መንግስት በ2017 በጀት ዓመት በመልካም አስተዳደር እና አገልግሎት አሰጣጥ በሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች ላይ ትኩረት አደርጎ እየሰራ ይገኛል - ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር)
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ዘርፍ አመራሮች "ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር የሥነ- ምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው መድረክ የተገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) መንግስት በ2017 በጀት ዓመት በመልካም አስተዳደር እና አገልግሎት አሰጣጥ በሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች ላይ ትኩረት አደርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
መንግስት በፌደራል የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጥናት ማድረጉን ጠቁመው፥ ከተቋማቱ መካከል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ዘርፍ አንዱ ነው ብለዋል። በጥናቱም በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ዘርፍ የብልሹ አሰራር አዝማሚያዎች መመላከቱን ተናግረዋል።
ሚኒሰትሩ አክለውም ለዘርፋ ይህን መሰል ስልጠና በየጊዜው በመስጠት የአመራሩንና የሠራተኛውን ብሎም የተገልጋዩን ባህሪ መቀየር ያስፈልጋል ብለዋል። እንዲሁም ሰዎችን የሚያግዝ የዲጂታል የአሰራር ስርዓት መዘርጋት እንደሚያስፈልግም ገልፀዋል።
በዘርፋ ውስጥ የሚፈፀም ብልሹ አሰራር የሰዎችን ህይወትን እንደሚቀጥፍ ጠቅሰው፥ ለአብነት የመንጃ ፍቃድ አሰጣጥ ተጠቃሽ መሆኑን አመላክተዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም በሙስና እና ብልሹ አሰራር ላይ ተዘፍቀው የሚገኙ ጥፋተኛ ግለሰቦችን ጠንከር ያለ ተጠያቂ የሚያደርግ ህግ እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ አንዳንድ አገሮች ሙሰኞችን በህይወት እስከመቅጣት ይደርሳሉ ብለዋል።
የፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው በዘርፋ የሚፈፀሙ የብልሹ አሰራር ችግሮች ከሰው ህይወት ጋር የተያያዘ መሆኑን ገልፀው፥ ስለሆነም በሥነምግባር አርዓያ የሆነ አመራርና ሠራተኛ ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይ ከመንጃ ፍቃድ አሰጣጥና ከመኪና የቴክኒክ ምርመራ ጋር በተያያዘ የሚፈፀሙ ብልሹ አሰራሮች የሠውን ህይወት እንደሚቀጥፍ ገልፀው፥ ችግሩን ለመፍታት በየጊዜው ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ስልጠናው ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ዘርፍ አመራሮች "ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር የሥነ- ምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው መድረክ የተገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) መንግስት በ2017 በጀት ዓመት በመልካም አስተዳደር እና አገልግሎት አሰጣጥ በሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች ላይ ትኩረት አደርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
መንግስት በፌደራል የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ጥናት ማድረጉን ጠቁመው፥ ከተቋማቱ መካከል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ዘርፍ አንዱ ነው ብለዋል። በጥናቱም በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ዘርፍ የብልሹ አሰራር አዝማሚያዎች መመላከቱን ተናግረዋል።
ሚኒሰትሩ አክለውም ለዘርፋ ይህን መሰል ስልጠና በየጊዜው በመስጠት የአመራሩንና የሠራተኛውን ብሎም የተገልጋዩን ባህሪ መቀየር ያስፈልጋል ብለዋል። እንዲሁም ሰዎችን የሚያግዝ የዲጂታል የአሰራር ስርዓት መዘርጋት እንደሚያስፈልግም ገልፀዋል።
በዘርፋ ውስጥ የሚፈፀም ብልሹ አሰራር የሰዎችን ህይወትን እንደሚቀጥፍ ጠቅሰው፥ ለአብነት የመንጃ ፍቃድ አሰጣጥ ተጠቃሽ መሆኑን አመላክተዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም በሙስና እና ብልሹ አሰራር ላይ ተዘፍቀው የሚገኙ ጥፋተኛ ግለሰቦችን ጠንከር ያለ ተጠያቂ የሚያደርግ ህግ እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ አንዳንድ አገሮች ሙሰኞችን በህይወት እስከመቅጣት ይደርሳሉ ብለዋል።
የፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው በዘርፋ የሚፈፀሙ የብልሹ አሰራር ችግሮች ከሰው ህይወት ጋር የተያያዘ መሆኑን ገልፀው፥ ስለሆነም በሥነምግባር አርዓያ የሆነ አመራርና ሠራተኛ ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይ ከመንጃ ፍቃድ አሰጣጥና ከመኪና የቴክኒክ ምርመራ ጋር በተያያዘ የሚፈፀሙ ብልሹ አሰራሮች የሠውን ህይወት እንደሚቀጥፍ ገልፀው፥ ችግሩን ለመፍታት በየጊዜው ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ስልጠናው ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
አመራሩ በመልካም ሥነምግባር አርዓያ በመሆንና ከብልሹ አሰራር በመራቅ የተሰጠውን ኃላፊነት መወጣት አለበት - አብርሃም በላይ (ዶ/ር)
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም ቢሾፍቱ) ለመስኖና ቆላማ አካባቢ ዘርፍ አመራሮች "ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር የሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው መድረክ የተገኙት የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚንስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) አመራሩ በመልካም ሥነምግባር አርዓያ በመሆንና ከብልሹ አሰራር በመራቅ የተሰጠውን ኃላፊነት መወጣት አለበት ብለዋል።
ሚንስትሩ አክለውም ስልጠናው ከሥነምግባር እና ከሞራል አንፃር ራሳችን የምናይበት በመሆኑ በትኩረት መከታተል እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ኮሚሽኑ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ሥራን የማስተባበር ሚናን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልፀው፥ በየዘርፉ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮችን የመከላከል ኃላፊነት የተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች መሆኑን ጠቁመዋል።
መንግስት ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ አመራሩ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት ገልፀዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም የመስኖና ቆላማ አካባቢ ዘርፍ በርካታ ፕሮጀክቶችን የሚያንቀሳቅስ ግዙፍ ተቋም መሆኑን ገልፀው፥ ተቋሙ በብልሹ አሰራር እንዳይዘፈቅ በየደረጃው ያላችሁ አመራሮች የተሰጣችሁን ኃላፊነት መወጣት ይኖርባችኋል ብለዋል።
ስልጠናው የሙስና ምንነት፣ ባህሪያትና አይነቶች ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በዘርፋ በተደረገ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነት ዳሰሳ ጥናት መነሻነት ከተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተወጣጡ ምሁራን በተዘጋጀ የማሰልጠኛ ሞጁል የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል።
ስልጠናው ለመስኖና ቆላማ አካባቢ ዘርፍ አመራሮች እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም ቢሾፍቱ) ለመስኖና ቆላማ አካባቢ ዘርፍ አመራሮች "ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር የሥነ-ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው መድረክ የተገኙት የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ሚንስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) አመራሩ በመልካም ሥነምግባር አርዓያ በመሆንና ከብልሹ አሰራር በመራቅ የተሰጠውን ኃላፊነት መወጣት አለበት ብለዋል።
ሚንስትሩ አክለውም ስልጠናው ከሥነምግባር እና ከሞራል አንፃር ራሳችን የምናይበት በመሆኑ በትኩረት መከታተል እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ኮሚሽኑ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሥነምግባር ግንባታ እና ሙስና መከላከል ሥራን የማስተባበር ሚናን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልፀው፥ በየዘርፉ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮችን የመከላከል ኃላፊነት የተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች መሆኑን ጠቁመዋል።
መንግስት ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ አመራሩ በፀረ-ሙስና ትግል ላይ በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት ገልፀዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም የመስኖና ቆላማ አካባቢ ዘርፍ በርካታ ፕሮጀክቶችን የሚያንቀሳቅስ ግዙፍ ተቋም መሆኑን ገልፀው፥ ተቋሙ በብልሹ አሰራር እንዳይዘፈቅ በየደረጃው ያላችሁ አመራሮች የተሰጣችሁን ኃላፊነት መወጣት ይኖርባችኋል ብለዋል።
ስልጠናው የሙስና ምንነት፣ ባህሪያትና አይነቶች ላይ ያተኮረ ብቻ ሳይሆን በዘርፋ በተደረገ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነት ዳሰሳ ጥናት መነሻነት ከተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተወጣጡ ምሁራን በተዘጋጀ የማሰልጠኛ ሞጁል የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል።
ስልጠናው ለመስኖና ቆላማ አካባቢ ዘርፍ አመራሮች እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የሀሰተኛ ማንነት ማስረጃ የሚያዘጋጅ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ሀሰተኛ ማስረጃ እያዘጋጀ ለተለያዩ ግለሰቦች ሲሰጥ የነበረ ግለሰብ በተሰጠ ጥቆማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረጉን አሳወቀ፡፡
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋለው ወደ ኤጀንሲው ዋና መስርያ ቤት ሃሰተኛ መታወቂያ እና ያላገባ ማስረጃ በመያዝ አገልግሎት ለማግኘት የመጣች ተገልጋይ በሰጠችው ጥቆማ መሆኑን የኤጀንሲው የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አስናቀች ሙህዬ አስታውቀዋል፡፡
ከግለሰቧ በተሰጠ ጥቆማ መሰረት ሀሰተኛ ሰነድ በሚያዘጋጀው ግለሰብ በተሰራ ኦፕሬሽን በብር 20,000 መታወቂያና ልደት እንዲያዘጋጅ በመደራደር መረጃው የሚያዘጋጅላት ግለሰብ ፎቶና ሌሎች መረጃዎችን እንዲሁም የቀብድ ክፍያ 10,000 ብር በሚቀበልበት ወቅት ከለሚ ኩራ ፖሊስ መመሪያ ጋር በመተባበር ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የኤጀንሲው ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ ገልፀዋል፡፡
ግለሰቡ በፖሊስ ዝርዝር ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ሀሰተኛ ማስረጃ እያዘጋጀ ለተለያዩ ግለሰቦች ሲሰጥ የነበረ ግለሰብ በተሰጠ ጥቆማ በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረጉን አሳወቀ፡፡
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋለው ወደ ኤጀንሲው ዋና መስርያ ቤት ሃሰተኛ መታወቂያ እና ያላገባ ማስረጃ በመያዝ አገልግሎት ለማግኘት የመጣች ተገልጋይ በሰጠችው ጥቆማ መሆኑን የኤጀንሲው የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አስናቀች ሙህዬ አስታውቀዋል፡፡
ከግለሰቧ በተሰጠ ጥቆማ መሰረት ሀሰተኛ ሰነድ በሚያዘጋጀው ግለሰብ በተሰራ ኦፕሬሽን በብር 20,000 መታወቂያና ልደት እንዲያዘጋጅ በመደራደር መረጃው የሚያዘጋጅላት ግለሰብ ፎቶና ሌሎች መረጃዎችን እንዲሁም የቀብድ ክፍያ 10,000 ብር በሚቀበልበት ወቅት ከለሚ ኩራ ፖሊስ መመሪያ ጋር በመተባበር ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የኤጀንሲው ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሯ ገልፀዋል፡፡
ግለሰቡ በፖሊስ ዝርዝር ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በዘርፉ ያለውን ብልሹ አሰራር ለመከላከል የተጀመሩ የዲጂታል አሰራሮችን አጠናክረን እንቀጥላለን - አለሙ ስሜ (ዶ/ር)
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር የሥነ-ምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል፡፡
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዘርፉ ያለውን ብልሹ አሰራር ለመከላከል የተጀመሩ የዲጂታል አሰራሮችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም ማህበራዊ እሴት የሆኑትን የሃይማኖት እና ባህል አስተምሮት ሙስናን ለመከላከል ጉልህ ሚና ስላላቸው እሴቶች ማጉላት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ሙስና እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ተቋም መኖሩን ገልፀው፥ በዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሌብነት የማይመች አደረጃጀት የመፍጠር ኃላፊነት አለብን ብለዋል።
ሀገርን እና ህዝብን የሚጎዳ ተግባር የሚፈፅም አካል ሲኖርም ጠበቅ ያለ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ሙስናን አስቀድሞ ለመከላከል በሰዎች የባህሪ ለውጥ እና ግንዛቤ መፍጠር ስለሚያስፈልግ እንዲህ ያለ ስልጠና መሰጠቱ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ዘርፍ ተኮር የሥነ-ምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል፡፡
በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ የተገኙት የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዘርፉ ያለውን ብልሹ አሰራር ለመከላከል የተጀመሩ የዲጂታል አሰራሮችን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም ማህበራዊ እሴት የሆኑትን የሃይማኖት እና ባህል አስተምሮት ሙስናን ለመከላከል ጉልህ ሚና ስላላቸው እሴቶች ማጉላት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ሙስና እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ተቋም መኖሩን ገልፀው፥ በዘርፉ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለሌብነት የማይመች አደረጃጀት የመፍጠር ኃላፊነት አለብን ብለዋል።
ሀገርን እና ህዝብን የሚጎዳ ተግባር የሚፈፅም አካል ሲኖርም ጠበቅ ያለ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ሙስናን አስቀድሞ ለመከላከል በሰዎች የባህሪ ለውጥ እና ግንዛቤ መፍጠር ስለሚያስፈልግ እንዲህ ያለ ስልጠና መሰጠቱ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319