ሙስና የኢኮኖሚ ብልሽትን፣ የባህል ስብራትን እና የፖለቲካ ዝቅጠትን ያመጣል - አቶ ብርሃኑ ጎሽም
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 28/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች ለ21ኛ ጊዜ "ወጣቶችን ያመከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በባህርዳር ከተማ በፓናል ውይይት አክብረዋል።
የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽም በመክፈቻ ንግግራቸው ባስተላለፉት መልዕክት ይህንን ቀን ስናከብር በዋናነት ሙስናን የሚጠላ ትውልድ ለመፍጠር፣ የሙስና አስከፊነትን ለመረዳት እና ወንጀሉን ለመከላከል የጋራ ግንዛቤ ለመያዝ ነው ብለዋል።
ሙስና ከህግ ውጭ በመስራት ራስን ወይም ሌላውን መጥቀም ሲሆን፣ መንስኤዎቹ የሥነምግባር ዝቅጠትና ብልሽት ቢሆኑም ትልቁና ዋነኛው መንስኤ ግን የስብዕና መጓደል እንደሆነ አብራርተዋል።
አቶ ብርሃኑ አክለውም የሰላምና የፖለቲካ አለመረጋት እና የኢኮኖሚ ዝቅተኛነት ሙስናን ከሚያባብሱ ጉዳዮች መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ሙስና የኢኮኖሚ ብልሽትን፣ የባህል ወለምታን እና የፖለቲካ ዝቅጠትን እንደሚያመጣ ገልፀው፥ የፀረ-ሙስና ትግላችን በመልካም መንገድ የሚሰራ ከሆነ ኢኮኖሚያችንና ባህላችን ያድጋል፣ ፖለቲካችንም የተረጋጋና ሁሉንም የሚያሻግር ይሆናል ብለዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ሙስናን ከመከላከል አኳያ ከሁሉም በፊት እኛ ራሳችን ንፁህ መሆን ይጠበቅብናል ብለው፥ የተጠያቂነትን ሚና በመወጣት የህዝብና የመንግስትን ሀብት ለታለመለት አላማ ለማዋል ሁሉም አካል የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አያሌው አባተ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለመጭው ትውልድ ከወንጀል ነፃ እና የበለፀገች ሀገርን ለማስተላለፍ ከሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ራስን ንፁህ አድርጎ በሥነምግባር አርአያ ሆኖ መገኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀኑን አስመልክቶ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ በበዓሉ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መገኘታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 28/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች ለ21ኛ ጊዜ "ወጣቶችን ያመከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በባህርዳር ከተማ በፓናል ውይይት አክብረዋል።
የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ጎሽም በመክፈቻ ንግግራቸው ባስተላለፉት መልዕክት ይህንን ቀን ስናከብር በዋናነት ሙስናን የሚጠላ ትውልድ ለመፍጠር፣ የሙስና አስከፊነትን ለመረዳት እና ወንጀሉን ለመከላከል የጋራ ግንዛቤ ለመያዝ ነው ብለዋል።
ሙስና ከህግ ውጭ በመስራት ራስን ወይም ሌላውን መጥቀም ሲሆን፣ መንስኤዎቹ የሥነምግባር ዝቅጠትና ብልሽት ቢሆኑም ትልቁና ዋነኛው መንስኤ ግን የስብዕና መጓደል እንደሆነ አብራርተዋል።
አቶ ብርሃኑ አክለውም የሰላምና የፖለቲካ አለመረጋት እና የኢኮኖሚ ዝቅተኛነት ሙስናን ከሚያባብሱ ጉዳዮች መካከል የሚጠቀሱ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ሙስና የኢኮኖሚ ብልሽትን፣ የባህል ወለምታን እና የፖለቲካ ዝቅጠትን እንደሚያመጣ ገልፀው፥ የፀረ-ሙስና ትግላችን በመልካም መንገድ የሚሰራ ከሆነ ኢኮኖሚያችንና ባህላችን ያድጋል፣ ፖለቲካችንም የተረጋጋና ሁሉንም የሚያሻግር ይሆናል ብለዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ሙስናን ከመከላከል አኳያ ከሁሉም በፊት እኛ ራሳችን ንፁህ መሆን ይጠበቅብናል ብለው፥ የተጠያቂነትን ሚና በመወጣት የህዝብና የመንግስትን ሀብት ለታለመለት አላማ ለማዋል ሁሉም አካል የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አያሌው አባተ (ዶ/ር) በበኩላቸው ለመጭው ትውልድ ከወንጀል ነፃ እና የበለፀገች ሀገርን ለማስተላለፍ ከሙስና እና ብልሹ አሰራሮች ራስን ንፁህ አድርጎ በሥነምግባር አርአያ ሆኖ መገኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀኑን አስመልክቶ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፣ በበዓሉ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መገኘታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በየደረጃው የሚገኙ የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አመራሮችና ሠራተኞች የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበሩ ይገኛል
**
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 28/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በየደረጃው የሚገኙ የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አመራሮችና ሠራተኞች 21ኛውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበሩ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በዓሉን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፤ የነገን ስብዕና ይገነባል!” በሚል መሪ ቃል የአብጅታ ሻላ ሀይቆች፣ የባሌ ተራራዎች፣ የአልጣሽ እና የሰሜን ተራራዎች ብሄራዊ ፓርክ ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበራቸውን ከባለስልጣኑ የማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
**
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 28/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በየደረጃው የሚገኙ የኢትዮጵያ የዱር እንሰሳት ጥበቃ ባለስልጣን አመራሮችና ሠራተኞች 21ኛውን አለምዓቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበሩ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በዓሉን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፤ የነገን ስብዕና ይገነባል!” በሚል መሪ ቃል የአብጅታ ሻላ ሀይቆች፣ የባሌ ተራራዎች፣ የአልጣሽ እና የሰሜን ተራራዎች ብሄራዊ ፓርክ ጽ/ቤት አመራሮች እና ሠራተኞች በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበራቸውን ከባለስልጣኑ የማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
በጤናው ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮችን ለመቀነስ የሥነምግባር ግንባታ ስልጠና አስፈላጊ ነው - ሚኒስትር ዴኤታ ደረጀ ድጉማ (ዶ/ር)
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 28/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚኒስቴሩ እና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
በመድረኩ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ደረጀ ድጉማ (ዶ/ር) በጤናው ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮችን ለመቀነስ የሥነምግባር ግንባታ ስልጠና አስፈላጊ ነው ብለዋል። በቀጣይም ስልጠና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና ሠራተኞች እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች የሠውን ህይወት የሚጎዱ መሆኑን ገልፀው፥ በተለይ የመድሃኒት አቅርቦት ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ማስወገድ ያስፈልጋል ብለዋል። ስለሆነም ለማህበረሰባችን የምንሰጠው አገልግሎት ከብልሹ አሰራር የፀዳ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በጤና ተቋማት የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መከላከል እንደሚያስፈልግ ጠቁመው፥ ካልሆነ ግን ችግሮች ተባብሰው ትውልዱን ይጎዳል ብለዋል። ችግሩን ለመቅረፍ በጤና ሴክተሩ የዲጂታል አሰራርን በመከተል ብልሹ አሰራርን መከላከል እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ኮሚሽኑ የሚሰጣቸው የሥነምግባር ግንባታ ስልጠናዎች በዘርፋ የተደረጉ የዳሰሳ ጥናቶችን መሠረት በማድረግ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተመረጡ ከፍተኛ ሙሁራን የማሰልጠኛ ሞጅሎችን በማዘጋጀት ዘርፍ ተኮር ስልጠናውን እየሰጠን እንገኛለን ብለዋል።
አቶ ፍቃዱ አክለውም የሀገራችንን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ እንቅፋት የሆነውን ሙስና ለመከላከል መንግስት ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፥ በትውልድ የሥነምግባር ግንባታ ላይም ትኩረት አድርገን መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ ለዚህም ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከፍትህ ሚኒስቴር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
ለጤና ዘርፍ አመራሮች ለሁለት ቀናት የተሰጠውን ስልጠና በበቃና ፈኬቻ (ዶ/ር) የተሰጠ ሲሆን፥ በቀጣይም ለሌሎች ዘርፎች ስልጠናው የሚሰጥ ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*******
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 28/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሚኒስቴሩ እና ለተጠሪ ተቋማት አመራሮች ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
በመድረኩ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ደረጀ ድጉማ (ዶ/ር) በጤናው ዘርፍ የሚስተዋሉ የሙስና እና ብልሹ አሰራር ችግሮችን ለመቀነስ የሥነምግባር ግንባታ ስልጠና አስፈላጊ ነው ብለዋል። በቀጣይም ስልጠና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮችና ሠራተኞች እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች የሠውን ህይወት የሚጎዱ መሆኑን ገልፀው፥ በተለይ የመድሃኒት አቅርቦት ላይ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ማስወገድ ያስፈልጋል ብለዋል። ስለሆነም ለማህበረሰባችን የምንሰጠው አገልግሎት ከብልሹ አሰራር የፀዳ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በጤና ተቋማት የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በጋራ መከላከል እንደሚያስፈልግ ጠቁመው፥ ካልሆነ ግን ችግሮች ተባብሰው ትውልዱን ይጎዳል ብለዋል። ችግሩን ለመቅረፍ በጤና ሴክተሩ የዲጂታል አሰራርን በመከተል ብልሹ አሰራርን መከላከል እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።
የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ በበኩላቸው ኮሚሽኑ የሚሰጣቸው የሥነምግባር ግንባታ ስልጠናዎች በዘርፋ የተደረጉ የዳሰሳ ጥናቶችን መሠረት በማድረግ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተመረጡ ከፍተኛ ሙሁራን የማሰልጠኛ ሞጅሎችን በማዘጋጀት ዘርፍ ተኮር ስልጠናውን እየሰጠን እንገኛለን ብለዋል።
አቶ ፍቃዱ አክለውም የሀገራችንን የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ እንቅፋት የሆነውን ሙስና ለመከላከል መንግስት ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፥ በትውልድ የሥነምግባር ግንባታ ላይም ትኩረት አድርገን መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀው፥ ለዚህም ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከፍትህ ሚኒስቴር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
ለጤና ዘርፍ አመራሮች ለሁለት ቀናት የተሰጠውን ስልጠና በበቃና ፈኬቻ (ዶ/ር) የተሰጠ ሲሆን፥ በቀጣይም ለሌሎች ዘርፎች ስልጠናው የሚሰጥ ይሆናል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319