ሙስና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የህይወታችን ዘርፎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር የሞራል ፈተና ነው - ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ
******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 21ኛው ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል በሚዛን አማን ከተማ በተለያዩ ሁነቶች በመከበር ላይ ይገኛል።
በበዓሉ ንግግር ያደረጉት የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ የበዓሉ መከበር አስተሳሰቦቻችን ሙስናን በወሳኝ መልኩ ሊያርም በሚችል ወጣቱን ባለቤት በማድረግ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ቀኑ በሁሉም መልክ ሙስናን ለመዋጋት እና በህብረተሰቡ ውስጥ ታማኝነትን ለማጎልበት ያለን የጋራ ኃላፊነት ጠንካራ ማስታወሻ ሆኖ ያገልግላል ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉሰው ተናግረዋል።
ሙስና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ በሁሉም የህይወታችን ዘርፎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር የሞራል ፈተና ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ዛሬ እዚህ በምንሰበሰብበት ወቅት እያንዳንዳችሁ በተለይም ወጣቶች አቅማችሁን እንደ የለውጥ ፈላጊዎች እንድትገነዝቡ እጠይቃለሁ ሲሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና በአስተዳደር ሂደቶች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ እኩዮቻችሁንና ማህበረሰቡ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ የማድረግ ችሎታ አላችሁ፣ ሙስናን በጋራ በመቆም፣ ታማኝነት ከምንም በላይ የሚከበርበትን የወደፊት ጊዜ ለመቅረጽ መርዳት ትችላላችሁ ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉ ሰው ዘውዴ ለወጣቶች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሙስና በጉቦ፣ ገንዘብ በማጭበርበር፣ ወገንተኝነት እና ስልጣንን አለአግባብ መጠቀም ከመገለጫዎቹ ጥቂቶች መሆናቸውን ያስታወሱት ኮሚሽነር ሙሉሰው፣ እነዚህ ተግባራት ተቋማትን ያዳክማል፣ የኢኮኖሚ ልማትን ያቀዘቅዛል፣ ለመንግስታዊ አለመረጋጋት አስተዋጽኦ ያደርጋል፣ በህብረተሰቡ ውስጥ በጣም ተጋላጭ የሆኑትን እንደሚጎዳም ገልጸዋል።
ሙስናን ለመዋጋት በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራትን የሚጠይቅ ተግባር መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ኃላፊነት ለሚሰማው ዜግነት ማዘጋጀት እንዳለባቸው አመላክተዋል።
የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ማህበረሰቡን በሥነምግባር አስተምህሮዎች ላይ የተመሰረተ ታማኝነትና ሙስና የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በመረዳት ትውልዱ ላይ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎች፣ በሥነግጥም፣ በድራማ፣ በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር እየተከበረ ሲሆን፣ ዕለቱን የተመለከተ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በቴክኖሎጂ የታገዘ ዌብሳይት አልምቶ ስራ ላይ ማዋሉንም በዕለቱ ገለጻና ማብራሪያ በአቶ ሙባረክ አበበ መቅረቡን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
በበዓሉ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ቡድን አስተባባሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319
******************
(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ህዳር 27/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ 21ኛው ዓለምአቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል፣ የነገን ስብዕና ይገነባል!" በሚል መሪ ቃል በሚዛን አማን ከተማ በተለያዩ ሁነቶች በመከበር ላይ ይገኛል።
በበዓሉ ንግግር ያደረጉት የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ የበዓሉ መከበር አስተሳሰቦቻችን ሙስናን በወሳኝ መልኩ ሊያርም በሚችል ወጣቱን ባለቤት በማድረግ ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ቀኑ በሁሉም መልክ ሙስናን ለመዋጋት እና በህብረተሰቡ ውስጥ ታማኝነትን ለማጎልበት ያለን የጋራ ኃላፊነት ጠንካራ ማስታወሻ ሆኖ ያገልግላል ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉሰው ተናግረዋል።
ሙስና የፖለቲካ ወይም የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ አይደለም፣ በሁሉም የህይወታችን ዘርፎች ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድር የሞራል ፈተና ነው ሲሉም ተናግረዋል።
ዛሬ እዚህ በምንሰበሰብበት ወቅት እያንዳንዳችሁ በተለይም ወጣቶች አቅማችሁን እንደ የለውጥ ፈላጊዎች እንድትገነዝቡ እጠይቃለሁ ሲሉ ገልጸዋል።
በትምህርትና በአስተዳደር ሂደቶች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ እኩዮቻችሁንና ማህበረሰቡ ላይ አዎንታዊ ተጽዕኖ የማድረግ ችሎታ አላችሁ፣ ሙስናን በጋራ በመቆም፣ ታማኝነት ከምንም በላይ የሚከበርበትን የወደፊት ጊዜ ለመቅረጽ መርዳት ትችላላችሁ ሲሉም ኮሚሽነር ሙሉ ሰው ዘውዴ ለወጣቶች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሙስና በጉቦ፣ ገንዘብ በማጭበርበር፣ ወገንተኝነት እና ስልጣንን አለአግባብ መጠቀም ከመገለጫዎቹ ጥቂቶች መሆናቸውን ያስታወሱት ኮሚሽነር ሙሉሰው፣ እነዚህ ተግባራት ተቋማትን ያዳክማል፣ የኢኮኖሚ ልማትን ያቀዘቅዛል፣ ለመንግስታዊ አለመረጋጋት አስተዋጽኦ ያደርጋል፣ በህብረተሰቡ ውስጥ በጣም ተጋላጭ የሆኑትን እንደሚጎዳም ገልጸዋል።
ሙስናን ለመዋጋት በተለያዩ ዘርፎች በትብብር መስራትን የሚጠይቅ ተግባር መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ኃላፊነት ለሚሰማው ዜግነት ማዘጋጀት እንዳለባቸው አመላክተዋል።
የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ማህበረሰቡን በሥነምግባር አስተምህሮዎች ላይ የተመሰረተ ታማኝነትና ሙስና የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በመረዳት ትውልዱ ላይ መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
የፀረ-ሙስና ቀን በተለያዩ ባህላዊ ጭፈራዎች፣ በሥነግጥም፣ በድራማ፣ በተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድድር እየተከበረ ሲሆን፣ ዕለቱን የተመለከተ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል።
የክልሉ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በቴክኖሎጂ የታገዘ ዌብሳይት አልምቶ ስራ ላይ ማዋሉንም በዕለቱ ገለጻና ማብራሪያ በአቶ ሙባረክ አበበ መቅረቡን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
በበዓሉ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ቡድን አስተባባሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ከሙስና የፀዳች እና የበለፀገች ኢትዮጵያን ዕውን እናድርግ!
#NCRS ሞባይል መተግበሪያ
#ለAndroid ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details
#ለApple or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id6593662319