ከ5 ሚሊየን ብር በላይ እንዲመዘበር በማድረግ የሙስና ወንጀል የተከሰሱ በእስራትና በገንዘብ ተቀጡ
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 4/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የባንክ መመሪያና የአሰራር ስርዓትን በመጣስ ከደንበኛ ሂሳብ ከ5 ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ ወጪ በማዘዝ እና በመመዝበር በከባድ የሙስና ወንጀል የተከሰሱ 5 ግለሰቦች ከ4 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ወሰነ።
ተከሳሾቹ 1ኛ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተፈራ ደግፌ ቅርንጫፍ ተጠባባቂ ተቀዳሚ ቅርንጫፍ ባንኪንግ መኮንን በረከት ሙሉ፣ 2ኛ በቅርንጫፉ ተጠባባቂ የውስጥ ተቆጣጣሪ ማርታ ሃይሉ፣ 3ኛ በንግድ ስራ ይተዳደራል የተባለው ተስፋ ገ/ስላሴ፣ 4ኛ ጌትነት አለማየሁ እና 5ኛ ሪያን ሰይድ ናቸው።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በ2016 ዓ.ም በተከሳሾቹ ላይ ማለትም በአንደኛው ክስ በ1ኛ እና በ2ኛ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 (1) (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 9 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር (2) ስር የተመላከተውን ድንጋጌ መተላለፍ የሚል ክስ አቅርቧል።
በሁለተኛው ክስ ደግሞ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር በተጠቀሱ ተከሳሾች ላይ ብቻ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብን እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 780/200 5 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 1 ሥር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፍ የሚል ክስ አቅርቦባቸዋል።
በዚህ መልኩ በቀረበው በአንደኛው ክስ ላይ እንደተመላከተው 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥቅምት 2013 ዓ.ም ያጸደቀው የቅርንጫፍ ባንኮች የአሰራር ስርዓት መመሪያ ደንብን በመተላለፍ የባንኩ ደንበኛ የሆኑት የግል ተበዳይ አቶ ይትባረክ ይኩኑ አምላክ ከሂሳብ ቁጥራቸው ላይ ገንዘብ ተቀናሽ ሆኖ ወደ ሌላ ሂሳብ እንዲተላለፍ ጥያቄ ባላቀረቡበት ሁኔታ ላይ ከደንበኛው ሂሳብ ያለአግባብ የገንዘብ ዝውውር ለመፈፀም እንዲያስችላቸው በባንኩ ተጥሎ የነበረውን የክልከላ ገደብ መተላለፋቸውን በክሱ ተጠቅሷል።
በዚህ መልኩ 1ኛ ተከሳሽ በባንኩ የተሰጠውን የሚስጥር ቁጥር ለ2ኛ ተከሳሽ አሳልፎ በመስጠት 2ኛ ተከሳሽ ደግሞ በመስከረም 8 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ምንም አይነት ግብይት በሌለበት ሁኔታ የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች የሆኑ ሰራተኞችን ኮምፒውተር በመጠቀም የደንበኛው የቀሪ ሂሳብ እና ፊርማ ምልከታ በማድረግ ፎቶ በማንሳት መረጃውን አሳልፋ ለሌላ የሰጠች መሆኑ ተመላክቷል።
በመስከረም 10 ቀን 2016 ዓ.ም ለጊዜው ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ ከቅርንጫፉ ውጪ የተዘጋጁ እና በግል ተበዳይ ያልተፈረሙ ሁለት በሐዋላ ገንዘብ መላኪያ ቅጽ ይዞ በመቅረብ ለ1ኛ ተከሳሽ የሰጠው ሲሆን ተከሳሹም 4ኛ የዐቃቤ ሕግ ምስክር ደንበኞች እያስተናገደች የነበረችበትን ኮምፒውተር በመጠቀም ለ3ኛ ተከሳሽ ሂሳብ ቁጥር ብር 3 ሚሊየን 240 ሺህ ብር እና ለ4ኛ ተከሳሽ ደግሞ 2 ሚሊየን 160 ሺህ ብር በአጠቃላይ 5 ሚሊየን 400 ሺህ ብር ዝውውር ከፈፀመ በኃላ በራሱ የኮምፒውተር መጠቀሚያ ዩዘር ግብይቶችን ያፀደቀ መሆኑ በክሱ ተዘርዝሯል።
2ኛ ተከሳሽም ደግሞ ግብይቶችን ኦዲት በማድረግ ያረጋገጠች በመሆኑም በአጠቃላይ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች የአሰራር ስርዓት መመሪያ በግልጽ ተግባር በመተላለፍ ደንበኛው ባልቀረቡበትና የክፍያ ጥያቄ ባላቀረቡበት ሁኔታ ከሂሳባቸው ገንዘብ ወጪ በማድረግ በባንኩ ላይ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ እና ለሌሎች ሰዎች ያልተገባ ጥቅም እንዲውል ያደረጉ መሆናቸው ተጠቅሶ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት ስልጣንን አለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡
በሁለተኛው ክስ ደግሞ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ላይ በቀረበው ክስ እንደተገለጸው፤ ተከሳሾች የንብረቱን ህገ-ወጥ ምንጭ ለመደበቅ እና ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ በማሰብ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድነት ቅርንጫፍ ደንበኛ ከሆኑት የግል ተበዳይ ከሂሳብ ቁጥራቸው ላይ ያለአግባብ ወጪ ከሆነው ብር ውስጥ በተለያዩ መጠኖች በተከፈተ ሒሳብ በማስተላለፍ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል ተከሰዋል፡፡
ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ችሎት ቀርበው ክሱ እንዲደርሳቸው ከተደረገ በኋላ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ማስረጃዎችን መርምሮ የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን መረጋገጡን ጠቅሶ ተከሳሾቹ በየደረጃው በተከሰሱበት ድንጋጌ ስር እንዲከላከሉ ብይን መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ሆኖም ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከል( ማስተባበል) አለመቻላቸው ተጠቅሶ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮና ተከሳሾች ያቀረቡትን የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶችን በመያዝ 1ኛ ተከሳሽን በ4 ዓመት ከ5 ወራት ጽኑ እስራት እና በ4 ሺህ ብር፣ 2ኛ ተከሳሽን በ4 ዓመት ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 4/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የባንክ መመሪያና የአሰራር ስርዓትን በመጣስ ከደንበኛ ሂሳብ ከ5 ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ ወጪ በማዘዝ እና በመመዝበር በከባድ የሙስና ወንጀል የተከሰሱ 5 ግለሰቦች ከ4 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ወሰነ።
ተከሳሾቹ 1ኛ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተፈራ ደግፌ ቅርንጫፍ ተጠባባቂ ተቀዳሚ ቅርንጫፍ ባንኪንግ መኮንን በረከት ሙሉ፣ 2ኛ በቅርንጫፉ ተጠባባቂ የውስጥ ተቆጣጣሪ ማርታ ሃይሉ፣ 3ኛ በንግድ ስራ ይተዳደራል የተባለው ተስፋ ገ/ስላሴ፣ 4ኛ ጌትነት አለማየሁ እና 5ኛ ሪያን ሰይድ ናቸው።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በ2016 ዓ.ም በተከሳሾቹ ላይ ማለትም በአንደኛው ክስ በ1ኛ እና በ2ኛ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 (1) (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 9 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና ንዑስ ቁጥር (2) ስር የተመላከተውን ድንጋጌ መተላለፍ የሚል ክስ አቅርቧል።
በሁለተኛው ክስ ደግሞ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር በተጠቀሱ ተከሳሾች ላይ ብቻ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብን እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 780/200 5 አንቀጽ 29 ንዑስ ቁጥር 1 ሥር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፍ የሚል ክስ አቅርቦባቸዋል።
በዚህ መልኩ በቀረበው በአንደኛው ክስ ላይ እንደተመላከተው 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥቅምት 2013 ዓ.ም ያጸደቀው የቅርንጫፍ ባንኮች የአሰራር ስርዓት መመሪያ ደንብን በመተላለፍ የባንኩ ደንበኛ የሆኑት የግል ተበዳይ አቶ ይትባረክ ይኩኑ አምላክ ከሂሳብ ቁጥራቸው ላይ ገንዘብ ተቀናሽ ሆኖ ወደ ሌላ ሂሳብ እንዲተላለፍ ጥያቄ ባላቀረቡበት ሁኔታ ላይ ከደንበኛው ሂሳብ ያለአግባብ የገንዘብ ዝውውር ለመፈፀም እንዲያስችላቸው በባንኩ ተጥሎ የነበረውን የክልከላ ገደብ መተላለፋቸውን በክሱ ተጠቅሷል።
በዚህ መልኩ 1ኛ ተከሳሽ በባንኩ የተሰጠውን የሚስጥር ቁጥር ለ2ኛ ተከሳሽ አሳልፎ በመስጠት 2ኛ ተከሳሽ ደግሞ በመስከረም 8 ቀን 2016 ዓ.ም ደግሞ ምንም አይነት ግብይት በሌለበት ሁኔታ የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች የሆኑ ሰራተኞችን ኮምፒውተር በመጠቀም የደንበኛው የቀሪ ሂሳብ እና ፊርማ ምልከታ በማድረግ ፎቶ በማንሳት መረጃውን አሳልፋ ለሌላ የሰጠች መሆኑ ተመላክቷል።
በመስከረም 10 ቀን 2016 ዓ.ም ለጊዜው ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ ከቅርንጫፉ ውጪ የተዘጋጁ እና በግል ተበዳይ ያልተፈረሙ ሁለት በሐዋላ ገንዘብ መላኪያ ቅጽ ይዞ በመቅረብ ለ1ኛ ተከሳሽ የሰጠው ሲሆን ተከሳሹም 4ኛ የዐቃቤ ሕግ ምስክር ደንበኞች እያስተናገደች የነበረችበትን ኮምፒውተር በመጠቀም ለ3ኛ ተከሳሽ ሂሳብ ቁጥር ብር 3 ሚሊየን 240 ሺህ ብር እና ለ4ኛ ተከሳሽ ደግሞ 2 ሚሊየን 160 ሺህ ብር በአጠቃላይ 5 ሚሊየን 400 ሺህ ብር ዝውውር ከፈፀመ በኃላ በራሱ የኮምፒውተር መጠቀሚያ ዩዘር ግብይቶችን ያፀደቀ መሆኑ በክሱ ተዘርዝሯል።
2ኛ ተከሳሽም ደግሞ ግብይቶችን ኦዲት በማድረግ ያረጋገጠች በመሆኑም በአጠቃላይ 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች የአሰራር ስርዓት መመሪያ በግልጽ ተግባር በመተላለፍ ደንበኛው ባልቀረቡበትና የክፍያ ጥያቄ ባላቀረቡበት ሁኔታ ከሂሳባቸው ገንዘብ ወጪ በማድረግ በባንኩ ላይ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ እና ለሌሎች ሰዎች ያልተገባ ጥቅም እንዲውል ያደረጉ መሆናቸው ተጠቅሶ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት ስልጣንን አለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡
በሁለተኛው ክስ ደግሞ ከ3ኛ እስከ 5ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ላይ በቀረበው ክስ እንደተገለጸው፤ ተከሳሾች የንብረቱን ህገ-ወጥ ምንጭ ለመደበቅ እና ከህግ ተጠያቂነት ለማምለጥ በማሰብ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድነት ቅርንጫፍ ደንበኛ ከሆኑት የግል ተበዳይ ከሂሳብ ቁጥራቸው ላይ ያለአግባብ ወጪ ከሆነው ብር ውስጥ በተለያዩ መጠኖች በተከፈተ ሒሳብ በማስተላለፍ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል ተከሰዋል፡፡
ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ችሎት ቀርበው ክሱ እንዲደርሳቸው ከተደረገ በኋላ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።
ዐቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ያቀረበ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ማስረጃዎችን መርምሮ የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን መረጋገጡን ጠቅሶ ተከሳሾቹ በየደረጃው በተከሰሱበት ድንጋጌ ስር እንዲከላከሉ ብይን መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ሆኖም ተከሳሾቹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው መከላከል( ማስተባበል) አለመቻላቸው ተጠቅሶ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮና ተከሳሾች ያቀረቡትን የቅጣት ማቅለያ አስተያየቶችን በመያዝ 1ኛ ተከሳሽን በ4 ዓመት ከ5 ወራት ጽኑ እስራት እና በ4 ሺህ ብር፣ 2ኛ ተከሳሽን በ4 ዓመት ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ተወስኗል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
"ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል ርዕስ ለፕላንና ልማት ዘርፍ አመራሮች ስልጠና እየተሠጠ ይገኛል
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 5/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን “ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት” በሚል ርዕስ ለፕላንና ልማት ዘርፍ አመራሮች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ድኤታ ክብርት ጥሩማር አባተ ሙስና የአንድን አገር መልካም አስተዳደር፣ የኢኮኖሚ እድገት እና የሰብአዊ መብት መከበር በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳ፣ ሐቀኝነትን በማጓደል የሕገወጥነትን ባህሪ የሚያላብስ እና ሀገርን ሊበትን የሚችል አለምአቀፋዊ ወንጀል ነው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ሙስና በዓለም አቀፍ፣ በአህጉር አቀፍ እና በሀገር ደረጃ እያስከተለ ያለው ችግር በጣም ከባድና ውስብስብ እየሆነ መምጣቱን አመላክተዋል።
እንደ መንግስትም ሙስና የሚያስከትለውን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ በመረዳት ችግሩ የከፋ ደረጃ ላይ ከመድረሱ በፊት በርካታ አሰራርና ህጎችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ሚንስትር ዴኤታዋ አክለውም ሁላችንም ብልሹ አሠራርን ለመታገል ከኔ በላይ ማንም የለም በሚል ስሜት ንቅናቄውን መቀላቀልና ከሌሎች በተሻለና ከፍ ባለ ሁኔታ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ለሀገር ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ፀር የሆነውን ሙስና በጋራ መከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ ስልጠናው ሲሰጥ የነበረው የሙስና ምንነት፣ አስፈላጊነትና መከላከያ ዘዴዎች መሆኑን አስታውሰው፥ አሁን ግን ዘርፍ ተኮር አሰራርን በመከተል በዘርፋ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ዳሰሳ ጥናት መነሻነት የሚሰጥ ስልጠና ነው ብለዋል።
ለዚህም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተወጣጡ ሙሁራን በተዘጋጁ የማሰልጠኛ ሞጅሎች የሚሰጥ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሆኑንም ጠቁመዋል።
ስልጠናው በመጀመሪያው ዙር ለዘርፋ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑን ገልፀው፥ በቀጣይም በየደረጃው ለሚገኙ መካከለኛ አመራሮችና ሠራተኞች የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም አንድ ተቋም ውጤታማ የሚሆነው የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በሥነምግባር አርዓያ ሲሆኑ መሆኑን ገልፀው፥ ለዚህም አመራሩ የተሰጣቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በዘርፋ የብልሹ አሰራር ችግሮች ሲኖሩም ችግር ፈጣሪዎችን ተጠያቂ በማድረግ ለፀረ-ሙስና ትግሉ አጋዥ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።
ስልጠናው በዶ/ር ዮሐንስ ጴጥሮስ፣ በዶ/ር አራጋው እሸቴ እና በዶ/ር በለጠ ደበበ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 5/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን “ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት” በሚል ርዕስ ለፕላንና ልማት ዘርፍ አመራሮች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ድኤታ ክብርት ጥሩማር አባተ ሙስና የአንድን አገር መልካም አስተዳደር፣ የኢኮኖሚ እድገት እና የሰብአዊ መብት መከበር በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳ፣ ሐቀኝነትን በማጓደል የሕገወጥነትን ባህሪ የሚያላብስ እና ሀገርን ሊበትን የሚችል አለምአቀፋዊ ወንጀል ነው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ሙስና በዓለም አቀፍ፣ በአህጉር አቀፍ እና በሀገር ደረጃ እያስከተለ ያለው ችግር በጣም ከባድና ውስብስብ እየሆነ መምጣቱን አመላክተዋል።
እንደ መንግስትም ሙስና የሚያስከትለውን የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ በመረዳት ችግሩ የከፋ ደረጃ ላይ ከመድረሱ በፊት በርካታ አሰራርና ህጎችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ሚንስትር ዴኤታዋ አክለውም ሁላችንም ብልሹ አሠራርን ለመታገል ከኔ በላይ ማንም የለም በሚል ስሜት ንቅናቄውን መቀላቀልና ከሌሎች በተሻለና ከፍ ባለ ሁኔታ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ለሀገር ዕድገትና ለህዝቦች ተጠቃሚነት ፀር የሆነውን ሙስና በጋራ መከላከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ ስልጠናው ሲሰጥ የነበረው የሙስና ምንነት፣ አስፈላጊነትና መከላከያ ዘዴዎች መሆኑን አስታውሰው፥ አሁን ግን ዘርፍ ተኮር አሰራርን በመከተል በዘርፋ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ዳሰሳ ጥናት መነሻነት የሚሰጥ ስልጠና ነው ብለዋል።
ለዚህም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተወጣጡ ሙሁራን በተዘጋጁ የማሰልጠኛ ሞጅሎች የሚሰጥ የአቅም ግንባታ ስልጠና መሆኑንም ጠቁመዋል።
ስልጠናው በመጀመሪያው ዙር ለዘርፋ አመራሮች የሚሰጥ መሆኑን ገልፀው፥ በቀጣይም በየደረጃው ለሚገኙ መካከለኛ አመራሮችና ሠራተኞች የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም አንድ ተቋም ውጤታማ የሚሆነው የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በሥነምግባር አርዓያ ሲሆኑ መሆኑን ገልፀው፥ ለዚህም አመራሩ የተሰጣቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።
በዘርፋ የብልሹ አሰራር ችግሮች ሲኖሩም ችግር ፈጣሪዎችን ተጠያቂ በማድረግ ለፀረ-ሙስና ትግሉ አጋዥ መሆን ያስፈልጋል ብለዋል።
ስልጠናው በዶ/ር ዮሐንስ ጴጥሮስ፣ በዶ/ር አራጋው እሸቴ እና በዶ/ር በለጠ ደበበ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ለፀረ-ሙስና ትግል ሁሉም ሊያግዝ እንደሚገባ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ አሳሰቡ
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ብልሹ አሠራርን እና ሙስናን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበራት ጋር በጥምረት ለመሥራት ሥምምነት ተፈራርሟል።
በሥነሥርዓቱ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በምክትል ርዕሰ መሥተዳደር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አሥተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኀላፊ ሙሉነሽ ደሴን (ዶ/ር) ጨምሮ የክልል ቢሮ ኀላፊዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሲቪክ ተቋማት እና የሙያ ማኅበራት ተገኝተዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች መካከል አንዱ የሕዝብ ሀብት እና ንብረት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሥነምግባርን በተከተለ መልኩ ሙስናን የመከላከል ሥራን መሥራት መኾኑን አንስተዋል።
ተጠያቂነትን አሠራር እንዲሰፍን ለተቋማት ግብዓት ማቅረብንም ጨምረዋል። ለምክር ቤቶች የጠራ መረጃ በማቅረብ እንዲታገሉበትና የሕዝብ ውክልናቸውንም እንዲወጡ እያደረገ መምጣቱንም አክለዋል።
የጥምረቱ መመሥረት ምክንያትም ተቋማት ከተናጠል ከሚሠሩት በተጨማሪ ኀላፊነታቸውን በጋራ በመሥራት የሙስናን ትግል ለማጠናከር እንደኾነም ነው አፈ ጉባኤዋ የገለጹት። ኮሚሽኑ ጥምረቱን ለማቋቋም የሕግ መሠረት እንዳለውም ጠቅሰዋል።
በሥነምግባር ግንባታ ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ በመፍጠር በኩል የሃይማኖት አባቶች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሙያ ማኅበራት እና ሌሎቹም ትልቅ ኀላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሥነምግባርን ከመገንባት አኳያ የሃይማኖት ተቋማት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰዋል።
ኅብረተሰቡ ከተራ አገልግሎት ጀምሮ ለማንኛውም አገልግሎት ክፍያ እየተጠየቀ መኾኑን ያነሱት ዋና አፈ ጉባኤዋ ችገሩን ለመቀነስ ከጥምረቱ መቋቋም በኋላ በሚቀመጡ አሠራሮች አማካይነት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን በመገንዘብ ሁሉም የአቅሙን ማበርከት እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል።
በየተቋማቱ ከእቅድ ጀምሮ ትኩረት በመስጠት የመሥራት ጅምር ቢኖርም ውጤቱ የሚጠበቀውን ያህል አይደለም። ይህንን ችግር ለመፍታት የጥምረቱ መመሥረት ታምኖበታል ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
የሥነምግባር ግንባታውን በየተቋማቱ በመሥራት በትውልድ ላይ የሚሠራውን ሥራ ለማጠናከር ነው። ተቋማት ይህንን ሥራ ለመሥራት የሚያጋጥመውን ችግር በጋራ እየገመገምን የመንግሥት እና የሕዝብ ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥረት ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
የጥምረቱ መቋቋም ግብ የፀረ-ሙስና ትግሉ በተገቢው ተመርቶ ሕዝብ ተገቢ አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ኹኔታ ለመፍጠር ነው። ለዚህም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አደራ ብለዋል ዋና አፈ ጉባኤዋ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ብልሹ አሠራርን እና ሙስናን ለመከላከል ከሚመለከታቸው ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበራት ጋር በጥምረት ለመሥራት ሥምምነት ተፈራርሟል።
በሥነሥርዓቱ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በምክትል ርዕሰ መሥተዳደር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አሥተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኀላፊ ሙሉነሽ ደሴን (ዶ/ር) ጨምሮ የክልል ቢሮ ኀላፊዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሲቪክ ተቋማት እና የሙያ ማኅበራት ተገኝተዋል።
የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከተቋቋመባቸው ዓላማዎች መካከል አንዱ የሕዝብ ሀብት እና ንብረት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ሥነምግባርን በተከተለ መልኩ ሙስናን የመከላከል ሥራን መሥራት መኾኑን አንስተዋል።
ተጠያቂነትን አሠራር እንዲሰፍን ለተቋማት ግብዓት ማቅረብንም ጨምረዋል። ለምክር ቤቶች የጠራ መረጃ በማቅረብ እንዲታገሉበትና የሕዝብ ውክልናቸውንም እንዲወጡ እያደረገ መምጣቱንም አክለዋል።
የጥምረቱ መመሥረት ምክንያትም ተቋማት ከተናጠል ከሚሠሩት በተጨማሪ ኀላፊነታቸውን በጋራ በመሥራት የሙስናን ትግል ለማጠናከር እንደኾነም ነው አፈ ጉባኤዋ የገለጹት። ኮሚሽኑ ጥምረቱን ለማቋቋም የሕግ መሠረት እንዳለውም ጠቅሰዋል።
በሥነምግባር ግንባታ ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ በመፍጠር በኩል የሃይማኖት አባቶች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የሚዲያ ተቋማት፣ የሙያ ማኅበራት እና ሌሎቹም ትልቅ ኀላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሥነምግባርን ከመገንባት አኳያ የሃይማኖት ተቋማት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ጠቅሰዋል።
ኅብረተሰቡ ከተራ አገልግሎት ጀምሮ ለማንኛውም አገልግሎት ክፍያ እየተጠየቀ መኾኑን ያነሱት ዋና አፈ ጉባኤዋ ችገሩን ለመቀነስ ከጥምረቱ መቋቋም በኋላ በሚቀመጡ አሠራሮች አማካይነት እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን በመገንዘብ ሁሉም የአቅሙን ማበርከት እንደሚጠበቅበት ገልጸዋል።
በየተቋማቱ ከእቅድ ጀምሮ ትኩረት በመስጠት የመሥራት ጅምር ቢኖርም ውጤቱ የሚጠበቀውን ያህል አይደለም። ይህንን ችግር ለመፍታት የጥምረቱ መመሥረት ታምኖበታል ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል።
የሥነምግባር ግንባታውን በየተቋማቱ በመሥራት በትውልድ ላይ የሚሠራውን ሥራ ለማጠናከር ነው። ተቋማት ይህንን ሥራ ለመሥራት የሚያጋጥመውን ችግር በጋራ እየገመገምን የመንግሥት እና የሕዝብ ሀብት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ጥረት ማድረግ ይጠበቃል ብለዋል።
የጥምረቱ መቋቋም ግብ የፀረ-ሙስና ትግሉ በተገቢው ተመርቶ ሕዝብ ተገቢ አገልግሎት እንዲያገኝ ምቹ ኹኔታ ለመፍጠር ነው። ለዚህም ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አደራ ብለዋል ዋና አፈ ጉባኤዋ።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የከተማና መሠረተልማት ዘርፍ ግዙፍ በጀት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ አመራሩ በላቀ ሥነምግባር መምራት እንደሚጠበቅበት ተገለፀ
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም፣ አለም ገና) ለከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማት ተልዕኮ ስኬት!" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በመድረኩ ዘርፉን ወክለው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ኢ/ር) የከተማና መሠረተልማት ዘርፍ በሀገር ደረጃ ግዙፍ የመንግስት እና የህዝብ ሀብት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ አመራሩ የላቀ ሥነምግባር ተላብሶ መምራት እንዳለበት አሳስበዋል።
የተበላሸ የአዕምሮ ውቅር ለብልሹ አሰራሮች መነሻ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፥ ችግሩን ለመቅረፍ የሥነምግባር ግንዛቤ ማሳደግና ሥልጠና ማስፋት አንዱ መሣሪያ መሆኑን አንስተዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው የፀረ-ሙስና ትግሉን ዘርፍ ተኮር በማድረግ ዘርፎች የፀረ-ሙስና ትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም ዘርፍ ተኮር አሠራር ከጥናት ጀምሮ መካሂዱን በመጠቆም፥ ጥናቱን መሠረት ያደረጉ የሥልጠና ሞጁሎች በዩኒቨርሲቲ ምሁራን በማዘጋጀት ሥልጠና መሠጠት መጀመሩን ጠቅሠዋል።
በተጀመረው ሥልጠና የአመራር ሥነምግባር በመገንባት በዘርፍ ተቋማት ለፀረ-ሙስና ትግል አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጠር ገልፀዋል።
ስልጠናው በዩኒቨርስቲ ምሁራን እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
***
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ታህሳስ 8/2017 ዓ.ም፣ አለም ገና) ለከተማና መሠረተ ልማት ዘርፍ አመራሮች "ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማት ተልዕኮ ስኬት!" በሚል መሪ ቃል ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በመድረኩ ዘርፉን ወክለው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ነገዎ (ኢ/ር) የከተማና መሠረተልማት ዘርፍ በሀገር ደረጃ ግዙፍ የመንግስት እና የህዝብ ሀብት የሚንቀሳቀስበት በመሆኑ አመራሩ የላቀ ሥነምግባር ተላብሶ መምራት እንዳለበት አሳስበዋል።
የተበላሸ የአዕምሮ ውቅር ለብልሹ አሰራሮች መነሻ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፥ ችግሩን ለመቅረፍ የሥነምግባር ግንዛቤ ማሳደግና ሥልጠና ማስፋት አንዱ መሣሪያ መሆኑን አንስተዋል።
የኮሚሽኑ የሥነምግባር ግንባታ ዘርፍ ም/ኮሚሽነር ክቡር ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው የፀረ-ሙስና ትግሉን ዘርፍ ተኮር በማድረግ ዘርፎች የፀረ-ሙስና ትግሉ ባለቤት እንዲሆኑ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል።
ም/ኮሚሽነሩ አክለውም ዘርፍ ተኮር አሠራር ከጥናት ጀምሮ መካሂዱን በመጠቆም፥ ጥናቱን መሠረት ያደረጉ የሥልጠና ሞጁሎች በዩኒቨርሲቲ ምሁራን በማዘጋጀት ሥልጠና መሠጠት መጀመሩን ጠቅሠዋል።
በተጀመረው ሥልጠና የአመራር ሥነምግባር በመገንባት በዘርፍ ተቋማት ለፀረ-ሙስና ትግል አመቺ ሁኔታ እንደሚፈጠር ገልፀዋል።
ስልጠናው በዩኒቨርስቲ ምሁራን እየተሰጠ ሲሆን፥ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319