ራሳችንን ለማወቅ የሌሎችን ሰዎች አይኖች መመልከታችን በጣም አስገራሚ ነው።
ሰው ሌሎች ሰዎች ስለሱ መጥፎ ነገር ሊናገሩ ይችላሉ ብሎ በማሰብ ይፈራል። እሱን በተመለከተ ሰዎች ጥሩ ሲናገሩ ይደሰታል፤ ምክንያቱም ስለ ራሱ ያለው እውቀት ሌሎች ስለሱ በሚሰጡት አስተያየት ላይ የተመሰረተ ነው። ስለራሱ ቅጽበታዊ የሆነ እውቀት የለውም፤ ራሱን የሚያውቅበት ቀጥተኛ ተሞክሮ የለውም። ራስን በቀጥታ የማወቅ ተሞክሮ ሊከሰት የሚችል ቢሆንም ከራሳችን ለማምለጥ ስለምንሞክር ግን አይከሰትም።
አይምሮን ለመጋፈጥ የመጀመርያው ዘዴ ሌሎች ስለሚሉት ወይም ለሌሎች እንዴት ሆነን መታየት እንደሚኖርብን አለመጨነቅ ነው። አንድ ሰው መሰረታዊ እሱነቱን በቀጥታ መጋፈጥ አለበት። ለብቻው ሆኖ አይምሮውን በመክፈት ውስጡ ያለውን ነገር መመልከት አለበት። ይህ የድፍረት ተግባር ነው። ከውስጥ ወዳለው ሲዖል ለመግባት የሚያስችል የድፍረት ተግባር። እርቃን ማንነትን ለመመልከት የሚወሰድ የድፍረት እርምጃ ነው። ታላቅ ድፍረት ያስፈልጋል።
:
#ኦሾ/Osho
#ምንጭ ፦ የነፍስ መንገድ
ሰው ሌሎች ሰዎች ስለሱ መጥፎ ነገር ሊናገሩ ይችላሉ ብሎ በማሰብ ይፈራል። እሱን በተመለከተ ሰዎች ጥሩ ሲናገሩ ይደሰታል፤ ምክንያቱም ስለ ራሱ ያለው እውቀት ሌሎች ስለሱ በሚሰጡት አስተያየት ላይ የተመሰረተ ነው። ስለራሱ ቅጽበታዊ የሆነ እውቀት የለውም፤ ራሱን የሚያውቅበት ቀጥተኛ ተሞክሮ የለውም። ራስን በቀጥታ የማወቅ ተሞክሮ ሊከሰት የሚችል ቢሆንም ከራሳችን ለማምለጥ ስለምንሞክር ግን አይከሰትም።
አይምሮን ለመጋፈጥ የመጀመርያው ዘዴ ሌሎች ስለሚሉት ወይም ለሌሎች እንዴት ሆነን መታየት እንደሚኖርብን አለመጨነቅ ነው። አንድ ሰው መሰረታዊ እሱነቱን በቀጥታ መጋፈጥ አለበት። ለብቻው ሆኖ አይምሮውን በመክፈት ውስጡ ያለውን ነገር መመልከት አለበት። ይህ የድፍረት ተግባር ነው። ከውስጥ ወዳለው ሲዖል ለመግባት የሚያስችል የድፍረት ተግባር። እርቃን ማንነትን ለመመልከት የሚወሰድ የድፍረት እርምጃ ነው። ታላቅ ድፍረት ያስፈልጋል።
:
#ኦሾ/Osho
#ምንጭ ፦ የነፍስ መንገድ
1. ሩቅ ካለ የለየኸው ጠላትህ በላይ ከጎንህ ያለው ውዳጅህ ጉዳት ይሰርግሃል።
2. መገንጠል.... መለየት እንጂ መበታተን አይደለም። መነጠል ራስን መለካት በራስ ልክ መወሰን... ልክን መሆን እንጂ መጀነን አይደለም።
ተነጥሎ ማሰብ ከአጀብ ጎርፍ ያድናል። መነጠል ጎራ መጎበን አይደለም። ከራስ ህሊና መታረቅ ነው። የራስ ታማኝ ሰብዕ መሆንና ንጥረ ስፍርን ለክቶ በመጠን ልኬታ መርጋት ነው።
......
ህገ-ሰው
1. ሰው ካለ ጉድለት አለ.... ሰው ማለት ከቶም ላይሞላ የሚባዝን ባለ መንታ እልህ ፍጡር ነው። በመደገፍም ሆነ በመቃወም እኩል ጉልበት አለው። ልዩነቱ የአቅጣጫ ጀርባ ጀርብነታቸው ብቻ ነው።
እንዲህ በተቃሮኖ የተማገረ ሰው... ዳር ከያዘ ውሎው ሁሉ ዳሩን ስለማስጠበቅ እንጂ መሀል ካለው ማዕድ ገድ እንዲል አይታሰበውም።
...
2. የሰው ችግሩ በሰልፍ ካሰበ ነው። ሰልፍ ለጦርነት እንጂ ለሀሳብ ባዕድ ነው። ሰው ቡድን ከሆነ የሚሳካለት የጦር ጀብዱ ነው።
ሀገር ላቅና ካለ ወይም ከፍ ያለ ዓላማ ማዝለቅ ሲሻ ግን የሚያዋጣው የግሉ የሆነን የመረዳት ስፍር ነውና አጀቡ ይከሳል ወይም ይቀንሳል።
ምክኒያቱም ለእያንዳንዱ አዋቂ በላጭ አዋቂ አለው። እናም በልህቀት ያስተዋሉ ጥቂት ራሶች በላቀ ስፍራቸው ስለብዙሃን የሚሆን ህብረ ፀሀይ ሆነው ህዝባቸውን ይፈነጥቁታል....
በአጀብ ስንጋፋ ግን... በቡድን የሚያስብ የጭንቅላት ተፈጥሮ የለምና በቀጥታ ጉዳዩ ወደ ስሜታሙ የስጋ ጦርነት ይጎመጃል። እያንዳንዷ ደቂቃ ክብረ ስብዕናን ወይም አምለካከትን በመሸንቆር ላይ ትገደባለች።
....
'ቆይ ጉዱን ነው አደባባይ እማወጣለት' እያሉ ከፍ ያለ ዓላማ አለኝ ማለት... ለራስም ካለመታመን ነው።
3. ማናችንም ከግድፈት አንጠራም። ምክኒያቱም ሰው ማለት እየተሳሳተ የሚነቃና በስተቱ የሚማር እንጂ በቅቶ የተመረተ ምርት አይደለም።
እንደ ብሔር እንደኃይማኖት ወይም እንደ ሀገር የ'በቅተናል...' ወይም 'ልከኞች እኛ ነን' ወረት (fashine) ውስጥ ሳንገባ አልቀረንም ብል እችል ይሆን?
2. መገንጠል.... መለየት እንጂ መበታተን አይደለም። መነጠል ራስን መለካት በራስ ልክ መወሰን... ልክን መሆን እንጂ መጀነን አይደለም።
ተነጥሎ ማሰብ ከአጀብ ጎርፍ ያድናል። መነጠል ጎራ መጎበን አይደለም። ከራስ ህሊና መታረቅ ነው። የራስ ታማኝ ሰብዕ መሆንና ንጥረ ስፍርን ለክቶ በመጠን ልኬታ መርጋት ነው።
......
ህገ-ሰው
1. ሰው ካለ ጉድለት አለ.... ሰው ማለት ከቶም ላይሞላ የሚባዝን ባለ መንታ እልህ ፍጡር ነው። በመደገፍም ሆነ በመቃወም እኩል ጉልበት አለው። ልዩነቱ የአቅጣጫ ጀርባ ጀርብነታቸው ብቻ ነው።
እንዲህ በተቃሮኖ የተማገረ ሰው... ዳር ከያዘ ውሎው ሁሉ ዳሩን ስለማስጠበቅ እንጂ መሀል ካለው ማዕድ ገድ እንዲል አይታሰበውም።
...
2. የሰው ችግሩ በሰልፍ ካሰበ ነው። ሰልፍ ለጦርነት እንጂ ለሀሳብ ባዕድ ነው። ሰው ቡድን ከሆነ የሚሳካለት የጦር ጀብዱ ነው።
ሀገር ላቅና ካለ ወይም ከፍ ያለ ዓላማ ማዝለቅ ሲሻ ግን የሚያዋጣው የግሉ የሆነን የመረዳት ስፍር ነውና አጀቡ ይከሳል ወይም ይቀንሳል።
ምክኒያቱም ለእያንዳንዱ አዋቂ በላጭ አዋቂ አለው። እናም በልህቀት ያስተዋሉ ጥቂት ራሶች በላቀ ስፍራቸው ስለብዙሃን የሚሆን ህብረ ፀሀይ ሆነው ህዝባቸውን ይፈነጥቁታል....
በአጀብ ስንጋፋ ግን... በቡድን የሚያስብ የጭንቅላት ተፈጥሮ የለምና በቀጥታ ጉዳዩ ወደ ስሜታሙ የስጋ ጦርነት ይጎመጃል። እያንዳንዷ ደቂቃ ክብረ ስብዕናን ወይም አምለካከትን በመሸንቆር ላይ ትገደባለች።
....
'ቆይ ጉዱን ነው አደባባይ እማወጣለት' እያሉ ከፍ ያለ ዓላማ አለኝ ማለት... ለራስም ካለመታመን ነው።
3. ማናችንም ከግድፈት አንጠራም። ምክኒያቱም ሰው ማለት እየተሳሳተ የሚነቃና በስተቱ የሚማር እንጂ በቅቶ የተመረተ ምርት አይደለም።
እንደ ብሔር እንደኃይማኖት ወይም እንደ ሀገር የ'በቅተናል...' ወይም 'ልከኞች እኛ ነን' ወረት (fashine) ውስጥ ሳንገባ አልቀረንም ብል እችል ይሆን?
በፀሎቱ ቋንቋ ከሚማርከኝ ይልቅ በልቡ ንፅህና የሚገዛኝ እኔ ፊት የተወደደ ነው "
💗
ሀሰን አልባስሪ አንድ ቀን ሀቢብ አልጃሚ ቤት የምሽት የፀሎት ሰአት ይደርስና ለመስገድ አበረው ይቆማሉ። ነገር ግን ፀሎት እንደጀመሩ አል-አጃሚ አንድ የፀሎት ቃል አበላሽተው ሲናገሩ ያስተዋሉት አል ባስሪ በተበላሸ ቃል ከሚሰግድ ሰው ጋር አልፀልይም ብለው ፀሎታቸውን አቋርጠው ሌላ ቦታ በመፀለይ ገብተው ይተኛሉ ።
💗
በእንቅልፍ ሰአታቸው ፈጣሪ ይመጣና ይጠይቃቸዋል ሀሰን በተበላሸ ቃላት ከፀለየው አል አጃሚ ኋላ ቆመህ ወደ እኔ ብትፀልይ ኖሮ በዘመንህ ከፀለይከው ሁሉ ይህን እሰማልህ ነበር" ።አንተ የቃላት መበላሸትን እንጂ የልብ ጉድፍን አላስተዋልክም ።እኔ ግን በፀሎቱ ቋንቋ ከሚማርከኝ ይልቅ በልቡ ንፅህና የሚገዛኝ እኔ ፊት የተወደደ ነው " በማለት ፈጣሪ አል ሀሰንን ገሰፀው ።
💗
#ሱፊዝም
#ከጲላጦስ
💗
ሀሰን አልባስሪ አንድ ቀን ሀቢብ አልጃሚ ቤት የምሽት የፀሎት ሰአት ይደርስና ለመስገድ አበረው ይቆማሉ። ነገር ግን ፀሎት እንደጀመሩ አል-አጃሚ አንድ የፀሎት ቃል አበላሽተው ሲናገሩ ያስተዋሉት አል ባስሪ በተበላሸ ቃል ከሚሰግድ ሰው ጋር አልፀልይም ብለው ፀሎታቸውን አቋርጠው ሌላ ቦታ በመፀለይ ገብተው ይተኛሉ ።
💗
በእንቅልፍ ሰአታቸው ፈጣሪ ይመጣና ይጠይቃቸዋል ሀሰን በተበላሸ ቃላት ከፀለየው አል አጃሚ ኋላ ቆመህ ወደ እኔ ብትፀልይ ኖሮ በዘመንህ ከፀለይከው ሁሉ ይህን እሰማልህ ነበር" ።አንተ የቃላት መበላሸትን እንጂ የልብ ጉድፍን አላስተዋልክም ።እኔ ግን በፀሎቱ ቋንቋ ከሚማርከኝ ይልቅ በልቡ ንፅህና የሚገዛኝ እኔ ፊት የተወደደ ነው " በማለት ፈጣሪ አል ሀሰንን ገሰፀው ።
💗
#ሱፊዝም
#ከጲላጦስ
ከ"ሕማማት" መጽሐፍ የተወሰደ
አዳም ረታ እንዳስነበበን
እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ያውቃል ማለት አስቀድሞ ይወስናል ማለት አይደለም ። ነገሮችም የሚሆኑት እግዚአብሔር አስቀድሞ ስላወቃቸው ሳይሆን በተቃራኒው እርሱ ያወቃቸው ስለሚሆኑ ነው ። እግዚአብሔር ስለወደፊት ያለው እውቀት እኛ ስላለፈው ታሪክ የዓይን ምስክሮች ሆነን እንደምናውቀው ያለ ነው።.../ አስቀድሞ የተነገሩ ትንቢቶች እንዴት ይታያሉ መጀመሪያ ትንቢት እንደ መንስኤ ሳይሆን እንደ ውጤት ካልተረዳነው ነገሩን ለመረዳት እንቸገራለን ። ትንቢቶች የሚነገሩት ነገሮች ስለሚሆኑ ነው እንጂ ነገሮች የሚሆኑት ትንቢት ስለተነገረ አይደለም "ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድይህ ሆነ ተብለው የተጻፉት ቃላት ሁሉም የተጻፉት ትንቢቱ እንደተፈጸመ ከተረጋገጠ በኋላ ነው እንጂ ትንቢቱ እስከሚፈጸምባት እስከመጨረሻዋ ቅጽበት ድረስ ትንቢቱ የተነገረበት ሰው ትንቢቱን የመለወጥ እድል አለው ። እግዚአብሔር የተናገርኩት ከሚጠፋ ብሎ የሰዎችን የመዳን በር የሚዘጋ ጨካኝ አይደለም ስለሰው ልጅ መጥፋትና መዳን የሚነገሩ ትንቢቶች እንደሁኔታው ሊፈጸሙ የሚችሉ ትንቢቶች (conditional prophecies ) ናቸው እንጂ እንደ ሰማይ ምድር ማለፍ የማይለወጡ ትንቢቶች (fixed prophecies )አይደሉም ።
"ሕማማት " መጽሐፍ
ከ ገፅ 72-ገፅ 82
አዳም ረታ እንዳስነበበን
እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ያውቃል ማለት አስቀድሞ ይወስናል ማለት አይደለም ። ነገሮችም የሚሆኑት እግዚአብሔር አስቀድሞ ስላወቃቸው ሳይሆን በተቃራኒው እርሱ ያወቃቸው ስለሚሆኑ ነው ። እግዚአብሔር ስለወደፊት ያለው እውቀት እኛ ስላለፈው ታሪክ የዓይን ምስክሮች ሆነን እንደምናውቀው ያለ ነው።.../ አስቀድሞ የተነገሩ ትንቢቶች እንዴት ይታያሉ መጀመሪያ ትንቢት እንደ መንስኤ ሳይሆን እንደ ውጤት ካልተረዳነው ነገሩን ለመረዳት እንቸገራለን ። ትንቢቶች የሚነገሩት ነገሮች ስለሚሆኑ ነው እንጂ ነገሮች የሚሆኑት ትንቢት ስለተነገረ አይደለም "ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድይህ ሆነ ተብለው የተጻፉት ቃላት ሁሉም የተጻፉት ትንቢቱ እንደተፈጸመ ከተረጋገጠ በኋላ ነው እንጂ ትንቢቱ እስከሚፈጸምባት እስከመጨረሻዋ ቅጽበት ድረስ ትንቢቱ የተነገረበት ሰው ትንቢቱን የመለወጥ እድል አለው ። እግዚአብሔር የተናገርኩት ከሚጠፋ ብሎ የሰዎችን የመዳን በር የሚዘጋ ጨካኝ አይደለም ስለሰው ልጅ መጥፋትና መዳን የሚነገሩ ትንቢቶች እንደሁኔታው ሊፈጸሙ የሚችሉ ትንቢቶች (conditional prophecies ) ናቸው እንጂ እንደ ሰማይ ምድር ማለፍ የማይለወጡ ትንቢቶች (fixed prophecies )አይደሉም ።
"ሕማማት " መጽሐፍ
ከ ገፅ 72-ገፅ 82
በሁለንተናው ኃይል ቅጽበቷን ኑራት
:
ይህ ቀላሉ የደስተኝነት ሚስጢር ነው። ምንም ነገር ስታደርግ ያለፈው ሁኔታ በጭንቅላትህ እንዲሄድ አትፍቀድለት ፣ ለወደፊት ያለውም እንዲረብሽህ አትፍቀድለት። ምክንያቱም ያለፈው አብቅቷል ፣ የወደፊቱ ገናአልመጣም። በትዝታ መኖር ፣ የወደፊቱን በማለም መኖር፣በሌለ ነገር ላይ መኖር ነው። በሌለ ነገር ላይ ስትኖር አሁን ያለው ነገር እያመለጠህ ነው።
በዚህም ብላሽ ትሆናለህ ምክንያቱም መላው ህይወትህን ትስታለህ።
:
#ኦሾ/OSho/
#የነፃነት መንገድ
:
ይህ ቀላሉ የደስተኝነት ሚስጢር ነው። ምንም ነገር ስታደርግ ያለፈው ሁኔታ በጭንቅላትህ እንዲሄድ አትፍቀድለት ፣ ለወደፊት ያለውም እንዲረብሽህ አትፍቀድለት። ምክንያቱም ያለፈው አብቅቷል ፣ የወደፊቱ ገናአልመጣም። በትዝታ መኖር ፣ የወደፊቱን በማለም መኖር፣በሌለ ነገር ላይ መኖር ነው። በሌለ ነገር ላይ ስትኖር አሁን ያለው ነገር እያመለጠህ ነው።
በዚህም ብላሽ ትሆናለህ ምክንያቱም መላው ህይወትህን ትስታለህ።
:
#ኦሾ/OSho/
#የነፃነት መንገድ
ፍቅር ማካፈል እንጂ ልመና አይደለም ፍቅር ንጉስ እንጂ ለማኝ አይደለም። ፍቅር የሚያውቀው መስጠትን ብቻ ነው። ስለልመና የሚያውቀው ነገር የለም።
ፍቅር ከውጪ የሚገኝ ነገር አይደለም። ፍቅር የውስጣዊ ህልውናችሁ ሙዚቃ ነው። ማንም ፍቅርን ሊሰጣችሁ አይችልም።
ፍቅር ከውስጣችሁ የሚፈልቅ እንጂ ከውጭ የሚገኝ አይደለም። ፍቅርን ልትገዙት የምትችሉበት ሱቅ ወይም ገበያ የለም። ፍቅር በየትኛውም ዋጋ ሊገዛ አይችልም። ፍቅር ውስጣዊ ማበብ ነው።
ኦሾ/osho
ፍቅር ከውጪ የሚገኝ ነገር አይደለም። ፍቅር የውስጣዊ ህልውናችሁ ሙዚቃ ነው። ማንም ፍቅርን ሊሰጣችሁ አይችልም።
ፍቅር ከውስጣችሁ የሚፈልቅ እንጂ ከውጭ የሚገኝ አይደለም። ፍቅርን ልትገዙት የምትችሉበት ሱቅ ወይም ገበያ የለም። ፍቅር በየትኛውም ዋጋ ሊገዛ አይችልም። ፍቅር ውስጣዊ ማበብ ነው።
ኦሾ/osho
ማህበረሠቡ ያለማቋረጥ እንድታገል ፣ እንድትወዳደር ይጠብቅሀል። ሌላውን ጥለህ እንድታልፍ የሌላውን እግር ጎትተህ አንተ ከፍታውን እንድትይዝ ፣ ስልጣኑን ሀይሉን እንድትሸከም ይጠብቅሀል።
ይህ አለም እኮ ከጦር ሜዳ አይተናነስም። እናም ቀዝቃዛ ጦርነት ያለማቋረጥ እየተካሄደ ነው። እያንዳንዱ ሰው የእያንዳንዱ ሰው ጠላት ነው። ወዳጅነት በሌለበት አለም ውስጥ ነው ያለነው።ጠላትነት ብቻ ነው ያለው።
:
#የአምላክነት ቅምሻ
ኦሾ/Osho
ይህ አለም እኮ ከጦር ሜዳ አይተናነስም። እናም ቀዝቃዛ ጦርነት ያለማቋረጥ እየተካሄደ ነው። እያንዳንዱ ሰው የእያንዳንዱ ሰው ጠላት ነው። ወዳጅነት በሌለበት አለም ውስጥ ነው ያለነው።ጠላትነት ብቻ ነው ያለው።
:
#የአምላክነት ቅምሻ
ኦሾ/Osho
ከሱፊዝም መንደር ጎራ ብለን ከሼኽ ሙዛፌር ወግ ቆነጠርን ።
:
በሱፊዝም ዕውቀት ታላቅ ክብር ከሚቸራቸው አንዱ ናቸው ሼኽ ሙዛፌር
:
ሼኽ ሙዛፌር ከተማሪዎቻቸወሰ አንዱ በውስጡ ለዓለም ሀብትና ምቾት የሚመኝ መሆኑን በተደጋጋሚ በማስተዋላቸው በጥበብ ምክራቸው ሊመልሱት ደጋግመው ደከሙ።
:
ነገር ግን የተማሪው ልብ ለመንፈሳዊው ዕውቀት በቀላሉ የሚከፈት አለመሆኑን ሼክ ሙዛፌር ስለተረዱ አንድ ቀን አስጠሩትና እንዲህ አለት:- እኔ በየትኛውም ጨለማ ውስጥ የማየት ብቃት እንዳለኝ ታውቃለህን? ተማሪውም ግራ በተጋባ መንፈሰሰ:- "ታዲያ ለምንድ ነው ማታ ማታ መብራት ይዘው ወደ ቤትዎ ሲያመሩ የማይዎት?" በማለት መልሶ ጠየቃቸው።
"መብራቱማ እንዳንተ በጨለማ የማያዩ ሰዎች እንዳይረግጡኝ ነው"በማለት የልቡን ስንፍና እግረ መንገዳቸውን ገለጡለት።
:
ለሱፊዎች ወደ ፈጣሪ መቅረቢያ ብቸኛው መንገድ ለእሱ የተከፈተ ልብና የተሰጠ አእምሮ ነው ልብን ለዓለማዊ ነገር እያስገዙ ፈጣሪን መለመን ትርፉ ከንቱ ድካም ነው። ለዚህም ነው ሼኽ ሙዛፌር ሲመክሩ "ከአንድ ዓመት ፀሎት የአንድ ሰዓት ማሰብ ይበልጣል" የሚሉን። ለአንድ ሰዓት በትክክል ያሰበ ሰው አንድ ዓመት ከፀለየ ይልቅ እውነትን የማግኘት ዕድሉ ሰፊ ነውና!
#እውነት እና እምነት
#ከጲላጦስ
:
በሱፊዝም ዕውቀት ታላቅ ክብር ከሚቸራቸው አንዱ ናቸው ሼኽ ሙዛፌር
:
ሼኽ ሙዛፌር ከተማሪዎቻቸወሰ አንዱ በውስጡ ለዓለም ሀብትና ምቾት የሚመኝ መሆኑን በተደጋጋሚ በማስተዋላቸው በጥበብ ምክራቸው ሊመልሱት ደጋግመው ደከሙ።
:
ነገር ግን የተማሪው ልብ ለመንፈሳዊው ዕውቀት በቀላሉ የሚከፈት አለመሆኑን ሼክ ሙዛፌር ስለተረዱ አንድ ቀን አስጠሩትና እንዲህ አለት:- እኔ በየትኛውም ጨለማ ውስጥ የማየት ብቃት እንዳለኝ ታውቃለህን? ተማሪውም ግራ በተጋባ መንፈሰሰ:- "ታዲያ ለምንድ ነው ማታ ማታ መብራት ይዘው ወደ ቤትዎ ሲያመሩ የማይዎት?" በማለት መልሶ ጠየቃቸው።
"መብራቱማ እንዳንተ በጨለማ የማያዩ ሰዎች እንዳይረግጡኝ ነው"በማለት የልቡን ስንፍና እግረ መንገዳቸውን ገለጡለት።
:
ለሱፊዎች ወደ ፈጣሪ መቅረቢያ ብቸኛው መንገድ ለእሱ የተከፈተ ልብና የተሰጠ አእምሮ ነው ልብን ለዓለማዊ ነገር እያስገዙ ፈጣሪን መለመን ትርፉ ከንቱ ድካም ነው። ለዚህም ነው ሼኽ ሙዛፌር ሲመክሩ "ከአንድ ዓመት ፀሎት የአንድ ሰዓት ማሰብ ይበልጣል" የሚሉን። ለአንድ ሰዓት በትክክል ያሰበ ሰው አንድ ዓመት ከፀለየ ይልቅ እውነትን የማግኘት ዕድሉ ሰፊ ነውና!
#እውነት እና እምነት
#ከጲላጦስ
"ሰው በሁለት ነገሮች ተጠምዶ ህይወቱን ያባክናል። ወይ በበታችነት ስሜት ወይ ደግሞ በበላይነት ስሜት ይሰቃያል። አንድ ሰው በበታችነት ስሜት ከተያዘ ውስጡ በጥልቀት ይታመማል። ከንቱ እንደሆነ እያሰበ ከኖረ በህይወት የመቆየቱ ጉዳይ አስቸጋሪ ይሆናል። በህይወት እየኖረ ቢሆንም ሙት ነው።
እስከ እለተ ሞታቸው ድረስ በህይወት የሚቆዩ በጣም ጥቂት ሰዎች አሉ። አብዛኞቹ ግን ከመሞታቸው በፊት የሚሞቱ ናቸው። በሰባ አመታቸው ቢቀበሩም የሞቱት ግን ቀደም ብለው ነው። በሞታቸውና በቀብራቸው መሀል የሰላሳ ፣ የአርባ ወይም የሃምሳ ዓመታት ክፍተት ሊኖር ይችላል።
በዙርያችሁ የተንሰራፋውን ግዝፈተ ተፈጥሮ ስትመለከቱ የበታችነት ሊሰማችሁ ይችላል።
ከዚህ አንፃር ሲታይ ሰው ምንም ነው። በውቅያኖስ ሞገዶች ላይ እንደተንሳፈፈ ገለባ ነው። እንደዚህ አይነት የበታችነት ስሜት ስሜት አይምሮን ጨምድዶ ከያዘ የሰው ህይወት በመከፋት የተሞላ ይሆናል። በህይወት የሚኖር ሙት ይሆናል።
ህይወቱ አመድና ትቢያ ይሆናል። የህይወታችሁ ነበልባል ከውስጣችሁ ከጠፋ ፣ የፋኖሳችሁ ነበልባል ከጠፋ ፣ በፀሃይ ብርሃንም ምንም ማድረግ አትችሉም። ለናንተ ፀሃይ ምንም ጥቅም አይኖራትም።"
#ኦሾ/Osho
#የንቃት ፀሐይ
እስከ እለተ ሞታቸው ድረስ በህይወት የሚቆዩ በጣም ጥቂት ሰዎች አሉ። አብዛኞቹ ግን ከመሞታቸው በፊት የሚሞቱ ናቸው። በሰባ አመታቸው ቢቀበሩም የሞቱት ግን ቀደም ብለው ነው። በሞታቸውና በቀብራቸው መሀል የሰላሳ ፣ የአርባ ወይም የሃምሳ ዓመታት ክፍተት ሊኖር ይችላል።
በዙርያችሁ የተንሰራፋውን ግዝፈተ ተፈጥሮ ስትመለከቱ የበታችነት ሊሰማችሁ ይችላል።
ከዚህ አንፃር ሲታይ ሰው ምንም ነው። በውቅያኖስ ሞገዶች ላይ እንደተንሳፈፈ ገለባ ነው። እንደዚህ አይነት የበታችነት ስሜት ስሜት አይምሮን ጨምድዶ ከያዘ የሰው ህይወት በመከፋት የተሞላ ይሆናል። በህይወት የሚኖር ሙት ይሆናል።
ህይወቱ አመድና ትቢያ ይሆናል። የህይወታችሁ ነበልባል ከውስጣችሁ ከጠፋ ፣ የፋኖሳችሁ ነበልባል ከጠፋ ፣ በፀሃይ ብርሃንም ምንም ማድረግ አትችሉም። ለናንተ ፀሃይ ምንም ጥቅም አይኖራትም።"
#ኦሾ/Osho
#የንቃት ፀሐይ
በተማሪ በተሞላው ክፍል ውስጥ የ ስነ ልቦና አስተማሪው እያስተማረ ነው። በመሀል ግን አንድ ትምህርት ያስተምራቸው ዘንድ ምሳሌም ይሰጣቸው ዘንድ ወደደና በ ብርጭቆ ውሃ ሞልቶ ወደ ተማሪዎቹ ዞረ። ሁሉም የጠበቁት ነገር ይሄ ብርጭቆ ግማሽ ሙሉ ነው ወይስ ግማሽ ጎዶል? የሚል የተለመደ ጥያቄ መስሏቸው ነበር።
ነገር ግን መምህሩ "ይሄ የያዝኩት ብርጭቆ ምን ያህል ይከብዳል? " የሚል ቀጥተኛ ጥያቄ ነበር። ሁሉም በየፊናው መልስ ይሆናል ያለውን ሁሉ ተናገረ። ከቁጥር መለያየት ውጪ ሁሉም ቀላል እንደሆነ ነው ያሰቡት።
ነገር ግን መምህሩ እንዲ ሲል መናገር ጀመረ " በርግጥ የያዝኩት ብርጭቆ ክብደቱ ትንሽ ነው። ብዙም አይከብድም። ነገር ግን የዚህ ብርጭቆ ክብደት በጊዜ የሚወሰን ይሆናል። ለምሳሌ ይሄን ብርጭቆ ለ 3 ወይም ለ አራት ደቂቃ ብይዘው ምንም ላይከብደኝ ይችላል። ነገር ግን ለ ሁለት ወይም ለ ሶስት ሰዓታት ይዜው ብቆይ የ እጄ መዛል የብርጭቆውን ክብደት ያገዝፈዋል። እንበል እና ሳልታክት ለ አንድ ቀን ብይዘው የብርጭቆው ክብደት ሳይሆን የእጄ መታመምና መብረክረክ አልፎም ፓራላዝ መሆን ብርጭቆውን አግዝፎ መሬት ላይ ያስወድቀዋል።" ሁሉም ተማሪዎች በአውንታ እራሳቸውን ነቀነቁ። መምህሩም ሁሉንም አይን አይናቸውን ካየ ቡዓላ መናገሩን ቀጠለ።
" በህይወትም ውስጥ አንድ አንድ ችግሮችና ጭንቀቶች መግዘፍ ሳይገባቸው በጭንቅላታችን ውስጥ ለረጅም ጊዜ ስለሚኒዛቸው ብቻ ይገዝፋሉ። ወድያው አሽቀንጥረን ባለመጣላችን ምክንያት እና ምክንያት እየፈጠርን ከመብሰልሰላችን ብዛት ቅንጣት ሆነው ሳለ ቋጥኝ ያክላሉ። በጊዜው መፍትሄ የሚሰጥበት ነገር ሆኖ እያለ ለሌላ ቀን ስላሳደርናቸው ብቻ ጭንቅላታችንን በውዘው ያሳምሙናል።
ጊዜ የማይፈታው ነገር ባይኖርም ጊዜ የሚያገዝፈውም ነገር አለ። በቅፅበት የሚፋታ ነገር በቅፅበት ካልተፈታ የጊዜ መርዘም ግዙፍ መስሎ እንዲታይ ሊያደርገው ይችላል።
ነገር ግን መምህሩ "ይሄ የያዝኩት ብርጭቆ ምን ያህል ይከብዳል? " የሚል ቀጥተኛ ጥያቄ ነበር። ሁሉም በየፊናው መልስ ይሆናል ያለውን ሁሉ ተናገረ። ከቁጥር መለያየት ውጪ ሁሉም ቀላል እንደሆነ ነው ያሰቡት።
ነገር ግን መምህሩ እንዲ ሲል መናገር ጀመረ " በርግጥ የያዝኩት ብርጭቆ ክብደቱ ትንሽ ነው። ብዙም አይከብድም። ነገር ግን የዚህ ብርጭቆ ክብደት በጊዜ የሚወሰን ይሆናል። ለምሳሌ ይሄን ብርጭቆ ለ 3 ወይም ለ አራት ደቂቃ ብይዘው ምንም ላይከብደኝ ይችላል። ነገር ግን ለ ሁለት ወይም ለ ሶስት ሰዓታት ይዜው ብቆይ የ እጄ መዛል የብርጭቆውን ክብደት ያገዝፈዋል። እንበል እና ሳልታክት ለ አንድ ቀን ብይዘው የብርጭቆው ክብደት ሳይሆን የእጄ መታመምና መብረክረክ አልፎም ፓራላዝ መሆን ብርጭቆውን አግዝፎ መሬት ላይ ያስወድቀዋል።" ሁሉም ተማሪዎች በአውንታ እራሳቸውን ነቀነቁ። መምህሩም ሁሉንም አይን አይናቸውን ካየ ቡዓላ መናገሩን ቀጠለ።
" በህይወትም ውስጥ አንድ አንድ ችግሮችና ጭንቀቶች መግዘፍ ሳይገባቸው በጭንቅላታችን ውስጥ ለረጅም ጊዜ ስለሚኒዛቸው ብቻ ይገዝፋሉ። ወድያው አሽቀንጥረን ባለመጣላችን ምክንያት እና ምክንያት እየፈጠርን ከመብሰልሰላችን ብዛት ቅንጣት ሆነው ሳለ ቋጥኝ ያክላሉ። በጊዜው መፍትሄ የሚሰጥበት ነገር ሆኖ እያለ ለሌላ ቀን ስላሳደርናቸው ብቻ ጭንቅላታችንን በውዘው ያሳምሙናል።
ጊዜ የማይፈታው ነገር ባይኖርም ጊዜ የሚያገዝፈውም ነገር አለ። በቅፅበት የሚፋታ ነገር በቅፅበት ካልተፈታ የጊዜ መርዘም ግዙፍ መስሎ እንዲታይ ሊያደርገው ይችላል።
የሌሊት ወፍ
“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
ከዶ/ር እዮብ ገፅ የተወሰደ
“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
ከዶ/ር እዮብ ገፅ የተወሰደ
#የኦሾ እይታ
በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር»
።።።።። //።።።።።። //።።።።።።
<<ሕይወትህን የምታከብራት ከሆነ ልታድናት የምትችለዉ አንተ ብቻ እንጂ ሌላ አዳኝ የላትም።የሚለዉ ኦሾ ህይወት የተፈጠረችዉ በሙላት ለመኖር ነዉ ስለዚህ ይህ ትክክል ነው ይህ ደግሞ ስህተት ነዉ አትበል ።በማለት ምሳሌ አስቀምጦልናል፧ ለምሳሌ እግዚአብሔር አለምን ፈጠረ።ሰይጣንም አብሮ ባይፈጠር ኖሮ አለም ላይ ምንም ባልኖረ ነበር። ለሆነዉ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ሀላፊነቱን ቢወስድም ሰይጣን በበኩሉ አዳምና ሄዋንን ከበለሱ እንዲበሉ ባያደርግ ኖሮ የዛሬዋ አለም እንዲህ ባልሆነ ነበር ።
#የመጀመሪያዉ አብዮተኛ ሰይጣን መሆኑን አታውቁም?መጀመሪያው አመፀኛ ምድራዊዉን ህይወት የገለፀው እኮ እሱ ነው።እንዲያ ባይሆን ዛሬም አዳም እና ሄዋን ሳር እየበሉ ይኖሩ
ነበር።በኤደን ገነት ታዲያ ምን ስራ ይኖራቸዉ ነበር? እግዚአብሔር እንደሆነ ከእውቀት ዛፍ አትብሉ ብሏቸዋል! ከዚህ ከዘላለም የህይወት ዛፍም አትብሉ በማለት አዟቸዋል። እና ምን ቀረ? ማወቅ በተከለከለበት መኖር በታገደበት አለም እንደ አጋዘን ጥንቸል ሳር ብሉ አላቸው,,,,, እናም በሰይጣን ምህረት ይችን አለም ለማየት በቃን። እግዚአብሄር የፈጠረው አዳም እና ሄዋን ያሉበት ምድር ብቻ ነው።ከዚያ ውጪ ነገር ግን የፈጠረው ሰይጣን ነው ።ልብ በሉ! ቡድሀ፣እየሱስ፣ሙሴ,,,,, የሀይማኖት መሪዎች ስም የሰማነው ሰይጣን በመኖሩ ብቻ ነው ።እናም ህይወት በተቃርኖዋ ውስጥ እንኖርባት ዘንድ የተገባ ነው ።"በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር!!"
#የኦሾ እይታ
በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር»
።።።።። //።።።።።። //።።።።።።
<<ሕይወትህን የምታከብራት ከሆነ ልታድናት የምትችለዉ አንተ ብቻ እንጂ ሌላ አዳኝ የላትም።የሚለዉ ኦሾ ህይወት የተፈጠረችዉ በሙላት ለመኖር ነዉ ስለዚህ ይህ ትክክል ነው ይህ ደግሞ ስህተት ነዉ አትበል ።በማለት ምሳሌ አስቀምጦልናል፧ ለምሳሌ እግዚአብሔር አለምን ፈጠረ።ሰይጣንም አብሮ ባይፈጠር ኖሮ አለም ላይ ምንም ባልኖረ ነበር። ለሆነዉ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ሀላፊነቱን ቢወስድም ሰይጣን በበኩሉ አዳምና ሄዋንን ከበለሱ እንዲበሉ ባያደርግ ኖሮ የዛሬዋ አለም እንዲህ ባልሆነ ነበር ።
#የመጀመሪያዉ አብዮተኛ ሰይጣን መሆኑን አታውቁም?መጀመሪያው አመፀኛ ምድራዊዉን ህይወት የገለፀው እኮ እሱ ነው።እንዲያ ባይሆን ዛሬም አዳም እና ሄዋን ሳር እየበሉ ይኖሩ
ነበር።በኤደን ገነት ታዲያ ምን ስራ ይኖራቸዉ ነበር? እግዚአብሔር እንደሆነ ከእውቀት ዛፍ አትብሉ ብሏቸዋል! ከዚህ ከዘላለም የህይወት ዛፍም አትብሉ በማለት አዟቸዋል። እና ምን ቀረ? ማወቅ በተከለከለበት መኖር በታገደበት አለም እንደ አጋዘን ጥንቸል ሳር ብሉ አላቸው,,,,, እናም በሰይጣን ምህረት ይችን አለም ለማየት በቃን። እግዚአብሄር የፈጠረው አዳም እና ሄዋን ያሉበት ምድር ብቻ ነው።ከዚያ ውጪ ነገር ግን የፈጠረው ሰይጣን ነው ።ልብ በሉ! ቡድሀ፣እየሱስ፣ሙሴ,,,,, የሀይማኖት መሪዎች ስም የሰማነው ሰይጣን በመኖሩ ብቻ ነው ።እናም ህይወት በተቃርኖዋ ውስጥ እንኖርባት ዘንድ የተገባ ነው ።"በአንዱ ላይ ቁመህ አንዱ ላይ ለመፍረድ አትሞክር!!"
#የኦሾ እይታ
ማንነት ምንድን ነው?
( ክፍል ፩ )
፨፨፨
ማንነት ስለሌላ ነገር የሚፈጠር ሀሳብ ሳይሆን ሰው መሆንን ማሰብ ነው ። ማንነት የውጫዊ ሀሳብ ሳይሆን የውስጥ ማሰብ ነው ። ሰው ማለት የሚያስብ እንስሳ ማለት ነው ። ማንነቱ ማሰቡ እንጂ አሳቡን መሆኑ አይደለም ። ሀሳብ ተለዋዋጭ ነው ። የማሰብ ማንነት ግን የማይለዋወጥ ቋሚ ሰው መሆን ነው ። ማንነት የሌላ መሆን ሀሳብ አይደለም ። ማንነት ሰው መሆንን ማሰብ ማለት ነው ። የምታስበው ሀሳብን ሆነህ መኖር አትችልም ።
፧
ማንነት ውጫዊ ሀሳብን ሆኖ መኖር ሳይሆን ሰው መሆንን በማሰብ መኖር ነው ። እያወራን ያለንው ስለሰው ልጅ ማንነት ከሆነ የሰው ልጅ ማንነት ሰው የመሆንን እውነት በማሰብ መኖር ነው ። ካልሆነ የማንነት አማራጩ ሁለት ነው ። አንደኛውና ትክክለኛው ውሳኔ ሰው ሆኖ በማሰብ የመኖር ማንነት ነው ። ይህ ካልሆነ የሌላን ሀሳብ ለመኖር ሰው የመሆንን ሕይወት በቁም መሰናበት ።
፧
ማንነት ራሽናል እውቀት ነው ። ማንነት ስሜት አይደለም ። ያለ-ራሽናል እውቀት ስሜት ግልብ ህልም ነው ። ለስሜት ለስሜት ከብትም ስሜት አለው ። የሰው ልጅ ማንነት ከከብት የሚለየው ግርድፉን ስሜቱን በራሽናል እውቀት መግራት ከቻለ ነው ። ስለራስህ የሚሰማህ ነገር ሁሉ የአንተ ማንነት አይደለም ። ማንነት የመሆን ስሜት ሳይሆን ራስን የማወቅ እውቀት ነው ። በራሽናል መንገድ ራስህን መዝነህ የምታውቀው እሱ የአንተ ማንነት ነው ። ማንነት ሀሳብ አይደለም ። ማንነት እውቀት ነው ። እውቀት ሀሳብ አይደለም ። እውቀት የማሰብ ብቃት ነው ። ስለዚህ እውቀት ማንነት የሚሆነው ያለማወቅን ማወቅ ካስቻለ ብቻ ነው ።
፧
ማንነት ክህሎት ነው ። ማንነት በገና መደርደር አይደለም ። በገና መደርደር ክህሎት ካልታከለበት የጉልበት ስራ ነው ። ማሲንቆ መገዝገዝ ማንነት አይደለም ። ማሲንቆ መገዝገዝ ክህሎት ከሌለው ክር መገዝገዝ ነው ። ክህሎት ከበሮ መምታር አይደለም ። ከበሮ መምታት ብቻውን እንጨት ማጋጨት ነው ። ማንነት ድምፆችን መፍጠር ሳይሆን የሙዚቃን ጥበብ የመፍጠር ክህሎት ነው ።
ማንነት...
ይቀጥላል...
ምንጭ ፦ ሰው መሆን
ደራሲ ፦ ቢልልኝ ሐብታሙ
፨ ማንነት ላንተ/ላንቺስ ምንድን ነው?
( ክፍል ፩ )
፨፨፨
ማንነት ስለሌላ ነገር የሚፈጠር ሀሳብ ሳይሆን ሰው መሆንን ማሰብ ነው ። ማንነት የውጫዊ ሀሳብ ሳይሆን የውስጥ ማሰብ ነው ። ሰው ማለት የሚያስብ እንስሳ ማለት ነው ። ማንነቱ ማሰቡ እንጂ አሳቡን መሆኑ አይደለም ። ሀሳብ ተለዋዋጭ ነው ። የማሰብ ማንነት ግን የማይለዋወጥ ቋሚ ሰው መሆን ነው ። ማንነት የሌላ መሆን ሀሳብ አይደለም ። ማንነት ሰው መሆንን ማሰብ ማለት ነው ። የምታስበው ሀሳብን ሆነህ መኖር አትችልም ።
፧
ማንነት ውጫዊ ሀሳብን ሆኖ መኖር ሳይሆን ሰው መሆንን በማሰብ መኖር ነው ። እያወራን ያለንው ስለሰው ልጅ ማንነት ከሆነ የሰው ልጅ ማንነት ሰው የመሆንን እውነት በማሰብ መኖር ነው ። ካልሆነ የማንነት አማራጩ ሁለት ነው ። አንደኛውና ትክክለኛው ውሳኔ ሰው ሆኖ በማሰብ የመኖር ማንነት ነው ። ይህ ካልሆነ የሌላን ሀሳብ ለመኖር ሰው የመሆንን ሕይወት በቁም መሰናበት ።
፧
ማንነት ራሽናል እውቀት ነው ። ማንነት ስሜት አይደለም ። ያለ-ራሽናል እውቀት ስሜት ግልብ ህልም ነው ። ለስሜት ለስሜት ከብትም ስሜት አለው ። የሰው ልጅ ማንነት ከከብት የሚለየው ግርድፉን ስሜቱን በራሽናል እውቀት መግራት ከቻለ ነው ። ስለራስህ የሚሰማህ ነገር ሁሉ የአንተ ማንነት አይደለም ። ማንነት የመሆን ስሜት ሳይሆን ራስን የማወቅ እውቀት ነው ። በራሽናል መንገድ ራስህን መዝነህ የምታውቀው እሱ የአንተ ማንነት ነው ። ማንነት ሀሳብ አይደለም ። ማንነት እውቀት ነው ። እውቀት ሀሳብ አይደለም ። እውቀት የማሰብ ብቃት ነው ። ስለዚህ እውቀት ማንነት የሚሆነው ያለማወቅን ማወቅ ካስቻለ ብቻ ነው ።
፧
ማንነት ክህሎት ነው ። ማንነት በገና መደርደር አይደለም ። በገና መደርደር ክህሎት ካልታከለበት የጉልበት ስራ ነው ። ማሲንቆ መገዝገዝ ማንነት አይደለም ። ማሲንቆ መገዝገዝ ክህሎት ከሌለው ክር መገዝገዝ ነው ። ክህሎት ከበሮ መምታር አይደለም ። ከበሮ መምታት ብቻውን እንጨት ማጋጨት ነው ። ማንነት ድምፆችን መፍጠር ሳይሆን የሙዚቃን ጥበብ የመፍጠር ክህሎት ነው ።
ማንነት...
ይቀጥላል...
ምንጭ ፦ ሰው መሆን
ደራሲ ፦ ቢልልኝ ሐብታሙ
፨ ማንነት ላንተ/ላንቺስ ምንድን ነው?
የሰው ልጅ የሚሰቃየው ራሱ ባጠረው አጥር ራሱ በገነባው ቅጥር ራሱ በሸበበው ውትርትር ነው። የዘር ፣ የሃይማኖት ፣ የርዕዮተ አለም ፣..... የፍልስፍና አጥር ። የብቸኝነት ፣ የአውሬነት ፣ የወፈፌነት ፣ ......አስማት የሚመስል አጥር።...
"ክቡር ድንጋይ"
"ክቡር ድንጋይ"
የትኛውም መሻትና ፍላጎትህ ወይም ውድቀትህና ስኬትህ በአንተ ማንነት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚገለጥ እውነት ነው::
ስለዚህ አንተ ከምታውቀውና ከምታምነው በላይ ሌላ ማንነት አለህና እሱን ፈልገህ አግኝ::''
።።//።።
#ተዓምራት እና ጣዖታት
ስለዚህ አንተ ከምታውቀውና ከምታምነው በላይ ሌላ ማንነት አለህና እሱን ፈልገህ አግኝ::''
።።//።።
#ተዓምራት እና ጣዖታት
#ማንም ሰዉ ክፋ ሆኖ የተወለደ የለም ነገር ግን ሰዉን ክፋ የምያደርገዉ እራሱ የሰዉ ልጅ በሚያደርጋቸዉ ክፋ ተግባር ክፋትን ያስተምረዋል እሾህ የሌለዉ መሬት
እንቅፋት የሌለዉ ህይወት የለም እና ሁሉንም በትግስት እንለፍ !!
እንቅፋት የሌለዉ ህይወት የለም እና ሁሉንም በትግስት እንለፍ !!
"በተመስጦ ማሰላሰል ለፅምናና ለብቻ ለመሆን መድፈር ነው። ቀስ በቀስ በራሳችሁ ላይ አዲስ ባህሪ አዲሲ የህያውነት መንፈስ፣ አዲስ ውብት እንዲሁም አዲስ አስተሳሰብ ሲለመልም ይሰማችኋል። ይህ ደግሞ ከማንም የተዋሳችሁት ሳይሆን በውስጣችሁ እያደገ ያለ ስሜት ነው።"
*
ኦሾ/osho
*
ኦሾ/osho
የሌሊት ወፍ
“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
ከዶ/ር እዮብ ገፅ የተወሰደ
“የሌሊት ወፍ በቀን የመኖር ስልጣን የላትም” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የጥንት አፈ-ታሪክ፡፡ “ለዚህ ነው ሌሊቱን እየጠበቀች ከመሸ ተደብቃ ወጥታ ሳይነጋ ተደብቃ የምትገባው”፡፡
በጥንት ጊዜ በሰማይ አእዋፍና በምድር አራዊት መካከል ውጊያ ነበር ይባላል፡፡ የአሁኗ የሌሊት ወፍ ያን ጊዜ እንደማንኛውም የወፍ ዝርያ ነበረች፡፡ ይህቺ ወፍ (የአሁኗ የሌሊት ወፍ) በውጊያው ጊዜ የምድር አራዊት ሲያሸነፍ ለእነሱ ታግዝ ነበር፤ የሰማዩ ሲያሸነፍ ደግሞ ተገልብጣ ለእነሱ ታግዝ ነበር፡፡
አንድ ጊዜ ግን እነዚህ ሁለት ጸበኞች ታረቁና የጦርነቱ ሁኔታና ትውስታ ሲነሳ ምን ስታደርግ እንደነበረ ታወቀባት፡፡ ከዚያ ቀን ጀምሮ በሁሉም የተጠላችና የተገፋች ወደመሆን ስለመጣች በቀን የመኖር ስልጣኗን አጣችና ሌሊት መኖር ጀመረች ይባላል፡፡
አስመሳይነት፣ ሁለት መልክ ያለው ሕይወት፣ አቋም የለሽነት፣ ውሸተኛነት፣ አታላይነት፣ መስሎ አዳሪነት፣ ባለ ሁለት ምላስነት፣ ሸንጋይነት፣ ለሆድ አዳሪነት . . . የዘመኑ ችግር!
የብዙዎችን በነጻነትና ቀና ብሎ በድፍረት የመኖር አቅም ያሳጣ የዘመኑ ወረርሽኝ!
አስመሳይ ሆነህ ወዳጅህ ከሚበዛ፣ እውነተኛ ሆነህ ጠላትህ ቢበዛ ይሻላል፡፡ ሁለት መልክ ይዘህ ትርፋማ ከምትሆን፣ አንድ መልክ ይዘህ ባለህ ነገር መኖር ይሻልሃል፡፡
ከዶ/ር እዮብ ገፅ የተወሰደ