ባለፉት 5 ወራት በሀሰተኛ የተጭበረበረ ደረሰኝ መንግስት ሊያጣ የነበረውን ከ345 ሚሊየን ብር በላይ ማዳን ተችሏል - የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በ2017 በጀት ዓመት 5 ወራት በሀሰተኛ ደረሰኝ ግብይት ተጭበርብሮ ያለ አግባብ ሊቀር የነበረ ከ345 ሚሊዮን ብር በላይ በማዳን የመንግስትን ጥቅም ማስጠበቅ መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የታክስ ኢንተለጀንስና ምርመራ ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ነጋሽ እንደገለፁት፣ ሀሰተኛ ደረሰኝ እንዲጣራ ከቀረቡት አጠቃላይ 16 ሺ 425 ደረሰኞች 2 ሺ 654 ሀሰተኛ ሆነው ተገኝተዋል።
ሀሰተኛ ደረሰኞቹ የያዙት 345 ሚሊየን 526 ሺህ 600 ብር በመሆኑ ይህንን ማዳን መቻሉን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ በዚህም ወጪና ያልተገባ ታክስ ያለ አግባብ እንዳይወራረድ መደረጉ ተገልጿል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በ2017 በጀት ዓመት 5 ወራት በሀሰተኛ ደረሰኝ ግብይት ተጭበርብሮ ያለ አግባብ ሊቀር የነበረ ከ345 ሚሊዮን ብር በላይ በማዳን የመንግስትን ጥቅም ማስጠበቅ መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የታክስ ኢንተለጀንስና ምርመራ ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ነጋሽ እንደገለፁት፣ ሀሰተኛ ደረሰኝ እንዲጣራ ከቀረቡት አጠቃላይ 16 ሺ 425 ደረሰኞች 2 ሺ 654 ሀሰተኛ ሆነው ተገኝተዋል።
ሀሰተኛ ደረሰኞቹ የያዙት 345 ሚሊየን 526 ሺህ 600 ብር በመሆኑ ይህንን ማዳን መቻሉን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ በዚህም ወጪና ያልተገባ ታክስ ያለ አግባብ እንዳይወራረድ መደረጉ ተገልጿል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የሙያ ሥነ-ምግባር የተላበሰ ሰራተኛን መፍጠር የተቋም ሀብት ከማዳን ባለፈ የመፈፀም አቅም እንደሚያሳድግ ተገለፀ
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ከአዲስ አበባ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር የሥነምግባር ምንነት፣ ሙያዊ ሥነምግባር፣ የሙስና ፅንሰ ሀሳብና መከላከያ ስልቶች ላይ ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሠራተኞች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና መጠናቀቁ ተገልጿል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ እንደገለፁት የሙያ ሥነምግባር መበላሸት ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር የሚከፍት፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚያባብስና ሰራተኞች ባልተገባ መንገድ ኃላፊነታቸውን እንዳይወጡ የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ጀንበሩ የሙያ ሥነ-ምግባር የተላበሰ ሰራተኛን መፍጠር የተቋሙን ሀብት ከብክነት ለመጠበቅ እና የመፈፀም አቅምን ለማሳደግ አዎንታዊ አስተዋፆኦ የሚያበረክት መሆኑን በመድረኩ ላይ አብረርተዋል፡፡
የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አባተ ገብረአምላክ በበኩላቸው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከሚያንቀሳቅሰው ሰፊ ሀብት አንፃር ለሙስና እና ብልሹ አሰራር የሚኖረውን ተጋላጭነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም የሠራተኛውን ግንዛቤ የሚያሰፉ መሰል ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ፋይዳው የጉላ መሆኑን ጠቁመው፥ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሀብት ሳይባክን ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ማድረግ የሁሉም የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።
ይህን ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡ መልዕክታቸውን ማስተላለፋቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ስልጠናው በሦስት ዙር የተሰጠ ሲሆን 300 የሚሆኑ የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ከአዲስ አበባ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር የሥነምግባር ምንነት፣ ሙያዊ ሥነምግባር፣ የሙስና ፅንሰ ሀሳብና መከላከያ ስልቶች ላይ ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሠራተኞች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና መጠናቀቁ ተገልጿል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ዳይሬክተር አቶ ጀንበሩ ኢርኮ እንደገለፁት የሙያ ሥነምግባር መበላሸት ለሙስና እና ብልሹ አሰራር በር የሚከፍት፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚያባብስና ሰራተኞች ባልተገባ መንገድ ኃላፊነታቸውን እንዳይወጡ የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡
አቶ ጀንበሩ የሙያ ሥነ-ምግባር የተላበሰ ሰራተኛን መፍጠር የተቋሙን ሀብት ከብክነት ለመጠበቅ እና የመፈፀም አቅምን ለማሳደግ አዎንታዊ አስተዋፆኦ የሚያበረክት መሆኑን በመድረኩ ላይ አብረርተዋል፡፡
የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አባተ ገብረአምላክ በበኩላቸው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከሚያንቀሳቅሰው ሰፊ ሀብት አንፃር ለሙስና እና ብልሹ አሰራር የሚኖረውን ተጋላጭነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ስልጠናው መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም የሠራተኛውን ግንዛቤ የሚያሰፉ መሰል ስልጠናዎች መዘጋጀታቸው ፋይዳው የጉላ መሆኑን ጠቁመው፥ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሀብት ሳይባክን ለታለመለት ዓላማ ብቻ እንዲውል ማድረግ የሁሉም የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ኃላፊነት መሆኑን ተናግረዋል።
ይህን ኃላፊነታቸውን በብቃት እንዲወጡ መልዕክታቸውን ማስተላለፋቸውን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ስልጠናው በሦስት ዙር የተሰጠ ሲሆን 300 የሚሆኑ የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ሂደት ላይ ለካፋ ዞን ማዕከል የመንግስት ሠራተኞች ስልጠና ሰጠ
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከአስር ቀን በኋላ ተግባራዊ የሚደረገውን የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ሂደት አስመልክቶ ከካፋ ዞን ማዕከል ለተወጣጡ መንግስት ሠራተኞች በቦንጋ ከተማ የግንዛቤ ስልጠና ሰጥቷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳግም ዳንኤል ሃብት ማሳወቅና ማስመዝገብ በመንግስት ተቋማት፣ በመንግስት የልማት ድርጅቶችና በህዝባዊ ድርጅቶች መካከል መልካም ሥነምግባርና እሴቶች እንዲጎለብቱ ከማድረግ ባሻገር ተቋማዊ አቅምን በመገንባት የመንግስትና የህዝብ ሥራዎች አሠራር ግልፀኝነት እንዲኖራቸው ያደርጋል ብለዋል።
የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዓለማና ተግባር የተሿሚዎችንና ሕጉ ግዴታ የጣለባቸዉን የመንግሥት ሠራተኞች እና የመንግስት ልማት ድርጅት ሠራተኞች ሀብትና የገቢ ምንጫቸዉን አሳወቀው እንዲያስመዘግቡ መሆኑን ተናግረዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መዘጋጀቱ ትክክለኛ መረጃ ለዜጎች በማድረስ ሃብታቸውን እንዲያሳውቁና እንዲያስመዘግቡ ለማስቻል እንደሆነም ገልጸዋል።
በየተቋማት የሚገኙ ሠራተኞች በሥነምግባርና በመልካም እሴት ተገንብተው ተገልጋዮቻቸውን በአገልግሎቶቻቸው ማርካት እንዲችሉ ያስችላል ብለዋል።
እንዲሁም የተቋማት አመራርና ሠራተኞች በሥራ ላይ ሥነ-ምግባር የታነጹ ሆነውና በቴክኖሎጂ ታግዘው በፍጥነትና በጥራት አገልግሎት እንዲሰጡ በሥራ ላይ ሥነ-ምግባር መቃኘት እንደሚገባቸውም ተጠቅሷል።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም የሥራ ሥነምግባር እና የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ አፈፃፀም መመሪያ ሰነዶች የቀረቡ ሲሆን፥ በቀረቡ ሰነዶች ላይ በኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ታደሰ አይበራ ማጠቃለያና የሥራ መመሪያ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
በመጨረሻም የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ቅጽ ከዞኑ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን ጋር ርክክብ የተደረገ ሲሆን፥ በቀጣይ 10 ቀናት ውስጥ የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ተደርጎ ይጠናቀቃልም ተብሏል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
****
(የፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከአስር ቀን በኋላ ተግባራዊ የሚደረገውን የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ሂደት አስመልክቶ ከካፋ ዞን ማዕከል ለተወጣጡ መንግስት ሠራተኞች በቦንጋ ከተማ የግንዛቤ ስልጠና ሰጥቷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳግም ዳንኤል ሃብት ማሳወቅና ማስመዝገብ በመንግስት ተቋማት፣ በመንግስት የልማት ድርጅቶችና በህዝባዊ ድርጅቶች መካከል መልካም ሥነምግባርና እሴቶች እንዲጎለብቱ ከማድረግ ባሻገር ተቋማዊ አቅምን በመገንባት የመንግስትና የህዝብ ሥራዎች አሠራር ግልፀኝነት እንዲኖራቸው ያደርጋል ብለዋል።
የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዓለማና ተግባር የተሿሚዎችንና ሕጉ ግዴታ የጣለባቸዉን የመንግሥት ሠራተኞች እና የመንግስት ልማት ድርጅት ሠራተኞች ሀብትና የገቢ ምንጫቸዉን አሳወቀው እንዲያስመዘግቡ መሆኑን ተናግረዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መዘጋጀቱ ትክክለኛ መረጃ ለዜጎች በማድረስ ሃብታቸውን እንዲያሳውቁና እንዲያስመዘግቡ ለማስቻል እንደሆነም ገልጸዋል።
በየተቋማት የሚገኙ ሠራተኞች በሥነምግባርና በመልካም እሴት ተገንብተው ተገልጋዮቻቸውን በአገልግሎቶቻቸው ማርካት እንዲችሉ ያስችላል ብለዋል።
እንዲሁም የተቋማት አመራርና ሠራተኞች በሥራ ላይ ሥነ-ምግባር የታነጹ ሆነውና በቴክኖሎጂ ታግዘው በፍጥነትና በጥራት አገልግሎት እንዲሰጡ በሥራ ላይ ሥነ-ምግባር መቃኘት እንደሚገባቸውም ተጠቅሷል።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም የሥራ ሥነምግባር እና የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ አፈፃፀም መመሪያ ሰነዶች የቀረቡ ሲሆን፥ በቀረቡ ሰነዶች ላይ በኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ ታደሰ አይበራ ማጠቃለያና የሥራ መመሪያ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
በመጨረሻም የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ቅጽ ከዞኑ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን ጋር ርክክብ የተደረገ ሲሆን፥ በቀጣይ 10 ቀናት ውስጥ የሃብት ማሳወቅና ምዝገባ ተደርጎ ይጠናቀቃልም ተብሏል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319