆኖ ከኢትዮጵያ ሰማይ በታች
አስደናቂ የፍልስፍና ሀሳቦችን የወለደ ቀዳማይ ፈላስፋችን ነው፡፡
#የዘር ካርድ...
#በሙሀመድ አሊ ቡርሃን
የሀሳብ ባይተዋሮች ነን እኛ፡፡ ከክፍለ ዘመናት በፊት ቀድሞን የኖረው ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ ይበልጠናል፡፡ ይህ ታላቅ አሳቢ አይዛክ ኒውተን ወይም ኢማኑኤል ካንትና ሄግል ሳይወለዱ በፊት የተወለደ ተራማጅ ፈላስፋ ነው፡፡ ሀሳቦቹ ዛሬ በታላላቅ የአዉሮፓና አሜሪካ የፍልስፍና ትምህርት ቤቶች ይጠናሉ፡፡በአፍሪካ ጭምር የመጀመሪያው ዘመናዊ ፍልስፍናን ያስተማረ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ከ400 ዓመታት በፊት የኖረ ሲሆን አስደናቂ ፍልስፍናዎችም ነበሩት፡፡ በኃይማኖት ትምህርት ብዙ የገፋ ነበር፡፡ሆኖም አካባቢው ላይ ያስተዋላቸው ችግሮች መለስ ብሎ እውቀቱን እንዲያሰላስል መነሻ ሆነው፡፡ የተለያዩ ኃይማኖቶች የተለያዩ አምላኮችና፣ ምግባሮች ያስተምራሉ፡፡ ሁሉም የኔ ልክ ነው ብለውም ይነሳሉ፡፡ ያ እንዴት ይሆናል? እውነት አንድ ሆና ሳለ የተለያዩ አማኞች የተለያዩ መንገዶችን እየተከተሉ እውነቱ የኔ ነው ብለው ማሰባቸው ልክ ሊሆን አይችልም፡፡ ይህን መሰረት ይዞ ተነሳ ዘርያቆብ እናም እምነቶችን ለመዳኘት ምክኒያት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት አስረገጠ፡፡ በዚያ እምነትን መንካት እሳትን ከመንካት በላይ አስፈሪ በነበረበት ዘመን ደፍሮ ፍልስፍናዊ አተያይ ያስተዋወቀ ጀግና ኢትዮጵያዊ ነበር፡፡ምክኒያትን ማዕከል አድርጎ ራሱን ብሎም ዓለምን ለማየት የሞከረ ‹ዘመናዊ› ፈላስፋ ነው፡፡ ስለሱ ማወቅ የቻልነው በቅርቡ ነው፡፡እንደኢትዮጵያዊ አሳቢ ግን ከሱ በኋላ የተነሳ እሱን የሚፎካከር ፈላስፋ አልተነሳም፡፡ከአራት መቶ ዓመታት በፊት የኖረ ኢትዮጵያዊ ነው፤ ረኔ ዴካርት፣
ፍራንሲስ ቤከን፣ ዊሊያም ሸክስፒር፣ ቶማስ ሆብስ፣ ጆን ሎክና ሌሎች ታዋቂ የአዉሮፓ ፈላስፎችና ጠበብት በተነሱበት ዘመን የኖረ ወርቅማ ልቅና የነበረው አፍሪካዊ ሊቅ ነው፡፡በተለይ ኃይማኖትን ደፍሮ በምክኒያት ለመረዳት ያደረገው ጥረት ብዙ ፈተና አስከትሎበታል፡፡
ያም ሆኖ ከኢትዮጵያ ሰማይ በታች
አስደናቂ የፍልስፍና ሀሳቦችን የወለደ ቀዳማይ ፈላስፋችን ነው፡፡
#የዘር ካርድ...
#በሙሀመድ አሊ ቡርሃን
"ትልቅ ሰው ትልቅ ሆኖ አይወለድም ፤ ትልቅ ለመሆን ራሱን ያሳድጋል እንጂ''/ሊዮ ቶልስቶይ /
አሁን ያለህበትን ሁኔታ እያየህ ለምን ትንሽ ሆንኩኝ ? ብለህ የምትቆጭ ከሆነ መቼም ቢሆን ትልቅ ሰው ልትሆን አትችልም።
:
ሁሉም በዓለም ላይ ያሉ ትልቅ ሰዎች መጀመሪያ ትንሽ ነበሩ። ማንም የማያውቃቸው ተራ ሰው ነበሩ ።
:
በጊዜ ሂደት ግን እውቀታቸውን እያዳበሩ አስተሳሰባቸውን እያሰፉ እምነታቸውን እያጠነከሩ ፍልስፍናቸውን እያጎለበቱ አመለካከታቸውን እያቀኑ ራእያቸውን እያገዘፉ ውሳኔያቸውን እያጠነከሩ አሁን ያላቸውን ትልቅ ማንነት ፈጠሩ ። አሁን
ያላቸውንም የማይደረስበት የመሰለ እጅግ ትልቅ ማንነትንም ፈጠሩ
:
ሊዮ ቶልስቶይ እንዳለው "ትልቅ ሰው ትልቅ ሆኖ
አይወለድም ፤ ትልቅ ለመሆን ራሱን ያሳድጋል እንጂ ።" አዎ ማንም ትልቅ ሆኖ አልተወለደም ።
:
ባራክ ኦባማ ፕሬዘዳንት ሆኖ አልተወለደም ። ራሱን ግን
የአሜሪካ መሪነት አዘጋጀ ። የመጀመሪ የአሜሪካ ጥቁር
ፕሬዘዳንትም ሆነ ።
:
ሀይሌ ገ/ስላሴ ሯጭ ሆኖ አልተወለደም ። ግን ራሱን
ለረጅም ርቀት ሯጭ ንጉስነት አዘጋጀው ። የ27 የዓለም
ሪከርዶችንም ሰባበረ ።
ሁለቱን ለምሳሌ አየን እንጂ ሁሉም ጀግኖች በአንድ ወቅት ራሳቸውን እንኳን መቆጣጠር የማይችሉ ህጻን ነበሩ ።
የሽንታቸውን ጨርቅ እንኳን እናታቸው ወይ አባታቸው
የሚቀይርላቸው የወላጆቻቸው ጥገኛ ነበሩ ።
ግን እነዚ ሰዎች ራሳቸውን ከጥገኝነት ህይወት አውጥተው አሁን ያሉበት ትልቅ ቦታ ደርሰዋል ።
አያችሁ ህይወት ሁላችንንም በልጅነታችን እንዴት ከጥገኝነት እንደምንላቀቅ አስተምራናለች ። አሁን ያለን ሂወት ላይ ያንን በልጅነታችን እንዴት ራሳችንን ከጥገኝነት እንዳወጣን በማስተማር ለድል እራሳችንን እናዘጋጅ ።
**
በልጅነታችን እየዳህን መሄድ ስንጀምር ምንም ያህል ጊዜ ብንወድቅ ተስፋ አንቆርጥም ፤ እንደገና እንሞክራለን እና ምን ልልህ ፈልጌ መሠለህ መውደቅን አትፍራ!!
#ከተነበበው
አሁን ያለህበትን ሁኔታ እያየህ ለምን ትንሽ ሆንኩኝ ? ብለህ የምትቆጭ ከሆነ መቼም ቢሆን ትልቅ ሰው ልትሆን አትችልም።
:
ሁሉም በዓለም ላይ ያሉ ትልቅ ሰዎች መጀመሪያ ትንሽ ነበሩ። ማንም የማያውቃቸው ተራ ሰው ነበሩ ።
:
በጊዜ ሂደት ግን እውቀታቸውን እያዳበሩ አስተሳሰባቸውን እያሰፉ እምነታቸውን እያጠነከሩ ፍልስፍናቸውን እያጎለበቱ አመለካከታቸውን እያቀኑ ራእያቸውን እያገዘፉ ውሳኔያቸውን እያጠነከሩ አሁን ያላቸውን ትልቅ ማንነት ፈጠሩ ። አሁን
ያላቸውንም የማይደረስበት የመሰለ እጅግ ትልቅ ማንነትንም ፈጠሩ
:
ሊዮ ቶልስቶይ እንዳለው "ትልቅ ሰው ትልቅ ሆኖ
አይወለድም ፤ ትልቅ ለመሆን ራሱን ያሳድጋል እንጂ ።" አዎ ማንም ትልቅ ሆኖ አልተወለደም ።
:
ባራክ ኦባማ ፕሬዘዳንት ሆኖ አልተወለደም ። ራሱን ግን
የአሜሪካ መሪነት አዘጋጀ ። የመጀመሪ የአሜሪካ ጥቁር
ፕሬዘዳንትም ሆነ ።
:
ሀይሌ ገ/ስላሴ ሯጭ ሆኖ አልተወለደም ። ግን ራሱን
ለረጅም ርቀት ሯጭ ንጉስነት አዘጋጀው ። የ27 የዓለም
ሪከርዶችንም ሰባበረ ።
ሁለቱን ለምሳሌ አየን እንጂ ሁሉም ጀግኖች በአንድ ወቅት ራሳቸውን እንኳን መቆጣጠር የማይችሉ ህጻን ነበሩ ።
የሽንታቸውን ጨርቅ እንኳን እናታቸው ወይ አባታቸው
የሚቀይርላቸው የወላጆቻቸው ጥገኛ ነበሩ ።
ግን እነዚ ሰዎች ራሳቸውን ከጥገኝነት ህይወት አውጥተው አሁን ያሉበት ትልቅ ቦታ ደርሰዋል ።
አያችሁ ህይወት ሁላችንንም በልጅነታችን እንዴት ከጥገኝነት እንደምንላቀቅ አስተምራናለች ። አሁን ያለን ሂወት ላይ ያንን በልጅነታችን እንዴት ራሳችንን ከጥገኝነት እንዳወጣን በማስተማር ለድል እራሳችንን እናዘጋጅ ።
**
በልጅነታችን እየዳህን መሄድ ስንጀምር ምንም ያህል ጊዜ ብንወድቅ ተስፋ አንቆርጥም ፤ እንደገና እንሞክራለን እና ምን ልልህ ፈልጌ መሠለህ መውደቅን አትፍራ!!
#ከተነበበው
#ማረጋገጫ አለህ ??
አማኙ ማረጋገጫ አለህ ስልህ የለም እያልኩህ አይደለም
ኤቲስቱ ማረጋገጫ አለህ ብዬ ስጠይቅህ አለ እያልኩህ
አይደለም።
ያመናችሁበትም ያላመናችሁበትም ምክንያት በጣም አስቂኝ
ነው።
ያመኑበት ስትጠይቃቸው ሊያስረዱት የሚፈልጉት በተፅፏል
ነው ኤቲስቶቹ ደግሞ ስላላየሁት የለም ይልሀል።
አማኞቹ ያለሱ እውነት የለም ብለው አዕምሮአቸውን ሳጥን
ውስጥ ከተውታል ኤቲስቶቹ ደግሞ ፈጣሪ የሚለውን ቃል
ሲሰሙ በቀጥታ ከሀይማኖቱ ከተሰጠው ትርጉም ጋር
ያገናኙታል የሀይማኖቱ ደግሞ አያሳምናቸውም ከሀይማኖት
ውጪ ፈጣሪን ማሰብ ለነሱ ዳገት ነውና የለም ይሉሀል።
ቢግባንግን የሚያመልክም አልጠፋም።ቢግባንግ event
እንጂ ፈጣሪ አይደለም።የዚህ ሁላ ነገር መሰረቱ አንድ
ሲንግል በአይን ልትታይ የማትችል አተም ነች ሊተመን
በማይችል ኢነርጂ ታምቃለች በመጨረሻም
ፈነዳች። የመጀመሪያው አተም ከየት መጣ???
በአለም ላይ ብዙ አምላኮች አሉ ሁሉም ደግሞ በጣም
አስገራሚው ነገር የሚወደቱን ፍጥረት የሰው ልጅን
የሚያቃጥሉበት የእሳት ባህር ባለቤት ናቸው which means hell. ይህንንም ፍርሀት የሰው ልጅ ያመልክ ይሰግድ ጀመር ገሀነም የሚለው ቃል ባይኖር አንድ አማኝ እዚህ ምድር ላይ አይኖርም ነበር። ታላቁ እስክንድርም እኔን አትፈራኝም ብሎ ጠየቀው ዲዮጋንም"ክፋ ነህ እንዴ??"ብሎ ጠየቀው
እስክንድርም"አይደለውም"ብሎ መለሰለት "ክፋ ካልሆንክ
ለምን እፈራሀለው???"የዲዮጋን ጥያቄ ነበር።
አምላካችን ደግ ቸር ነው ይሉሀል መልሰው ደግሞ ገሀነም
ይጥልሀል ይሉሀል።
ቸር ከሆነ ለምን ስትላቸው ቤተሰቦችህ እያጠፋህ ዝም
ይሉህ ነበር መልሳቸው ነው።ይቅርታ ሳጠፋ ዝም ባይሉኝም
የጋለ ብረት ምጣድ ላይ ግን ጥደውኝ አያውቁም።
ሳይንስ ብዙ ያልሆነ ጥቂትም የማይባል ግኝቶችን እያገኘ
ይገኛል።በአማኙና በኤቲስቱ መካከል ያለው ዱላ ቀረሽ
ንትርክ ሳይንስ ላይም ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛልን።በቅርብ ጊዜ
እንኳን በ big bang theory በራሱ አምላክ ያስፈልገዋል
አያስፈልገውም እየተነታረኩ ነው።
ማመን ትክክል ሊሆን አይችልም ኤቲስት መሆን ደግሞ
ጠቢብነት አይደለም።አንዱ ተነስቶ There is no GOD ቢል
ለኤቲስቱ የህይወት ቃል፣ለአማኙ ደግሞ የሞት ነው።
መልስ የሌለው ጥያቄ ሊኖር እንደሚችል መጠርጠር
አስፈላጊ ነው።
አማኙ ቅዠት ውስጥ ነው ኤቲስቱ ደግሞ በሎጂክ ስም
ይማግጣል።ከአማኙም ከኤቲስቱም አለመሆን !!
ኦሾ/osho
ምንጭ ብርሃነ ሂሊና
አማኙ ማረጋገጫ አለህ ስልህ የለም እያልኩህ አይደለም
ኤቲስቱ ማረጋገጫ አለህ ብዬ ስጠይቅህ አለ እያልኩህ
አይደለም።
ያመናችሁበትም ያላመናችሁበትም ምክንያት በጣም አስቂኝ
ነው።
ያመኑበት ስትጠይቃቸው ሊያስረዱት የሚፈልጉት በተፅፏል
ነው ኤቲስቶቹ ደግሞ ስላላየሁት የለም ይልሀል።
አማኞቹ ያለሱ እውነት የለም ብለው አዕምሮአቸውን ሳጥን
ውስጥ ከተውታል ኤቲስቶቹ ደግሞ ፈጣሪ የሚለውን ቃል
ሲሰሙ በቀጥታ ከሀይማኖቱ ከተሰጠው ትርጉም ጋር
ያገናኙታል የሀይማኖቱ ደግሞ አያሳምናቸውም ከሀይማኖት
ውጪ ፈጣሪን ማሰብ ለነሱ ዳገት ነውና የለም ይሉሀል።
ቢግባንግን የሚያመልክም አልጠፋም።ቢግባንግ event
እንጂ ፈጣሪ አይደለም።የዚህ ሁላ ነገር መሰረቱ አንድ
ሲንግል በአይን ልትታይ የማትችል አተም ነች ሊተመን
በማይችል ኢነርጂ ታምቃለች በመጨረሻም
ፈነዳች። የመጀመሪያው አተም ከየት መጣ???
በአለም ላይ ብዙ አምላኮች አሉ ሁሉም ደግሞ በጣም
አስገራሚው ነገር የሚወደቱን ፍጥረት የሰው ልጅን
የሚያቃጥሉበት የእሳት ባህር ባለቤት ናቸው which means hell. ይህንንም ፍርሀት የሰው ልጅ ያመልክ ይሰግድ ጀመር ገሀነም የሚለው ቃል ባይኖር አንድ አማኝ እዚህ ምድር ላይ አይኖርም ነበር። ታላቁ እስክንድርም እኔን አትፈራኝም ብሎ ጠየቀው ዲዮጋንም"ክፋ ነህ እንዴ??"ብሎ ጠየቀው
እስክንድርም"አይደለውም"ብሎ መለሰለት "ክፋ ካልሆንክ
ለምን እፈራሀለው???"የዲዮጋን ጥያቄ ነበር።
አምላካችን ደግ ቸር ነው ይሉሀል መልሰው ደግሞ ገሀነም
ይጥልሀል ይሉሀል።
ቸር ከሆነ ለምን ስትላቸው ቤተሰቦችህ እያጠፋህ ዝም
ይሉህ ነበር መልሳቸው ነው።ይቅርታ ሳጠፋ ዝም ባይሉኝም
የጋለ ብረት ምጣድ ላይ ግን ጥደውኝ አያውቁም።
ሳይንስ ብዙ ያልሆነ ጥቂትም የማይባል ግኝቶችን እያገኘ
ይገኛል።በአማኙና በኤቲስቱ መካከል ያለው ዱላ ቀረሽ
ንትርክ ሳይንስ ላይም ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛልን።በቅርብ ጊዜ
እንኳን በ big bang theory በራሱ አምላክ ያስፈልገዋል
አያስፈልገውም እየተነታረኩ ነው።
ማመን ትክክል ሊሆን አይችልም ኤቲስት መሆን ደግሞ
ጠቢብነት አይደለም።አንዱ ተነስቶ There is no GOD ቢል
ለኤቲስቱ የህይወት ቃል፣ለአማኙ ደግሞ የሞት ነው።
መልስ የሌለው ጥያቄ ሊኖር እንደሚችል መጠርጠር
አስፈላጊ ነው።
አማኙ ቅዠት ውስጥ ነው ኤቲስቱ ደግሞ በሎጂክ ስም
ይማግጣል።ከአማኙም ከኤቲስቱም አለመሆን !!
ኦሾ/osho
ምንጭ ብርሃነ ሂሊና
💞 💕 💘
#ለማወቅ የምንፈልገውን ነገር ሁሉ መጀመርያ እናፈቅረው ዘንድ የተገባ ነው። ለማንኛውም የህይወት ዘርፍ የስኬት ቁልፍ ፍቅር ነው። ዳቪንቺ ስዕልን ከምንም በላይ አፈቀራት ታወቀባትም። ሞዛርት ሙዚቃን አፈቀራት ፥ ከፍ ከፍም አረገችው። ሼክስፒር ስነፅሁፍ ፍቅረኛው ሆነች፥በስሟም አነገሰችው። የፍቅር ንጉስ እየሱስ ክርስቶስ በፍቅሩ አለምን ማረከ ፥ አለም ተንበረከከችለትም።
እውነተኛ ታላቅነት እንግዲ ሚመጣው ከማፍቀር ነው። እየሱስን መምሰል ሚቻለው በፍቅር ብቻ ነው። ቡድሃን ለመሆን ማፍቀር ግዴታ ነው። ቡድሃ ማፍቀር ስትችል እግዚሃብሔርን መምሰል ትጀምራለህ ይላል።
ፍቅር ነፍስን በሚወዱት ሰው ውስጥ መግደል ነው ይለናል ኦሾ። ፍቅር ከስግብግብነት የፀዳ ማንነት ነው። እውነተኛ አፍቃሪ የሚያፈቅረውን ሰው ደስታ ለማየት ለ መሰዋት የተዘጋጀ ነው።
ሀዲስ አለማየው ስለ ፍቅር እንዲ ይላሉ፥ አይንን ክፉ ከማየት ምላስን ክፉ ከማውራት ጆሮንም ከመስማት ፥ምናብንም ከፉ ከማለም የማይከለክል ፍቅር ፥ ፍቅር አይደለም። ፍቅር ለ አሉታዊ ውጤት ምንም ግምት አይሰጥም። ለፍቅር አለም ሁሌም ብሩህ ናት።
ፍቅር ሙሉነትን የመፈለግ መንገድ ነው። ግን ይለናል ኦሾ ቀጥሎ ፦ እንደመሰለው እንደመሰላት እንደመሰለን እንፋቀራለን። በማይረባ መንገድ። እራስ ወዳድነትን በተላበሰ መንገድ እናፈቅራለን። ማፍቀር ግዴት ይመስል እናፈቅራለን። ጥላቻ አርግዘን እናፈቅራለን። እራስ ወዳድነትን አርግዘን እናፈቅራለን። ፈርተን እናፈቅራለን። ከዛም ሲሰለችን ስለ እውነተኛ ፍቅር መሞት ማላዘን እንጅምራለን። ባዶነት ይሰማናል። ትላንት ያፈቀርነው ዛሬ ጠላት ይሆንብናል። የማናውቀው ሰው ጠላት ሊሆነን አይችልም ። ጠላት እንኳን ጠላት ለመሆን የግድ በጓደኝነት ውስጥ ማለፍ አለበት። ልክ ያልሆነ ፍቅር ወዳጅ ሳይሆን ጠላት ያተርፋል። የማፍቀር ብቸኛው ምክንያት ፍቅር ካልሆነ ሌላው አላፊ ነውና ጭንቀትን ይወልዳል።
#ጥበብ ከጲላጦስ ቅፅ አንድ የተቀነጫጨበ
#ለማወቅ የምንፈልገውን ነገር ሁሉ መጀመርያ እናፈቅረው ዘንድ የተገባ ነው። ለማንኛውም የህይወት ዘርፍ የስኬት ቁልፍ ፍቅር ነው። ዳቪንቺ ስዕልን ከምንም በላይ አፈቀራት ታወቀባትም። ሞዛርት ሙዚቃን አፈቀራት ፥ ከፍ ከፍም አረገችው። ሼክስፒር ስነፅሁፍ ፍቅረኛው ሆነች፥በስሟም አነገሰችው። የፍቅር ንጉስ እየሱስ ክርስቶስ በፍቅሩ አለምን ማረከ ፥ አለም ተንበረከከችለትም።
እውነተኛ ታላቅነት እንግዲ ሚመጣው ከማፍቀር ነው። እየሱስን መምሰል ሚቻለው በፍቅር ብቻ ነው። ቡድሃን ለመሆን ማፍቀር ግዴታ ነው። ቡድሃ ማፍቀር ስትችል እግዚሃብሔርን መምሰል ትጀምራለህ ይላል።
ፍቅር ነፍስን በሚወዱት ሰው ውስጥ መግደል ነው ይለናል ኦሾ። ፍቅር ከስግብግብነት የፀዳ ማንነት ነው። እውነተኛ አፍቃሪ የሚያፈቅረውን ሰው ደስታ ለማየት ለ መሰዋት የተዘጋጀ ነው።
ሀዲስ አለማየው ስለ ፍቅር እንዲ ይላሉ፥ አይንን ክፉ ከማየት ምላስን ክፉ ከማውራት ጆሮንም ከመስማት ፥ምናብንም ከፉ ከማለም የማይከለክል ፍቅር ፥ ፍቅር አይደለም። ፍቅር ለ አሉታዊ ውጤት ምንም ግምት አይሰጥም። ለፍቅር አለም ሁሌም ብሩህ ናት።
ፍቅር ሙሉነትን የመፈለግ መንገድ ነው። ግን ይለናል ኦሾ ቀጥሎ ፦ እንደመሰለው እንደመሰላት እንደመሰለን እንፋቀራለን። በማይረባ መንገድ። እራስ ወዳድነትን በተላበሰ መንገድ እናፈቅራለን። ማፍቀር ግዴት ይመስል እናፈቅራለን። ጥላቻ አርግዘን እናፈቅራለን። እራስ ወዳድነትን አርግዘን እናፈቅራለን። ፈርተን እናፈቅራለን። ከዛም ሲሰለችን ስለ እውነተኛ ፍቅር መሞት ማላዘን እንጅምራለን። ባዶነት ይሰማናል። ትላንት ያፈቀርነው ዛሬ ጠላት ይሆንብናል። የማናውቀው ሰው ጠላት ሊሆነን አይችልም ። ጠላት እንኳን ጠላት ለመሆን የግድ በጓደኝነት ውስጥ ማለፍ አለበት። ልክ ያልሆነ ፍቅር ወዳጅ ሳይሆን ጠላት ያተርፋል። የማፍቀር ብቸኛው ምክንያት ፍቅር ካልሆነ ሌላው አላፊ ነውና ጭንቀትን ይወልዳል።
#ጥበብ ከጲላጦስ ቅፅ አንድ የተቀነጫጨበ
.. የተፈጠረው ሰውም የፈጠረው አምላክም አያልቅባቸውም። ምናልባት ሰውን ከሁሉ ሌላ ፍጡር የተለየ ብቸኛ የሚያደርገው፣ ከመልአክ እኩል ደግና በጎ አድራጊ ለመሆን መቻሉ፣ እና በዚያም መጠን ከሰይጣን እኩል ከይሲ እርኩስ ስራዎችን እንደ ቅዱስ ተግባር እያመለካቸውና እየታዘዛቸው መፈፀሙ ነው። ሂትለር ብዙ ሚሊዮን የሚኖሩባትን ሀገር አፀዳታለሁ፣ አይሁድ የሚባለውን ቆሻሻ ከኛ ከንፁሀን ነጮች አገር እየጠረግኩም፣ እያቃጠልኩም አስወጣዋለሁ ብሎ ተነስቶ ዛቻውን ፈፀመ።
.. ሂትለር ሰው አይደለም አንልም መቸስ። ግን ሂትለር ሰው ከሆነ "ሰው ሰይጣን ነው፣ ሰይጣን ሰው ነው" አንዳንዴ።
.. የሰው ልጅ ምድርን እስኪያጣብባት መብዛቱ እነ ሂትለርን በይህ በኩል፣ እነ ማህታማ ጋንድሂን በያ በኩል ማስገኘት ምን ያቅተዋል ?"
*
👉 ስብሀት ገብረ እግዚአብሄር
("ሰውና ማስመሰል".. ከተሰኘው መጣጥፉ የተቀነጨ
.. ሂትለር ሰው አይደለም አንልም መቸስ። ግን ሂትለር ሰው ከሆነ "ሰው ሰይጣን ነው፣ ሰይጣን ሰው ነው" አንዳንዴ።
.. የሰው ልጅ ምድርን እስኪያጣብባት መብዛቱ እነ ሂትለርን በይህ በኩል፣ እነ ማህታማ ጋንድሂን በያ በኩል ማስገኘት ምን ያቅተዋል ?"
*
👉 ስብሀት ገብረ እግዚአብሄር
("ሰውና ማስመሰል".. ከተሰኘው መጣጥፉ የተቀነጨ
