21ኛዉ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በጅግጅጋ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 29/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) 21ኛዉ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በጅግጅጋ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች መከበሩ ተገልጿል።
በመርሀግብሩ ላይ የተገኙት የሶማሊ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አብዲወሊ ጃማ ኮሚሽኑ ከለዉጡ ወዲህ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ሙስናን በመከላከል ረገድ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሰፊ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል።
ኮሚሽነሩ አክለዉም ኮሚሽኑ በባለፈዉ አመት ያስጀመረውን የመንግስት ሰራተኞችና አመራሮች የሀብት ምዝገባ በ2017 በጀት ዓመት አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ጠቁመው፥ ይህንን እንቅስቃሴ በክልል፣ ዞን እና ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ሙስና በሀገር ልማትና እድገት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ የሚያስከትል በመሆኑ በክልሉ ሙስና እና ብልሹ አራሮችን ለማስወገድ ኮሚሽኑ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ወጣቱን አሳታፊ ባደረገ መልኩ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ በቀረበው የመወያያ ሰነድ ላይ ተመላክቷል።
በመርሀግብሩ ላይ የሶማሊ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዋና እና ምክትል ኮሚሽነሮችን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ሴቶች እና ወጣቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል ።
በጅግጅጋ ከተማ የተከበረዉ 21ኛዉ አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በተመሳሳይ በክልሉ ቢሮዎች፣ በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች መከበሩን የሶማሊ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 29/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) 21ኛዉ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በጅግጅጋ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች መከበሩ ተገልጿል።
በመርሀግብሩ ላይ የተገኙት የሶማሊ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አብዲወሊ ጃማ ኮሚሽኑ ከለዉጡ ወዲህ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ሙስናን በመከላከል ረገድ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ሰፊ ስራዎችን ማከናወኑን ተናግረዋል።
ኮሚሽነሩ አክለዉም ኮሚሽኑ በባለፈዉ አመት ያስጀመረውን የመንግስት ሰራተኞችና አመራሮች የሀብት ምዝገባ በ2017 በጀት ዓመት አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ጠቁመው፥ ይህንን እንቅስቃሴ በክልል፣ ዞን እና ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
ሙስና በሀገር ልማትና እድገት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ የሚያስከትል በመሆኑ በክልሉ ሙስና እና ብልሹ አራሮችን ለማስወገድ ኮሚሽኑ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ወጣቱን አሳታፊ ባደረገ መልኩ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ በቀረበው የመወያያ ሰነድ ላይ ተመላክቷል።
በመርሀግብሩ ላይ የሶማሊ ክልል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዋና እና ምክትል ኮሚሽነሮችን ጨምሮ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ሴቶች እና ወጣቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል ።
በጅግጅጋ ከተማ የተከበረዉ 21ኛዉ አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በተመሳሳይ በክልሉ ቢሮዎች፣ በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች መከበሩን የሶማሊ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በሐረሪ ክልል የመንግስትና የህዝብ ጥቅም ለማስጠበቅ ውጤታማ ስራ ተከናውኗል
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 29/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በሐረሪ ክልል ባለፉት አምስት አመታት የመንግስትና የህዝብ ጥቅም ለማስጠበቅ ውጤታማ ስራ መከናወኑን የሐረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ።
በክልሉ ሙስናን ጨምሮ የተፈፀሙ የተለያዩ ወንጀሎችን በማጣራት 7,493 በሚሆኑ መዝገቦች ላይ የወንጀል ክስ ለፍ/ቤት በማቅረብ አጥፊዎች በወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉን የሀረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አዩብ አህመድ ገልጸዋል።
በዚህም ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት የፍትህ ሥርዓትን ለመገንባት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የተለያዩ ወንጀሎችን በማጣራት አጥፊዎችን በፍርድ ቤት ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉን ጠቁመው፥ በክልል ደረጃ የወንጀል መዝገብ የማስቀጣት ምጠኔ 95 በመቶ ማድረስ እንደተቻለ ተናግረዋል።
በተጨማሪ በክልሉ ክሪምስ (CRIMS) የሚባል ዘመናዊ የወንጀል ምርመራ እና ምዝገባ ስርዓት መገንባት ተችሏል ብለዋል።
ለዚህም በክልሉ ሙስናን ጨምሮ የተፈፀሙ የተለያዩ ወንጀሎችን በማጣራት 7493 በሚሆኑ መዝገቦች ላይ የወንጀል ክስ በማቅረብ አጥፊዎች በወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉን ገልጸዋል።
ባለፉት አምስት አመታት መንግስት ሊያጣው የነበረን 231 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር ለመንግሰት ገቢ እንዲሆን መደረጉን ጠቁመዋል።
በክልሉ ህገወጥ የሰነድ ዝግጅትን ለመከላከል እና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንፃርም 51 ሺህ 418 ሰነዶችን የማረጋገጥ ስራ እንደተከናወነ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 29/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በሐረሪ ክልል ባለፉት አምስት አመታት የመንግስትና የህዝብ ጥቅም ለማስጠበቅ ውጤታማ ስራ መከናወኑን የሐረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ።
በክልሉ ሙስናን ጨምሮ የተፈፀሙ የተለያዩ ወንጀሎችን በማጣራት 7,493 በሚሆኑ መዝገቦች ላይ የወንጀል ክስ ለፍ/ቤት በማቅረብ አጥፊዎች በወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉን የሀረሪ ክልል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አዩብ አህመድ ገልጸዋል።
በዚህም ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት የፍትህ ሥርዓትን ለመገንባት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
የተለያዩ ወንጀሎችን በማጣራት አጥፊዎችን በፍርድ ቤት ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉን ጠቁመው፥ በክልል ደረጃ የወንጀል መዝገብ የማስቀጣት ምጠኔ 95 በመቶ ማድረስ እንደተቻለ ተናግረዋል።
በተጨማሪ በክልሉ ክሪምስ (CRIMS) የሚባል ዘመናዊ የወንጀል ምርመራ እና ምዝገባ ስርዓት መገንባት ተችሏል ብለዋል።
ለዚህም በክልሉ ሙስናን ጨምሮ የተፈፀሙ የተለያዩ ወንጀሎችን በማጣራት 7493 በሚሆኑ መዝገቦች ላይ የወንጀል ክስ በማቅረብ አጥፊዎች በወንጀል ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉን ገልጸዋል።
ባለፉት አምስት አመታት መንግስት ሊያጣው የነበረን 231 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር ለመንግሰት ገቢ እንዲሆን መደረጉን ጠቁመዋል።
በክልሉ ህገወጥ የሰነድ ዝግጅትን ለመከላከል እና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንፃርም 51 ሺህ 418 ሰነዶችን የማረጋገጥ ስራ እንደተከናወነ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የፀረ-ሙስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ በትምህርት ቤት ደረጃ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ አንዳንድ አስተያዬት ሰጪዎች ጠየቁ
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 30/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፀረ-ሙስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ በትምህርት ቤት ደረጃ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በተካሄደው የዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ማጠቃለያ በዓል ተሳታፊ የነበሩ ተማሪዎች ጠይቀዋል።
በክልሉ አለምዓቀፍ የሙስና ቀን በተከበረበት የተገኙ ተማሪዎች ሙስናን ለመከላከል በትምህርት ቤት ደረጃ በትኩረት ሊሰራበት ይገባል ብለዋል።
ተማሪ በእምነት አትርሳው፣ ተማሪ ኤርሚያስ ቆጭቶና ተማሪ መልካሙ በለጠ ከሸኮ፣ ከጉራፈርዳ እና ከሚዛን አማን ከተማ ካሉት ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ሙስናን ለመከላከል በትምህርት ቤት ደረጃ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
በርካታ ወጣቶች በትምህርት ቤቶች በሚቋቋሙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት በመሳተፍ በሙስና መከላከል ስራ የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በትምህርት ገበታ በሰዓቱ መገኘት፣ ኩረጃን በመጠየፍና ከመምህራን ጋር አባታዊ ግንኙነት በመፍጠር በሙስና መከላከሉ ስራ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ባለሙያ አቶ ገብረዮሐንስ አብርሃ ሙስናን ለመከላከል በትምህርት ቤቶች ክበባትን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
በርካታ ወጣቶች በትምህርት ቤቶች እንደሚገኙ የገለጹት ባለሙያው፣ ተከታታይነት ያለውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በተማሪዎች ላይ መስራት ይገባልም ብለዋል።
በክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ባለሙያ ወ/ሮ ትብለጥ እንግሊዝ ሙስናን ለመከላከል ከትምህርት ቤቶች ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ወጣቶች ለብዙ ነገሮች ተጋላጭ መሆናቸውን የገለጹት ባለሙያዋ፣ ሙስናን በመጠየፍና ተዋናይ ከመሆን ወጣቶች እንዲታቀቡ አመለካከትና አስተሳሰብ ላይ የተጀመረው ስራ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራበት ይገባል ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 30/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የፀረ-ሙስና ትግሉን ውጤታማ ለማድረግ በትምህርት ቤት ደረጃ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በተካሄደው የዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ማጠቃለያ በዓል ተሳታፊ የነበሩ ተማሪዎች ጠይቀዋል።
በክልሉ አለምዓቀፍ የሙስና ቀን በተከበረበት የተገኙ ተማሪዎች ሙስናን ለመከላከል በትምህርት ቤት ደረጃ በትኩረት ሊሰራበት ይገባል ብለዋል።
ተማሪ በእምነት አትርሳው፣ ተማሪ ኤርሚያስ ቆጭቶና ተማሪ መልካሙ በለጠ ከሸኮ፣ ከጉራፈርዳ እና ከሚዛን አማን ከተማ ካሉት ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ሙስናን ለመከላከል በትምህርት ቤት ደረጃ በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
በርካታ ወጣቶች በትምህርት ቤቶች በሚቋቋሙ የሥነምግባርና ፀረ-ሙስና ክበባት በመሳተፍ በሙስና መከላከል ስራ የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በትምህርት ገበታ በሰዓቱ መገኘት፣ ኩረጃን በመጠየፍና ከመምህራን ጋር አባታዊ ግንኙነት በመፍጠር በሙስና መከላከሉ ስራ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ባለሙያ አቶ ገብረዮሐንስ አብርሃ ሙስናን ለመከላከል በትምህርት ቤቶች ክበባትን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።
በርካታ ወጣቶች በትምህርት ቤቶች እንደሚገኙ የገለጹት ባለሙያው፣ ተከታታይነት ያለውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በተማሪዎች ላይ መስራት ይገባልም ብለዋል።
በክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የትምህርትና ስልጠና ባለሙያ ወ/ሮ ትብለጥ እንግሊዝ ሙስናን ለመከላከል ከትምህርት ቤቶች ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ወጣቶች ለብዙ ነገሮች ተጋላጭ መሆናቸውን የገለጹት ባለሙያዋ፣ ሙስናን በመጠየፍና ተዋናይ ከመሆን ወጣቶች እንዲታቀቡ አመለካከትና አስተሳሰብ ላይ የተጀመረው ስራ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራበት ይገባል ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሐሰተኛ የደረሰኝ ህትመትን ለመከላከል ያለመ ስምምነት ተፈረመ
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 30/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ገቢዎች ሚኒስቴር እና ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በደረሠኞች ላይ ልዩ መለያ ኮድ (QR-Code) አካቶ ማተም በሚያስችል አሠራር ላይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ ከታክስ ደረሰኝ ህትመት ጋር በተያያዘ ልዩ መለያ ኮድ ተካቶ ማተም፣ የህትመት ጥያቄ መቀበል፣ ከታተመ በኋላ የስርጭት እና የቁጥጥር ሥርዓትን ማስፈን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት የሚያስችል ነው፡፡
ስምምነቱን የፈረሙት የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ የሐሰተኛ ደረሰኝ ህትመት በግብር አሰባበሰቡ ላይ ፈተና ሆኖ መቆየቱን ገልጸው÷ ይህን ችግር ለመፍታት ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት ስምምነቱ መፈረሙን አስረድተዋል፡፡
የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሽታሁን ዋለ ድርጅታቸው ሚስጥራዊ ህትመቶችን በማተም የካበት ልምድ እንዳለው ጠቅሰው÷ ደረጃውን የጠበቀ፣ ልዩ መለያ ኮድ (unique QR code) የተካተተበት እና አስመስሎ መስራት በማይቻል መልኩ የህትመት ሥራውን ለማከናወን ዝግጅት ማድረጉን መግለፃቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡
ግብር ከፋዮች ለገቢዎች ሚኒስቴር በሚያቀርቡት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ መሠረት የሚቀርቡ የህትምት ትዕዛዞችን ተቀብሎ ደረሰኞችን ለማተም በቂ ዝግጅት ማድረጉንም አንስተዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 30/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) ገቢዎች ሚኒስቴር እና ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በደረሠኞች ላይ ልዩ መለያ ኮድ (QR-Code) አካቶ ማተም በሚያስችል አሠራር ላይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱ ከታክስ ደረሰኝ ህትመት ጋር በተያያዘ ልዩ መለያ ኮድ ተካቶ ማተም፣ የህትመት ጥያቄ መቀበል፣ ከታተመ በኋላ የስርጭት እና የቁጥጥር ሥርዓትን ማስፈን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት የሚያስችል ነው፡፡
ስምምነቱን የፈረሙት የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ የሐሰተኛ ደረሰኝ ህትመት በግብር አሰባበሰቡ ላይ ፈተና ሆኖ መቆየቱን ገልጸው÷ ይህን ችግር ለመፍታት ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት ስምምነቱ መፈረሙን አስረድተዋል፡፡
የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሽታሁን ዋለ ድርጅታቸው ሚስጥራዊ ህትመቶችን በማተም የካበት ልምድ እንዳለው ጠቅሰው÷ ደረጃውን የጠበቀ፣ ልዩ መለያ ኮድ (unique QR code) የተካተተበት እና አስመስሎ መስራት በማይቻል መልኩ የህትመት ሥራውን ለማከናወን ዝግጅት ማድረጉን መግለፃቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡
ግብር ከፋዮች ለገቢዎች ሚኒስቴር በሚያቀርቡት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ መሠረት የሚቀርቡ የህትምት ትዕዛዞችን ተቀብሎ ደረሰኞችን ለማተም በቂ ዝግጅት ማድረጉንም አንስተዋል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319