Federal Ethics And Anti- Corruption Commission
9.89K subscribers
10.4K photos
246 videos
32 files
3.06K links
Download Telegram
በመዲናዋ ሊመዘበር የነበረን 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ማዳን ተቻለ

*******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በአዲስ አበባ በህገ ወጥ መንገድ ሊመዘበር የነበረ 1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ሃብት ማዳን መቻሉን የከተማዋ ፍትህ ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ም/ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ደጀኔ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷በመዲናዋ ብልሹ አሰራሮችን ከመቅረፍ አንጻር በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡

በተለይም በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የሚስተዋሉ ውስንነቶችን ለማስተካከል በትብብር መሠራቱን አንስተዋል።

ባለፉት አምስት ወራትም በ3 ሺህ 933 ጉዳዮች ክሶች ቀርበው የፍርድ ቤት ክርክሮች እንደተደረጉ ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ውስጥም 1ሺህ 314 መዝገቦችን በመከራከር በፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኙ መደረጉን ነው ያስረዱት።

ቢሮው በ1 ሺህ 266 መዝገቦች ማሸነፋን ጠቁመው ÷ በዚህም መንግስት ሊያጣው የነበረ 1ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ማዳን መቻሉን ገልጸዋል፡፡

በመዲናዋ የሚስተዋሉ ሕገ ወጥ ተግባራትን ከስር መሠረታቸው ለማድረቅም ነዋሪዎች ጥቆማ በመስጠት የበኩላቸውን እንዲወጡ መጠየቃቸውን ኤፍኤምሲ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ምክር ቤቱ በብልሹ አሰራር ላይ ተገኝተዋል ያላቸውን ሁለት የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞችን አሰናበተ

*******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 6/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት 6ኛ ዙር ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 15ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል፡፡

የፌደራል ዳኞች አስተዳዳር ጉባዔ ሁለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ላይ ያቀረበውን የስንበት ውሳኔ አስመልክቶ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መመርመሩን ኢፕድ ዘግቧል፡፡

በዚህም መሰረት አዱኛ ነጋሳ እና አክሊሉ ዘሪሁን የተባሉ ሁለት የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች በሙስና እና በብልሹ አሰራር ላይ በመገኘታቸውና ሁለቱ ዳኞች በሥራ ላይ በነበሩ ጊዜ ኃላፊነታቸውን ያላግባባ በመጠቀማቸው ምክር ቤቱ የቀረበውን የስንብት ደብዳቤ አጽድቋል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የዩኬ የግምጃ ቤት ሚኒስትር በባንግላዴሽ በቀረበባቸው የሙስና ክስ ከሥልጣናቸው ለቀቁ

***********************

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 7/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የዩናይትድ ኪንግደም የግምጃ ቤት ሚኒስትር ቱሊፕ ሲዲቅ በባንግላዴሽ እየተካሄደባቸው ካለው የሙስና ምርመራ ጋር በተያያዘ በደረሰባቸው ጫና ከሥልጣናቸው ለቀቁ።

ሚኒስትሯ ባለፈው ዓመት ከሥልጣናቸው ከተወገዱት አክስታቸው ጋር ባላቸው ግንኙነት ላይ ጥያቄ ከተነሳባቸው በኋላ ጉዳዩን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ሲር ላውሪ ማንጉሰ ጋር ወስደውት ነበር።

ሰር ላውሪም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ምንም አይነት ትክክለኛ ማስረጃ እንዳላገኙ፤ ነገርግን ሚኒስትሯ ከአክስታቸው ጋር ባላቸው ግንኙነት ሳቢያ የስም ማጥፋት አደጋ ሊገጥማቸው እንደሚችል በማሰብ ጥንቃቄ አለማድረጋቸው የሚያፀፅት ነው ብለዋል።

ሲዲቅ በበኩላቸው በኃላፊነታቸው ላይ መቆየት ለመንግሥታቸው ጥሩ ሊሆን እንደማይችል ገልጸው፤ ነገር ግን ምንም የሰሩት ወንጀል እንደሌለ ተናግረዋል።

የሲዲቅ ከሥራ መልቀቅ ከመገለጹ አስቀድሞ በባንግላዴሽ የሙስና ምርመራ ከሚካሄድባቸው ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ስማቸው ተካቷል።

የወግ አጥባቂው መሪ ኬሚ ባደኖች በኤክስ ገጻቸው ባጋሩት ጽሑፍ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሚኒስትሯን ለመከላከል እና ለመጠበቅ ዘግይተዋል ሲሉ ወቅሰዋል።

መሪው ጨምረውም አሁንም ባንግላዲሽ በቱሊፕ ላይ የወንጀል ክስ ሲመሰርት ሚኒስትሯ ከሥራ በመልቀቃቸው ሃዘናቸውን ከመግለጽ ባሻገር ያደረጉት ነገር የለም ሲሉ ኮንነዋል።

"ከደካማ ጠቅላይ ሚኒስትር ደካማ አስተዳዳር" ሲሉም ተችተዋል።

ሰር ኬር የሲዲቅን የሥራ መልቀቂያ መቀበላቸውን በገለጹበት ደብዳቤ ለሳዲቅ በራቸው ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ገልጸዋል።

በዩኬ የፋይናንስ ገበያ ያለውን ሙስና መከላከልን ጨምሮ ለግምጃ ቤቱ የኢኮኖሚ ኃላፊነት ሚና የነበራቸው ሲዲቅ፣ ባለፈው ወር ቤተሰባቸው በባንግላዴሽ በተሰራ የመሰረተ ልማት ግንባታ ጋር በተያያዘ 3.9 ቢሊየን ፓውንድ ገንዘብ ዘርፈዋል በሚል ስማቸው ተጠቅሶ ነበር።

የቀድሞው የባንግላዴሽ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት አክስታቸው ሼይክህ ሃሲና የአዋሚ ሊግ ኃላፊ የነበሩ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት ከሥልጣን ከተወገዱ በኋላ በስደት ነው ያሉት።

ቢቢሲ የተመለከተው የፍርድ ቤት ሰነድ ሃጃጂ፣ እአአ በ2013 በባንግላዴሽ አዲስ የኒውክሌር ኃይል ጋር በተያያዘ አክስቷ ከሩሲያ ጋር ለማስማማት ሲዲቅ ረድተዋል ሲሉ ከሰዋል።

የኃይል ማበልጸጊያውን የስምምነት ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙ ሲሆን፣ ከሩሲያው ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ፎቶ ተነስተዋል።

ሆኖም ሰር ላውሬ እና ሲዲቅ በወቅቱ የነበረውን አውድ ማህበራዊ ግንኙነትና ጉብኝት እንደነበር አስረድተዋል።

ሰር ላውሪ እንዳሉት ሲዲቅ በባንግላዴሽ እና በሩሲያ መንግሥታት መካከል በተካሄደው ውይይት ምንም ዓይነት ግንኙነት የላትም።

የባንግላዴሽ ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ሲዲቅ እናቷን ሬሂና ሲዲቅ ሃሲናን ሥልጣኗን በመጠቀም በጣም ወሳኝ በሆነ እና ዲፕሎማቲክ ቦታ መሬት ለማግኘት ተፅዕኖ ለማሳደር እናቷን ስትደግፍ ነበር ሲል ከሷል።

ከዚህም በተጨማሪ የባንግላዴሽ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩትን አክስታቸውን ለመርዳት ሥልጣናቸውን ተጠቅመዋል ብሏል።

የሲዲቅ ቃል አቀባይ በበኩላቸው በሚኒስትሯ ላይ ለቀረቡት ክሶች ምንም አይነት ማስረጃ አልቀረበም ብለዋል።

የሲዲቅን ከሥልጣን መልቀቅ ተከትሎም የሌበር የፓርላማ አባል ኢማ ሪይኖልድስ ለግምጃ ቤቱ አዲስ የኢኮኖሚ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ከአፍሪካ ህብረት ሂሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ለመመዝበር ሙከራ በማድረግ የተከሰሱት እነ ቀሲስ በላይ ጥፋተኛ ተባሉ

*******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 7/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ከአፍሪካ ህብረት ሂሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ለለመዝበር ሙከራ በማድረግ የሙስና ወንጀል የተከሰሱት እነ ቀሲስ በላይ ጥፋተኛ ተባሉ።

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በተከሰሱበት ድንጋጌ ስር የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፎባቸዋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

በዚህ መልኩ የቀረበው ክስ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።

ከዚህም በኋላ ተከሳኞቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ የአፍሪካ ህብረት ቅርጫፍ የባንክ ባለሙያዎችን አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።

ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በተከሰሱበት ድንጋጌ ስር እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን ተከሳሾቹ ባቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸውን ጠቅሷል።

በዚህም በዛሬው ቀጠሮ 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።

የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት ተመልክቶ የቅጣት ውሳኔ ለመወሰን ለጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም መቅጠሩን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል ።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የንብረት ማስመለስ አዋጁ ያለአግባብ ሀብት የማካበት እሳቤን ለማስቀረት ያግዛል - የህግ ምሁር

*******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 7/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የንብረት ማስመለስ አዋጁ ያለአግባብ ሀብት የማካበት እሳቤን ለማስቀረት እንደሚያግዝ የህግ ምሁሩ ገልጸዋል።

ኤኤምኤን የንብረት ማስመለስ አዋጁ አስፈላጊነት፣ አተገበባር እና በሚጠበቁ ውጤቶች ዙሪያ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቱ የህግ ምሁር እና ጠበቃ ከሆኑት አቶ ዘመድኩን መካሻ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡

የንብረት ማስመለስ አዋጁ ህጋዊነትን የሚያሰፍን እና በአቋራጭ የመክበር እሳቤን በማስቀረት ሰርቶ ማደግ እና ሀብት ማካበት እንደሚቻል የሚረዳ፣ ትውልድን ለመቅረጽ እንደሚያስችል የህግ ምሁሩ አቶ ዘመድኩን ተናግረዋል፡፡

ለሚያካብትው ሀብትም ህጋዊ አሰራርን የሚከተል ትውልድን በመቅረጽ በኩል ትልቅ ትርጉም ያለው ስለመሆኑ ምሁሩ አብራርተዋል፡፡

በተጨማሪም አዋጁ ከዚህ ቀደም የነበሩ ህጎች ይስተዋልባችው የነበሩ ክፍተቶችን የሚሞላ እንዲሁም አለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማስቻል ያለመ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

አዋጁ ተግባራዊ ሲሆን የመንግስትን የመፈፀምና ወንጀልን የመከላከል ምጣኔ ያሳድጋልም ብለዋል፡፡

እንዲሁም በህዝብ እና በሀገር ላይ ትልቅ ለውጥን የሚያመጣና በሀገር ኢኮኖሚ ላይም ሚናዉ የጎላ በመሆኑ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማዳበር አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል፡፡

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሰሞኑ ባካሄደው14ኛ መደበኛ ስብሰባው የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን በአብላጫ ድምጽ ማጽደቁ ይታወሳል፡፡

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በህገወጥ ድለላና የማጭበርበር ተግባር የተሰማሩ 126 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል - የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት

***

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 7/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በህገወጥ ድለላና የማጭበርበር ተግባር የተሰማሩ 126 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት አስታውቀዋል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት አገልግሎቱ የአሰራርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ማሻሻያ ማድረጉን ተከትሎ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን የኢ-ፓስፖርት ቡክሌቶች ተመርተው ወደ አገር ውስጥ እየገቡ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢ-ፓስፖርት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስፈልጉ የመሰረተልማትና ቴክኖሎጂ ስራዎች መጠናቀቃቸውንም ገልፀዋል።

በህገወጥ ድለላና የማጭበርበር ተግባር የተሰማሩ 126 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በሀሰተኛና የተጭበረበረ የጉዞ ሰነድ ለመገልገል የሞከሩ ከ 13 ሺህ በላይ ዜጎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።

ተገልጋዮች የቀጠሮ ቀናቸውን አክብረው አገልግሎት ማግኘት እንዳለባቸውና ተመሳስለው በተሰሩ ሶሻል ሚዲያና ዌብሳይቶች እንዳይታለሉ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ለባህር ዳር አካዳሚ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የሥነምግባር ግንባታ ስልጠና ተሰጠ

*******

(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ጥር 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በክልሉ የትውልድ ሥነምግባርን ለመገንባት በት/ቤቶች ተከታታይ የሥነምግባር ግንባታ ስራ እየተሰራ ነው።

የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ተማሪዎች በሥነምግባር ታንፀው ነገ እራሳቸውን፣ ቤተሰቦቻቸውንና ሀገራቸውን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል እንዲችሉ በየትኛውም የትም/ት ደረጃ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች የሥነምግባር ስልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጿል።

የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስልጠና ባለሙያ ወ/ሮ በላይነሽ አሰፋ በከተማው ለሚገኘው ለባህር ዳር አካዳሚ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ከ9ኛ- 10ኛ ክፍል ለተወጣጡ ተማሪዎች የሥነምግባር ግንባታ ስልጠና ሰጥተዋል።

ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!

#NCRS ሞባይል መተግበሪያ

#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details

#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319