#ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም።
የባግዳድ ነዋሪ የነበረ አንድ ባለጸጋ በጣም የሚወደው ባሪያውን ወደ ገበያ ይልከዋል፡፡ የተላከው ባሪያ ብዙም ሳይቆይ ላብ በላብ ሆኖ በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ይመለሳል፡፡
ጌታውም ምን እንደሆነ ሲጠይቀው ፦ “አንዲት ሴት በገበያው መሀከል ስትዘዋወር አየሁ፡፡ ቀረብ ብዬ ሳስተውላት ሞት ናት፡፡ እሷም ልክ እንዳዬችኝ በጣቷ የዛቻ ምልክት አሳየችኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ፦ እባክህ ፈረስህን ስጠኝና ወደ ሳማራ ከተማ ሸሽቼ ሞትን ላምልጣት፡" አለው።
ባለፀጋውም ለባሪያው ፈረሱን ሰጠው፡፡
ባሪያውም ሞትን ሽሽት ወዲያውኑ ፈረሱ ላይ ወጥቶ ሽምጥ እየጋለበ ወደ ሳማራ ከተማ ገሰገሰ።
ባለፀጋውም የሚያስፈልገውን ነገር ራሱ ለመገብዬት ከጥቂት ከቆይታ በኋላ ወደ ገበያ ሄዶ ሲዘዋወር ሞትን አገኛት፡፡ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላም፦ “ቅድም ባሪያዬ ስታይው ስለምን አስፈራራሽው?” ሲል ጠየቃት፡፡ ሞትም ፈገግ ብላ፦ “እያስፈራራኹትኮ አይደለም። ዛሬ ማታ ሳማራ ከተማ ላይ ቀጠሮ ስላለን፣ እዚህ ሳየው ተገርሜ ነው” አለችው።
ፈጣሪ የቀጠራት ቀን ከደረሰች ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም።ከባግዳድ አመለጥኳት ያልካት ሞት- ቀድሞ ሳማራ ገብታ ትጠብቅሀለች።
የባግዳድ ነዋሪ የነበረ አንድ ባለጸጋ በጣም የሚወደው ባሪያውን ወደ ገበያ ይልከዋል፡፡ የተላከው ባሪያ ብዙም ሳይቆይ ላብ በላብ ሆኖ በፍርሀት እየተንቀጠቀጠ ይመለሳል፡፡
ጌታውም ምን እንደሆነ ሲጠይቀው ፦ “አንዲት ሴት በገበያው መሀከል ስትዘዋወር አየሁ፡፡ ቀረብ ብዬ ሳስተውላት ሞት ናት፡፡ እሷም ልክ እንዳዬችኝ በጣቷ የዛቻ ምልክት አሳየችኝ፡፡ ጌታዬ ሆይ፦ እባክህ ፈረስህን ስጠኝና ወደ ሳማራ ከተማ ሸሽቼ ሞትን ላምልጣት፡" አለው።
ባለፀጋውም ለባሪያው ፈረሱን ሰጠው፡፡
ባሪያውም ሞትን ሽሽት ወዲያውኑ ፈረሱ ላይ ወጥቶ ሽምጥ እየጋለበ ወደ ሳማራ ከተማ ገሰገሰ።
ባለፀጋውም የሚያስፈልገውን ነገር ራሱ ለመገብዬት ከጥቂት ከቆይታ በኋላ ወደ ገበያ ሄዶ ሲዘዋወር ሞትን አገኛት፡፡ ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላም፦ “ቅድም ባሪያዬ ስታይው ስለምን አስፈራራሽው?” ሲል ጠየቃት፡፡ ሞትም ፈገግ ብላ፦ “እያስፈራራኹትኮ አይደለም። ዛሬ ማታ ሳማራ ከተማ ላይ ቀጠሮ ስላለን፣ እዚህ ሳየው ተገርሜ ነው” አለችው።
ፈጣሪ የቀጠራት ቀን ከደረሰች ሞትን ሸሽተህ አታመልጣትም።ከባግዳድ አመለጥኳት ያልካት ሞት- ቀድሞ ሳማራ ገብታ ትጠብቅሀለች።
"ሰብአዊነት ሊወለድ የሚችለው ከፍቅር ልብ ነው!"
❤ ❤ ❤
በፍቅር በተሞላ ልብ መኖር እጅግ አስፈላጊ ነው።የፍቅር አመለካከት ሁላችንም ውስጥ ሊኖር ይገባል።ሰብአዊነት ሊወለድ የሚችለው ከፍቅር ልብ ነው፤በፍቅር ልብ ውስጥ ጥልቅ የደስታ ስሜት ይኖራል።ትንሽ ፍቅር ለሰው ከለገሷችሁ በኃላ የሚሰማችሁ የሀሴት ስሜት አስተውላችሁ ታውቁታላችሁ?
መስፈርት በሌለው ፍቅር(unconditional love) ወስጥ ሆናችሁ የሚኖረውን ሰላም አስተውላችሁ ታውቃላችሁ?
ንፁህ ፍቅር ሊኖር የሚችለው በምክንያቶችና በመሥፈርቶች ካልታጀበ ብቻ ነው፤በሁኔታ የሚወሰን ፍቅር (conditional love) ፍቅር አይደለም የማታውቁትን ሰው መንገድ ላይ ፊት ለፊት ፈገግታውን ተመልክታችሁ የሚሰማችሁን ደስታ አስተውላችሁታል?
የወደቀን ስታነሱ የደከመን ስትረዱ የታመመን አበባ ስታበረክቱና ስጠይቁ የሚሰማችሁ የደስታ ስሜት ወሰን የለውም፤ ይህን የምታደርጉት አባታችሁ ወይም እናታችሁ ስለሆኑ አይደለም በሰውነት የምታበረክቱት ስጦታ ለእናንተ በተራው ታላቅ ደስታና እርካታና ስለሚያበረክት እንጂ።ለዚህም ነው ሰብአዊነት ሊወለድ የሚችለው ከፍቅር ልብ ነው የምላችሁ።
➦ኦሾ/Osho /
❤ ❤ ❤
በፍቅር በተሞላ ልብ መኖር እጅግ አስፈላጊ ነው።የፍቅር አመለካከት ሁላችንም ውስጥ ሊኖር ይገባል።ሰብአዊነት ሊወለድ የሚችለው ከፍቅር ልብ ነው፤በፍቅር ልብ ውስጥ ጥልቅ የደስታ ስሜት ይኖራል።ትንሽ ፍቅር ለሰው ከለገሷችሁ በኃላ የሚሰማችሁ የሀሴት ስሜት አስተውላችሁ ታውቁታላችሁ?
መስፈርት በሌለው ፍቅር(unconditional love) ወስጥ ሆናችሁ የሚኖረውን ሰላም አስተውላችሁ ታውቃላችሁ?
ንፁህ ፍቅር ሊኖር የሚችለው በምክንያቶችና በመሥፈርቶች ካልታጀበ ብቻ ነው፤በሁኔታ የሚወሰን ፍቅር (conditional love) ፍቅር አይደለም የማታውቁትን ሰው መንገድ ላይ ፊት ለፊት ፈገግታውን ተመልክታችሁ የሚሰማችሁን ደስታ አስተውላችሁታል?
የወደቀን ስታነሱ የደከመን ስትረዱ የታመመን አበባ ስታበረክቱና ስጠይቁ የሚሰማችሁ የደስታ ስሜት ወሰን የለውም፤ ይህን የምታደርጉት አባታችሁ ወይም እናታችሁ ስለሆኑ አይደለም በሰውነት የምታበረክቱት ስጦታ ለእናንተ በተራው ታላቅ ደስታና እርካታና ስለሚያበረክት እንጂ።ለዚህም ነው ሰብአዊነት ሊወለድ የሚችለው ከፍቅር ልብ ነው የምላችሁ።
➦ኦሾ/Osho /
የሚሸነፍ ትግል የለም፤ የሚሸነፍ ሰው እንጂ”
:
ይገርምሃል ወንድሜ፤ በሕይወትህ ድል አድርገህ ዋንጫ ወሰድክ ማለት እዚያው የልዕልና ማማ ላይ እንደተሰቀልክ ትቀራለህ ማለት አይደለም።ብዙዎች‘ኮ ሲወጡ መውረድን ይረሱታል፡፡ለሚወጣ ሰው ግን መውረድ የጥላውን ያህል ቅርብ ነው፡፡ ‹እኖራለሁ ብለህ ሥራ፤ እሞታለሁ ብለህ ኑር› ሲባል አልሰማህም? መውረድን የረሳ ባለ ሥልጣን፣ ሕመምን የረሳ ጤነኛ፣ ድህነትን የረሳ ሀብታም፣ ሞትን የረሳ ነዋሪ፣ ድቀትን የረሳ ጻድቅ፣ ውርደትን የረሳ ክቡር፣ ወደረሳው ነገር ለመጓዝ እንዴት ይፈጥናል መሰለህ? ድቅድቁ ጨለማ ያለው ከሻማው ሥር ነው፡፡ወዳጄ በዚህ ዓለም ላይ የማይነጠቅ የተጨበጠ፣የማይንሸራተት የተረገጠ የለም፡፡ nothing for granted ይሉ የለም ። የጨበጥክበት እጅህ፣ የረገጥክበት እግርህ አንድ ቀን ይዝላል፡፡የትናንት አይበገሬነትህ፣ የትናንት ጀግንነትህ፣ የትናንት ክብርህ፣የትናንት አሸናፊነትህ፣ የትናንት ተፈሪነትህ በዛሬ ጥረት ካልታገዘ ታሪክና ቅርስ እንጂ ድልና ውጤት አይኖርህም፡፡ድል ማለት ጥረትና ዕድል የሚገናኙባት አጋጣሚ ናት› ይላሉ፡፡ አንተ ትታገላለህ፣ ትጥራለህ፣ ትለፋለህ፣ ትደክማለህ፣ ትወጣለህ፣ ትወርዳለህ፤ እንዲህ ባለማቋረጥ ስትታገል አንድ ቀን የአንተ የጥረትህ መንገድ ከዕድል መንገድ ጋር ይገናኝና ታቋርጠዋለህ፡፡ ያኔ አይወድቅም የተባለው ወድቆ፣ አይሸነፍም የተባለው ተሸንፎ፣ አይነቀነቅም የተባለው ተነቅንቆ፣አይፈርስም የተባለው ፈርሶ፣ አይነካም የተባለው ተነክቶ ቦታውን ሲለቅ ታየዋለህ፡፡አንተ ካልጣርክና ካልታገልክ፣ ካልሠራህና ካልሞከርክ ግን በዕድል ብቻ የሚሆን ነገር የለም። ዛሬ አላሸነፍክም? ተስፋ አትቁረጥ፤ ቢያንስ የማሸነፍ ሞራልና የማሸነፍ ተስፋ አለህና፡፡ የሚሸነፍ ትግል የለም፡፡ የሚሸነፍ ሰው እንጂ፡፡ ትግል ትግልን ይወልዳል፣ ጥረት ጥረትን ይተካል፣ ሙከራ ሙከራን ያመጣል፡፡ዛሬ አንድ አካፋ አፈር ከተራራው ላይ ስታነሣ ተራራውን አልናድከው ይሆናል፡፡ በርግጠኝነት ግን የተራራውን መልክ ቀይረኸዋል፡፡ በአካባቢው የሚያልፉ ሰዎች፣ ወይም አንተ ራስህ እንኳን የተራራው መልክ መቀየሩን ላታውቀው ትችላለህ፡፡ ተራራው ራሱ ግን ያውቀዋል፡፡ የመሬት መሸርሸር የሚባለው ግማሽ ተራራ ተሸርሽሮ አይደለም‘ኮ፡፡ ውኃ እያሳሳቀ አፈሩን በየጊዜው ሲወስደው ነው፡፡ ምናልባትም ምንም አታመጣም ብለው ሰዎች ይነግሩህ ይሆናል፡፡
ዳንኤል ክብረት
:
ይገርምሃል ወንድሜ፤ በሕይወትህ ድል አድርገህ ዋንጫ ወሰድክ ማለት እዚያው የልዕልና ማማ ላይ እንደተሰቀልክ ትቀራለህ ማለት አይደለም።ብዙዎች‘ኮ ሲወጡ መውረድን ይረሱታል፡፡ለሚወጣ ሰው ግን መውረድ የጥላውን ያህል ቅርብ ነው፡፡ ‹እኖራለሁ ብለህ ሥራ፤ እሞታለሁ ብለህ ኑር› ሲባል አልሰማህም? መውረድን የረሳ ባለ ሥልጣን፣ ሕመምን የረሳ ጤነኛ፣ ድህነትን የረሳ ሀብታም፣ ሞትን የረሳ ነዋሪ፣ ድቀትን የረሳ ጻድቅ፣ ውርደትን የረሳ ክቡር፣ ወደረሳው ነገር ለመጓዝ እንዴት ይፈጥናል መሰለህ? ድቅድቁ ጨለማ ያለው ከሻማው ሥር ነው፡፡ወዳጄ በዚህ ዓለም ላይ የማይነጠቅ የተጨበጠ፣የማይንሸራተት የተረገጠ የለም፡፡ nothing for granted ይሉ የለም ። የጨበጥክበት እጅህ፣ የረገጥክበት እግርህ አንድ ቀን ይዝላል፡፡የትናንት አይበገሬነትህ፣ የትናንት ጀግንነትህ፣ የትናንት ክብርህ፣የትናንት አሸናፊነትህ፣ የትናንት ተፈሪነትህ በዛሬ ጥረት ካልታገዘ ታሪክና ቅርስ እንጂ ድልና ውጤት አይኖርህም፡፡ድል ማለት ጥረትና ዕድል የሚገናኙባት አጋጣሚ ናት› ይላሉ፡፡ አንተ ትታገላለህ፣ ትጥራለህ፣ ትለፋለህ፣ ትደክማለህ፣ ትወጣለህ፣ ትወርዳለህ፤ እንዲህ ባለማቋረጥ ስትታገል አንድ ቀን የአንተ የጥረትህ መንገድ ከዕድል መንገድ ጋር ይገናኝና ታቋርጠዋለህ፡፡ ያኔ አይወድቅም የተባለው ወድቆ፣ አይሸነፍም የተባለው ተሸንፎ፣ አይነቀነቅም የተባለው ተነቅንቆ፣አይፈርስም የተባለው ፈርሶ፣ አይነካም የተባለው ተነክቶ ቦታውን ሲለቅ ታየዋለህ፡፡አንተ ካልጣርክና ካልታገልክ፣ ካልሠራህና ካልሞከርክ ግን በዕድል ብቻ የሚሆን ነገር የለም። ዛሬ አላሸነፍክም? ተስፋ አትቁረጥ፤ ቢያንስ የማሸነፍ ሞራልና የማሸነፍ ተስፋ አለህና፡፡ የሚሸነፍ ትግል የለም፡፡ የሚሸነፍ ሰው እንጂ፡፡ ትግል ትግልን ይወልዳል፣ ጥረት ጥረትን ይተካል፣ ሙከራ ሙከራን ያመጣል፡፡ዛሬ አንድ አካፋ አፈር ከተራራው ላይ ስታነሣ ተራራውን አልናድከው ይሆናል፡፡ በርግጠኝነት ግን የተራራውን መልክ ቀይረኸዋል፡፡ በአካባቢው የሚያልፉ ሰዎች፣ ወይም አንተ ራስህ እንኳን የተራራው መልክ መቀየሩን ላታውቀው ትችላለህ፡፡ ተራራው ራሱ ግን ያውቀዋል፡፡ የመሬት መሸርሸር የሚባለው ግማሽ ተራራ ተሸርሽሮ አይደለም‘ኮ፡፡ ውኃ እያሳሳቀ አፈሩን በየጊዜው ሲወስደው ነው፡፡ ምናልባትም ምንም አታመጣም ብለው ሰዎች ይነግሩህ ይሆናል፡፡
ዳንኤል ክብረት
#ራስን ማወቅ ሌላውንም ማወቅ ይሆናል!!
"...የሰው ልጅ የተፈጥሮን ህግ ሊለውጥ አይችልም። ለምሳሌ ቀንና ጨለማን፣ ሞትና ህይወትን፣ ማደግና ማርጀትን፣ ማበብና መክሰምን ሊለውጥ አይችልም። የማይለወጡ የተፈጥሮ ህግጋት አሉ ማለት ነው። እነዚህን አሜን ብሎ መቀበል አንዱ የደስታ ምንጭ ማለት ነው። አሜን ብሎ ተቀብሎ ዝም ማለት ብቻ አይደለም።
የህይወት መጨረሻ ግቡ የሰው ልጅ በዚህች አለም ላይ በሚኖርበት አጭር ጊዜ ውስጥ ተፈጥሮውን አሟልቶና ተደስቶ ለመኖር ስለሆነ፤ እያንዳንዱ ሰው ተፈጥሮውን እንዳያሟላና እንዳይደሰት የሚያደርጉትን መጥፎ ነገሮች ሁሉ ከራሱ ልብ ውስጥም ሆነ ከአካባቢው ለማስወገድ መጣር አለበት። ይህን ለማድረግ... ልበ ሙሉ መሆን ያስፈልጋል። የሰው ልጅ ክብር ዋስትና መስዋዕትነት ነው። መስዋዕትነት ደግሞ ያለ ልበ ሙሉነት መች ይሆናል። ራሳቸው እየነደዱ አልቀው ለሌላው ብርሀን የሚሆኑ ልበ ሙሉዎች ብቻ ናቸው። መፅሀፉም'ኮ እሹ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ያለው ሌላ ሳይሆን የራሳችንን ልብ ነው። ራስን ማወቅ የመጨረሻ ጥበብ ነው።
ራስን ማወቅ ሌላውንም ማወቅ ይሆናል። ካወክ ዘንድ ለራስህ የምትሻውን ለሌላውም ትመኛለህ። ለራስህና ለሰው ልጅ ሁሉ በጎ ፈቃድና ፍቅር ይኖርሀል። ከዚህ ዕውቀት ደረጃ ላይ ስትደርስ ለምታደርገው ነገር ሁሉ ምስጋናም ሆነ ጥቅም ከሰው ዘንድ አትሻም። ልብህ ጥቅም ላይ ካተኮረ የተፈጥሮን በጎ ምግባር ትስታለህ።
#"ደራሲው" በዓሉ ግርማ
"...የሰው ልጅ የተፈጥሮን ህግ ሊለውጥ አይችልም። ለምሳሌ ቀንና ጨለማን፣ ሞትና ህይወትን፣ ማደግና ማርጀትን፣ ማበብና መክሰምን ሊለውጥ አይችልም። የማይለወጡ የተፈጥሮ ህግጋት አሉ ማለት ነው። እነዚህን አሜን ብሎ መቀበል አንዱ የደስታ ምንጭ ማለት ነው። አሜን ብሎ ተቀብሎ ዝም ማለት ብቻ አይደለም።
የህይወት መጨረሻ ግቡ የሰው ልጅ በዚህች አለም ላይ በሚኖርበት አጭር ጊዜ ውስጥ ተፈጥሮውን አሟልቶና ተደስቶ ለመኖር ስለሆነ፤ እያንዳንዱ ሰው ተፈጥሮውን እንዳያሟላና እንዳይደሰት የሚያደርጉትን መጥፎ ነገሮች ሁሉ ከራሱ ልብ ውስጥም ሆነ ከአካባቢው ለማስወገድ መጣር አለበት። ይህን ለማድረግ... ልበ ሙሉ መሆን ያስፈልጋል። የሰው ልጅ ክብር ዋስትና መስዋዕትነት ነው። መስዋዕትነት ደግሞ ያለ ልበ ሙሉነት መች ይሆናል። ራሳቸው እየነደዱ አልቀው ለሌላው ብርሀን የሚሆኑ ልበ ሙሉዎች ብቻ ናቸው። መፅሀፉም'ኮ እሹ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ያለው ሌላ ሳይሆን የራሳችንን ልብ ነው። ራስን ማወቅ የመጨረሻ ጥበብ ነው።
ራስን ማወቅ ሌላውንም ማወቅ ይሆናል። ካወክ ዘንድ ለራስህ የምትሻውን ለሌላውም ትመኛለህ። ለራስህና ለሰው ልጅ ሁሉ በጎ ፈቃድና ፍቅር ይኖርሀል። ከዚህ ዕውቀት ደረጃ ላይ ስትደርስ ለምታደርገው ነገር ሁሉ ምስጋናም ሆነ ጥቅም ከሰው ዘንድ አትሻም። ልብህ ጥቅም ላይ ካተኮረ የተፈጥሮን በጎ ምግባር ትስታለህ።
#"ደራሲው" በዓሉ ግርማ
በድሮ ጊዜ ውስጥ ታስራችሁ እንዳትቀሩ!
:
"እኔ ፀረ ሰላም አይደለሁም ፣ብጥብጥን አልደግፍም። አለም የበለጠ ውብ ፣የበለጠ ተስማሚ እንድትሆን እፈልጋለሁ። ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ግን ግርግርን አሞካሻለሁ የሚለን ኦሾ። ስለ ምክንያቱ ምክንያት ሲሰጠን የበሰበሰውን ስርአት ለመንቀል ነው ይለናል።
አመፀኝነትን አሞካሻለሁ ለምን ካላችሁ አዲስ ነገር ይፈጠር ዘንድ የተገባ ነውና ፣ በአንድ ቦታ ላይ ረግቶ የበሰበሰ ስርአት ተጠራርጎ ይሄድ ዘንድ ነው። ተቀባይነት የሌላቸው ልማዶች ፣ ስምምነቶች ፣ ያረጁ ያፈጁ ባህሎችን እነሱንም እፃረራለሁ። ለምን ? ብትሉ አዳዲስ አለማትን መፍጠር እንድትችሉ ፣ በድሮ ጊዜ ውስጥ ታስራችሁ እንዳትቀሩ ፣ለወደፊቱ የተሻለ ነገር እንዲኖራችሁ ነፃ ላደርጋችሁ ስል ብቻ ነው። እኔ አጥፊ አይደለሁም።
◌
ኦሾ/Osho
:
"እኔ ፀረ ሰላም አይደለሁም ፣ብጥብጥን አልደግፍም። አለም የበለጠ ውብ ፣የበለጠ ተስማሚ እንድትሆን እፈልጋለሁ። ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ግን ግርግርን አሞካሻለሁ የሚለን ኦሾ። ስለ ምክንያቱ ምክንያት ሲሰጠን የበሰበሰውን ስርአት ለመንቀል ነው ይለናል።
አመፀኝነትን አሞካሻለሁ ለምን ካላችሁ አዲስ ነገር ይፈጠር ዘንድ የተገባ ነውና ፣ በአንድ ቦታ ላይ ረግቶ የበሰበሰ ስርአት ተጠራርጎ ይሄድ ዘንድ ነው። ተቀባይነት የሌላቸው ልማዶች ፣ ስምምነቶች ፣ ያረጁ ያፈጁ ባህሎችን እነሱንም እፃረራለሁ። ለምን ? ብትሉ አዳዲስ አለማትን መፍጠር እንድትችሉ ፣ በድሮ ጊዜ ውስጥ ታስራችሁ እንዳትቀሩ ፣ለወደፊቱ የተሻለ ነገር እንዲኖራችሁ ነፃ ላደርጋችሁ ስል ብቻ ነው። እኔ አጥፊ አይደለሁም።
◌
ኦሾ/Osho
"መሸበርና መፍራት የነገን ችግር አያስወግድልንም ይልቁኑስ የዛሬን ደስታ ያሳጣናል ።
... ሕይወት፣ የመዘጋጃና የመኖሪያ ዕድሜ የሌላት፣ ከአፈር ለተሠራ ሰው የተሰጠች ስጦታ ነች ፡፡ የሰው ልጅም ከተፈጠረ ጀምሮ ሕይወትን በውስጡ ለማሰንበት በትግል የሚኖር፣ ሲያጣትም እጅግ ጠሊቅ ሐዘን ውስጥ የሚገባ ፍጡር ነው፡፡ ሰዉ የራሱንና የሚወዳቸውን እስትንፋስ ለማቈየት፣ ከሰከንድ እስከ ሰዓታት ከዛሬው እየተበደረ ለማያውቀው ነገ ሲገብር፣ ለማያውቀው ነገ ደስታ ዛሬ ሲያለቅስ፣ ለማያውቀው ነገ ጥጋብ ዛሬ ሲራብ ሲታረዝ፣ ከማያውቀው ነገ ተበድሮ ዛሬ ሲጨነቅ የሚኖርና መኖሩን ሳያውቅ የሚሞት ፍጡር…፡፡"
*
ሜሎሪና ገጽ 9
... ሕይወት፣ የመዘጋጃና የመኖሪያ ዕድሜ የሌላት፣ ከአፈር ለተሠራ ሰው የተሰጠች ስጦታ ነች ፡፡ የሰው ልጅም ከተፈጠረ ጀምሮ ሕይወትን በውስጡ ለማሰንበት በትግል የሚኖር፣ ሲያጣትም እጅግ ጠሊቅ ሐዘን ውስጥ የሚገባ ፍጡር ነው፡፡ ሰዉ የራሱንና የሚወዳቸውን እስትንፋስ ለማቈየት፣ ከሰከንድ እስከ ሰዓታት ከዛሬው እየተበደረ ለማያውቀው ነገ ሲገብር፣ ለማያውቀው ነገ ደስታ ዛሬ ሲያለቅስ፣ ለማያውቀው ነገ ጥጋብ ዛሬ ሲራብ ሲታረዝ፣ ከማያውቀው ነገ ተበድሮ ዛሬ ሲጨነቅ የሚኖርና መኖሩን ሳያውቅ የሚሞት ፍጡር…፡፡"
*
ሜሎሪና ገጽ 9
"እውነትን ገድዬ እኔ ነፃ ከምሆን እኔ ሞቼ ሕግ ነፃ ትሁን !"
/ሶቅራጠስ/
"ፕሌቶን ከቀደምት የግሪክ ፈላስፋዎች ለየት የሚያደርገው በፊት የነበሩት የግርክ ፍልስፍናዎች በተወሰነ መልኩ በአንድ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚያጠነጥኑ ሲሆኑ ፕሌቶ ግን በሁሉም የእውቀት ዘርፎች ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ መስጠት መቻሉ ነበር፡፡ ደህና ደረጃ ከነበራቸው ቤተሰቦቹ ከክርስቶስ ልደት በፊት 427 ም.አ በአቴንስ የተወለደው ፕሌቶ በምዕራባዉያን ፍልስፍና ታሪክ እጅግ በጣም ጎላ ያለ ቦታ የሚሰጠውና ከሶቅራጥስ ተማሪዎች አንዱ በመሆን ጎልቶ መውጣት የቻለ ፈላስፋ ነው፡፡ ፕሌቶ በኖረበት ዘመን አቴናዉያን ዴሞክራሲ እየተዳከመ የመጣበት ዘመን በመሆኑና እንደ መሲህ የሚያየው የቀለም አባቱ ሰቆራጥስ በአቴናዉያን ፊት ለፊቱ በመርዝ ሲደፋ በማየቱ ለአቴናውያን የነበረው አስተሳሰብ በአሉታዊ ገጽታ የሚቀምጥ ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ ፕሌቶ እየዘመመ የመጣውን የአቴናዉያን ዴሞክራሲን እንዲንሰራራ ለማድረግ የተለያዩ የፖለቲካ አስተሳሰቦችን ለመቀመር መነሳሳት ጀመረ፡፡ በ387 ም.አ ገደማ በአዉሮፓ ከቀደምት ጥንታዊ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አንዱ ሊባል የሚችለውንና ለብዙ ተማሪዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ትምህርት የሚሰጥበትን አካዳሚ መስርቶ በመምህርነት እና ፍልስፍ በመፃፍ ከ40 አመት በኋላ ያለውን እድሜውን አሳልፏል፡፡ የፕሌቶ ስራዎች በርካታ ሲሆኑ አብዛኞቹ አስተማሪው ከነበረው የሶቅራጥስ ትምህርቶችን የያዙ ነበሩ፡፡
:
ታላቁ የፍልስፍና ሰው ሶቅራጦስ ከመገደሉ አንድ ቀን በፊት የእሱ ደቀመዝሙር የነበረው ፕሌቶ ገንዘብ ሰብስቦ ለጠባቂዎች ጉቦ በመስጠት እሱን ለማስመለጥ እየሞከረ መሆኑን ነገረው ። ሶቅራጦስም ፦ "በዘመኔ ሁሉ ለሕግ እንደኖርኩ አሁንም ለእሷ ለመሞት እንደተዘጋጀሁ ታውቃለህ ፤ እውነትን ገድዬ እኔ ነፃ ከምሆን እኔ ሞቼ ሕግ ነፃ ትሁን !" በማለት የፕሌቶን ሀሳብ ሳይቀበል ቀረ ። ለዚህም ነው የሶቅራጦስ አድናቂዎች ፦ " ማሰብ ሳይችሉ እንደ ካሊባን ዙፋን ላይ ከመቀመጥ በወህኒ ቤት እንደ ሶቅራጦስ እያሰቡ መኖር ይሻላል!" የሚሉት ። እኔ ደሞ እንዲህ አልኩ በንባብ የሀሳብ አድማሳችንን እናስፉ።
:
ጥበብ ከጲላጦስ ቁ1/ኃይለጊዮጊስ ማሞ
/ሶቅራጠስ/
"ፕሌቶን ከቀደምት የግሪክ ፈላስፋዎች ለየት የሚያደርገው በፊት የነበሩት የግርክ ፍልስፍናዎች በተወሰነ መልኩ በአንድ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚያጠነጥኑ ሲሆኑ ፕሌቶ ግን በሁሉም የእውቀት ዘርፎች ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ መስጠት መቻሉ ነበር፡፡ ደህና ደረጃ ከነበራቸው ቤተሰቦቹ ከክርስቶስ ልደት በፊት 427 ም.አ በአቴንስ የተወለደው ፕሌቶ በምዕራባዉያን ፍልስፍና ታሪክ እጅግ በጣም ጎላ ያለ ቦታ የሚሰጠውና ከሶቅራጥስ ተማሪዎች አንዱ በመሆን ጎልቶ መውጣት የቻለ ፈላስፋ ነው፡፡ ፕሌቶ በኖረበት ዘመን አቴናዉያን ዴሞክራሲ እየተዳከመ የመጣበት ዘመን በመሆኑና እንደ መሲህ የሚያየው የቀለም አባቱ ሰቆራጥስ በአቴናዉያን ፊት ለፊቱ በመርዝ ሲደፋ በማየቱ ለአቴናውያን የነበረው አስተሳሰብ በአሉታዊ ገጽታ የሚቀምጥ ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ ፕሌቶ እየዘመመ የመጣውን የአቴናዉያን ዴሞክራሲን እንዲንሰራራ ለማድረግ የተለያዩ የፖለቲካ አስተሳሰቦችን ለመቀመር መነሳሳት ጀመረ፡፡ በ387 ም.አ ገደማ በአዉሮፓ ከቀደምት ጥንታዊ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አንዱ ሊባል የሚችለውንና ለብዙ ተማሪዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ትምህርት የሚሰጥበትን አካዳሚ መስርቶ በመምህርነት እና ፍልስፍ በመፃፍ ከ40 አመት በኋላ ያለውን እድሜውን አሳልፏል፡፡ የፕሌቶ ስራዎች በርካታ ሲሆኑ አብዛኞቹ አስተማሪው ከነበረው የሶቅራጥስ ትምህርቶችን የያዙ ነበሩ፡፡
:
ታላቁ የፍልስፍና ሰው ሶቅራጦስ ከመገደሉ አንድ ቀን በፊት የእሱ ደቀመዝሙር የነበረው ፕሌቶ ገንዘብ ሰብስቦ ለጠባቂዎች ጉቦ በመስጠት እሱን ለማስመለጥ እየሞከረ መሆኑን ነገረው ። ሶቅራጦስም ፦ "በዘመኔ ሁሉ ለሕግ እንደኖርኩ አሁንም ለእሷ ለመሞት እንደተዘጋጀሁ ታውቃለህ ፤ እውነትን ገድዬ እኔ ነፃ ከምሆን እኔ ሞቼ ሕግ ነፃ ትሁን !" በማለት የፕሌቶን ሀሳብ ሳይቀበል ቀረ ። ለዚህም ነው የሶቅራጦስ አድናቂዎች ፦ " ማሰብ ሳይችሉ እንደ ካሊባን ዙፋን ላይ ከመቀመጥ በወህኒ ቤት እንደ ሶቅራጦስ እያሰቡ መኖር ይሻላል!" የሚሉት ። እኔ ደሞ እንዲህ አልኩ በንባብ የሀሳብ አድማሳችንን እናስፉ።
:
ጥበብ ከጲላጦስ ቁ1/ኃይለጊዮጊስ ማሞ
ሰው ላይ እንድትፈርድ የሚያስቸኩልህ ባህሪ የሚያሳየው ሁሉንም ሰው ከአንተ በታች ለማድረግ የምታደርገውን ጥረት ነው።
አንድ ሰው ልእለ ሰብነት (ታላቅነት) ላይ ለመድረስ ታላቅ ንቃት ይጠይቃል። ከውስጣችሁ ካለው ተራራ ጫፍ ላይ መውጣትይጠበቅ ባችኋል። ይህ ደግሞ አስቸጋሪ ይመስላል።
ስለዚህ ቀላሉና ርካሹ መንገዱ ራሳችሁን የበላይ ለማድረግ ከመጣር ይልቅ ....ምንም ድካም እማያስፈልገው ሌሎችን የበታች አርጎ መቁጠር ነው።
ለዛ ነው ሰው ላይ ለመፍረድ የምትቸኩለው። ሌላው ላይ ለመፍረድ የምታደርገው ጥረት አንተ የተሻልክ እንደሆንክ ለማሳየት ያለህን ፍላጎት ያረጋግጣል። "ይህ ሰውየ እኮ ሌባ ነው፤ ይህ ሰውየ እኮ ሴት ተደፍሯል፤ ይህኮ የለየለት እብድ ነው.............."
ለሁሉም ሰው ልክ ታወጣና መጨረሻ አንተ ብቻ ንፁህ ሆነህ ትቀራለህ። ግን ሰው ላይ መፍረድ የዝቅተኛ ሰው መለያ ነው።
ኦሾ
አንድ ሰው ልእለ ሰብነት (ታላቅነት) ላይ ለመድረስ ታላቅ ንቃት ይጠይቃል። ከውስጣችሁ ካለው ተራራ ጫፍ ላይ መውጣትይጠበቅ ባችኋል። ይህ ደግሞ አስቸጋሪ ይመስላል።
ስለዚህ ቀላሉና ርካሹ መንገዱ ራሳችሁን የበላይ ለማድረግ ከመጣር ይልቅ ....ምንም ድካም እማያስፈልገው ሌሎችን የበታች አርጎ መቁጠር ነው።
ለዛ ነው ሰው ላይ ለመፍረድ የምትቸኩለው። ሌላው ላይ ለመፍረድ የምታደርገው ጥረት አንተ የተሻልክ እንደሆንክ ለማሳየት ያለህን ፍላጎት ያረጋግጣል። "ይህ ሰውየ እኮ ሌባ ነው፤ ይህ ሰውየ እኮ ሴት ተደፍሯል፤ ይህኮ የለየለት እብድ ነው.............."
ለሁሉም ሰው ልክ ታወጣና መጨረሻ አንተ ብቻ ንፁህ ሆነህ ትቀራለህ። ግን ሰው ላይ መፍረድ የዝቅተኛ ሰው መለያ ነው።
ኦሾ
"የተነገራችሁን ሁሉ ቀጥታ እንደወረደ አምናችሁ አትቀበሉ ከዚያ ይልቅ እውነትን በብልሃትና በንቃት ለማግኘት ሞክሩ።
እውነት ሁልጊዜ ተሞክሮ ነው። የእኔ እውነት የእናንተ ሊሆን አይችልም ፤ ያለማወላወል የእኔ ብቻ ነው። እውነትን ልንጋራው አንችልም።እኔ የምሰጣችሁ ግንዛቤ ብቻ ነው። ከዚያ በተረፈ እያንዳንዱ ሰው እውነትን ደጋግሞ በራሱ ማግኝት አለበት ። ስለሆነም ለመመራመር ፣ ለመጠየቅ፣ ለመሞከር ለመተግበር ትጉ።"
#ኦሾ
እውነት ሁልጊዜ ተሞክሮ ነው። የእኔ እውነት የእናንተ ሊሆን አይችልም ፤ ያለማወላወል የእኔ ብቻ ነው። እውነትን ልንጋራው አንችልም።እኔ የምሰጣችሁ ግንዛቤ ብቻ ነው። ከዚያ በተረፈ እያንዳንዱ ሰው እውነትን ደጋግሞ በራሱ ማግኝት አለበት ። ስለሆነም ለመመራመር ፣ ለመጠየቅ፣ ለመሞከር ለመተግበር ትጉ።"
#ኦሾ
#ለፈገግታ ያህል ከሙጋቤ ንግግሮች አንዱን
============
የ CNN ጋዜጠኛ የዚምባቡዌ ፕሬዝደንት ሙጋቤን እየጠየቃቸው ነው፡-
ጋዜጠኛ፡- ሩሲያ ወደ ጠፈር ለመሄድ የመጀመሪያዋ አገር ነበረች፡፡ አሜሪካ ደግሞ ጨረቃ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በማረፍ ታሪክ አስመዝግባለች፡፡ አፍሪካስ ምን ዓይነት ታሪክ በመስራት አለምን ታስደንቅ ይሆናል ብለው ያስባሉ?
ሙጋቤ፡- እኛ ፀሃይ ላይ በማረፍ የመጀመሪያውን ታሪክ እንሰራለን፡፡
ጋዜጠኛ፡- ግን ፀሃይ በጣም የሚያቃጥል ነገር ነው፡፡
ፀሃይ ላይ ማረፍ አይቻልም፡፡
ሙጋቤ፡- እኛ ጅል መሰልንህ እንዴ ፣ ሲመሽ ነው ወደ ፀሃይ የምንሄደው፡፡
============
የ CNN ጋዜጠኛ የዚምባቡዌ ፕሬዝደንት ሙጋቤን እየጠየቃቸው ነው፡-
ጋዜጠኛ፡- ሩሲያ ወደ ጠፈር ለመሄድ የመጀመሪያዋ አገር ነበረች፡፡ አሜሪካ ደግሞ ጨረቃ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በማረፍ ታሪክ አስመዝግባለች፡፡ አፍሪካስ ምን ዓይነት ታሪክ በመስራት አለምን ታስደንቅ ይሆናል ብለው ያስባሉ?
ሙጋቤ፡- እኛ ፀሃይ ላይ በማረፍ የመጀመሪያውን ታሪክ እንሰራለን፡፡
ጋዜጠኛ፡- ግን ፀሃይ በጣም የሚያቃጥል ነገር ነው፡፡
ፀሃይ ላይ ማረፍ አይቻልም፡፡
ሙጋቤ፡- እኛ ጅል መሰልንህ እንዴ ፣ ሲመሽ ነው ወደ ፀሃይ የምንሄደው፡፡
ሞሀንዳስ ካራምቻንድ ጋንዲ (ማህተመ ጋንዲ) የሚከተሉትን ተግባራት በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ሀጢያቶች (sins against humanity) ናቸው ብሎ ያምናል ።
1. Wealth without work -
ያለሥራ የተገኘ ሀብት
2. Enjoyment without work conscience -ሕሊና የማይቀበለው ደስታ
3.knowledge without character -
ምግባር ያልታከለበት እውቀት
4.Business without Morality -
ግብረገብነት የጎደለው ንግድ
5.science without Humanity -
ሰብአዊነት የሌለበት ሳይንስ
6.Religion without compassion
ሀይማኖት ያለ ከፍተኛ ርህራሔ
7.Politics without principle
- መርህ የሌለው ፖለቲካ
8.Rights with out Responsibility
ሀላፊነት ያልታከለበት መብት
9.Power without Accountability -
ተጠያቂነት የሌለበት ሥልጣን
10.Development Without Sustainability -ቀጣይነት የሌለው ልማት
1. Wealth without work -
ያለሥራ የተገኘ ሀብት
2. Enjoyment without work conscience -ሕሊና የማይቀበለው ደስታ
3.knowledge without character -
ምግባር ያልታከለበት እውቀት
4.Business without Morality -
ግብረገብነት የጎደለው ንግድ
5.science without Humanity -
ሰብአዊነት የሌለበት ሳይንስ
6.Religion without compassion
ሀይማኖት ያለ ከፍተኛ ርህራሔ
7.Politics without principle
- መርህ የሌለው ፖለቲካ
8.Rights with out Responsibility
ሀላፊነት ያልታከለበት መብት
9.Power without Accountability -
ተጠያቂነት የሌለበት ሥልጣን
10.Development Without Sustainability -ቀጣይነት የሌለው ልማት
የሌለህን ነገር ብቻ ካሰብክ ያለህንም ታጣዋለህ፡፡ ያለህን ነገር ካሰብክ ግን የሌለህንም ታገኘዋለህ፡፡
#ዲ/ን ዳንኤል ክብረት)
ሰውዬው በሚስቱ ሞያ ይማረራል፡፡ ገና ወደ ቤቱ ለመምጣት ሲያስብ የሚበላው እንጀራና ወጥ ትዝ ሲለው ሐሞቱ ፍስስ ይላል፡፡ «እንግዲህ ለዚያ ሊጥ ልሂድለት» ብሎ ይመጣል፡፡ ይህ ነገር ሰለቸውና ከሚስቱ ጋር ተፋታ፡፡ ወደ ጓደኛውም ቤት ሄደ፡፡ ጓደኛው አልጋ አንጥፎ ተቀበለው፡፡
ማታ ራት ቀረበ፡፡ ምን የመሰለ ነጭ ጤፍ ላይ አልጫና ቀዩ ተጋድሞ ቀረበለት፡፡ በአንድ በኩል ቃሪያው፣ በአንድ በኩል ስልጆው፣ በአንድ በኩል ፍትፍቱ፣ በአንድ በኩል አተር ክኩ ተሰለፈ፡፡ «ወይ ሞያ እኔማ ኖርኩ አይባልምኮ» እያለ ያማርር ጀመር፡፡ «አንተማ ታድለህ» ይለዋል ጓደኛውን፡፡ «ይሁን እስኪ» ይላል ያኛውም፡፡ ጠላው ሲቀርብ ደግሞ እያደነቀ ጠጣ፡፡ «ከኖሩ ላይቀር እንዲህ ነው» ይል ጀመር፡፡ ያችንም ባለሞያ ሚስት በምስጋናና በአድናቆት አረሰረሳት፡፡
በልተው ሊያጠናቅቁ ሲሉ ጋባዡ ሊጠጣበት ያነሣው ብርጭቆ ተሰበረ፡፡ ደነገጠ፡፡ ሚስት ከጓዳ መጣች፡፡ «ምንድን ነው የተሰበረው?» አለች፡፡
«ያ የምትወጅው ብርጭቆ ተሰበረ፡፡» አላት ባልዋ በተስለመለመ ድምፅ፡፡ ተናደደችና አንዴ በጥፊ አላሰችው፡፡ ጓደኛው ደነገጠ፡፡ «እንዲህ ሰብረህ ሰብረህ የአባት የናቴን ስጦታ ጨረስከው፡፡ አንተ ምን ታደርግ ተንቀባርረህ ከነ ጓደኛህ ትልፋለህ» እያለች ቁም ስቅሉን ታሳየው ጀመር፡፡ ባልዬው ጠባይዋን ያውቃልና ዝም አለ፡፡ ያም ጓደኛው «ምን ለብርጭቆ ደግሞ ነገ ይገዛል፤ ዋናው ጤና ነው» አለ ነገር ያበረደ መስሎት፡፡ «አንተ ደግሞ አርፈህ ተቀመጥ፤ ሚስትህን እንደዚህ አማረሃት ይሆናል ይኼኔ፤ ቀላዋጭ» አለችና አቀመሰችው፡፡ ተፈታተነው ስሜቱ፡፡ ግን እንግድነቱ በልጦበት «ኧረ የኔዋስ እንዳንቺ» አለና ጀምሮ ተወው፡፡ ወደ ጓዳ ገባችና አንድ ፍልጥ ይዛ መጣች፡፡ እስኪ ጨርሰው አለቺው፡፡ ዓይኑ ተቁለጨለጨ፡፡ «እንዳንቺ የባሰባት አይደለችም» ሲላት ፍልጡን ይዛ መጣች፡፡
ይህንን ሲያይ ባልዬው «ቀስ ብለህ አምልጥ» አለው፡፡
በዚያ ሌሊት እየገሠገሠ የሚስቱ እናት ጋ ሄደ፡፡
እናቲቱም «ምነው ልጄ» አሉት
«እማማ፤ ከሌሊት ፍልጥ፣ የቀን ሊጥ ይሻለኛል ብዬ መጣሁ፡፡ አላቸው ይባላል፡፡
ወዳጄ ያለህን ካላሰብከው የባሰው ላይ ትወድቃለህ ያልኩ ለዚህ ነው፡፡
እስኪ ወዳጄ ያለህን ዕወቀው፤ አክብረው፤ አሟጠህ በሚገባ ተጠቀምበት፤ በዚያ ኑርበት፤ አጊጥበት፡፡ ከዚያ ሌላውን ለመያዝ ፈልግ፡፡ ባለህ የማትረካ ከሆንክ ግን ሩጫህ የተሻለ ነገር ፍለጋ ሳይሆን ሌላ ነገር ፍለጋ ብቻ ይሆናል፡፡
:
#ዲ/ን ዳንኤል ክብረት)
#ዲ/ን ዳንኤል ክብረት)
ሰውዬው በሚስቱ ሞያ ይማረራል፡፡ ገና ወደ ቤቱ ለመምጣት ሲያስብ የሚበላው እንጀራና ወጥ ትዝ ሲለው ሐሞቱ ፍስስ ይላል፡፡ «እንግዲህ ለዚያ ሊጥ ልሂድለት» ብሎ ይመጣል፡፡ ይህ ነገር ሰለቸውና ከሚስቱ ጋር ተፋታ፡፡ ወደ ጓደኛውም ቤት ሄደ፡፡ ጓደኛው አልጋ አንጥፎ ተቀበለው፡፡
ማታ ራት ቀረበ፡፡ ምን የመሰለ ነጭ ጤፍ ላይ አልጫና ቀዩ ተጋድሞ ቀረበለት፡፡ በአንድ በኩል ቃሪያው፣ በአንድ በኩል ስልጆው፣ በአንድ በኩል ፍትፍቱ፣ በአንድ በኩል አተር ክኩ ተሰለፈ፡፡ «ወይ ሞያ እኔማ ኖርኩ አይባልምኮ» እያለ ያማርር ጀመር፡፡ «አንተማ ታድለህ» ይለዋል ጓደኛውን፡፡ «ይሁን እስኪ» ይላል ያኛውም፡፡ ጠላው ሲቀርብ ደግሞ እያደነቀ ጠጣ፡፡ «ከኖሩ ላይቀር እንዲህ ነው» ይል ጀመር፡፡ ያችንም ባለሞያ ሚስት በምስጋናና በአድናቆት አረሰረሳት፡፡
በልተው ሊያጠናቅቁ ሲሉ ጋባዡ ሊጠጣበት ያነሣው ብርጭቆ ተሰበረ፡፡ ደነገጠ፡፡ ሚስት ከጓዳ መጣች፡፡ «ምንድን ነው የተሰበረው?» አለች፡፡
«ያ የምትወጅው ብርጭቆ ተሰበረ፡፡» አላት ባልዋ በተስለመለመ ድምፅ፡፡ ተናደደችና አንዴ በጥፊ አላሰችው፡፡ ጓደኛው ደነገጠ፡፡ «እንዲህ ሰብረህ ሰብረህ የአባት የናቴን ስጦታ ጨረስከው፡፡ አንተ ምን ታደርግ ተንቀባርረህ ከነ ጓደኛህ ትልፋለህ» እያለች ቁም ስቅሉን ታሳየው ጀመር፡፡ ባልዬው ጠባይዋን ያውቃልና ዝም አለ፡፡ ያም ጓደኛው «ምን ለብርጭቆ ደግሞ ነገ ይገዛል፤ ዋናው ጤና ነው» አለ ነገር ያበረደ መስሎት፡፡ «አንተ ደግሞ አርፈህ ተቀመጥ፤ ሚስትህን እንደዚህ አማረሃት ይሆናል ይኼኔ፤ ቀላዋጭ» አለችና አቀመሰችው፡፡ ተፈታተነው ስሜቱ፡፡ ግን እንግድነቱ በልጦበት «ኧረ የኔዋስ እንዳንቺ» አለና ጀምሮ ተወው፡፡ ወደ ጓዳ ገባችና አንድ ፍልጥ ይዛ መጣች፡፡ እስኪ ጨርሰው አለቺው፡፡ ዓይኑ ተቁለጨለጨ፡፡ «እንዳንቺ የባሰባት አይደለችም» ሲላት ፍልጡን ይዛ መጣች፡፡
ይህንን ሲያይ ባልዬው «ቀስ ብለህ አምልጥ» አለው፡፡
በዚያ ሌሊት እየገሠገሠ የሚስቱ እናት ጋ ሄደ፡፡
እናቲቱም «ምነው ልጄ» አሉት
«እማማ፤ ከሌሊት ፍልጥ፣ የቀን ሊጥ ይሻለኛል ብዬ መጣሁ፡፡ አላቸው ይባላል፡፡
ወዳጄ ያለህን ካላሰብከው የባሰው ላይ ትወድቃለህ ያልኩ ለዚህ ነው፡፡
እስኪ ወዳጄ ያለህን ዕወቀው፤ አክብረው፤ አሟጠህ በሚገባ ተጠቀምበት፤ በዚያ ኑርበት፤ አጊጥበት፡፡ ከዚያ ሌላውን ለመያዝ ፈልግ፡፡ ባለህ የማትረካ ከሆንክ ግን ሩጫህ የተሻለ ነገር ፍለጋ ሳይሆን ሌላ ነገር ፍለጋ ብቻ ይሆናል፡፡
:
#ዲ/ን ዳንኤል ክብረት)
የስብሃት ለአብ ትውስታዎች!!
* * *
"ሠይጣን ወደ ኢትዮጵያ ቢመጣ ስራ የለውም ምክንያቱም የሰው ልጅ እሱ የሚሰራውን ሥራ ቀድሞ ሠርቶ ጨርሶቷል።ምን ሊሰራ ይመጣል?"የሚል ሀሳብ ያዘለ ጽሑፍ ጋዜጣ ላይ ጻፍኩ።
ታድያ ጹሑፉን ያነበቡ ጓደኞቼ...
"ጋሽ ስብሐት ህዝቡ በፅሑፉ ቅር ተሰኝቷል÷ የሰው ልጅ ለመልካም ሥራ እንዲነሳሳ በተቃራኒው ብትጽፈውስ?" አሉኝ።
በሳምንቱ...
"መልዓክ ወደ ወደ ኢትዮጵያ ቢመጣ ቦታ የለውም÷ ምክንያቱም የሰው ልጅ የሱን ተግባር ቀድሞ ሠርቶ ጨርሶቷል።ምን ሊሰራ ይመጣል?"
በማለት ጻፍኩ::
ነገር ግን ይሄ የባሰ የቁጣ ማዕበል አስነሳ!"
ሲል ፅፏል፡፡
* * *
#እንዲህ ነን እኛ!!
* * *
"ሠይጣን ወደ ኢትዮጵያ ቢመጣ ስራ የለውም ምክንያቱም የሰው ልጅ እሱ የሚሰራውን ሥራ ቀድሞ ሠርቶ ጨርሶቷል።ምን ሊሰራ ይመጣል?"የሚል ሀሳብ ያዘለ ጽሑፍ ጋዜጣ ላይ ጻፍኩ።
ታድያ ጹሑፉን ያነበቡ ጓደኞቼ...
"ጋሽ ስብሐት ህዝቡ በፅሑፉ ቅር ተሰኝቷል÷ የሰው ልጅ ለመልካም ሥራ እንዲነሳሳ በተቃራኒው ብትጽፈውስ?" አሉኝ።
በሳምንቱ...
"መልዓክ ወደ ወደ ኢትዮጵያ ቢመጣ ቦታ የለውም÷ ምክንያቱም የሰው ልጅ የሱን ተግባር ቀድሞ ሠርቶ ጨርሶቷል።ምን ሊሰራ ይመጣል?"
በማለት ጻፍኩ::
ነገር ግን ይሄ የባሰ የቁጣ ማዕበል አስነሳ!"
ሲል ፅፏል፡፡
* * *
#እንዲህ ነን እኛ!!
አንድ ሀብታም ሰው ዘመናዊ መኪናውን አቁሞ ለጉዳዩ ገባ ይላል ጉዳዩን ጨርሶ ወደ መኪናው ሲመለስ የአንዱ ጎማው 4 ብሎኖች ተፈተው ተወስዶበት ያያል፡፡ ይህኔ ይበሳጭ እና አከባቢው ላይ ዞር ዞር ብሎ ብሎን ፈልጎ ያጣል፡፡
ያኔ መኪናውን ተደግፎ በጭንቀት ቆዝሞ ሳለ አከባቢው ላይ ያለ አንድ እብድ ነገሩን ተከታትሎ ኖራልና "ምን ሆነህ ነው?" ይለዋል፡፡ሰውየውም በንቀት አይን አየት እያደረገው "የጎማዬ ብሎኖች ተፈተው ተወስዶብኝ ነው እንዳልገዛ አከባቢው ላይ የለም" ይለዋል በብስጭት ስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡
ይህኔ እብዱ "ነው እንዴ? ታዲያ ለምን ከ3 ጎማዎች አንድ አንድ ብሎን ፈተህ አራተኛውን ጎማ አታስርም" አለው፡፡
ሰውየውም በመገረም ሀሳቡ በጣም አስደሰተውና አንዳለውም አደረገ፡፡
"ቆይ አንተ እብድ አይደለህ እንዴ! አንዴት ይህ ሀሳብ ሊመጣልህ ቻለ?" ብሎ ጠየቀው፡፡
እብዱም ቀበል አድርጎ "ታዲያ እኔ እብድ ነኝ እንጂ ደደብ አይደለሁም" ብሎ ይመልስለታል፡፡
"ዝቅ በል፤ ዝቅ ስትል ከፍ ትላለህ፤ ተናነስ፤ ራስህን አትቆልል፤ ሁሌም እኔ አዋቂነኝ አትበል"
"ዲ/ን ዳንኤል ክብረት"
ያኔ መኪናውን ተደግፎ በጭንቀት ቆዝሞ ሳለ አከባቢው ላይ ያለ አንድ እብድ ነገሩን ተከታትሎ ኖራልና "ምን ሆነህ ነው?" ይለዋል፡፡ሰውየውም በንቀት አይን አየት እያደረገው "የጎማዬ ብሎኖች ተፈተው ተወስዶብኝ ነው እንዳልገዛ አከባቢው ላይ የለም" ይለዋል በብስጭት ስሜት ውስጥ ሆኖ፡፡
ይህኔ እብዱ "ነው እንዴ? ታዲያ ለምን ከ3 ጎማዎች አንድ አንድ ብሎን ፈተህ አራተኛውን ጎማ አታስርም" አለው፡፡
ሰውየውም በመገረም ሀሳቡ በጣም አስደሰተውና አንዳለውም አደረገ፡፡
"ቆይ አንተ እብድ አይደለህ እንዴ! አንዴት ይህ ሀሳብ ሊመጣልህ ቻለ?" ብሎ ጠየቀው፡፡
እብዱም ቀበል አድርጎ "ታዲያ እኔ እብድ ነኝ እንጂ ደደብ አይደለሁም" ብሎ ይመልስለታል፡፡
"ዝቅ በል፤ ዝቅ ስትል ከፍ ትላለህ፤ ተናነስ፤ ራስህን አትቆልል፤ ሁሌም እኔ አዋቂነኝ አትበል"
"ዲ/ን ዳንኤል ክብረት"
ሁሉንም ልምዶች እቃወማለሁ!!!
እኔ ሁሉንም ልምዶች እቃወማለሁ። ጥሩና መጥፎ ብየ አልከፋፍላቸውም። ምክንያቱም ጥሩም ሆነ መጥፎ የሚባል ልምድ ስለሌኝ ነው። ልምዶች ሁሉ ጎጂ ናቸው። ምክንያቱም ልማድ ማለት አንድ ያለንቃት የምናደርገው ተደጋጋሚ የሆነ ነገር በህይወታችን ላይ እእጅግ ወሳኝና የበላይ ሆኖ እየተቆጣጠረን ሲመጣ የሚፈጠር ሁኔታ ማለት ነው። ያኔ አንተ በህይወትህ ላይ የበላይነትህ ያበቃለታል። ለነገሮች ያለህ ምላሽ ከንቃት የመነጨ ሳይሆን ካለፈው ግዜ ከተማርካቸው መዋቅራዊ ከሆኑ ተግባሮች ነው።
ኦሾ/osho
እኔ ሁሉንም ልምዶች እቃወማለሁ። ጥሩና መጥፎ ብየ አልከፋፍላቸውም። ምክንያቱም ጥሩም ሆነ መጥፎ የሚባል ልምድ ስለሌኝ ነው። ልምዶች ሁሉ ጎጂ ናቸው። ምክንያቱም ልማድ ማለት አንድ ያለንቃት የምናደርገው ተደጋጋሚ የሆነ ነገር በህይወታችን ላይ እእጅግ ወሳኝና የበላይ ሆኖ እየተቆጣጠረን ሲመጣ የሚፈጠር ሁኔታ ማለት ነው። ያኔ አንተ በህይወትህ ላይ የበላይነትህ ያበቃለታል። ለነገሮች ያለህ ምላሽ ከንቃት የመነጨ ሳይሆን ካለፈው ግዜ ከተማርካቸው መዋቅራዊ ከሆኑ ተግባሮች ነው።
ኦሾ/osho
"ለሕይወት የከበሬታ ስሜት ካልፈጠረ እና ክብር ካልሰጠ በስተቀረ ፣ ማንም የሰው ልጅ የህይወት መሠረታዊ መብትን የመጎናጸፍ አላማን አይረዳውም።"
Osho/ኦሾ
Osho/ኦሾ