ለባህል እና ስፓርት ዘርፍ አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ነው
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለባህል እና ስፖርት አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ሃሳብ የሥነ- ምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው ተገኝተው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባህል እና ስፖርት ሚኒሰቴር የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ነፊሳ አለመሀዲ የዘርፉ አመራሮች ተግባራትን ከሙስና እና ብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ማከናወን እንዳለባቸው ገልፀዋል።
የኮሚሽኑ ሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥልጠና መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሐረጎት አብርሃ በበኩላቸው ሥልጠናው ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፥ ሥነምግባራዊ አመራር በስሩ ላሉት ሠራተኞች ምሳሌ ከመሆን ባለፈ ለሀገር እና ተቋም እድገት ግንባታ ሚናው የላቀ ነው ብለዋል።
ስልጠናው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ለባህል እና ስፖርት አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መሪ ሃሳብ የሥነ- ምግባር ግንባታና የሙስና መከላከል ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናው ተገኝተው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባህል እና ስፖርት ሚኒሰቴር የኪነ-ጥበብና ሥነ-ጥበብ ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ነፊሳ አለመሀዲ የዘርፉ አመራሮች ተግባራትን ከሙስና እና ብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ማከናወን እንዳለባቸው ገልፀዋል።
የኮሚሽኑ ሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ሥልጠና መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሐረጎት አብርሃ በበኩላቸው ሥልጠናው ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፥ ሥነምግባራዊ አመራር በስሩ ላሉት ሠራተኞች ምሳሌ ከመሆን ባለፈ ለሀገር እና ተቋም እድገት ግንባታ ሚናው የላቀ ነው ብለዋል።
ስልጠናው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ወቅታዊና ጥራት ያለው ግዥ በመፈፀም ያለንን ውስን ሀብት ከብክነት መከላከል እንደሚገባ ተገለፀ
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በሥራ ሥነምግባርና በግዢ አስተዳደር ሥርዓት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ ለባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ እየሰጠ ነው።
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የቢሮው ኃላፊ ዶክተር መሀመድ ኑሪዬ ሙስና እንደሀገር ማደግና መበልፀግ እንዳንችል እንቅፋት እየፈጠረ ያለ ችግር መሆኑን ተናግረዋል።
ሙስና በሀገር ኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ላይ ቀውስ የሚፈጥር በመሆኑ ለተግባራዊነቱ አመራሩ ቁርጠኝነት መሳተፍ እንደሚገባውም ተናግረዋል።
በቢሮው በርካታ ለህዝብ ተደራሽ የሆኑ የመንገድ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ያነሱት ዶክተር መሀመድ፥ በግዢ ሥርዓት የሚፈፀሙ ብልሹ አሰራሮችን መከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።
መመሪያን የተከተለ፣ ወቅታዊና ጥራት ያለው ግዥ በመፈፀም ያለንን ውስን ሀብት ከብክነት በመከላከል ለዜጎች ልማት ማዋል እንደሚገባ ኃላፊው መናገራቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
በውይይት መድረኩ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ፋሲካ ጌታቸው ጨምሮ የቢሮው አመራርና ሠራተኞች እና የዞንና ልዩ ወረዳ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን መሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ በሥራ ሥነምግባርና በግዢ አስተዳደር ሥርዓት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ ለባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ እየሰጠ ነው።
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የቢሮው ኃላፊ ዶክተር መሀመድ ኑሪዬ ሙስና እንደሀገር ማደግና መበልፀግ እንዳንችል እንቅፋት እየፈጠረ ያለ ችግር መሆኑን ተናግረዋል።
ሙስና በሀገር ኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ላይ ቀውስ የሚፈጥር በመሆኑ ለተግባራዊነቱ አመራሩ ቁርጠኝነት መሳተፍ እንደሚገባውም ተናግረዋል።
በቢሮው በርካታ ለህዝብ ተደራሽ የሆኑ የመንገድ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ያነሱት ዶክተር መሀመድ፥ በግዢ ሥርዓት የሚፈፀሙ ብልሹ አሰራሮችን መከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።
መመሪያን የተከተለ፣ ወቅታዊና ጥራት ያለው ግዥ በመፈፀም ያለንን ውስን ሀብት ከብክነት በመከላከል ለዜጎች ልማት ማዋል እንደሚገባ ኃላፊው መናገራቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
በውይይት መድረኩ የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ፋሲካ ጌታቸው ጨምሮ የቢሮው አመራርና ሠራተኞች እና የዞንና ልዩ ወረዳ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን መሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሀገር አቀፍ የዳኝነትና የፍትህ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ እየተካሄ ይገኛል
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጆይንድ አፕ ጀስቲስ ሴክረተሪያት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ለሁለት ቀናት የሚቆየው የፌደራል እና የክልል የዳኝነት እና የፍትህ አካላት እንዲሁም የመንግስት ተቋማትን ያሳተፈ ሀገር አቀፍ የዳኝነትና የፍትህ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ጸሀይ ዋረሳ እና የጋሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳደር ክብርት ወ/ሮ ልሳነወርቅ ካሳዬ ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የምክክር መድረኩ በዋናነት በፍትህ አካላት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከርና የጋራ ችግሮች ላይ መክሮ የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ በፍትህ አካላት መካከል የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር አላማውን አድርጎ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
መድረኩ በፍትህ አካላት ውስጥ የተበታተነና የማይናበብ ስርዓት የሚፈጥረውን ተግዳሮት ከግምት በማስገባት በአፈጻጸም እና በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ መናበብ እንዲኖር የሚያደርግ በመሆኑ አገራዊ ፋይዳው ከፍተኛ ነውም ብለዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ አክለውም የዳኝነትና የፍትህ ዘርፉ አፈጻጻጸም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በማህበራዊ እና በሌሎችም ዘርፎች የሚንጸባረቅ እንዲሁም ሀገራዊ ህልውና እና የዜጎች ዋስትና ላይ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ ለህዝብ ጥያቄዎች በወቅቱና በአግባቡ ምላሽ ከመስጠት ባሻገር ስኬቶችን በማላቅና ጉድለቶችን በመሙላት፣ በየተቋማቱ ያሉ የማሻሻያ ስራዎችን በማጋራት እንዲሁም የተለያዩ ተሞክሮዎች ላይ ለመወያየት እድል በመፍጠር የፍትህ ስርዓቱ ውጤታማ እንዲሆን ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የኢ.ፌ.ዴ.ሬ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስተር ክብርት ወ/ሮ ሃና ዓርአያስላሴ በበኩላቸው የፍትህና የዳኝነት ተቋማት ተልዕኳቸውን ሲወጡ ህግን ባከበረ መልኩ መንቀሳቀስና የህግ የበላይነትን በማስከበር ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸው፥ እንዲህ አይነት የቅንጅት መድረክ ትርጉም ያለውና ጠንካራ የትብብር ማዕቀፍ በመፍጠር ለሀገር ግንባታ፣ ለሰላማዊ እና የበለጸገ ማህበረሰብ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።
በመድረኩ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ) ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት እየተሳተፋ ሲሆን፥ ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ፍትህ ሚኒስቴር የተለያዩ ሰነዶች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው እንደሚሆን ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጆይንድ አፕ ጀስቲስ ሴክረተሪያት ከጀስቲስ ፎር ኦል ፕሪዝን ፌሎሺፕ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ለሁለት ቀናት የሚቆየው የፌደራል እና የክልል የዳኝነት እና የፍትህ አካላት እንዲሁም የመንግስት ተቋማትን ያሳተፈ ሀገር አቀፍ የዳኝነትና የፍትህ አካላት የጋራ የምክክር መድረክ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ጸሀይ ዋረሳ እና የጋሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳደር ክብርት ወ/ሮ ልሳነወርቅ ካሳዬ ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት የምክክር መድረኩ በዋናነት በፍትህ አካላት መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከርና የጋራ ችግሮች ላይ መክሮ የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ በፍትህ አካላት መካከል የመረጃ ልውውጥ እንዲኖር አላማውን አድርጎ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
መድረኩ በፍትህ አካላት ውስጥ የተበታተነና የማይናበብ ስርዓት የሚፈጥረውን ተግዳሮት ከግምት በማስገባት በአፈጻጸም እና በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ መናበብ እንዲኖር የሚያደርግ በመሆኑ አገራዊ ፋይዳው ከፍተኛ ነውም ብለዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ አክለውም የዳኝነትና የፍትህ ዘርፉ አፈጻጻጸም በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በማህበራዊ እና በሌሎችም ዘርፎች የሚንጸባረቅ እንዲሁም ሀገራዊ ህልውና እና የዜጎች ዋስትና ላይ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ ለህዝብ ጥያቄዎች በወቅቱና በአግባቡ ምላሽ ከመስጠት ባሻገር ስኬቶችን በማላቅና ጉድለቶችን በመሙላት፣ በየተቋማቱ ያሉ የማሻሻያ ስራዎችን በማጋራት እንዲሁም የተለያዩ ተሞክሮዎች ላይ ለመወያየት እድል በመፍጠር የፍትህ ስርዓቱ ውጤታማ እንዲሆን ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
የኢ.ፌ.ዴ.ሬ ፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስተር ክብርት ወ/ሮ ሃና ዓርአያስላሴ በበኩላቸው የፍትህና የዳኝነት ተቋማት ተልዕኳቸውን ሲወጡ ህግን ባከበረ መልኩ መንቀሳቀስና የህግ የበላይነትን በማስከበር ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልጸው፥ እንዲህ አይነት የቅንጅት መድረክ ትርጉም ያለውና ጠንካራ የትብብር ማዕቀፍ በመፍጠር ለሀገር ግንባታ፣ ለሰላማዊ እና የበለጸገ ማህበረሰብ ግንባታ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።
በመድረኩ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ፒኤችዲ) ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት እየተሳተፋ ሲሆን፥ ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ፍትህ ሚኒስቴር የተለያዩ ሰነዶች ቀርበው ውይይት የሚደረግባቸው እንደሚሆን ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319