➲ ቅቤና ማር ተከራከሩ
//ዳንኤል ክብረት//
ማርም ተናገረች፡- “የምጣፍጠው እኔ አናት ላይ የምትወጪው ግን አንቺ ነሽ ለምንድነው?” አለቻት። ቅቤም፡- “እኔም ወድጄ አይደለም ገፍተው፣ ገፍተው ነው አናት ላይ ያወጡኝ” አለች ይባላል። ቅቤ፣ ቅቤ የሚኮነው ተንጦ፣ ተንጦ ነው። እግዚአብሔር ሁሉም ሎሌው ነው። በክፉዎች ሳይቀር ይሠራል። ወዳሰበልን የሚያደርሰን እየገፋን ነው። ካልተገፋን ያለንበትን ትንሽ ቦታ ተላምደን እንኖራለን። እርሱ በደጎች አይገፋንም፣ ደጎች መግፋት ባሕርያቸው አይደለምና። ክፉዎች ግን ቅድስናም ይሉኝታም የላቸውምና በእነርሱ ይገፋናል። እነርሱ የሚያውቁት ወደ ገደል እንደሚገፉን ነው፣ ሳያውቁት ግን ወደ ተራራ ይገፉናል። ጠላቶች የነጻ ሠረገላ ናቸው። ለኛ ከ ማይገባን ቦታ እየገፉን ወደ ሚገባን ቦታ ... ከ ዝቅታ ወደ ከፍታ ቦታ ያደርሱናል። በእውነት ጌታ ሆይ ጠላቶቻችንን ባርክልን። እነርሱ ባይኖሩ ሥራው አይበዛልንም ነበር። ይህን ጥንቁቅ ሕይወት፣ ይህን ዝግጅት፣ ይህን ቶሎ ቶሎ መሥራት ያገኘነው ከጠላቶቻችን ነው። እያንዳንዱን ቀን በትክክል እንድንኖር ያተጉንን ጠላቶች እባክህ ባርክልን። የሰዓት ደወል ብንሞላ ጠዋት 12 ሰዓት ሞልተነው፣ ማታ 12 ሰዓት ሊጮህ ይችላል። ቀስቅሱን ብንላቸው ወዳጆቻችን ከሥራችን ለእንቅልፋችን አዝነው ይተውናል። ክፉዎች ግን በሰዓቱ ያነቁናል። እንደዚህ ያሉ ነጻ ደወሎችን ያስቀመጠልን አምላክ ስሙ ይባረክ። እነርሱ እንዳይነቅፉን ስንጠነቀቅ የቅድስናን ሕይወት ያለማምዱናልና እነዚህ ጠባቂዎቻችን ናቸው። የተገፉ ሁሉ ከፍ እንጂ ዝቅ ሲሉ አይተን አናውቅም። ገፊዎች ሲገፉን ከእኛ የክፋት ሰፈር ምን ትሠራላችሁ? እልፍ በሉ እያሉን ነው። ጠላቶች ሐሰተኛ ወዳጆችን ወስደው እውነተኛ ወዳጆችን ያስቀሩልናል። ክፉዎች ጥሩ ማጣሪያ ናቸው። ተረስተን የምንኖረውን እነርሱ ያሳውቁናል። በነጻ ማስታወቂያ ይሠሩልናል። ሰዎች ስማችንን የሚያነሡት በሁለት ነገር ነው። ስለሚወዱንና ስላስደሰትናቸው ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ ስለሚጠሉንና ስላስጨነቅናቸው ነው። እንዲሁ ርእስ መሆን አይገኝም። የአትርሱኝ ሳንከፍል ላስታወሱን በረከት ይሁን። ዮሴፍ ባይገፋ ኖሮ ጎበዝ እረኛ ሆኖ ይቀር ነበር። በመገፋቱ የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ። ጠላት ያውቃል እንላለን፣ እንደ ጠላት ግን አላዋቂ የለም። ኢየሱስን ከኢየሩሳሌም ሊያጠፋ ገደለው፣ በሞቱ ግን በዓለም ሁሉ አበራ። ጠላት ሰፈር እየቀማ ዓለም ያወርሳል። ሰው ማፍረስ ይችል ይሆናል፣ እግዚአብሔር ደግሞ ማስነሣት ይችላል ።
.
"መገፋት ጥሩ ነው እጅግም ሳይወድቁ፣ የተገፉት ቆመው የገፉት ወደቁ"
//ዳንኤል ክብረት//
ማርም ተናገረች፡- “የምጣፍጠው እኔ አናት ላይ የምትወጪው ግን አንቺ ነሽ ለምንድነው?” አለቻት። ቅቤም፡- “እኔም ወድጄ አይደለም ገፍተው፣ ገፍተው ነው አናት ላይ ያወጡኝ” አለች ይባላል። ቅቤ፣ ቅቤ የሚኮነው ተንጦ፣ ተንጦ ነው። እግዚአብሔር ሁሉም ሎሌው ነው። በክፉዎች ሳይቀር ይሠራል። ወዳሰበልን የሚያደርሰን እየገፋን ነው። ካልተገፋን ያለንበትን ትንሽ ቦታ ተላምደን እንኖራለን። እርሱ በደጎች አይገፋንም፣ ደጎች መግፋት ባሕርያቸው አይደለምና። ክፉዎች ግን ቅድስናም ይሉኝታም የላቸውምና በእነርሱ ይገፋናል። እነርሱ የሚያውቁት ወደ ገደል እንደሚገፉን ነው፣ ሳያውቁት ግን ወደ ተራራ ይገፉናል። ጠላቶች የነጻ ሠረገላ ናቸው። ለኛ ከ ማይገባን ቦታ እየገፉን ወደ ሚገባን ቦታ ... ከ ዝቅታ ወደ ከፍታ ቦታ ያደርሱናል። በእውነት ጌታ ሆይ ጠላቶቻችንን ባርክልን። እነርሱ ባይኖሩ ሥራው አይበዛልንም ነበር። ይህን ጥንቁቅ ሕይወት፣ ይህን ዝግጅት፣ ይህን ቶሎ ቶሎ መሥራት ያገኘነው ከጠላቶቻችን ነው። እያንዳንዱን ቀን በትክክል እንድንኖር ያተጉንን ጠላቶች እባክህ ባርክልን። የሰዓት ደወል ብንሞላ ጠዋት 12 ሰዓት ሞልተነው፣ ማታ 12 ሰዓት ሊጮህ ይችላል። ቀስቅሱን ብንላቸው ወዳጆቻችን ከሥራችን ለእንቅልፋችን አዝነው ይተውናል። ክፉዎች ግን በሰዓቱ ያነቁናል። እንደዚህ ያሉ ነጻ ደወሎችን ያስቀመጠልን አምላክ ስሙ ይባረክ። እነርሱ እንዳይነቅፉን ስንጠነቀቅ የቅድስናን ሕይወት ያለማምዱናልና እነዚህ ጠባቂዎቻችን ናቸው። የተገፉ ሁሉ ከፍ እንጂ ዝቅ ሲሉ አይተን አናውቅም። ገፊዎች ሲገፉን ከእኛ የክፋት ሰፈር ምን ትሠራላችሁ? እልፍ በሉ እያሉን ነው። ጠላቶች ሐሰተኛ ወዳጆችን ወስደው እውነተኛ ወዳጆችን ያስቀሩልናል። ክፉዎች ጥሩ ማጣሪያ ናቸው። ተረስተን የምንኖረውን እነርሱ ያሳውቁናል። በነጻ ማስታወቂያ ይሠሩልናል። ሰዎች ስማችንን የሚያነሡት በሁለት ነገር ነው። ስለሚወዱንና ስላስደሰትናቸው ሲሆን በተቃራኒው ደግሞ ስለሚጠሉንና ስላስጨነቅናቸው ነው። እንዲሁ ርእስ መሆን አይገኝም። የአትርሱኝ ሳንከፍል ላስታወሱን በረከት ይሁን። ዮሴፍ ባይገፋ ኖሮ ጎበዝ እረኛ ሆኖ ይቀር ነበር። በመገፋቱ የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ። ጠላት ያውቃል እንላለን፣ እንደ ጠላት ግን አላዋቂ የለም። ኢየሱስን ከኢየሩሳሌም ሊያጠፋ ገደለው፣ በሞቱ ግን በዓለም ሁሉ አበራ። ጠላት ሰፈር እየቀማ ዓለም ያወርሳል። ሰው ማፍረስ ይችል ይሆናል፣ እግዚአብሔር ደግሞ ማስነሣት ይችላል ።
.
"መገፋት ጥሩ ነው እጅግም ሳይወድቁ፣ የተገፉት ቆመው የገፉት ወደቁ"
ጠቃሚ ምክር !
★★★
በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ ውጣ ፤ ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል ። ሰምቶ ማመን ፣ ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ ። የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብህም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ይገባሃል ።
:
ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ ። ምክርን አልሰማ ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው ። በዋጋ መማር ግን አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው ። ብልህ ከሆንህ በሰው ከደረሰው ትማራለህ ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ ትማራለህ ።
:
የታየህን አሳይ ፣ ያልታየህን አጥራው ። በደንብ ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው አትጋብዝ ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን ። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ ፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል ። የሰጠኽውን እርሳ እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ ። ቀኑ ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል ።
:
ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ ። ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ የመጣህበትን አትዘንጋ ።
:
የአባቶችህን መልካም ሥራ አብነት አድርግ ። ካሳለፉት ሕይወት ተማር እንጂ አወዳሽና ወቃሽ አትሁን ። ሌሎች መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ ። ደግሞም አንተም በታሪክ ፊት መሆንህን እወቀው ።
:
ክፋት አይሙቅህ ፣ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ አይበልህ ። ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም አለህና ተግባርህ የምርጫ ውጤት ነውና አስብበት ።
:
ገንዘብ የሚመልሰው የገንዘብን ጥያቄ ብቻ ነውና ሁሉንም ነገር ገንዘብ ያስገኝልኛል ብለህ አታስብ ። ላለው አትሩጥ ፣ ምጽዋትህና ተግባርህ በአቅምህ መጠን ይሁን እንጂ ከአቅምህ አትነስ ። ድሃም ሆነህ ተበድረህ ስጦታ አትስጥ ። በጣም ካልቸገረህ ለቅንጦት አትበደር ። ያንተን ድርሻ ከጨረስህ ያልተጨረሰ የሌሎችን ድርሻ ፈፅምላቸው ።
:
ለሀብታም አትሳቅ ፣ የደሀ ጉልበት አይለፍብህ ፣ ያለ ሰው ሰው አልሆንክምና ሰው አትጥላ ፣ የወጣህበትን መሰላል አትገፍትር ፣ ለመውረድም ያስፈልግሃልና ፣ ያየኽውን ሴት ሁሉ የመውደድ ጠባይህ ካለቀቀህ ትዳር አትያዝ ፣ ካልጋበዙህ በቀር አማካሪ አትሁን ፣ ባልጠሩህ ሥፍራ አቤት አትበል ፣ ካልሾሙህ መሪ አትሁን ፣ ጉድለት በሌለበት ቦታ ጊዜህን አታባክን ፣ የሰው ፊት ጥገኛ ሁነህ ሲስቁልህ የምትስቅ ሲቆጡህ የምታለቅስ አትሁን ፣ ነገርህን በልክ ፣ ቃልህን በጣዕም ፣ ድምፅህን በዝግታ ፈፅመው ።
:
እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል ። ጨካኝ እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል ። ንፉግ እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል ። ነገር አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ አትለፍ ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን እንደ ኖርክበት አትቁጠረው ፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ ።
:
ሥልጣን ሲሰጥህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን ፤ ከፊት እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከኋላ ሆነህ አትቅደም ።
:
በዓላማ ኑር ፤ እንቅፋቶች የሚያጸኑህ እንጂ ተግባርህን የሚያስተውህ አይሁኑ ። ሕይወት ትምህርት ቤት መሆኑና ባለማወቅ ብዙ ትህምርቶች እንዳያመልጡህ ተጠንቀቅ ።
:
የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን ፤ የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።
:
ዓለም ዋዣቂ ናት ። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ ፤ ፀሐይ ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች ። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ መፅናናት ይሆናል ። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም ። ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
:
መነቀፍን አትፍራ ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው ፤ ስለ ሀሰት ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች አንቀጽ አትካሰስ ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው ። ብዙዎች ስለወደዱህ ይወድሃል ፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል ።
:
ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም ተመልከት ። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት ተሟገትላቸው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው ።
:
ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና ። ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ ።
:
ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው ።
:
ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ። በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።
:
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው !!
፡
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
፡
ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ ። አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ ፤ ቆንጆ ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ ነውና በሚፈርስ አካል ፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል።
፡
እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው ፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣ ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ ። መወደድህን ለመስማት አትጠብቅ ።
፡
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው ።
፡
ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን ፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ ትምክህት ፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ ።
★★★
በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ ውጣ ፤ ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል ። ሰምቶ ማመን ፣ ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ ። የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብህም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ይገባሃል ።
:
ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ ። ምክርን አልሰማ ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው ። በዋጋ መማር ግን አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው ። ብልህ ከሆንህ በሰው ከደረሰው ትማራለህ ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ ትማራለህ ።
:
የታየህን አሳይ ፣ ያልታየህን አጥራው ። በደንብ ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው አትጋብዝ ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን ። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ ፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል ። የሰጠኽውን እርሳ እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ ። ቀኑ ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል ።
:
ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ ። ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ የመጣህበትን አትዘንጋ ።
:
የአባቶችህን መልካም ሥራ አብነት አድርግ ። ካሳለፉት ሕይወት ተማር እንጂ አወዳሽና ወቃሽ አትሁን ። ሌሎች መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ ። ደግሞም አንተም በታሪክ ፊት መሆንህን እወቀው ።
:
ክፋት አይሙቅህ ፣ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ አይበልህ ። ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም አለህና ተግባርህ የምርጫ ውጤት ነውና አስብበት ።
:
ገንዘብ የሚመልሰው የገንዘብን ጥያቄ ብቻ ነውና ሁሉንም ነገር ገንዘብ ያስገኝልኛል ብለህ አታስብ ። ላለው አትሩጥ ፣ ምጽዋትህና ተግባርህ በአቅምህ መጠን ይሁን እንጂ ከአቅምህ አትነስ ። ድሃም ሆነህ ተበድረህ ስጦታ አትስጥ ። በጣም ካልቸገረህ ለቅንጦት አትበደር ። ያንተን ድርሻ ከጨረስህ ያልተጨረሰ የሌሎችን ድርሻ ፈፅምላቸው ።
:
ለሀብታም አትሳቅ ፣ የደሀ ጉልበት አይለፍብህ ፣ ያለ ሰው ሰው አልሆንክምና ሰው አትጥላ ፣ የወጣህበትን መሰላል አትገፍትር ፣ ለመውረድም ያስፈልግሃልና ፣ ያየኽውን ሴት ሁሉ የመውደድ ጠባይህ ካለቀቀህ ትዳር አትያዝ ፣ ካልጋበዙህ በቀር አማካሪ አትሁን ፣ ባልጠሩህ ሥፍራ አቤት አትበል ፣ ካልሾሙህ መሪ አትሁን ፣ ጉድለት በሌለበት ቦታ ጊዜህን አታባክን ፣ የሰው ፊት ጥገኛ ሁነህ ሲስቁልህ የምትስቅ ሲቆጡህ የምታለቅስ አትሁን ፣ ነገርህን በልክ ፣ ቃልህን በጣዕም ፣ ድምፅህን በዝግታ ፈፅመው ።
:
እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል ። ጨካኝ እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል ። ንፉግ እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል ። ነገር አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ አትለፍ ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን እንደ ኖርክበት አትቁጠረው ፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ ፣ አዋቂዎችን ጠይቅ ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ ።
:
ሥልጣን ሲሰጥህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን ፤ ከፊት እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከኋላ ሆነህ አትቅደም ።
:
በዓላማ ኑር ፤ እንቅፋቶች የሚያጸኑህ እንጂ ተግባርህን የሚያስተውህ አይሁኑ ። ሕይወት ትምህርት ቤት መሆኑና ባለማወቅ ብዙ ትህምርቶች እንዳያመልጡህ ተጠንቀቅ ።
:
የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን ፤ የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።
:
ዓለም ዋዣቂ ናት ። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ ፤ ፀሐይ ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች ። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ መፅናናት ይሆናል ። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም ። ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
:
መነቀፍን አትፍራ ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው ፤ ስለ ሀሰት ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች አንቀጽ አትካሰስ ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው ። ብዙዎች ስለወደዱህ ይወድሃል ፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል ።
:
ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም ተመልከት ። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት ተሟገትላቸው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው ።
:
ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና ። ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን ድንበር አታሳጣው ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት ተጠንቀቅ ።
:
ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና ስታከብርላቸው ነው ።
:
ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣ ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ። በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።
:
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው !!
፡
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
፡
ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ ። አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ ፤ ቆንጆ ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ ነውና በሚፈርስ አካል ፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል።
፡
እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው ፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣ ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ ። መወደድህን ለመስማት አትጠብቅ ።
፡
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን እርዳቸው ።
፡
ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን ፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ ትምክህት ፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ ።
፡
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ። ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
፡
ቂም አፍን የሚያመር ፣ ልብን የሚያነቅዝ ፣ ተግባርን የሚያልፈሰፍስ ነውና ለበደለህ ሰው ቅያሜህን ግለጥለት ፤ ቂመኝነት በክፉ መሸነፍ እንጂ ጀግንነት አይምሰልህ ።
፡
ከህሊናህና ከመንፈሳዊ አማካሪህ ሳትመክር ምንም ነገር አትወስን ፤ አጥርተህ ሳትሰማ ቃል አትግባ ። መከራ ካልደረሰ በቀር ባል በሌለበት ቤት ውስጥ ከሚስቲቱ ጋር ብቻህን አትቀመጥ ።
:
የሚበልጥህ ልኩራብህ እንዳይልህ ፣ ያነሰህ ልድረስብህ ብሎ እንዳያጠፋህ የሀብትህን ልክ እንዳታወራ ፤ በገዛ አፍህ ባንዱ ትከብራለህ ባንዱ ትቀላለህና።
፡
በጣም በማክበርህ እንዳታመልከው ፤ በጣም በመናቅህ እንዳታዋርደው ሠው እንዳንተ መሆኑን እወቀው ።
፡
የእኔ መናገር ምን ይለውጣል? ብለህም ስህተትን አትለፍ ፤ የእኔ አስተዋፅኦ ምን ይጠቅማል ? ብለህም ስጦታህን አትጠፍ ።
፡
መልካም ቃል ከስጦታ ይበልጣልና መልካም ቃል ተናገር ፤ ማንኛውም ስጦታ ከልመና ወንበር አያስነሣም ። የተስፋ ቃል ግን እንደሚያስነሣ አውቀህ ለሰዎች የተስፋ ቃል ስጣቸው ።
፡
ትምህርት ለዕውቀት ያዘጋጃል እንጂ ዕውቀትን አይጨርስም ። ዕውቀትህን የምትይዝበትን ሥነ-ሥርዓት ግን ያሳይሃል ። አእምሮህን ለማረቅ ትምህርት ፣ ሰውነትህን ለመግዛት ትዕግስት ፣ ከማንም ጋር ለመኖር ሥነ-ሥርዓት ያስፈልግሃል ። ለህሊናህ እረፍት ግን እምነት ያሻሃል ። ተከታይ ለማበጀት ደግሞ ግልጽ መሆንና ታማኝነት ግድ ይልሃል ።
፡
አንተው እውነትን ጠልተሃት ዘመኑ እውነትን ጠልቷል አትበል ። ዘመን እኔና አንተ ነን ፤ በራሱ ክፉና ደግ የሆነ ዘመን የለም።
፡
መልካም ምክር ብትሰማ ሕይወት ቀላል ይሆንልሃል ። ትክክለኛም ውሳኔ ከመልካም ምክር ነውና..!!
ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ። ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።
፡
ቂም አፍን የሚያመር ፣ ልብን የሚያነቅዝ ፣ ተግባርን የሚያልፈሰፍስ ነውና ለበደለህ ሰው ቅያሜህን ግለጥለት ፤ ቂመኝነት በክፉ መሸነፍ እንጂ ጀግንነት አይምሰልህ ።
፡
ከህሊናህና ከመንፈሳዊ አማካሪህ ሳትመክር ምንም ነገር አትወስን ፤ አጥርተህ ሳትሰማ ቃል አትግባ ። መከራ ካልደረሰ በቀር ባል በሌለበት ቤት ውስጥ ከሚስቲቱ ጋር ብቻህን አትቀመጥ ።
:
የሚበልጥህ ልኩራብህ እንዳይልህ ፣ ያነሰህ ልድረስብህ ብሎ እንዳያጠፋህ የሀብትህን ልክ እንዳታወራ ፤ በገዛ አፍህ ባንዱ ትከብራለህ ባንዱ ትቀላለህና።
፡
በጣም በማክበርህ እንዳታመልከው ፤ በጣም በመናቅህ እንዳታዋርደው ሠው እንዳንተ መሆኑን እወቀው ።
፡
የእኔ መናገር ምን ይለውጣል? ብለህም ስህተትን አትለፍ ፤ የእኔ አስተዋፅኦ ምን ይጠቅማል ? ብለህም ስጦታህን አትጠፍ ።
፡
መልካም ቃል ከስጦታ ይበልጣልና መልካም ቃል ተናገር ፤ ማንኛውም ስጦታ ከልመና ወንበር አያስነሣም ። የተስፋ ቃል ግን እንደሚያስነሣ አውቀህ ለሰዎች የተስፋ ቃል ስጣቸው ።
፡
ትምህርት ለዕውቀት ያዘጋጃል እንጂ ዕውቀትን አይጨርስም ። ዕውቀትህን የምትይዝበትን ሥነ-ሥርዓት ግን ያሳይሃል ። አእምሮህን ለማረቅ ትምህርት ፣ ሰውነትህን ለመግዛት ትዕግስት ፣ ከማንም ጋር ለመኖር ሥነ-ሥርዓት ያስፈልግሃል ። ለህሊናህ እረፍት ግን እምነት ያሻሃል ። ተከታይ ለማበጀት ደግሞ ግልጽ መሆንና ታማኝነት ግድ ይልሃል ።
፡
አንተው እውነትን ጠልተሃት ዘመኑ እውነትን ጠልቷል አትበል ። ዘመን እኔና አንተ ነን ፤ በራሱ ክፉና ደግ የሆነ ዘመን የለም።
፡
መልካም ምክር ብትሰማ ሕይወት ቀላል ይሆንልሃል ። ትክክለኛም ውሳኔ ከመልካም ምክር ነውና..!!
"መንጋው ስሜታዊ እንጂ ምክንያታዊ አይደለም "
:
ከ"አልገባኝም መጽሐፉ የተወሰደ በዚህ አጋጣሚ እንድታነቡት ጋበዝኳችሁ!!!
:
"ምን አይነት መጽሐፍ ቢያነቡ ይመከራል ?" የዳግም ጥያቄ ነበር በአንድ በኩል ብቻ የተሳለ ሰይፍ ባይሆን ይመረጣል ታሪክ ፣ ፍልስፍና ፣ ግለ ታሪክ ፣ ጥናታዊ ስራዎች ፣ ልብ ወለድ ፣ ግጥም . . . ሌላንም ቢያነብ ቢያጣጥም መታደል ነው ።
:
ከዚህ ጋር ተያይዞ ምን ትዝ አለኝ ? እዚህ አገር እስከ ቅርብ ጊዜያት ድረስ መጽሐፍ ይዞ መታየት በተለይ የፍልስፍና ይዘት ያላቸው መጽሐፍትን ማንበብ ከወፈፌነት ከኢ- አማኝነት ጋር የማያያዝ ልማድ ነበር። አሁን አሁን አንዳንድ ሰዎች ጋር ይህ አመለካከት አይጠፋም። ኢ- አማኝ መሆን ፍልስፍና መጽሀፍትን ማንበብ ፣ ሲልም ፍልስፍናን እንደ አንድ ዘርፍ ወስዶ ማጥናት ምን አይነት ምክንያታዊ ግንኙነት የለም። በዚህ ዙሪያ ሰዎች የሚጠቅሷቸው እንደ #ኦሾ ፣ #ራምፖ ፣ #ፍሮይድ ፣#ኒቼ . . .ዓይነት መጽሐፍት አሉ።
በመጽሐፍ ደረጃ ፍሮይድ የጻፈው ' the future of an illusion' የሚለውን መጽሐፍ አንብቤ "ከሃይማኖት ጋር ፍቺ ፈጽሜያለሁ " ባለው ሰው ላይ ሰዎች ሲነጋገሩ ሰምቻለሁ። ነገሩ አዲስ አይደለም ። ኢ- አማኝ የሆንኩት 'እንዲህ አይነት ' መጽሐፍ አንብቤ ነው ማለት ተለምዷል። በእርግጥ እያንዳንዱ ሰው ያሻውን የማለት መብት አለው። አንድ መጽሐፍ አንብበን ኢ-አማኝ እንሆናለን ብለን እየተቀባበልን ያንኑ መጽሐፍ በተራ ብናነብ የሚፈጠር ነገር የለም ።
አፍላጦን "መንጋው ስሜታዊ እንጂ ምክንያታዊ አይደለም " ለምሳሌ እንደ አንድ አንባቢ መጽሐፉን አንብቤዋለሁ ። ነገር ግን እሱን መጽሐፍ አንብቤ ኢ-አማኝ አልሆንኩም።
*
#አልገባኝም
#ዮናስ ዘውዴ ከበደ
:
ከ"አልገባኝም መጽሐፉ የተወሰደ በዚህ አጋጣሚ እንድታነቡት ጋበዝኳችሁ!!!
:
"ምን አይነት መጽሐፍ ቢያነቡ ይመከራል ?" የዳግም ጥያቄ ነበር በአንድ በኩል ብቻ የተሳለ ሰይፍ ባይሆን ይመረጣል ታሪክ ፣ ፍልስፍና ፣ ግለ ታሪክ ፣ ጥናታዊ ስራዎች ፣ ልብ ወለድ ፣ ግጥም . . . ሌላንም ቢያነብ ቢያጣጥም መታደል ነው ።
:
ከዚህ ጋር ተያይዞ ምን ትዝ አለኝ ? እዚህ አገር እስከ ቅርብ ጊዜያት ድረስ መጽሐፍ ይዞ መታየት በተለይ የፍልስፍና ይዘት ያላቸው መጽሐፍትን ማንበብ ከወፈፌነት ከኢ- አማኝነት ጋር የማያያዝ ልማድ ነበር። አሁን አሁን አንዳንድ ሰዎች ጋር ይህ አመለካከት አይጠፋም። ኢ- አማኝ መሆን ፍልስፍና መጽሀፍትን ማንበብ ፣ ሲልም ፍልስፍናን እንደ አንድ ዘርፍ ወስዶ ማጥናት ምን አይነት ምክንያታዊ ግንኙነት የለም። በዚህ ዙሪያ ሰዎች የሚጠቅሷቸው እንደ #ኦሾ ፣ #ራምፖ ፣ #ፍሮይድ ፣#ኒቼ . . .ዓይነት መጽሐፍት አሉ።
በመጽሐፍ ደረጃ ፍሮይድ የጻፈው ' the future of an illusion' የሚለውን መጽሐፍ አንብቤ "ከሃይማኖት ጋር ፍቺ ፈጽሜያለሁ " ባለው ሰው ላይ ሰዎች ሲነጋገሩ ሰምቻለሁ። ነገሩ አዲስ አይደለም ። ኢ- አማኝ የሆንኩት 'እንዲህ አይነት ' መጽሐፍ አንብቤ ነው ማለት ተለምዷል። በእርግጥ እያንዳንዱ ሰው ያሻውን የማለት መብት አለው። አንድ መጽሐፍ አንብበን ኢ-አማኝ እንሆናለን ብለን እየተቀባበልን ያንኑ መጽሐፍ በተራ ብናነብ የሚፈጠር ነገር የለም ።
አፍላጦን "መንጋው ስሜታዊ እንጂ ምክንያታዊ አይደለም " ለምሳሌ እንደ አንድ አንባቢ መጽሐፉን አንብቤዋለሁ ። ነገር ግን እሱን መጽሐፍ አንብቤ ኢ-አማኝ አልሆንኩም።
*
#አልገባኝም
#ዮናስ ዘውዴ ከበደ
በመጀመርያ ወላጆችህ ፣አስተማሪዎችህ፣ ጎረቤቶችህ፣ ህብረተሰቡ፣ አንተን እንደ አንተነትህ ተቀብለውህ አያውቁም።
ሁሉም አንተን ሌላ ስብዕና ይዘህ እንድትኖር እንደ አዲስ ያርሙሃል።ያንተ ራስህን መሆን መቻል ግን አይመሰገንም። ገና ወደፊት የምትመስለው ስብዕና ነው የሚመሰገነው።
Osho/ኦሾ
ሁሉም አንተን ሌላ ስብዕና ይዘህ እንድትኖር እንደ አዲስ ያርሙሃል።ያንተ ራስህን መሆን መቻል ግን አይመሰገንም። ገና ወደፊት የምትመስለው ስብዕና ነው የሚመሰገነው።
Osho/ኦሾ
አንተ ትክክል መሆን አለመሆንህን ለማወቅ
የህሊናህ እና የድርጊትህ እንጂ የሌሎች ሰዎች
ድጋፍና ምስክርነት አያሻህም ። ትክክለኛውን
እንጂ አብዛኛውን ለመሆን አልተፈጠርክም።
ትክክል ባትሆን እንኳን መቶ በመቶ የሌላ ሰው
ቅጂ አትሁን።"
#ኦሾ/Osho
የህሊናህ እና የድርጊትህ እንጂ የሌሎች ሰዎች
ድጋፍና ምስክርነት አያሻህም ። ትክክለኛውን
እንጂ አብዛኛውን ለመሆን አልተፈጠርክም።
ትክክል ባትሆን እንኳን መቶ በመቶ የሌላ ሰው
ቅጂ አትሁን።"
#ኦሾ/Osho
የመኖር አካል ሁን ለመኖር የወደፊቱን የገና ለገና ውጥን አትጠብቅ ወይም ወደ ኃላ በትዝታ ምናብ አትጓዝ ህይወት ወደ ፊትም ወደ ኃላም አትጓዝም አዕምሮ እንጂ ህይወት አሁን ናት!!
OSHO/ኦሾ
OSHO/ኦሾ
"አንዳንድ ጊዜ ብዙም ማህበራዊ መስተጋብር የሌላቸው ከሰው መሀል ወጥተው ዳር የሚይዙ ሰዎች ማህበራዊ ኑሮ የሚጠሉ አይደለም ፤ ከዚህ ይልቅ የውሸት ድራማን ፣ ድድብናንና አስመሳይነትን መቋቋም ስለሚከብዳቸው ነው።"
#Osho /ኦሾ
#Osho /ኦሾ
የመጀመርያው እና ከሁሉ የሚቀድመው የገዛ ራስን ማፍቀር ነው። ልባችሁ የሳሳ እንጂ ልበ- ደንዳኖች አትሁኑ። ለገዛ ራሳችሁ ግድ ይኑራችሁ።
እንዴት ለራሳችሁ ይቅርታ እንደምታደርጉለት እወቁ። ጨካኞች አትሁኑ ፤ ራሳችሁን አትቃረኑ። የዚያን ጊዜ እንደ አበባ ትፈካላችሁ።
ህያውነት 2
Osho/ኦሾ
እንዴት ለራሳችሁ ይቅርታ እንደምታደርጉለት እወቁ። ጨካኞች አትሁኑ ፤ ራሳችሁን አትቃረኑ። የዚያን ጊዜ እንደ አበባ ትፈካላችሁ።
ህያውነት 2
Osho/ኦሾ
አንተ ትክክል መሆን አለመሆንህን ለማወቅ
የህሊናህ እና የድርጊትህ እንጂ የሌሎች ሰዎች
ድጋፍና ምስክርነት አያሻህም ። ትክክለኛውን
እንጂ አብዛኛውን ለመሆን አልተፈጠርክም።
ትክክል ባትሆን እንኳን መቶ በመቶ የሌላ ሰው
ቅጂ አትሁን።"
#ኦሾ/Osho
የህሊናህ እና የድርጊትህ እንጂ የሌሎች ሰዎች
ድጋፍና ምስክርነት አያሻህም ። ትክክለኛውን
እንጂ አብዛኛውን ለመሆን አልተፈጠርክም።
ትክክል ባትሆን እንኳን መቶ በመቶ የሌላ ሰው
ቅጂ አትሁን።"
#ኦሾ/Osho
የመኖር አካል ሁን ለመኖር የወደፊቱን የገና ለገና ውጥን አትጠብቅ ወይም ወደ ኃላ በትዝታ ምናብ አትጓዝ ህይወት ወደ ፊትም ወደ ኃላም አትጓዝም አዕምሮ እንጂ ህይወት አሁን ናት!!
OSHO/ኦሾ
OSHO/ኦሾ
የመጀመርያው እና ከሁሉ የሚቀድመው የገዛ ራስን ማፍቀር ነው። ልባችሁ የሳሳ እንጂ ልበ- ደንዳኖች አትሁኑ። ለገዛ ራሳችሁ ግድ ይኑራችሁ።
እንዴት ለራሳችሁ ይቅርታ እንደምታደርጉለት እወቁ። ጨካኞች አትሁኑ ፤ ራሳችሁን አትቃረኑ። የዚያን ጊዜ እንደ አበባ ትፈካላችሁ።
ህያውነት 2
Osho/ኦሾ
እንዴት ለራሳችሁ ይቅርታ እንደምታደርጉለት እወቁ። ጨካኞች አትሁኑ ፤ ራሳችሁን አትቃረኑ። የዚያን ጊዜ እንደ አበባ ትፈካላችሁ።
ህያውነት 2
Osho/ኦሾ
"አንዳንድ ጊዜ ብዙም ማህበራዊ መስተጋብር የሌላቸው ከሰው መሀል ወጥተው ዳር የሚይዙ ሰዎች ማህበራዊ ኑሮ የሚጠሉ አይደለም ፤ ከዚህ ይልቅ የውሸት ድራማን ፣ ድድብናንና አስመሳይነትን መቋቋም ስለሚከብዳቸው ነው።"
#Osho /ኦሾ
#Osho /ኦሾ
የመጀመርያው እና ከሁሉ የሚቀድመው የገዛ ራስን ማፍቀር ነው። ልባችሁ የሳሳ እንጂ ልበ- ደንዳኖች አትሁኑ። ለገዛ ራሳችሁ ግድ ይኑራችሁ።
እንዴት ለራሳችሁ ይቅርታ እንደምታደርጉለት እወቁ። ጨካኞች አትሁኑ ፤ ራሳችሁን አትቃረኑ። የዚያን ጊዜ እንደ አበባ ትፈካላችሁ።
ህያውነት 2
Osho/ኦሾ
እንዴት ለራሳችሁ ይቅርታ እንደምታደርጉለት እወቁ። ጨካኞች አትሁኑ ፤ ራሳችሁን አትቃረኑ። የዚያን ጊዜ እንደ አበባ ትፈካላችሁ።
ህያውነት 2
Osho/ኦሾ