ሙስና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የህይወታችን ዘርፎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር የሞራል ፈተና ነው - ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ
******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 21ኛው ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል በሚዛን አማን ከተማ በተለያዩ ሁነቶች በመከበር ላይ ይገኛል።
በበዓሉ ንግግር ያደረጉት የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ የበዓሉ መከበር አስተሳሰቦቻችን ሙስናን በወሳኝ መልኩ ሊያርም በሚችል ወጣቱን ባለቤት በማድረግ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ቀኑ በሁሉም መልክ ሙስናን ለመዋጋት እና በህብረተሰቡ ውስጥ ታማኝነትን ለማጎልበት ያለን የጋራ ኃላፊነት ጠንካራ ማስታወሻ ሆኖ ያገልግላል ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉሰው ተናግረዋል።
ሙስና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ በሁሉም የህይወታችን ዘርፎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር የሞራል ፈተና ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ዛሬ እዚህ በምንሰበሰብበት ወቅት እያንዳንዳችሁ በተለይም ወጣቶች አቅማችሁን እንደ የለውጥ ፈላጊዎች እንድትገነዝቡ እጠይቃለሁ ሲሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና በአስተዳደር ሂደቶች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ እኩዮቻችሁንና ማህበረሰቡ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ የማድረግ ችሎታ አላችሁ፣ ሙስናን በጋራ በመቆም፣ ታማኝነት ከምንም በላይ የሚከበርበትን የወደፊት ጊዜ ለመቅረጽ መርዳት ትችላላችሁ ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉ ሰው ዘውዴ ለወጣቶች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሙስና በጉቦ፣ ገንዘብ በማጭበርበር፣ ወገንተኝነት እና ስልጣንን አለአግባብ መጠቀም ከመገለጫዎቹ ጥቂቶች መሆናቸውን ያስታወሱት ኮሚሽነር ሙሉሰው፣ እነዚህ ተግባራት ተቋማትን ያዳክማል፣ የኢኮኖሚ ልማትን ያቀዘቅዛል፣ ለመንግስታዊ አለመረጋጋት አስተዋጽኦ ያደርጋል፣ በህብረተሰቡ ውስጥ በጣም ተጋላጭ የሆኑትን እንደሚጎዳም ገልጸዋል።
ሙስናን ለመዋጋት በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራትን የሚጠይቅ ተግባር መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ኃላፊነት ለሚሰማው ዜግነት ማዘጋጀት እንዳለባቸው አመላክተዋል።
የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ማህበረሰቡን በሥነምግባር አስተምህሮዎች ላይ የተመሰረተ ታማኝነትና ሙስና የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በመረዳት ትውልዱ ላይ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎች፣ በሥነግጥም፣ በድራማ፣ በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር እየተከበረ ሲሆን፣ ዕለቱን የተመለከተ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በቴክኖሎጂ የታገዘ ዌብሳይት አልምቶ ስራ ላይ ማዋሉንም በዕለቱ ገለጻና ማብራሪያ በአቶ ሙባረክ አበበ መቅረቡን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
በበዓሉ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ቡድን አስተባባሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 21ኛው ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል በሚዛን አማን ከተማ በተለያዩ ሁነቶች በመከበር ላይ ይገኛል።
በበዓሉ ንግግር ያደረጉት የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ የበዓሉ መከበር አስተሳሰቦቻችን ሙስናን በወሳኝ መልኩ ሊያርም በሚችል ወጣቱን ባለቤት በማድረግ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ቀኑ በሁሉም መልክ ሙስናን ለመዋጋት እና በህብረተሰቡ ውስጥ ታማኝነትን ለማጎልበት ያለን የጋራ ኃላፊነት ጠንካራ ማስታወሻ ሆኖ ያገልግላል ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉሰው ተናግረዋል።
ሙስና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ በሁሉም የህይወታችን ዘርፎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር የሞራል ፈተና ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ዛሬ እዚህ በምንሰበሰብበት ወቅት እያንዳንዳችሁ በተለይም ወጣቶች አቅማችሁን እንደ የለውጥ ፈላጊዎች እንድትገነዝቡ እጠይቃለሁ ሲሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና በአስተዳደር ሂደቶች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ እኩዮቻችሁንና ማህበረሰቡ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ የማድረግ ችሎታ አላችሁ፣ ሙስናን በጋራ በመቆም፣ ታማኝነት ከምንም በላይ የሚከበርበትን የወደፊት ጊዜ ለመቅረጽ መርዳት ትችላላችሁ ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉ ሰው ዘውዴ ለወጣቶች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሙስና በጉቦ፣ ገንዘብ በማጭበርበር፣ ወገንተኝነት እና ስልጣንን አለአግባብ መጠቀም ከመገለጫዎቹ ጥቂቶች መሆናቸውን ያስታወሱት ኮሚሽነር ሙሉሰው፣ እነዚህ ተግባራት ተቋማትን ያዳክማል፣ የኢኮኖሚ ልማትን ያቀዘቅዛል፣ ለመንግስታዊ አለመረጋጋት አስተዋጽኦ ያደርጋል፣ በህብረተሰቡ ውስጥ በጣም ተጋላጭ የሆኑትን እንደሚጎዳም ገልጸዋል።
ሙስናን ለመዋጋት በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራትን የሚጠይቅ ተግባር መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ኃላፊነት ለሚሰማው ዜግነት ማዘጋጀት እንዳለባቸው አመላክተዋል።
የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ማህበረሰቡን በሥነምግባር አስተምህሮዎች ላይ የተመሰረተ ታማኝነትና ሙስና የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በመረዳት ትውልዱ ላይ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎች፣ በሥነግጥም፣ በድራማ፣ በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር እየተከበረ ሲሆን፣ ዕለቱን የተመለከተ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በቴክኖሎጂ የታገዘ ዌብሳይት አልምቶ ስራ ላይ ማዋሉንም በዕለቱ ገለጻና ማብራሪያ በአቶ ሙባረክ አበበ መቅረቡን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
በበዓሉ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ቡድን አስተባባሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
ሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋም ተልዕኮ ስኬት ወሳኝ ነው - ም/ኮሚሽነር ፍቃዱ ሰቦቃ
*********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለፋይናንስ ዘርፍ አመራሮች ‘‘ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት’’ በሚል ርዕስ በአዳማ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናዉ የተገኙት የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋም ተልዕኮ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፣ ሙስና ለመከላከል ትውልድን የሚገነባ የሥነምግባር ስልጠናዎችን ማብቃት ሲቻል እንደሆነ ጠቁመዋል።
ስልጠናው ሙስና ስጋት ዳሰሳዊ ጥናት ግኝት መነሻ ተደርጎ፣ የብልሹ አሰራር መገለጫዎችና ምልክቶቹን በማየት የሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረቱን ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ አክለውም የፀረ-ሙስና ትግሉን ግንባር ቀደም ሆነን በማስተባበር በተለይም ተቋም ተኮር ችግሮችን ለመፍታት በየዘርፎቹ የሚሰጡ ስልጠናዎች በመውሰድ፣ ከብልሹ አሰራር የፀዳ አመራር እና ሰራተኛን በማብቃት፣ ንቅናቄ በመፍጠር እና በማነፅ ሀገራዊ ግዳታን መወጣት አለበት ብለዋል።
አመራሩ እራሱን ከሙስና እና ብልሹ አሰራር በማራቅ ከመንግስትና ከህዝብ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልኮ መወጣት እንደሚገባ አሳስበው፣ በተቋም ለሚፈጠሩ አስተዳደራዊ ችግሮች በራሱ አቅም እርምጃ የመውሰድ እና የማስወሰድ ግዴታ እንዳለውም ጠቁመዋል።
የሙስና መከላከል ስራው መሰረት እንዲኖረው ለማድረግ 26 ዘርፎች ተለይተው የስነ ምግባር ግንባታ ስልጠናና አቅም መገንቢያ ማሰልጠኛ ሞጅሎች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
በጥቂት ግለሰቦች ብልሹ አሰራር ተቋማት እና የንፁሀን ግለሰቦች ስም መጥፋት እንደሌለበት ገልፀው፣ አመራሩ እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች በትኩረት በመውሰድ ተቋምን እና ሰራተኛውን በሥነምግባር ማብቃት አለበት ብለዋል፡፡
ምክትል ኮሚሽነሩ አያይዘውም የተጀመሩ የሙስና መከላከል ስራዎች በማጠናከር ዘርፉን በግልፅነትና ተጠያቂነት ለመምራት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።
በሙስና መከላከል ሂደት ውስጥ አመራሩና ፈፃሚ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ ስልጠና መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።
ስልጠናው በዶ/ር ሀይለየሱስ ተሰማ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዳማ) የፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለፋይናንስ ዘርፍ አመራሮች ‘‘ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት’’ በሚል ርዕስ በአዳማ ከተማ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በስልጠናዉ የተገኙት የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃሥነምግባራዊ አመራርነት ለተቋም ተልዕኮ ስኬት ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፣ ሙስና ለመከላከል ትውልድን የሚገነባ የሥነምግባር ስልጠናዎችን ማብቃት ሲቻል እንደሆነ ጠቁመዋል።
ስልጠናው ሙስና ስጋት ዳሰሳዊ ጥናት ግኝት መነሻ ተደርጎ፣ የብልሹ አሰራር መገለጫዎችና ምልክቶቹን በማየት የሙስና እና ብልሹ አሰራር መከላከያ ስልቶች ላይ ትኩረቱን ያደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ምክትል ኮሚሽነር ፈቃዱ ሰቦቃ አክለውም የፀረ-ሙስና ትግሉን ግንባር ቀደም ሆነን በማስተባበር በተለይም ተቋም ተኮር ችግሮችን ለመፍታት በየዘርፎቹ የሚሰጡ ስልጠናዎች በመውሰድ፣ ከብልሹ አሰራር የፀዳ አመራር እና ሰራተኛን በማብቃት፣ ንቅናቄ በመፍጠር እና በማነፅ ሀገራዊ ግዳታን መወጣት አለበት ብለዋል።
አመራሩ እራሱን ከሙስና እና ብልሹ አሰራር በማራቅ ከመንግስትና ከህዝብ የተሰጠውን ሀገራዊ ተልኮ መወጣት እንደሚገባ አሳስበው፣ በተቋም ለሚፈጠሩ አስተዳደራዊ ችግሮች በራሱ አቅም እርምጃ የመውሰድ እና የማስወሰድ ግዴታ እንዳለውም ጠቁመዋል።
የሙስና መከላከል ስራው መሰረት እንዲኖረው ለማድረግ 26 ዘርፎች ተለይተው የስነ ምግባር ግንባታ ስልጠናና አቅም መገንቢያ ማሰልጠኛ ሞጅሎች መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
በጥቂት ግለሰቦች ብልሹ አሰራር ተቋማት እና የንፁሀን ግለሰቦች ስም መጥፋት እንደሌለበት ገልፀው፣ አመራሩ እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች በትኩረት በመውሰድ ተቋምን እና ሰራተኛውን በሥነምግባር ማብቃት አለበት ብለዋል፡፡
ምክትል ኮሚሽነሩ አያይዘውም የተጀመሩ የሙስና መከላከል ስራዎች በማጠናከር ዘርፉን በግልፅነትና ተጠያቂነት ለመምራት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።
በሙስና መከላከል ሂደት ውስጥ አመራሩና ፈፃሚ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ ስልጠና መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።
ስልጠናው በዶ/ር ሀይለየሱስ ተሰማ እየተሰጠ ሲሆን፣ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
የአብክመ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ባለስልጣን አመራሮችና ሠራተኞች 21ኛውን ዓለምአቀፍ የፀረ- ሙስና ቀን አከበሩ
*********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአብክመ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ባለስልጣን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት በፓናል ውይይት አከበሩ።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን፣ መድረኩ በተለያዩ ትዕይንቶች በአማረና በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
*********************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) የአብክመ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ባለስልጣን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት በፓናል ውይይት አከበሩ።
በመድረኩ የመወያያ ሰነድ ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን፣ መድረኩ በተለያዩ ትዕይንቶች በአማረና በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319