ለፀረ-ሙስና ትግል ሁሉም ሊያግዝ እንደሚገባ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ አሳሰቡ
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ብልሹ አሠራርን እና ሙስናን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበራት ጋር በጥምረት ለመሥራት ሥምምነት ተፈራርሟል።
በሥነሥርዓቱ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በምክትል ርዕሰ መሥተዳደር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አሥተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኀላፊ ሙሉነሽ ደሴን (ዶ/ር) ጨምሮ የክልል ቢሮ ኀላፊዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሲቪክ ተቋማት እና የሙያ ማኅበራት ተገኝተዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች መካከል አንዱ የሕዝብ ሀብት እና ንብረት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሥነምግባርን በተከተለ መልኩ ሙስናን የመከላከል ሥራን መሥራት መኾኑን አንስተዋል።
ተጠያቂነትን አሠራር እንዲሰፍን ለተቋማት ግብዓት ማቅረብንም ጨምረዋል። ለምክር ቤቶች የጠራ መረጃ በማቅረብ እንዲታገሉበትና የሕዝብ ውክልናቸውንም እንዲወጡ እያደረገ መምጣቱንም አክለዋል።
የጥምረቱ መመሥረት ምክንያትም ተቋማት ከተናጠል ከሚሠሩት በተጨማሪ ኀላፊነታቸውን በጋራ በመሥራት የሙስናን ትግል ለማጠናከር እንደኾነም ነው አፈ ጉባኤዋ የገለጹት። ኮሚሽኑ ጥምረቱን ለማቋቋም የሕግ መሠረት እንዳለውም ጠቅሰዋል።
በሥነምግባር ግንባታ ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ በመፍጠር በኩል የሃይማኖት አባቶች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሙያ ማኅበራት እና ሌሎቹም ትልቅ ኀላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሥነምግባርን ከመገንባት አኳያ የሃይማኖት ተቋማት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰዋል።
ኅብረተሰቡ ከተራ አገልግሎት ጀምሮ ለማንኛውም አገልግሎት ክፍያ እየተጠየቀ መኾኑን ያነሱት ዋና አፈ ጉባኤዋ ችገሩን ለመቀነስ ከጥምረቱ መቋቋም በኋላ በሚቀመጡ አሠራሮች አማካይነት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን በመገንዘብ ሁሉም የአቅሙን ማበርከት እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል።
በየተቋማቱ ከእቅድ ጀምሮ ትኩረት በመስጠት የመሥራት ጅምር ቢኖርም ውጤቱ የሚጠበቀውን ያህል አይደለም። ይህንን ችግር ለመፍታት የጥምረቱ መመሥረት ታምኖበታል ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
የሥነምግባር ግንባታውን በየተቋማቱ በመሥራት በትውልድ ላይ የሚሠራውን ሥራ ለማጠናከር ነው። ተቋማት ይህንን ሥራ ለመሥራት የሚያጋጥመውን ችግር በጋራ እየገመገምን የመንግሥት እና የሕዝብ ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥረት ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
የጥምረቱ መቋቋም ግብ የፀረ-ሙስና ትግሉ በተገቢው ተመርቶ ሕዝብ ተገቢ አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ኹኔታ ለመፍጠር ነው። ለዚህም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አደራ ብለዋል ዋና አፈ ጉባኤዋ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ብልሹ አሠራርን እና ሙስናን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበራት ጋር በጥምረት ለመሥራት ሥምምነት ተፈራርሟል።
በሥነሥርዓቱ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በምክትል ርዕሰ መሥተዳደር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አሥተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኀላፊ ሙሉነሽ ደሴን (ዶ/ር) ጨምሮ የክልል ቢሮ ኀላፊዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሲቪክ ተቋማት እና የሙያ ማኅበራት ተገኝተዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች መካከል አንዱ የሕዝብ ሀብት እና ንብረት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሥነምግባርን በተከተለ መልኩ ሙስናን የመከላከል ሥራን መሥራት መኾኑን አንስተዋል።
ተጠያቂነትን አሠራር እንዲሰፍን ለተቋማት ግብዓት ማቅረብንም ጨምረዋል። ለምክር ቤቶች የጠራ መረጃ በማቅረብ እንዲታገሉበትና የሕዝብ ውክልናቸውንም እንዲወጡ እያደረገ መምጣቱንም አክለዋል።
የጥምረቱ መመሥረት ምክንያትም ተቋማት ከተናጠል ከሚሠሩት በተጨማሪ ኀላፊነታቸውን በጋራ በመሥራት የሙስናን ትግል ለማጠናከር እንደኾነም ነው አፈ ጉባኤዋ የገለጹት። ኮሚሽኑ ጥምረቱን ለማቋቋም የሕግ መሠረት እንዳለውም ጠቅሰዋል።
በሥነምግባር ግንባታ ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ በመፍጠር በኩል የሃይማኖት አባቶች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሙያ ማኅበራት እና ሌሎቹም ትልቅ ኀላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሥነምግባርን ከመገንባት አኳያ የሃይማኖት ተቋማት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰዋል።
ኅብረተሰቡ ከተራ አገልግሎት ጀምሮ ለማንኛውም አገልግሎት ክፍያ እየተጠየቀ መኾኑን ያነሱት ዋና አፈ ጉባኤዋ ችገሩን ለመቀነስ ከጥምረቱ መቋቋም በኋላ በሚቀመጡ አሠራሮች አማካይነት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን በመገንዘብ ሁሉም የአቅሙን ማበርከት እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል።
በየተቋማቱ ከእቅድ ጀምሮ ትኩረት በመስጠት የመሥራት ጅምር ቢኖርም ውጤቱ የሚጠበቀውን ያህል አይደለም። ይህንን ችግር ለመፍታት የጥምረቱ መመሥረት ታምኖበታል ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
የሥነምግባር ግንባታውን በየተቋማቱ በመሥራት በትውልድ ላይ የሚሠራውን ሥራ ለማጠናከር ነው። ተቋማት ይህንን ሥራ ለመሥራት የሚያጋጥመውን ችግር በጋራ እየገመገምን የመንግሥት እና የሕዝብ ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥረት ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
የጥምረቱ መቋቋም ግብ የፀረ-ሙስና ትግሉ በተገቢው ተመርቶ ሕዝብ ተገቢ አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ኹኔታ ለመፍጠር ነው። ለዚህም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አደራ ብለዋል ዋና አፈ ጉባኤዋ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የከተማና መሠረተልማት ዘርፍ ግዙፍ በጀት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ አመራሩ በላቀ ሥነምግባር መምራት እንደሚጠበቅበት ተገለፀ
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም፣ አለም ገና) ለከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማት ተልዕኮ ስኬት!" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በመድረኩ ዘርፉን ወክለው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ኢ/ር) የከተማና መሠረተልማት ዘርፍ በሀገር ደረጃ ግዙፍ የመንግስት እና የህዝብ ሀብት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ አመራሩ የላቀ ሥነምግባር ተላብሶ መምራት እንዳለበት አሳስበዋል።
የተበላሸ የአዕምሮ ውቅር ለብልሹ አሰራሮች መነሻ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፥ ችግሩን ለመቅረፍ የሥነምግባር ግንዛቤ ማሳደግና ሥልጠና ማስፋት አንዱ መሣሪያ መሆኑን አንስተዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው የፀረ-ሙስና ትግሉን ዘርፍ ተኮር በማድረግ ዘርፎች የፀረ-ሙስና ትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም ዘርፍ ተኮር አሠራር ከጥናት ጀምሮ መካሂዱን በመጠቆም፥ ጥናቱን መሠረት ያደረጉ የሥልጠና ሞጁሎች በዩኒቨርሲቲ ምሁራን በማዘጋጀት ሥልጠና መሠጠት መጀመሩን ጠቅሠዋል።
በተጀመረው ሥልጠና የአመራር ሥነምግባር በመገንባት በዘርፍ ተቋማት ለፀረ-ሙስና ትግል አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጠር ገልፀዋል።
ስልጠናው በዩኒቨርስቲ ምሁራን እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም፣ አለም ገና) ለከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማት ተልዕኮ ስኬት!" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በመድረኩ ዘርፉን ወክለው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ኢ/ር) የከተማና መሠረተልማት ዘርፍ በሀገር ደረጃ ግዙፍ የመንግስት እና የህዝብ ሀብት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ አመራሩ የላቀ ሥነምግባር ተላብሶ መምራት እንዳለበት አሳስበዋል።
የተበላሸ የአዕምሮ ውቅር ለብልሹ አሰራሮች መነሻ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፥ ችግሩን ለመቅረፍ የሥነምግባር ግንዛቤ ማሳደግና ሥልጠና ማስፋት አንዱ መሣሪያ መሆኑን አንስተዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው የፀረ-ሙስና ትግሉን ዘርፍ ተኮር በማድረግ ዘርፎች የፀረ-ሙስና ትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም ዘርፍ ተኮር አሠራር ከጥናት ጀምሮ መካሂዱን በመጠቆም፥ ጥናቱን መሠረት ያደረጉ የሥልጠና ሞጁሎች በዩኒቨርሲቲ ምሁራን በማዘጋጀት ሥልጠና መሠጠት መጀመሩን ጠቅሠዋል።
በተጀመረው ሥልጠና የአመራር ሥነምግባር በመገንባት በዘርፍ ተቋማት ለፀረ-ሙስና ትግል አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጠር ገልፀዋል።
ስልጠናው በዩኒቨርስቲ ምሁራን እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የሌላ ደንበኛ ሂሳብን ‘የእኔ ነው’ በማለት 12 ሚሊየን ብር ሊያዘዋውር የሞከረው ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሌላ ደንበኛ ሂሳብ ‘ባለቤት ነኝ’ ብሎ 12 ሚሊየን ብር ሊያዘዋውር ሲሞክር በባንኩ ሰራተኞች የተያዘው ተከሳሽ በአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ወሰነ።
ተከሳሹ መምህር መንግስቱ ተመስገን በወንጀል ምርመራ ሂሳቡ የታገደበትን ተማም መሃር የተባለ ግለሰብ ስም ተመሳስሎ የተዘጋጀ ሀሰተኛ የነዋሪነት መታወቂያ በመያዝ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጂ ክፍለ ከተማ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡራዩ ቅርጫፍ በመሄድ ለባንኩ ባለሙያዎች ተማም መሃር የተባለ ቡና ላኪ ባለሃብት እንደሆነ በመግለጽ እንደተዋወቃቸው በክሱ ላይ ተጠቅሷል።
ተከሳሹ በሌላ ቅርንጫፍ ከ12 ሚሊየን በላይ ገንዘብ ያለው ሂሳብ መክፈቱን በመግለጽ እንዲሁም "ያንን ሂሳብ ዘግቼ እናንተ ቅርጫፍ አዲስ ሂሳብ ልክፈትና 12 ሚሊየን ብሩን በዚህ ቅርጫፍ ወደ ምከፍተው ሂሳቤ አዘዋውሩልኝ " በማለት መጠየቁ ተመላክቷል፡፡
በባንኩ አሰራር መሰረት የጠየቀው የገንዘብ መጠን ከፍ ያለ በመሆኑ የባንኩ ማናጀር ማረጋገጫ መስጠት ስላለበት ባለሙያዎቹ ወደ ባንኩ ማናጀር ይልኩታል፡፡
የባንኩ ማናጀርም በቀረበው ጥያቄ መነሻ መንጃ ፍቃድ ወይም ፓስፖር፣ ቪዛ እንዲያሳየው ሲጠይቀው ተከሳሹ አለመያዙን መልስ የሰጠ ሲሆን የባንኩ ማናጀር ተማም መሃር በተባለ ግለሰብ ስም የተከፈተው ሂሳብ ባለቤት መሆኑንና አለመሆኑን ለማረጋገጥ ኮምፒዩተር ከፍቶ ሲመለከት ሂሳቡ በወንጀል ምርመራ እንዳይንቀሳቀስ የታገደ የሌላ ሰው ሂሳብ መሆኑን በማረጋገጥ ከሰራተኞቹ ጋር የባንኩን ጥበቃ ጠርቶ ተከሳሹን በማስያዝ ለፀጥታ አካላት አሳልፎ መስጠቱ በክስ ዝርዝሩ ላይ ተጠቅሷል።
ተከሳሹ በቁጥጥር ስር ከዋለና ምርመራ ከተደረገበት በኋላ የኦሮሚያ ክልል የሸገር ከተማ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ዐቃቤ ሕግ ተከሳሹ ላይ የሙስና ወንጀልን ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ጠቅሶ ክስ አቅርቦበታል።
ተከሳሹ የክሱ ዝርዝር ከደረሰው በኋላ የወንጀል ድርጊቱን አለመፈጸሙን ጠቅሶ የዕምነት ክህደት ቃል በመስጠቱ፤ ዐቃቤ ሕግ የሰው ምስክርና የሰነድ ማስረጃ ማቅረቡን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ተከሳሹ እንዲከላከል በሰጠው ብይን ተከሳሹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል ባለመቻሉ የጥፋተኝነት ፍርድ ሰጥቶበታል።
በዚህም ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየትን መርምሮና ይዞ ተከሳሹን በአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና በ5 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የሌላ ደንበኛ ሂሳብ ‘ባለቤት ነኝ’ ብሎ 12 ሚሊየን ብር ሊያዘዋውር ሲሞክር በባንኩ ሰራተኞች የተያዘው ተከሳሽ በአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ወሰነ።
ተከሳሹ መምህር መንግስቱ ተመስገን በወንጀል ምርመራ ሂሳቡ የታገደበትን ተማም መሃር የተባለ ግለሰብ ስም ተመሳስሎ የተዘጋጀ ሀሰተኛ የነዋሪነት መታወቂያ በመያዝ መስከረም 11 ቀን 2016 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጂ ክፍለ ከተማ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቡራዩ ቅርጫፍ በመሄድ ለባንኩ ባለሙያዎች ተማም መሃር የተባለ ቡና ላኪ ባለሃብት እንደሆነ በመግለጽ እንደተዋወቃቸው በክሱ ላይ ተጠቅሷል።
ተከሳሹ በሌላ ቅርንጫፍ ከ12 ሚሊየን በላይ ገንዘብ ያለው ሂሳብ መክፈቱን በመግለጽ እንዲሁም "ያንን ሂሳብ ዘግቼ እናንተ ቅርጫፍ አዲስ ሂሳብ ልክፈትና 12 ሚሊየን ብሩን በዚህ ቅርጫፍ ወደ ምከፍተው ሂሳቤ አዘዋውሩልኝ " በማለት መጠየቁ ተመላክቷል፡፡
በባንኩ አሰራር መሰረት የጠየቀው የገንዘብ መጠን ከፍ ያለ በመሆኑ የባንኩ ማናጀር ማረጋገጫ መስጠት ስላለበት ባለሙያዎቹ ወደ ባንኩ ማናጀር ይልኩታል፡፡
የባንኩ ማናጀርም በቀረበው ጥያቄ መነሻ መንጃ ፍቃድ ወይም ፓስፖር፣ ቪዛ እንዲያሳየው ሲጠይቀው ተከሳሹ አለመያዙን መልስ የሰጠ ሲሆን የባንኩ ማናጀር ተማም መሃር በተባለ ግለሰብ ስም የተከፈተው ሂሳብ ባለቤት መሆኑንና አለመሆኑን ለማረጋገጥ ኮምፒዩተር ከፍቶ ሲመለከት ሂሳቡ በወንጀል ምርመራ እንዳይንቀሳቀስ የታገደ የሌላ ሰው ሂሳብ መሆኑን በማረጋገጥ ከሰራተኞቹ ጋር የባንኩን ጥበቃ ጠርቶ ተከሳሹን በማስያዝ ለፀጥታ አካላት አሳልፎ መስጠቱ በክስ ዝርዝሩ ላይ ተጠቅሷል።
ተከሳሹ በቁጥጥር ስር ከዋለና ምርመራ ከተደረገበት በኋላ የኦሮሚያ ክልል የሸገር ከተማ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ዐቃቤ ሕግ ተከሳሹ ላይ የሙስና ወንጀልን ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ጠቅሶ ክስ አቅርቦበታል።
ተከሳሹ የክሱ ዝርዝር ከደረሰው በኋላ የወንጀል ድርጊቱን አለመፈጸሙን ጠቅሶ የዕምነት ክህደት ቃል በመስጠቱ፤ ዐቃቤ ሕግ የሰው ምስክርና የሰነድ ማስረጃ ማቅረቡን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ተከሳሹ እንዲከላከል በሰጠው ብይን ተከሳሹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል ባለመቻሉ የጥፋተኝነት ፍርድ ሰጥቶበታል።
በዚህም ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየትን መርምሮና ይዞ ተከሳሹን በአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና በ5 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኗል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሙስናን መታገል ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑን የጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ገለፀ
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሥነ-ምግባር ግንባታ፣ በሙስና ጽንሰ ሀሳብ እና መከላከል ዙሪያ ለኮሌጁ አሰልጣኞችና ለአስተዳደር ሰራተኞች ለ2 ቀናት ስልጠና ሰጥቷል፡፡
የኮሌጁ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት አቦነህ በስልጠናው የተሳተፉ ከ300 በላይ የኮሌጁ አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች በሥነምግባር የታነፀ ትውልድ በማፍራትና ሙስናን በመከላከል የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የስልጠናው ዓላማ የሙስና አስከፊነት ላይ ግንዛቤ በማዳበር ለፀረ-ሙስና ትግሉ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲችል ለማገዝ መሆኑን ዳይሬከረተሯ ገልፀዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጠው በአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ባለሙያ አቶ ደረጀ ግርማ ስልጠናው በመንግስት ተቋማት የሚታዩትን ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመቀነስ የሥራ ክፍሎችና ሰራተኞች የሚሰጡ አገልግሎቶች ከሙስና የፀዳ እንዲሆን ለማስቻልና የሙስና መከሰቻ መንገዶቹን በማወቅ ሙስናን ለመከላከል እንደሚረዳ አስረድተዋል፡፡
ሙስናን የሚጸየፍ ማህረሰብ ለመፍጠር ቤተሰብ፣ ት/ቤቶችና ማህበረሰቡ ትልቅ ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ሙስናን መታገል ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑን ባለሙያው መናገሩን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የስልጠና ተሳታፊዎችም የሙስና አስከፊነት ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ የሄደበት ሁኔታ ማህበረሰቡን እያማረረ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ለዚህም በቅንጅት በመስራት ሙሰኞችን መታገልና በሙስና የተከሰሱ ወንጀለኞችም አስተማሪ ቅጣት አለማግኘታቸው ሙሰኞችን እያበረታታ መሄዱን ገልፀው፤ መንግስት፣ ህዝብና የሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥቶ በጋራ ለመስራት ወሳኝ ወቅት ላይ ነን ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የጀኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሥነ-ምግባር ግንባታ፣ በሙስና ጽንሰ ሀሳብ እና መከላከል ዙሪያ ለኮሌጁ አሰልጣኞችና ለአስተዳደር ሰራተኞች ለ2 ቀናት ስልጠና ሰጥቷል፡፡
የኮሌጁ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት አቦነህ በስልጠናው የተሳተፉ ከ300 በላይ የኮሌጁ አሰልጣኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች በሥነምግባር የታነፀ ትውልድ በማፍራትና ሙስናን በመከላከል የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
የስልጠናው ዓላማ የሙስና አስከፊነት ላይ ግንዛቤ በማዳበር ለፀረ-ሙስና ትግሉ የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲችል ለማገዝ መሆኑን ዳይሬከረተሯ ገልፀዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጠው በአዲስ አበባ ከተማ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የስልጠና ባለሙያ አቶ ደረጀ ግርማ ስልጠናው በመንግስት ተቋማት የሚታዩትን ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመቀነስ የሥራ ክፍሎችና ሰራተኞች የሚሰጡ አገልግሎቶች ከሙስና የፀዳ እንዲሆን ለማስቻልና የሙስና መከሰቻ መንገዶቹን በማወቅ ሙስናን ለመከላከል እንደሚረዳ አስረድተዋል፡፡
ሙስናን የሚጸየፍ ማህረሰብ ለመፍጠር ቤተሰብ፣ ት/ቤቶችና ማህበረሰቡ ትልቅ ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ሙስናን መታገል ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑን ባለሙያው መናገሩን ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
የስልጠና ተሳታፊዎችም የሙስና አስከፊነት ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ የሄደበት ሁኔታ ማህበረሰቡን እያማረረ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ለዚህም በቅንጅት በመስራት ሙሰኞችን መታገልና በሙስና የተከሰሱ ወንጀለኞችም አስተማሪ ቅጣት አለማግኘታቸው ሙሰኞችን እያበረታታ መሄዱን ገልፀው፤ መንግስት፣ ህዝብና የሚመለከተው ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥቶ በጋራ ለመስራት ወሳኝ ወቅት ላይ ነን ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319