የሌሊት ወፍ
“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
ከዶ/ር እዮብ ገፅ የተወሰደ
“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
ከዶ/ር እዮብ ገፅ የተወሰደ
#የኦሾ እይታ
በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር»
።።።።። //።።።።።። //።።።።።።
<<ሕይወትህን የምታከብራት ከሆነ ልታድናት የምትችለዉ አንተ ብቻ እንጂ ሌላ አዳኝ የላትም።የሚለዉ ኦሾ ህይወት የተፈጠረችዉ በሙላት ለመኖር ነዉ ስለዚህ ይህ ትክክል ነው ይህ ደግሞ ስህተት ነዉ አትበል ።በማለት ምሳሌ አስቀምጦልናል፧ ለምሳሌ እግዚአብሔር አለምን ፈጠረ።ሰይጣንም አብሮ ባይፈጠር ኖሮ አለም ላይ ምንም ባልኖረ ነበር። ለሆነዉ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ሀላፊነቱን ቢወስድም ሰይጣን በበኩሉ አዳምና ሄዋንን ከበለሱ እንዲበሉ ባያደርግ ኖሮ የዛሬዋ አለም እንዲህ ባልሆነ ነበር ።
#የመጀመሪያዉ አብዮተኛ ሰይጣን መሆኑን አታውቁም?መጀመሪያው አመፀኛ ምድራዊዉን ህይወት የገለፀው እኮ እሱ ነው።እንዲያ ባይሆን ዛሬም አዳም እና ሄዋን ሳር እየበሉ ይኖሩ
ነበር።በኤደን ገነት ታዲያ ምን ስራ ይኖራቸዉ ነበር? እግዚአብሔር እንደሆነ ከእውቀት ዛፍ አትብሉ ብሏቸዋል! ከዚህ ከዘላለም የህይወት ዛፍም አትብሉ በማለት አዟቸዋል። እና ምን ቀረ? ማወቅ በተከለከለበት መኖር በታገደበት አለም እንደ አጋዘን ጥንቸል ሳር ብሉ አላቸው,,,,, እናም በሰይጣን ምህረት ይችን አለም ለማየት በቃን። እግዚአብሄር የፈጠረው አዳም እና ሄዋን ያሉበት ምድር ብቻ ነው።ከዚያ ውጪ ነገር ግን የፈጠረው ሰይጣን ነው ።ልብ በሉ! ቡድሀ፣እየሱስ፣ሙሴ,,,,, የሀይማኖት መሪዎች ስም የሰማነው ሰይጣን በመኖሩ ብቻ ነው ።እናም ህይወት በተቃርኖዋ ውስጥ እንኖርባት ዘንድ የተገባ ነው ።"በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር!!"
#የኦሾ እይታ
በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር»
።።።።። //።።።።።። //።።።።።።
<<ሕይወትህን የምታከብራት ከሆነ ልታድናት የምትችለዉ አንተ ብቻ እንጂ ሌላ አዳኝ የላትም።የሚለዉ ኦሾ ህይወት የተፈጠረችዉ በሙላት ለመኖር ነዉ ስለዚህ ይህ ትክክል ነው ይህ ደግሞ ስህተት ነዉ አትበል ።በማለት ምሳሌ አስቀምጦልናል፧ ለምሳሌ እግዚአብሔር አለምን ፈጠረ።ሰይጣንም አብሮ ባይፈጠር ኖሮ አለም ላይ ምንም ባልኖረ ነበር። ለሆነዉ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ሀላፊነቱን ቢወስድም ሰይጣን በበኩሉ አዳምና ሄዋንን ከበለሱ እንዲበሉ ባያደርግ ኖሮ የዛሬዋ አለም እንዲህ ባልሆነ ነበር ።
#የመጀመሪያዉ አብዮተኛ ሰይጣን መሆኑን አታውቁም?መጀመሪያው አመፀኛ ምድራዊዉን ህይወት የገለፀው እኮ እሱ ነው።እንዲያ ባይሆን ዛሬም አዳም እና ሄዋን ሳር እየበሉ ይኖሩ
ነበር።በኤደን ገነት ታዲያ ምን ስራ ይኖራቸዉ ነበር? እግዚአብሔር እንደሆነ ከእውቀት ዛፍ አትብሉ ብሏቸዋል! ከዚህ ከዘላለም የህይወት ዛፍም አትብሉ በማለት አዟቸዋል። እና ምን ቀረ? ማወቅ በተከለከለበት መኖር በታገደበት አለም እንደ አጋዘን ጥንቸል ሳር ብሉ አላቸው,,,,, እናም በሰይጣን ምህረት ይችን አለም ለማየት በቃን። እግዚአብሄር የፈጠረው አዳም እና ሄዋን ያሉበት ምድር ብቻ ነው።ከዚያ ውጪ ነገር ግን የፈጠረው ሰይጣን ነው ።ልብ በሉ! ቡድሀ፣እየሱስ፣ሙሴ,,,,, የሀይማኖት መሪዎች ስም የሰማነው ሰይጣን በመኖሩ ብቻ ነው ።እናም ህይወት በተቃርኖዋ ውስጥ እንኖርባት ዘንድ የተገባ ነው ።"በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር!!"
#የኦሾ እይታ
ማንነት ምንድን ነው?
( ክፍል ፩ )
፨፨፨
ማንነት ስለሌላ ነገር የሚፈጠር ሀሳብ ሳይሆን ሰው መሆንን ማሰብ ነው ። ማንነት የውጫዊ ሀሳብ ሳይሆን የውስጥ ማሰብ ነው ። ሰው ማለት የሚያስብ እንስሳ ማለት ነው ። ማንነቱ ማሰቡ እንጂ አሳቡን መሆኑ አይደለም ። ሀሳብ ተለዋዋጭ ነው ። የማሰብ ማንነት ግን የማይለዋወጥ ቋሚ ሰው መሆን ነው ። ማንነት የሌላ መሆን ሀሳብ አይደለም ። ማንነት ሰው መሆንን ማሰብ ማለት ነው ። የምታስበው ሀሳብን ሆነህ መኖር አትችልም ።
፧
ማንነት ውጫዊ ሀሳብን ሆኖ መኖር ሳይሆን ሰው መሆንን በማሰብ መኖር ነው ። እያወራን ያለንው ስለሰው ልጅ ማንነት ከሆነ የሰው ልጅ ማንነት ሰው የመሆንን እውነት በማሰብ መኖር ነው ። ካልሆነ የማንነት አማራጩ ሁለት ነው ። አንደኛውና ትክክለኛው ውሳኔ ሰው ሆኖ በማሰብ የመኖር ማንነት ነው ። ይህ ካልሆነ የሌላን ሀሳብ ለመኖር ሰው የመሆንን ሕይወት በቁም መሰናበት ።
፧
ማንነት ራሽናል እውቀት ነው ። ማንነት ስሜት አይደለም ። ያለ-ራሽናል እውቀት ስሜት ግልብ ህልም ነው ። ለስሜት ለስሜት ከብትም ስሜት አለው ። የሰው ልጅ ማንነት ከከብት የሚለየው ግርድፉን ስሜቱን በራሽናል እውቀት መግራት ከቻለ ነው ። ስለራስህ የሚሰማህ ነገር ሁሉ የአንተ ማንነት አይደለም ። ማንነት የመሆን ስሜት ሳይሆን ራስን የማወቅ እውቀት ነው ። በራሽናል መንገድ ራስህን መዝነህ የምታውቀው እሱ የአንተ ማንነት ነው ። ማንነት ሀሳብ አይደለም ። ማንነት እውቀት ነው ። እውቀት ሀሳብ አይደለም ። እውቀት የማሰብ ብቃት ነው ። ስለዚህ እውቀት ማንነት የሚሆነው ያለማወቅን ማወቅ ካስቻለ ብቻ ነው ።
፧
ማንነት ክህሎት ነው ። ማንነት በገና መደርደር አይደለም ። በገና መደርደር ክህሎት ካልታከለበት የጉልበት ስራ ነው ። ማሲንቆ መገዝገዝ ማንነት አይደለም ። ማሲንቆ መገዝገዝ ክህሎት ከሌለው ክር መገዝገዝ ነው ። ክህሎት ከበሮ መምታር አይደለም ። ከበሮ መምታት ብቻውን እንጨት ማጋጨት ነው ። ማንነት ድምፆችን መፍጠር ሳይሆን የሙዚቃን ጥበብ የመፍጠር ክህሎት ነው ።
ማንነት...
ይቀጥላል...
ምንጭ ፦ ሰው መሆን
ደራሲ ፦ ቢልልኝ ሐብታሙ
፨ ማንነት ላንተ/ላንቺስ ምንድን ነው?
( ክፍል ፩ )
፨፨፨
ማንነት ስለሌላ ነገር የሚፈጠር ሀሳብ ሳይሆን ሰው መሆንን ማሰብ ነው ። ማንነት የውጫዊ ሀሳብ ሳይሆን የውስጥ ማሰብ ነው ። ሰው ማለት የሚያስብ እንስሳ ማለት ነው ። ማንነቱ ማሰቡ እንጂ አሳቡን መሆኑ አይደለም ። ሀሳብ ተለዋዋጭ ነው ። የማሰብ ማንነት ግን የማይለዋወጥ ቋሚ ሰው መሆን ነው ። ማንነት የሌላ መሆን ሀሳብ አይደለም ። ማንነት ሰው መሆንን ማሰብ ማለት ነው ። የምታስበው ሀሳብን ሆነህ መኖር አትችልም ።
፧
ማንነት ውጫዊ ሀሳብን ሆኖ መኖር ሳይሆን ሰው መሆንን በማሰብ መኖር ነው ። እያወራን ያለንው ስለሰው ልጅ ማንነት ከሆነ የሰው ልጅ ማንነት ሰው የመሆንን እውነት በማሰብ መኖር ነው ። ካልሆነ የማንነት አማራጩ ሁለት ነው ። አንደኛውና ትክክለኛው ውሳኔ ሰው ሆኖ በማሰብ የመኖር ማንነት ነው ። ይህ ካልሆነ የሌላን ሀሳብ ለመኖር ሰው የመሆንን ሕይወት በቁም መሰናበት ።
፧
ማንነት ራሽናል እውቀት ነው ። ማንነት ስሜት አይደለም ። ያለ-ራሽናል እውቀት ስሜት ግልብ ህልም ነው ። ለስሜት ለስሜት ከብትም ስሜት አለው ። የሰው ልጅ ማንነት ከከብት የሚለየው ግርድፉን ስሜቱን በራሽናል እውቀት መግራት ከቻለ ነው ። ስለራስህ የሚሰማህ ነገር ሁሉ የአንተ ማንነት አይደለም ። ማንነት የመሆን ስሜት ሳይሆን ራስን የማወቅ እውቀት ነው ። በራሽናል መንገድ ራስህን መዝነህ የምታውቀው እሱ የአንተ ማንነት ነው ። ማንነት ሀሳብ አይደለም ። ማንነት እውቀት ነው ። እውቀት ሀሳብ አይደለም ። እውቀት የማሰብ ብቃት ነው ። ስለዚህ እውቀት ማንነት የሚሆነው ያለማወቅን ማወቅ ካስቻለ ብቻ ነው ።
፧
ማንነት ክህሎት ነው ። ማንነት በገና መደርደር አይደለም ። በገና መደርደር ክህሎት ካልታከለበት የጉልበት ስራ ነው ። ማሲንቆ መገዝገዝ ማንነት አይደለም ። ማሲንቆ መገዝገዝ ክህሎት ከሌለው ክር መገዝገዝ ነው ። ክህሎት ከበሮ መምታር አይደለም ። ከበሮ መምታት ብቻውን እንጨት ማጋጨት ነው ። ማንነት ድምፆችን መፍጠር ሳይሆን የሙዚቃን ጥበብ የመፍጠር ክህሎት ነው ።
ማንነት...
ይቀጥላል...
ምንጭ ፦ ሰው መሆን
ደራሲ ፦ ቢልልኝ ሐብታሙ
፨ ማንነት ላንተ/ላንቺስ ምንድን ነው?
የሰው ልጅ የሚሰቃየው ራሱ ባጠረው አጥር ራሱ በገነባው ቅጥር ራሱ በሸበበው ውትርትር ነው። የዘር ፣ የሃይማኖት ፣ የርዕዮተ አለም ፣..... የፍልስፍና አጥር ። የብቸኝነት ፣ የአውሬነት ፣ የወፈፌነት ፣ ......አስማት የሚመስል አጥር።...
"ክቡር ድንጋይ"
"ክቡር ድንጋይ"
የትኛውም መሻትና ፍላጎትህ ወይም ውድቀትህና ስኬትህ በአንተ ማንነት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚገለጥ እውነት ነው::
ስለዚህ አንተ ከምታውቀውና ከምታምነው በላይ ሌላ ማንነት አለህና እሱን ፈልገህ አግኝ::''
።።//።።
#ተዓምራት እና ጣዖታት
ስለዚህ አንተ ከምታውቀውና ከምታምነው በላይ ሌላ ማንነት አለህና እሱን ፈልገህ አግኝ::''
።።//።።
#ተዓምራት እና ጣዖታት
"በተመስጦ ማሰላሰል ለፅምናና ለብቻ ለመሆን መድፈር ነው። ቀስ በቀስ በራሳችሁ ላይ አዲስ ባህሪ አዲሲ የህያውነት መንፈስ፣ አዲስ ውብት እንዲሁም አዲስ አስተሳሰብ ሲለመልም ይሰማችኋል። ይህ ደግሞ ከማንም የተዋሳችሁት ሳይሆን በውስጣችሁ እያደገ ያለ ስሜት ነው።"
*
ኦሾ/osho
*
ኦሾ/osho
#ማንም ሰዉ ክፋ ሆኖ የተወለደ የለም ነገር ግን ሰዉን ክፋ የምያደርገዉ እራሱ የሰዉ ልጅ በሚያደርጋቸዉ ክፋ ተግባር ክፋትን ያስተምረዋል እሾህ የሌለዉ መሬት
እንቅፋት የሌለዉ ህይወት የለም እና ሁሉንም በትግስት እንለፍ !!
እንቅፋት የሌለዉ ህይወት የለም እና ሁሉንም በትግስት እንለፍ !!
#እናትነት ፍቅር ነው -ንፁህ ፍቅር ፣ ያልተከለሰ ፍቅር።
እናት መሆን ማለት ንፁህ ፍቅር መስጠት መቻል ፣ ሰውን በፍቅር ማፍቀር ፣ ሰውን ሲያደግ ለማየት ባለ ጉጉት ሳቢያ መርዳት ማለት ነው።
# እውነተኛ ሃኪም እናት ናት!!!
ኦሾ/Osho
እናት መሆን ማለት ንፁህ ፍቅር መስጠት መቻል ፣ ሰውን በፍቅር ማፍቀር ፣ ሰውን ሲያደግ ለማየት ባለ ጉጉት ሳቢያ መርዳት ማለት ነው።
# እውነተኛ ሃኪም እናት ናት!!!
ኦሾ/Osho
ያለ ቅድመ ሁኔታ የሚያፈቅሩ አፍቃሪ ይሁኑ ፍቅር ወሰን ወደሌለው መጨረሻ ወደሌለው ዓለም የሚያስገባ በር ነው ።
ፍቅር መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ የለውም ይጀምራል እንጂ አያበቃም ።
ኦሾ/osho
ፍቅር መጀመሪያ እንጂ መጨረሻ የለውም ይጀምራል እንጂ አያበቃም ።
ኦሾ/osho
❤ ፍቅር በኦሾ እይታ ❤
<< ብዙ ሰዎች በፍቅርና በወዳጅነት መካከል ያለው ልዩነት ጠፍቶአቸው በጎዳናው ላይ ሲዳክሩ ይስተዋላል ። አንድ መስለው ይታዩዋቸዋል ፤ ነገር ግን አንድ አይደሉም ። ይመሳሰሉባቸዋል ነገር ግን በእውነታው አይመሳሰሉም ። እንዳውም ከወዳጅነት ይልቅ ከፍቅር ጋር የሚመሳሰለው ጥላቻ ነው ። ጥላቻ ተቃራኒውን ነው - ወዳጅነት የጥላቻን እውነታ ደብቆ የፍቅርን መልክ ይይዛል ። ነገር ግን ፍቅርን እየገደለ ነው ። አንድን ሰው የግል ንብረት አድርጎ እንደማሰብ (Possessiveness) መርዘኛ ነገር የለም ። ይኽን በሚገባ ከተረዳችሁ ወደ ቀጣዩ ጉዳይ እንዝለቅ... >> ይላል ።
💗
<< ለብዙዎች እንዲህ ሆኗልና ለእናንተም እንዳይሆንባችሁ ልንገራችሁ፤ ምክንያቱም በፍቅርና በግንኙነት መካከል ያለው ልዩነት ግራ አጋብቷችኋል ። በተለይም ከውጭ ሆነው ሲመለከቱ የኖሩ ሰዎች ሰለባው ሲሆኑ ኖረዋል ወዳጅነትንና የግል ማድረግን እንደ ፍቅር ወስደውት አይቻለሁ ። በዚህ መንገድም እውነተኛውን ነገር አጥተውታል ።
💗
ሰውን የግል ለማድረግ መሻት የውሸት ፍቅር ነው ። ከእንዲህ አይነቱ ስሜት ቢያንስ ጥላቻ ይሻላል ። በጥላቻ ውስጥ ውሸት የለም ። ከዚያ በላይ ደግሞ ጥላቻ አንድ ቀን ፍቅር ሆኖ ሊቀየር ይችላል የሰውን ልጅ የግል የማድረግ ፍላጎት ግን ፈጽሞ ወደ ፍቅር ሊቀየር አይችልም ።
💕
<< ፍቅር ማለት በምትወደው ሰው ነፍስ ውስጥ ራስህን መግደል ነው ። ፍቅር ማለት ሞት ነው ፤ የሚቻልህን ያህል ጥልቅ በሆነ ሞት ውስጥ ትገባለህ ፤ የምትሞተውም በምትወዳት ሴት ነፍስ ውስጥ ነው ። ዕለት ዕለት ወደ ጥልቅ የነፍሷም ቦታ ትወሰዳለህ ፤ ፍቅር ወደምታፈቅራት ሴት የነፍስ ቦታ የምታደርገው ዘላለማዊ ጉዞ ነው ። ጉዞውም ማቆሚያ የለውም ። አንዲትን ሴት ስታፈቅራት በአንተ ሕይወት ውስጥ ከአንተ በላይ ዋጋ አላት ። ፍቅር ማለት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መማረክ ማለት ነው ። ምክንያቱም አንዳች ቅድሙ ሁኔታ የምታስቀምጥለት ከሆነ ከምታፈቅረው ሰው በላይ ለራስህ ዋጋ ሰጥተሃል ማለት ነው ። ራስህን ዋነኛው ጉዳይ አድርገህ በፍቅር ውስጥ ስትመለከት ተፈቃሪዋ መጠቀሚያህ ሆነች ፤ የፍላጎትህ ማርኪያ አደረግሃት፤ በሌሎች ዘንድ መደነቂያህ ሆነች...መነሻውም መድረሻውም አንተ ሆነሃል ።
💕
ፍቅር ደግሞ መነሻው አንተ መድረሻው ግን ተፈቃሪው ይሁን ይልሃል ። በተፈቃሪው ውስጥ ትሟላለህ ፣ ትጠፋለህ ። የመሞት ሂደትና ክስተት ነው ። ለዚህም ነው ሰዎች ፍቅር የሚፈሩት ። ስለፍቅር ልታወራ ፣ ልትዘፍን ፣ ትችላለህ ነገር ግን የልብህ ጥልቅ ስሜት ቢመረመር ፍቅርን በመፍራት የተሞላ ነው ....
ኦሾ/Osho
ጥበብ 6
<< ብዙ ሰዎች በፍቅርና በወዳጅነት መካከል ያለው ልዩነት ጠፍቶአቸው በጎዳናው ላይ ሲዳክሩ ይስተዋላል ። አንድ መስለው ይታዩዋቸዋል ፤ ነገር ግን አንድ አይደሉም ። ይመሳሰሉባቸዋል ነገር ግን በእውነታው አይመሳሰሉም ። እንዳውም ከወዳጅነት ይልቅ ከፍቅር ጋር የሚመሳሰለው ጥላቻ ነው ። ጥላቻ ተቃራኒውን ነው - ወዳጅነት የጥላቻን እውነታ ደብቆ የፍቅርን መልክ ይይዛል ። ነገር ግን ፍቅርን እየገደለ ነው ። አንድን ሰው የግል ንብረት አድርጎ እንደማሰብ (Possessiveness) መርዘኛ ነገር የለም ። ይኽን በሚገባ ከተረዳችሁ ወደ ቀጣዩ ጉዳይ እንዝለቅ... >> ይላል ።
💗
<< ለብዙዎች እንዲህ ሆኗልና ለእናንተም እንዳይሆንባችሁ ልንገራችሁ፤ ምክንያቱም በፍቅርና በግንኙነት መካከል ያለው ልዩነት ግራ አጋብቷችኋል ። በተለይም ከውጭ ሆነው ሲመለከቱ የኖሩ ሰዎች ሰለባው ሲሆኑ ኖረዋል ወዳጅነትንና የግል ማድረግን እንደ ፍቅር ወስደውት አይቻለሁ ። በዚህ መንገድም እውነተኛውን ነገር አጥተውታል ።
💗
ሰውን የግል ለማድረግ መሻት የውሸት ፍቅር ነው ። ከእንዲህ አይነቱ ስሜት ቢያንስ ጥላቻ ይሻላል ። በጥላቻ ውስጥ ውሸት የለም ። ከዚያ በላይ ደግሞ ጥላቻ አንድ ቀን ፍቅር ሆኖ ሊቀየር ይችላል የሰውን ልጅ የግል የማድረግ ፍላጎት ግን ፈጽሞ ወደ ፍቅር ሊቀየር አይችልም ።
💕
<< ፍቅር ማለት በምትወደው ሰው ነፍስ ውስጥ ራስህን መግደል ነው ። ፍቅር ማለት ሞት ነው ፤ የሚቻልህን ያህል ጥልቅ በሆነ ሞት ውስጥ ትገባለህ ፤ የምትሞተውም በምትወዳት ሴት ነፍስ ውስጥ ነው ። ዕለት ዕለት ወደ ጥልቅ የነፍሷም ቦታ ትወሰዳለህ ፤ ፍቅር ወደምታፈቅራት ሴት የነፍስ ቦታ የምታደርገው ዘላለማዊ ጉዞ ነው ። ጉዞውም ማቆሚያ የለውም ። አንዲትን ሴት ስታፈቅራት በአንተ ሕይወት ውስጥ ከአንተ በላይ ዋጋ አላት ። ፍቅር ማለት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መማረክ ማለት ነው ። ምክንያቱም አንዳች ቅድሙ ሁኔታ የምታስቀምጥለት ከሆነ ከምታፈቅረው ሰው በላይ ለራስህ ዋጋ ሰጥተሃል ማለት ነው ። ራስህን ዋነኛው ጉዳይ አድርገህ በፍቅር ውስጥ ስትመለከት ተፈቃሪዋ መጠቀሚያህ ሆነች ፤ የፍላጎትህ ማርኪያ አደረግሃት፤ በሌሎች ዘንድ መደነቂያህ ሆነች...መነሻውም መድረሻውም አንተ ሆነሃል ።
💕
ፍቅር ደግሞ መነሻው አንተ መድረሻው ግን ተፈቃሪው ይሁን ይልሃል ። በተፈቃሪው ውስጥ ትሟላለህ ፣ ትጠፋለህ ። የመሞት ሂደትና ክስተት ነው ። ለዚህም ነው ሰዎች ፍቅር የሚፈሩት ። ስለፍቅር ልታወራ ፣ ልትዘፍን ፣ ትችላለህ ነገር ግን የልብህ ጥልቅ ስሜት ቢመረመር ፍቅርን በመፍራት የተሞላ ነው ....
ኦሾ/Osho
ጥበብ 6
በተፈጥሮ የበላይ እና የበታች የሚባል ነገር የለም ። ትንሿ ሳር ሰማይ ካለው ትልቅ ኮከብ ጋር እኩል ዎጋ አላት ። በተፈጥሮ የስልጣን ተዋረድ የለም ፤ ማንም የበታች ማንም የበላይ አይደለም ፤ ሁሉም ራሱን ነው ። አንዳንድ ዛፎች ረጃጅም፣ሌሎች ደግሞ አጫጭሮች ናቸው ። ይህ ማለት ግን ረጅሙ ዛፍ ታላቅ፣የበላይ ነው ፣ እንደዚሁም ትንሹ ዛፍ የበታች ነው ማለት አይደለም።
በተፈጥሮ የሰዎች የስልጣን ተዋረድ የሚባል ነገር የለም።
➣Osho/ኦሾ
ኃይማኖትን መመርመር
በተፈጥሮ የሰዎች የስልጣን ተዋረድ የሚባል ነገር የለም።
➣Osho/ኦሾ
ኃይማኖትን መመርመር
#መልአከ ሞት!
****
#የሞት መልአክ የአብረሃምን ቤት አንክዋክቶ ነፍሱን ሊወስዳት እንደመጣ ይነግረዋል።አብረሃምም በቅድምያ ከእግዚአብሄር ጋር እንዲነጋገር እድሉን ጠይቆ ወደ ቤቱ ውስጥ ይገባና እግዚአብሄርን በፀሎት ጠርቶ ይጠይቀዋል፣-"ለመሆኑ ጌታ ሆይ! የወዳጁን ነፍስ የሚወስድ ወዳጅ አይተህ ታውቃለህን?"
እግዚአብሄርም መለሰለት "አንተስ ከወዳጁ ለመገናኘት የማይናፍቅ ወዳጅ አይተህ ታውቃለህን?"
አብረሃም መልስ አጥሮት በሩን ከፍቶ ሲወጣ መልአከ ሞት ቆሞ ሲጠብቀው ተመለከተ።
* ** *
ጥበብ ከጲላጦስ
****
#የሞት መልአክ የአብረሃምን ቤት አንክዋክቶ ነፍሱን ሊወስዳት እንደመጣ ይነግረዋል።አብረሃምም በቅድምያ ከእግዚአብሄር ጋር እንዲነጋገር እድሉን ጠይቆ ወደ ቤቱ ውስጥ ይገባና እግዚአብሄርን በፀሎት ጠርቶ ይጠይቀዋል፣-"ለመሆኑ ጌታ ሆይ! የወዳጁን ነፍስ የሚወስድ ወዳጅ አይተህ ታውቃለህን?"
እግዚአብሄርም መለሰለት "አንተስ ከወዳጁ ለመገናኘት የማይናፍቅ ወዳጅ አይተህ ታውቃለህን?"
አብረሃም መልስ አጥሮት በሩን ከፍቶ ሲወጣ መልአከ ሞት ቆሞ ሲጠብቀው ተመለከተ።
* ** *
ጥበብ ከጲላጦስ
"ህይወታችሁን አክብሩ ። ህይወታችሁን በማክበርም የሌሎችን ህይወት ማክበር ትጀምራላችሁ።"
:
እንድታስታውሱ የምመክራቹሁ በህይወት እንድትኖሩ እና ህይወት ምን እንደሆነች ለማወቅ እንድትሞክሩ ነው። በሕይወት መኖራችሁ በጣም ውድ ነገር መሆኑ አስታውሱ። ህይወትን አክብሩ ። ከህይወት የበለጠ የተቀደሰ ፣ ከሕይወት የበለጠ መለኰታዊ የሆነ ነገር የለም።
#ህይወታችሁን አክብሩ። ህይወታችሁን በማክበርም የሌሎችን ህይወት ማክበር ትጀምራላችሁ። ዋናው ምክንያት ህይወትን ካከበራችሁ #አበባን እንኳን መቅጠፍ ይከብዳችኃል። አበባው ያስደስታችኃል ፣
ትወዱታላችሁ ፣ ትዳስሱታላችሁ ፣ ታሸቱታላችሁ ነገር ግን አበባውን መቅጠፍ ልክ እንደ እናንተ ህይወት ያለውን አካል ማጥፋት እና ማሰቃየት ነው።
#Osho/ኦሾ
#ኃይማኖትን መመርመር
:
እንድታስታውሱ የምመክራቹሁ በህይወት እንድትኖሩ እና ህይወት ምን እንደሆነች ለማወቅ እንድትሞክሩ ነው። በሕይወት መኖራችሁ በጣም ውድ ነገር መሆኑ አስታውሱ። ህይወትን አክብሩ ። ከህይወት የበለጠ የተቀደሰ ፣ ከሕይወት የበለጠ መለኰታዊ የሆነ ነገር የለም።
#ህይወታችሁን አክብሩ። ህይወታችሁን በማክበርም የሌሎችን ህይወት ማክበር ትጀምራላችሁ። ዋናው ምክንያት ህይወትን ካከበራችሁ #አበባን እንኳን መቅጠፍ ይከብዳችኃል። አበባው ያስደስታችኃል ፣
ትወዱታላችሁ ፣ ትዳስሱታላችሁ ፣ ታሸቱታላችሁ ነገር ግን አበባውን መቅጠፍ ልክ እንደ እናንተ ህይወት ያለውን አካል ማጥፋት እና ማሰቃየት ነው።
#Osho/ኦሾ
#ኃይማኖትን መመርመር
ከባህልና ከህግ የታሰረው ማህበረሰብ በፍቅር ተይዞ የምኳትቱን የልጆቻቸውን ጭወት አይሰሙም፡፡ ምክንያቱም ፍቅር ከባህልና ከህግ በላይ ነው፡፡
ማህበረሰቡ ከባህልና ከህግ በታች ናቸው፡፡ ሰው ከሁሉም በላይ በፍቅር ከፍ ብሎ መኖር ስችል እራሱ ባወጣው ህግና ደንብ እራሱን አስሮ በውስጡ የበታችነትን ስሜት ተከናንቦ ያልፋል፡፡
በፍቅር ውስጥ የምትኖር ነፍስ ብቻ ባሀልና ድክምታቼውን ለመሸፈን የምጠቀሙትን ህግ በላይ ሆና ለፍቅር አምላክ ትቀርባለች፡፡
ቅናት ፍቅርን የምንንድበት መሳርያ ነው፡፡ ፍቅር መልካም ስሜት ስሆን ቅናት ክፉ ስሜት ነው፡፡
:
መልካም የፍቅር ስሜት እንደ ውሃና ግባቶች ተጠቅመ ፍቅርን
በውስጥ ስታንከባክበውና ስታለመልመው ቅናት ደግሞ ክፉ የስሜት መሳርያ ነው ያለመለምከውን የምቆራርጡበት፡፡
የአንድ ጠቢብ ነፍስ
በዮሐንስ አሰማሃኝ/ቁቤ
ማህበረሰቡ ከባህልና ከህግ በታች ናቸው፡፡ ሰው ከሁሉም በላይ በፍቅር ከፍ ብሎ መኖር ስችል እራሱ ባወጣው ህግና ደንብ እራሱን አስሮ በውስጡ የበታችነትን ስሜት ተከናንቦ ያልፋል፡፡
በፍቅር ውስጥ የምትኖር ነፍስ ብቻ ባሀልና ድክምታቼውን ለመሸፈን የምጠቀሙትን ህግ በላይ ሆና ለፍቅር አምላክ ትቀርባለች፡፡
ቅናት ፍቅርን የምንንድበት መሳርያ ነው፡፡ ፍቅር መልካም ስሜት ስሆን ቅናት ክፉ ስሜት ነው፡፡
:
መልካም የፍቅር ስሜት እንደ ውሃና ግባቶች ተጠቅመ ፍቅርን
በውስጥ ስታንከባክበውና ስታለመልመው ቅናት ደግሞ ክፉ የስሜት መሳርያ ነው ያለመለምከውን የምቆራርጡበት፡፡
የአንድ ጠቢብ ነፍስ
በዮሐንስ አሰማሃኝ/ቁቤ